Ethio Beteseb Media

Ethio Beteseb Media ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ እንዲሁም ወቅታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መረጃን የሚያደርስ ሚዲያ ነው ።
501(c)(3) Registered
(6)

በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢው ለምትገኙ ማኅበረ ካህናት እና ምዕመናን በሙሉ  የቀረበ ጥሪ ነው  ፣ የስብሰባው አድራሻ በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው   በደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል  ሲሆ...
08/16/2024

በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢው ለምትገኙ ማኅበረ ካህናት እና ምዕመናን በሙሉ የቀረበ ጥሪ ነው ፣ የስብሰባው አድራሻ በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው በደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሲሆን ሁላችሁም ተጋብዛችኋል 👇

✏ልብ ሰባሪ ዜና♣ካህናቱ እና ምዕመኑ ተሳደው ፣ ቤተክርስቲያኑ ምሽግ ሆናል።  ( ለሀገረስብከቱ ሊቀ ጳጳሱ  አድርሱልን ይላሉ ••• ) 👉በሰሜን ሸዋ ዞን ፣ሚዳ ወረዳ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገ...
08/16/2024

✏ልብ ሰባሪ ዜና

♣ካህናቱ እና ምዕመኑ ተሳደው ፣ ቤተክርስቲያኑ ምሽግ ሆናል። ( ለሀገረስብከቱ ሊቀ ጳጳሱ አድርሱልን ይላሉ ••• )

👉በሰሜን ሸዋ ዞን ፣ሚዳ ወረዳ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በዐብይ ሠራዊት ተወሮ እርኩሰት እየተፈጸመበት እንዳለ የመረጃ ምንጮቻችን አድርሰውናል ፣

👉ነሐሴ 6,ቀን 2016ዓ.ም የቤተክርስቲያኑን አስተዳዳሪ በማሰር እና ካህናቱን ፣ ዲያቆናቱን እና ምዕመኑንን በማባረር የሱባዔውን ቅዳሴ እንዳያከናውኑ በማገድ ጭምር ፣ ቤተክርስቲያኑ የሚገኘው ተራራ ላይ በመሆኑ ፣ ሠራዊቱ ለምሽግ ይፈለገዋል፣ የቤተክርስቲያኑ የጸበል ገንዳም ለሠራዊቱ ውሃ ማቅረቢያ እንጠቀምበታል በሚል በቤተክርስቲያኑን ተቆጣጥሮ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ሲጋራ እንደሚጨስበት፣ ጫት እንደሚቃምበት እና እርኩሰት እየተፈጸመበት እንዳለ ብሎም በቤተክርስቲያኑ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ምሽግ እየተቆፈረ እንደሆነ የመረጃ ምንጮቻችን አድርሰውናል።

👉ይሁን እንጂ ይህ በእንዲህ እንዳለ ይህንን በቤተክርስቲያን ላይ የሚፈጸመውን ግፍ እና እግዚኦ የሚያሰኝ ነውር ሲፈጸም የወረዳ ቤተክህነቱም ሆነ የሀገረስብከቱ ጽ/ቤት ብሎም የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እስካሁን ምንም ያሉት ነገር የለም ፣

👉የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሚገኘውም ሚዲያ እንዲህ ዓይነቱ ግፍ እና መከራ ለመዘገብ ጊዜ የለውም ነገርግን ትንሽ ቆይቶ ይህንን ዘገባ መንግሥት በነገረን መሠረት መረጃው ትክክል አይደለም በማለት ለመንግሥት ጥብቅና ለመቆም ግን ሚዲያውን ለመጠቀም ጊዜ አይፈጅበትም ፣ ይህንን መልእክት ሼር በማድረግ ለኦርቶዶክሳዊያን ድምፅ እንሁናቸው ሼር ቤተሰቦች ፦ የሚመለከታችሁም ለሀገረስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አድርሱልን ፦

👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

✏የካህናት ደም መፍሰሻ ምድር አርሲ ኦሮምያ  👉በዚህ ቦታ በተደጋጋሚ ካህናት ፣ ምዕመናን በግፍ ይገደላሉ ፣ ዛሬም አልቆመም በዚህ በጾመ ፍልሰታ ካህኑ ስጋ ወደሙን አቀብለው ምእመናንን እያሳ...
08/15/2024

✏የካህናት ደም መፍሰሻ ምድር አርሲ ኦሮምያ

👉በዚህ ቦታ በተደጋጋሚ ካህናት ፣ ምዕመናን በግፍ ይገደላሉ ፣ ዛሬም አልቆመም በዚህ በጾመ ፍልሰታ
ካህኑ ስጋ ወደሙን አቀብለው ምእመናንን እያሳለሙ ሳለ በታጣቂዎች መገደላቸው ተገለጸ ፡፡

👉በአርሲ ሀገረ ስብከት አሰኮ ወረዳ ጢዮ ቀበሌ ጠለታ ጨፋ ከተማ የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህንን ጨምሮ 6 ኦርቶዶክሳውያን ኦነግ ሸኔ ተብለው በሚጠሩ ታጣቂዎች መገደላቸውን የአካባቢው ምእመናን መስክረዋል ።

👉ግድያው የተፈጸመው ከነሐሴ 7 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሲሆን ከሞቱት በተጨማሪም 3 ኦርቶዶክሳውያን ከባድ ጥቃት ደርሶባቸው በህክምና ላይ እንደሚገኙ ተሰምቷል፡፡ካህኑን ጨምሮ የተገደሉት ምእመናንን አስከሬናቸውን ለማንሳትና ለመቅበር አስቸጋሪ እንደነበር ገልጸው በዚህም ሁኔታ ከአጥቢያው ራቅ ወዳለ ቦታ በመውሰድ የቀብር ሥርዓቱን መፈጸም መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡

👉ይህ ሁሉ ሲሆን ግን ቤተክህነቱ ዝምታን መርጧል፣ ይህንን የሚያወግዝ ጳጳስ ብሎም ይህንን መናገር ፓለቲካ ነው በሚል ፍራቻ ብዙዎች እጃቸውን አፋቸዉ ላይ ጭነዋል፣ ዛሬም እንደትላንቱ የዘካርያስ ደም በቤተመቅደሱ ይጮሃል ።


👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

✏ጥያቄ ••• ይህ ሰው ማን ነው ?  👉 ከዳንኤክ ክብረት ጋር ያለው ቁልፍ ትስስር ምንድን ነው ? በኦርቶዶስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማልያ የሚጫወቱ የሶሻል ሚዲያ አርበኞች ለምን ከፊት አስቀ...
08/13/2024

✏ጥያቄ ••• ይህ ሰው ማን ነው ?

👉 ከዳንኤክ ክብረት ጋር ያለው ቁልፍ ትስስር ምንድን ነው ? በኦርቶዶስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማልያ የሚጫወቱ የሶሻል ሚዲያ አርበኞች ለምን ከፊት አስቀድመው የሕዝቡን ልብ እንዲያማልል ሰፊ ሽፋን ሊሰጡት ቻሉ ?

👉 ስለዳንኤል መጽሐፍ በዚህ ልክ ደፍሮ በአደባባይ ማንበብ ሳይሆን አንብቡ ብሎ ለማስተዋወቅ ስንት ተከፈለው ? ( ያለ ክፍያ እንደማይሰራ በአሐዱ ባንክ ስላየነው ማለት ነው )

👉 የሕዝብ አስተያየት ከተሰጠው በኃላ በንቀት እና ማን ያገባዋል በሚል የለጠፍኩትን አላነሳም ማለቱ ዳንኤል አይዞህ በርታ ብሎት ወይስ ኅሊናውን አሳምኖ? ዝምታው ይበቃል የሚዲያ ሰዎች ለአከበራችሁ አድማጭ ክብር ከሌላችሁ እናንተም የዚሁ ግለሰብ ሀሳብ ደጋፊ እና ጉዳይ አስፈፃሚ በመሆናችሁ በመረጃ የተደገፈ ግልጽ ሥራዎች በቪዲዮ ጭምር ይቀጥላል •••• ይቆየን

ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ
የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

✏መልእክት 👉እጅግ ተናፋቂ ለሆናችሁ ቤተሰቦች በተለያዩ ምክንያቶች መርሀግብር ማድረግ ባለመቻላችን ከሚዲያው ለተወሰኑ ሳምንታት እንደጠፋን  ይታወቃል ይሁን እንጂ  ከሱባዔው በኃላ መደበኛ ፕሮ...
08/13/2024

✏መልእክት

👉እጅግ ተናፋቂ ለሆናችሁ ቤተሰቦች በተለያዩ ምክንያቶች መርሀግብር ማድረግ ባለመቻላችን ከሚዲያው ለተወሰኑ ሳምንታት እንደጠፋን ይታወቃል ይሁን እንጂ ከሱባዔው በኃላ መደበኛ ፕሮግራማችን ይጀምራል ፣ ሱባዔውን በሰላም ያስፈጽመን ፣ እስከዛው ቸር ይግጠመን ባላችሁበት ሰላማችሁ ይብዛ ፣ የኢትዮጵያን ትንሣኤ ፈጣሪ ያቅርብልን 🙏

ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ
የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

"ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ" "ማርያም ሆይ እንወድሻልለን"       ቅዱስ አባ ሕርያቆስበአዳም ዘር መካከል በእሾህ ውስጥ እንዳጌጠች ጽጌረዳ በማዕዛ ቅድስና ተጠብቃ የንጉስ ክርስቶስ አማ...
08/09/2024

"ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ"
"ማርያም ሆይ እንወድሻልለን"
ቅዱስ አባ ሕርያቆስ

በአዳም ዘር መካከል በእሾህ ውስጥ እንዳጌጠች ጽጌረዳ በማዕዛ ቅድስና ተጠብቃ የንጉስ ክርስቶስ አማናዊት መቅደስ በመሆን ዓለም ሁሉ የሚድንበትን እውነተኛውን መብልና መጠጥ ስላስገኘችልን ዛሬም እንላታለን እንደ ቅዱስ አባ ሕርያቆስ

" ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ ወናዐብየኪ እስመ ወለኪ ለነ መብልዐ ጽድቅ ዘበአማን ወስቴ ሕይወት ዘበአማን"

👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

መንፈሳዊ ጥሪ ሱባኤውን በደብራችን እናሳልፍ
08/06/2024

መንፈሳዊ ጥሪ ሱባኤውን በደብራችን እናሳልፍ

🙏 መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክበስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ኢ...
08/06/2024

🙏 መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ!

በማሕፀነ ማርያም በፈጸመው እውነተኛ ተዋሕዶ የሰው ልጅን ከኃሣር ወደ ክብር የመለሰ እግዚአብሔር አምላካችን፣ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስድስት ዓመተ ምሕረት ጾመ ቅድስት ማርያም በደኅና አደረሰን አደረሳችሁ!፤

‹‹ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ፣ ተፈሥሒ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፡- ምልእተ ጸጋ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ በእግዚአብሔ ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› (ሉቃ. 1÷28-30")
የክብር አምላክ እግዚአብሔር የሰው ልጅን ከወደቀበት ዐዘቅተ ኵነኔ የሚያድንበት ዕድል እንዳዘጋጀ በብሉይ ኪዳን በስፋት ገልፆል፤ የማዳን ስራውም ከሰው ወገን ከሆነች ቅድስት ድንግል በሚወለደው መሲሕ እንደሚፈጸም አስረድቶአል፤ የማዳን ቀኑ በደረሰ ጊዜም መልእክቱን በፊቱ በሚቆመው በቅዱስ ገብርኤል በኩል ልኮአል፤ ቅዱስ ገብርኤልም የተነገረውን መልእክት ለድንግል ማርያም አድርሶአል፡፡

ቅዱስ ገብርኤል ለድንግል ማርያም እንዲነግር ከታዘዘባቸው መካከል ‹‹ጸጋን የተመላሽ ደስተኛይቱ ሆይ÷በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› የሚል አስደናቂ መልእክት ይገኝበታል፡፡

የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን!

ከእግዚአብሔር መንጭቶ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለድንግል ማርያም የተነገረ ይህ መልእክት፣ የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር ከመግለጽ ባሻገር ለሰው ልጆች ሁሉ ያለው ፋይዳ በእጅጉ የላቀ ነው፤

‹‹ጸጋ›› የሚለው ቃል እንደ ቅዱስ መጽሐፍ አስተምህሮ ያልተወሰነ፣ ገደብና ቅድመ ሁኔታ የሌለው ስጦታን ሲያመለክት ‹‹ሞገስ›› የሚለው ቃል ደግሞ ተወዳጅነትን ተደማጭነትን ተሰሚነትን የሚያመለክት የክብርና የባለሟልነት መግለጫ ቃል ነው፡፡

እነዚህ ቃላት ከእግዚአብሔር ዘንድ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለቅድስት ድንግል ማርያም ተነግረዋል፤ የእግዚአብሔር ቃል የማይለወጥ ነውና ቃላቶቹ ለድንግል ማርያም ቃል ኪዳን ሆነው የተሰጡ ናቸው፤ የተሰጡበትም ምክንያት ሰውን ለማዳን ስራ እንዲውሉ እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡

ምክንያቱም የእግዚአብሔር የማይናወጥ ፈቃድ ሰውን ማዳን ነውና፤ በመሆኑም ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት በዚህ ገደብ የሌለው ቃል ኪዳኗ ሰውን ልትታደግ በቅታለች፤ይህም በቃና ዘገሊላ ባደረገችው ምልጃ በጭንቀት የተዋጡትን ሠርገኞች እንዴት እንደታደገች በቅዱስ ወንጌል ተጽፎ እናገኘዋለን፤ቅድስት ድንግል ማርያም ቀድሞውኑም ከፍ ያለ ሞገስ ተሰጥቶአታልና የሠርጉ አሳላፊዎችን ‹‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ›› በማለት ስታዝዝ እናያለን፤ ይህ ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ አስደናቂ የትድግና ስጦታ ነው፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን!

የድንግል ማርያም የጸጋ ስጦታ በብሥራተ ገብርኤል ተገልጾ፣ በቃና ዘገሊላ ተተግብሮ በዕለተ ስቅለት ‹‹እነሆ ልጅሽ፣ እነኋት እናትህ›› በሚል መለኮታዊ ማኅተም የታተመ ነው፤ ይህ ቃል እሷ እናታችን መሆኗን፤ እኛም ልጆችዋ መሆናችንን ያረጋገጠ ማኅተመ ቃል ኪዳን ነው፤ የቃል ኪዳኑ ይዘት እሷ በአማላጅነቷ እንደ ልጅ ልትንከባከበን እኛም እንደ እናት ልናከብራትና ልንማፀናት የሚገባን መሆኑን ያሳያል፤ የእናትነትና የልጅነት ማረጋገጫ የሆነ ይህንን የቃል ኪዳን ማኅተም ሊሰርዝም ሆነ ሊፍቅ ሊደመስስም የሚችል ኃይል የለም፡፡

ይህ ጸጋና ሞገስ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም የሚቀጥል እንጂ የሚገደብ አይደለም፤ ሞት፣ ቦታና ዘመንም አይወስኑትም፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን በሞት በቦታና በዘመን አይገደብምና ነው፤ ‹‹ኪዳኑንም ለዘለዓለም ያስባል›› ተብሎ የተገለጸውም ለዚህ ነው፤ (መዝ. )111÷5)
መንፈስ ቅዱስም በእሷ አንደበት ‹‹እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ነሽ ይሉኛል›› በማለት የተናገረው ይህንን ለማስረዳት እንደሆነ ማስተዋል ያሻል፡፡

በእግዚአብሔር ተሰጥቶ፣ በቃል ኪዳን ታትሞ፣ በቅዱስ ገብርኤል ተብራርቶ፣ በጌታችን ተረጋግጦና በሐዋርያት በኩል የተላለፈልን፣ ሰውን ማዳን ግቡ የሆነ የድንግል ማርያም ምልጃ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ በሁሉ ያለች፣ አንዲትና ቅድስት ኦርቶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ሺሕ ዓመታት ያህል አምና እና ተቀብላ ስትጠቀምበት ኖራለች፤ አሁንም በዚሁ ትቀጥላለች፡፡

በኦርቶዶክሱ ዓለም ዛሬ የሚጀመረው የጾመ ማርያም ሱባዔም የዚሁ ጭብጥ ማሳያ ነው፤ ዋናው መልእክቱም ድንግል ማርያም በተሰጣት ጸጋና ሞገስ በጸሎቷ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ይቅርታን የምታሰጠን ስለሆነች እሷን በመማፀን ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ የሚል ሆኖ ይመሰጠራል፡፡

የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ልጆቻችን!

ጾም ፈቃደ ሥጋን በማድከምና ፈቃደ ነፍስን በማጎልበት ምሕረተ እግዚአብሔር መሻታችንን የምናሳይበት መንፈሳዊ ማመልከቻ ነው፤ ጾም ከጥንት ጀምሮ የነበረ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው፤ ቀደምት አበው በጾም ምክንያት ከጥፋት ድነዋል፤ የለመኑትንም አግኝተዋል፤ ምስጢርም ተገልጾላቸዋል፤ ዲያብሎስም ድል አድርገውበታል፡፡

እኛም ዛሬ ጾምን ስንጾም በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን ብሎም በዓለም ዙሪያ ሁሉ ስጋትን እየጫረ ያለው የጥፋት እንቅስቃሴ እግዚአብሔር እንዲያስቆምልን ከልብ በመጸለይ ሊሆን ይገባል፤ ይህንንም ስናደርግ በጸሎት ብቻ ሳይሆን ንስሐ በመግባትና ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል እንደዚሁም የሰላም የፍቅርና የዕርቅ ሰው ሆኖ በእግዚአብሔር ፊት በመቆም ሊሆን ይገባል፡፡

ችግሮችንና አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በምክክር ለመፍታት የሚደረገው ጥረትም በእጅጉ ሊደገፍ ይገባል፤ ግጭትና ጦርነት ከሚያጠፋን በቀር ሊያተርፍልን የሚችል አንዳች ጥቅም የለም፡፡

በመሆኑም በየትኛውም የሀገራችን አካባቢ ያላችሁ ልጆቻችን እባካችሁ ለሰላም ለውይይትና ለሰው ልጆች መብት መከበር ቅድሚያ ስጡ፤ ግድያ፣ ዕገታ፣ አብያተ ሃይማኖትን መዳፈር፣ ዘረፋና ቅሚያ፣ የሴት ልጅን መድፈርና ሰውን ማንገላታት አቁሙ፤
እነዚህ ድርጊቶች ሰብአዊነትን ዝቅ የሚያደርጉ፣ እግዚብሔርን የሚያስቆጡ፣ በታሪክም የሚያሳፍሩ ናቸው፤ እነዚህን ሳናርም የምንጾመው ጾም ትርጉም ስለሌለው ንስሐ ገብተን ከእንደዚህ ያለው ድርጊ ርቀን ጾሙን መጾም ይገባል፤ ይህን ስናደርግ ጾማችን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ ይኖረዋል፡፡

በመጨረሻም
የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ በተለይም በጾመ ማርያም ሱባዔ በንስሐና በጸሎት የሚያሳልፉ ሕዝበ ክርስቲያን ስለ ሃይማኖት መጠበቅ፣ ስለሀገር ሰላምና አንድነት፣ እንደዚሁም ስለሕዝቦች ደኅንነትና ጤንነት አጥብቀው እንዲጸልዩ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡
መልካም የሱባዔ ወቅት ያድርግልን
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ነሐሴ 2016 ዓ.

ዋሽንግተን ዲሲ - ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ

👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

✏ስንት ቢከፈልህ ነው ,...? "ኅሊናህ ሲታወር ሆድህ ሲቀድም ማዕረግህንም ክብርህንም ያሳጣሀል "  ይባላል እውነት ወይስ ሀሰት መልሱን ለብዙሀኑ  ይድረስ  ••• 👉 ሰው በብዙ ነገር ሊታወ...
08/06/2024

✏ስንት ቢከፈልህ ነው ,...?

"ኅሊናህ ሲታወር ሆድህ ሲቀድም ማዕረግህንም ክብርህንም ያሳጣሀል " ይባላል እውነት ወይስ ሀሰት መልሱን ለብዙሀኑ ይድረስ •••

👉 ሰው በብዙ ነገር ሊታወቅ ብሎም ዝነኛ ሊሆን ይችላል ፣ ከሁሉም የሚበልጠው ግን እግዚአብሔርን በማገልገል ታውቀህ እና ከአመድ ላይ ያነሳህን ፈጣሪ አብዝቶ በሰጠህን የወንጌል አገልግሎት ፀጋ መታወቅህ እጅግ ልዩ ያደርገዋል ፦

👉ይሁን እንጂ ዛሬ ዛሬ በብዙዎች ዐይን ውስጥ በአገልግሎትህ እንድትገባ ሲያደርግህ ፣ የረዳህን እግዚአብሔርን ከማመስገን ይልቅና ለተጠራህለት የወንጌል አገልግሎት እውነተኛ አርበኛ ( የጌታ ታማኝ ወታደር ) ከመሆን ይልቅ ኅሊናህን ሸጠህ ሆድህን ስታስቀድም ሰው ምን ሊለኝ ይቻላል ? የተጠራሁበትስ ዓለማ ይህ ነውን ? የሚለውን ጥያቄ ሆድህ ባገኘው ገንዘብ እና ለጊዜው በተሰጠህ ምድራዊ ቀቢጸ ተስፋ ኅሊናህ ይታወራል ፦

👉ዲያቆን ምትኩ አበራ በወንጌል አገልግሎት በብዙዎች የሚታወቅ ከድሬደዋ ወደ አዲስ አበባ እንደ ባቡር ሀዲድ መሸጋገሪያ ድልድይ ሆኖ ከሕዝብ ጋር በደንብ ያስተዋወቀው የሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎቱ እና የማኅበረ ቅዱሳን ተቋም ነው ።

👉 በመልካም አገልግሎቱ ብዙች ቢያውቁትም ከቅርብ ጊዜ ወዲም በድኅረ ገፁ ላይ የሚለጥፋቸውን መፃፅፎች ያየ ምን ሆኖ ነው ? ስንት ቢከፈለው ነው ? ምን ነካው የሚሉ አይጠፉም?

👉በወንጌል አገልግሎቱ ያገኘውን መታወቅ እና በብዙዎች ተደራሽነቱን ተጥቅሞ በሚሄድበት አገልግሎት ሁሉ ,,,ባንክን ( •••Bank ) ለማስተዋወቅ በግልጽ ፈርሚያለው ደንበኛ ሁኑ በማለት ሲያውጅ እንደንበረ የቅርብ ቀን ትዝታ ነው ፣ ይኽስ ይሁን ያው እንደስራም ሊይታይ ይችላል ፣ኑሮም ተወዶል የገቢም ምንጭም ሊሆን ይችላል በሚል ሊያዝ ይችላል ፦

👉እንደ አንድ የወንጌል አርበኛ እውነቱን እውነት ፣ ሀሰቱን ሀሰት ብሎ መናገር የሕልም እንጀራ በሆነበት ዘመን በማንኛውም የቤተክርስቲያን መከራእና ስደት ዝምታን መርጦ ያለ ፣እጃቸውን አፋቸው ላይ ጭነው አይተው እንዳላዩ ሰምተው እንዳልሰሙ ዝምታን ከመረጡ አገልጋዮች አንዱ ቢሆንም ፣

👉ዛሬ ስንት እንደተከፈለው ባናውቅም የአቶ ዳንኤን ክብረት ደንገጡር መሆኑንን በአደባባይ መስክሮ መጽሐፉን አንቤ ባልጨርሰውም እያነበብኩት
"በተመስጦ በደመና ጭኖ ወሰዶኝ. ዓለም አንሸራሽሮ ሲመልሰኝ ስነቃ የአውሮፕላን በረራ አመለጠኝ " ይለናል

👉 ኅሊናህ ሲታወር ሆድህ ሲቀድም እንዲህ ነው በባንክ ማስተዋወቅ የተጀመረ ማንነት የዘቀጠ የጎሣ ፓለቲካ ምንነት ውስጥ ትዘፈቃለህ ትላንት ዝምታን በመረጥክበት አንደበትህ ዛሬ ራስህ በራስህ ለፍልፈህ ማንነትህ ትገልጣለህ ፣ ወንድማችን የተጠራህበትን የወንጌል አገልግሎት ይሻልህ ነበር በማለት ሀሳብ እየስጠን ለጊዜው ይቆየን •••

👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

✏ እውነተኛ ኖላዊ አባት 👉ታላቁ የወንጌል አርበኛ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ በሠራዊት እና በመሳሪያ  ሳይታጀቡ መስቀል ብቻ ይዘው ወደ ጎፋና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ ስብከት  የሥራ አጋሮቻቸውን ይዘው...
07/27/2024

✏ እውነተኛ ኖላዊ አባት

👉ታላቁ የወንጌል አርበኛ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ በሠራዊት እና በመሳሪያ ሳይታጀቡ መስቀል ብቻ ይዘው ወደ ጎፋና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ ስብከት
የሥራ አጋሮቻቸውን ይዘው እባታው ድረስ በመገኘት ፣ በእንባ ሀዘናቸውን በመግለጽ ፣ ሕዝቡን በማጽናናት ለተጎዱ ቤተሰቦች 300,000 ( ሦስት መቶ ሺህ ) ለግሰዋል ፣ ብፁዕ አባታችን በእውነት ቡራኬዎ ይድረሰን ፣

👉የሚገርመው ግን ለመንጋው ግድ የማይላቸው
የሀገረስብከቱ ሊቀጳጳስ ነኝ የሚሉት አቡነ ኤልያስ ግን እስካሁን በአካባቢው ድርሽ እንዳላሉ የመረጃ ምንጮቻችን ፣መረጃውን አጋርተውናል፣ በዚህም የሕዝቡ ስነልቦና እንደተጎዳ ቀደም ሲልም ሕዝቡ ያቀረበውን ጳጳስ ይመደብልኝ ጥያቄ ተገቢ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ

👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

✏ሕሊናህ ሲታወር  •••ልቡ ለተሰበረው ሕዝብ የሚያስፈልገውን ከመስጠት ይልቅ ፣አዘነ ፣ አዘኑ ፣ ገበኙ ፦ ጎበኘ እንዲባል ለሞቱት መታሰቢ ችግኝ መትከሉ ግን የጤና ነው ?😭👉  የበለጠ መረጃ...
07/27/2024

✏ሕሊናህ ሲታወር •••

ልቡ ለተሰበረው ሕዝብ የሚያስፈልገውን ከመስጠት ይልቅ ፣አዘነ ፣ አዘኑ ፣ ገበኙ ፦ ጎበኘ እንዲባል ለሞቱት መታሰቢ ችግኝ መትከሉ ግን የጤና ነው ?😭

👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

✏  "ጥቡዕ ልቡ ለሕጻን እንዘ ሀሎ ውሥተ ምኩነን"               "በፍርድ ቦታ የህጻኑ ልብ ቆራጥ ነው"                         (ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ)👉እንኳን ለታ...
07/26/2024

✏ "ጥቡዕ ልቡ ለሕጻን እንዘ ሀሎ ውሥተ ምኩነን"
"በፍርድ ቦታ የህጻኑ ልብ ቆራጥ ነው"
(ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ)

👉እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ሐምሌ 19 ቀን ዓመታዊ ክብረ በዐል አደረሳችሁ አደረሰን!!!

👉"ጥቡዕ ልቡ ለሕጻን እንዘ ሀሎ ውሥተ ምኩናን ይቤላ ሕጻን ለእሙ ጥብኢኬ እም ንፈጽም ገድለነ ወስምአነ ንፈጽም ገድለነ ወስምአነ ከመ ንርአይ ገጾ ለአምላክነ ፣"

ትርጉም
👉 በፍርድ ቦታ የህጻኑ ልብ ቆራጥ ነው። እምዬ (እናቴ ) ሆይ ምሥክርነታችንን ገድላችንን እንፈጽም ዘንድ ቁረጭ የአምላካችንን ፊቱን እናይ ዘንድ (ዚቅ ዘማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ)

👉የዛሬ በዐል ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስን ከሚነደው እቶነ እሳት የታደገበት ታላቅ በዐል ነው ።

👉ቂርቆስ ኢየሉጣን ከሚነድ እሳት ያዳነ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል የሀገራችንን የሰላም ብስራት ፈጥኖ ያሰማን🙏 አሜን🙏

የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ በደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ቨርጅኒያ
07/25/2024

የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ በደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ቨርጅኒያ

"የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል "ዮሐ.11÷25በቅርቡ ከኢትዮጵያ የመጡትና በቦስተን የደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩትና ዘ...
07/25/2024

"የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል "ዮሐ.11÷25

በቅርቡ ከኢትዮጵያ የመጡትና በቦስተን የደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩትና ዘማሪ ቀሲስ ግርማ አዳነ (ወልደ ሰማዕት) ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በድንገት ዐረፈዋል።

ቀሲስ ግርማ አዳነ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በገጠር በከተማ፣በሙያ በገንዘብ በትጋት በቅዳሴ፤ ዝማሬ፤ ስብከት እና ትምህርት በመልካም አርአያነት ያገለገሉ ሲሆን ፤ ባለትዳር እና የ 6 ወር ህፃን አባት ነበሩ፤፤ አስከሬናቸውን ወደ ሃገር ቤት በክብር ለመሸኘት፤ የአገር ቤት የቀብር ሥነ ሥርዓት ማስፈፀሚያ ወጭዎችን ለማገዝ እና ቤተሰቦቹን ለመደገፍ እንዲቻል በዚህ ጎፈንድሚ የበኩላችንን ድጋፍ እንድናደርግ እናሳውቃለን።
እግዚአብሔር አምላካችን የአገልጋዩ ወልደ ሰማዕትን ነፍስ በመካነ ቅዱሳን ያሳርፍልን።
https://gofund.me/5039dc2a
ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ ለቤተሰቦቹ መጽናናትን ይመኛል።
https://gofund.me/5039dc2a

🙏የሀዘን መግለጫ ሰጥተዋል  "በጎፋባና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ-ስብከት አስተዳደር ጉባኤ“እናት ልጅዋን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ" ኢሳ 66፥13👉በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ...
07/25/2024

🙏የሀዘን መግለጫ ሰጥተዋል

"በጎፋባና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ-ስብከት አስተዳደር ጉባኤ

“እናት ልጅዋን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ" ኢሳ 66፥13

👉በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ድንገት በተከሰተው የመሬት ናዳና መንሸራተት ብዛት ያላቸው ወገኖቻችን ላይ በደረሰው አሰቃቂና ልብ ሰባሪ አሳዛኝ አደጋ በአስተዳደር ጉባኤ ስም ጥልቅና መራር ሀዘን ተሰምቶናል፡፡

👉የአደጋው መንስኤ ሐምሌ 14 ቀን 2016 ዓ/ም በነበረው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት የመሬት ናዳውና መንሸራተት አጋጥሟል፡፡ ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ 260 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ከፍተኛ የንብረት ውድመት ደርሷል፡፡ በጉዳቱም ከ500 በላይ የሚሆኑ ዜጎች መፈናቀላቸው ትላንት የአስተዳደር ጉባኤ አባላት እስከ ቦታው ድረስ በመሄድ አጽናንተው ተመልሰዋል፡፡

👉አደጋ የደረሰባቸውንና የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን በሀገረ-ስብከቱ ሥር ያሉ ምዕመናን ሰንበት ት/ቤት ማህበራት አጥቢያዎች እና ወረዳዎች በአንድነት በማስተባበር ሁለንተናዊ ድጋፋችን እንደምናደርግ ከወገኖቻችን ጎን እንደምንቆም እየገለጽን መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሰው ልጆች በሙሉ ለተጎዱ ወገኖች የድርሻችሁን ድጋፍና አስተዋጽኦ እንድታርጉ በጎፋና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ-ስብከት አስተዳደር ጉባኤ ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

👉እግዚአብሔር የሞቱ ወገኖቻችንን በቅዱሳኑ ዘንድ ያሳርፍልን ለቤተሰቦቻቸው ለመላው ህዝባችንና ለጎፋ ዞን አስተዳደር መጽናናትን ያድልልን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

የጎፋና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ-ስብከት አስተዳደር ጉባኤ

ሳውላ"

👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን በተከሰተ የመሬት መንሸራተት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 229 መድረሱን   ከጎፋ ዞኑ የተለያዩ ኃላፊዎች የተገኘው   መረጃ ያመላክታል ።ለሞቱት ወገኖቻችን እግዚአብሔ...
07/23/2024

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን በተከሰተ የመሬት መንሸራተት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 229 መድረሱን ከጎፋ ዞኑ የተለያዩ ኃላፊዎች የተገኘው መረጃ ያመላክታል ።

ለሞቱት ወገኖቻችን እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር ፣ ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናቱን ይስጥልን በዚህ አጋጣሚ የተሰማንን ሀዘን ለመግለጽ እንወዳለን ።

👉 የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

07/20/2024

መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ

ኑ ይሳተፉ  በመካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ቨርጅኒያ ልዩ የወንጌል አገልግሎት
07/19/2024

ኑ ይሳተፉ በመካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ቨርጅኒያ ልዩ የወንጌል አገልግሎት

07/13/2024

መልካም ገደል ተጋድያለዉ

✏ያስሩታል ፦ ይፈቱታል 👉ያስሩታል ፣ ይፈቱታል ፣ ነገም  ላለመታሰሩ ምን ዋስትና የለው ፣ እሱ ግን ተስፋው እንደብረት የጠነከረ ፣ ለሀገሩ እና ለቤተክርስቲያኑ እጅግ በጣም የታመነ ፣ የእም...
07/02/2024

✏ያስሩታል ፦ ይፈቱታል

👉ያስሩታል ፣ ይፈቱታል ፣ ነገም ላለመታሰሩ ምን ዋስትና የለው ፣ እሱ ግን ተስፋው እንደብረት የጠነከረ ፣ ለሀገሩ እና ለቤተክርስቲያኑ እጅግ በጣም የታመነ ፣ የእምነት ሰው ፣ ትጉህ እና ቅን አገልጋይ ፣ ያመነበትን ለመናገር ቅንጣት ታህል የማይሳቀቅ ፣

👉እውነትን በጀርባው ያነገበ ፣ ከብዙ የስቃይ ቀን እና የመከራ እስራት ዛሬ ፈተውታል ፣ ብሬ እንኳን ለቤትህ አበቃህ ፣ አናምናለን ከደረስብህ ስቃይ በ መከራ የልጅህ ናፍቆት እና ለጄሪ የምታቀርበው መልስ የሌላቸው የአንቀጹ ጥያቄዎች ውስጥን እንደሚረብሹት ፣ ግን ይህ ቢሆን ዛሬ ዐይኗን ለማያት በቅተሀል እና እግዚአብሔር ይመስገን ፣ ጄሪ እንኳን ደስ አለሽ🙏

👉 ምቀኞች የቤተክህነቱ ምንደኞች ነገስ ምን ወንጀል ይዛችሁ ትቀርቡ ይሆን ?

👉 በኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ
https://t.me/ethiobeteseb

06/29/2024

በመካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን

06/28/2024

ነገ ቅዳሜ ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ ከቅዳሴ በኃላ ከመምህር ጳውሎስ እና ከዘማሪ አለምሰገድ ጋር በመካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ቨርጅኒያ

06/28/2024

ፊት ለፊት ግልጽ ዉይይት //
የሻለቃ ዳዊት ጥያቄ? ቆይታ እንግዶች ጋር

06/27/2024

ድርድር፣ሽግግር... // ቆይታ ከዘመዴ ጋር

✏ሼር ቤተሰቦች 👇
06/24/2024

✏ሼር ቤተሰቦች 👇

የደረሰን መረጃ : የሕዝቡ ቁጣ ጳጳሱ ላይ //የሻለቃ ዳዊት ደብዳቤ የጳጳሱ ምላሽ

Address

Maryland City, MD
20876

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Beteseb Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share


Other Social Media Agencies in Maryland City

Show All