Ermiyas Girma - ዘማሪ

Ermiyas Girma - ዘማሪ "እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ ትእዛዛትህን ግን አልረሳሁም"
መዝ:- 118 - 141

እህቴ ሣራ ተስፋዬ እንኳን ደስ አለሽ ስለ አንቺ እግዚአብሔር አመሰግናለሁ ደስታችሁ ደስታዬ ነው  መራቅ ክፉ ሆነና ከዚህ ፍሥሃ በአካል ተገኝቼ ባለመካፈሌ ባዝንም ደስታዬን ግን አልነጠቀኝም ...
02/04/2025

እህቴ ሣራ ተስፋዬ እንኳን ደስ አለሽ ስለ አንቺ እግዚአብሔር አመሰግናለሁ ደስታችሁ ደስታዬ ነው መራቅ ክፉ ሆነና ከዚህ ፍሥሃ በአካል ተገኝቼ ባለመካፈሌ ባዝንም ደስታዬን ግን አልነጠቀኝም ..!
እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ትዳራችሁን ትባርክ በልጅ ፍሬ ቤታችሁን ታድምቅ ..🙏

👉" ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው" ዮሐ. 8፥12👉"እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ...
02/04/2025

👉" ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው" ዮሐ. 8፥12

👉"እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ" ማቴ. 11፥28

02/03/2025

"የራሳችንን ነገር ካቃለልነው ማንም እኛን አያከብረንም!

👉ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ

ዘማሪት መስከረም ወልዴ እንኳን ደስ አለሽ እህቴ እመ አምላክ ድንግል ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ትዳራችሁን ትባርክ ..!እንኳን ደስ አላችሁ ..!
02/02/2025

ዘማሪት መስከረም ወልዴ
እንኳን ደስ አለሽ እህቴ እመ አምላክ ድንግል ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ትዳራችሁን ትባርክ ..!
እንኳን ደስ አላችሁ ..!

"ሰላም ለመርቆሬዎስ ሰማዕት ንጹሕ ድንግል፤ ፈጻሜ ቃለ ወንጌል።"አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫተአምኆ ቅዱሳን
02/02/2025

"ሰላም ለመርቆሬዎስ ሰማዕት ንጹሕ ድንግል፤ ፈጻሜ ቃለ ወንጌል።"
አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ
ተአምኆ ቅዱሳን

02/01/2025

"እኔ የሚወዱኝን እወዳለሁ
ተግተው የሚሹኝም ያገኙኛል"
መጽሐፈ ምሳሌ. ፰ - ፲፯

02/01/2025
👉“ክርስቲያኖች እዚህ (በምድር) መላእክትን ከሆኑ፤ ካረፉ በኋላማ እንዴት ይሆኑ?! እንግዳ በሆኑባት ዓለም እንዲህ እጅጉን ካበሩ፤ የገዛ ሃገራቸውን ሲቀዳጁማ እንዴት ታላቅ ይሆኑ!”- ቅዱስ ...
02/01/2025

👉“ክርስቲያኖች እዚህ (በምድር) መላእክትን ከሆኑ፤ ካረፉ በኋላማ እንዴት ይሆኑ?! እንግዳ በሆኑባት ዓለም እንዲህ እጅጉን ካበሩ፤ የገዛ ሃገራቸውን ሲቀዳጁማ እንዴት ታላቅ ይሆኑ!”
- ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (የማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜ)

01/29/2025

"የእግዚአብሔርን ሥራ ነው ያየንበት የእመብርሃን ሥራ"
የካሊፎርኒያው እሳት ተዓምር

ወ/ሮ ተዋበች ፈረደ በላይ

በካሊፎርንያ ቤታቸው ምንም እሳት ሳይነካው የተረፈላቸው
ምንጭ:- VOA Amharic

አስተርዮ ማርያም በአክሱም ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ፅዮን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ጸሎተ ምሕላ.. እንኳን አደረሳችሁ .!ቪዲዮውን ከቦታው ያደረሰን ወንድማችን:- ኵሉብርሃን ካ...
01/29/2025

አስተርዮ ማርያም በአክሱም ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ፅዮን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ጸሎተ ምሕላ.. እንኳን አደረሳችሁ .!

ቪዲዮውን ከቦታው ያደረሰን ወንድማችን:- ኵሉብርሃን ካኽሳይን ከልብ እናመሰግናለን ..!

ይኽ የዘማሪ ኤርምያስ ግርማ መንፈሳዊ ዩቲዩብ ገጽ ነው...! እንኳን ኦርቶዶክሳዊ አገልግሎትን ወቅቱ በሚፈቅደው መጠን ተደራሽ ወደሚያደርግበት ገጹ እና ቻናሉ በሰላም መጡ። This is Zemari Ermiyas ...

👉"ጥር ሃያ አንድ (21) በዚች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ ነው" - ስንክሳር ዘጥር 21👉"ስልሳ አራት ዘመን ሲሆናት በጥር ኻያ ...
01/28/2025

👉"ጥር ሃያ አንድ (21) በዚች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ ነው"
- ስንክሳር ዘጥር 21

👉"ስልሳ አራት ዘመን ሲሆናት በጥር ኻያ አንድ ቀን ዐርፋለች"
- ውዳሴ ማርያም ዘእሑድ አንድምታ ትርጓሜ

ለምንት ይዜኃር ኃያል በኃይሉ
ወባዕል በብዝኀ ብዕሉ
ኢያድለወ ሞተ ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ
ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ
ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኩሉ፠

"ለተቸገረው ሰው በጎ ነገርን ማድረግ አትከልክል ልታደርግለት የሚቻልህ ሲሆን"መጽሐፈ ምሳሌ . ፫ - ፳፯"ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል"መጽሐ...
01/27/2025

"ለተቸገረው ሰው በጎ ነገርን ማድረግ አትከልክል ልታደርግለት የሚቻልህ ሲሆን"
መጽሐፈ ምሳሌ . ፫ - ፳፯

"ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል"
መጽሐፈ ምሳሌ . ፲፱ - ፲፯

"ለድሃ የሚሰጥ አያጣም ዐይኖቹን የሚጨፍን ግን እጅግ ይረገማል"
መጽሐፈ ተግሳጽ. ፬ - ፳፯

"ለታናሹም ለታላቁም በጎ ሥራን ሥራ በጎ ነገርንም ተናገር"
መጽሐፈ ሲራክ. ፳፱ - ፳፫

01/27/2025
 #የጥር  #ድርሳነ  #ገብርኤልአንድነቱ በሦስትነቱ ሳይከፈል ሦስትነቱ በአንድነቱ ሳይጠቃለል በአንድነቱና በሦስትነቱ ለዘለዓለሙ ጸንቶ የሚኖር፣ በባሕርዩ የማይመረመር ሲሆን በፍጥረቱ የሚታወቅ...
01/26/2025

#የጥር #ድርሳነ #ገብርኤል

አንድነቱ በሦስትነቱ ሳይከፈል ሦስትነቱ በአንድነቱ ሳይጠቃለል በአንድነቱና በሦስትነቱ ለዘለዓለሙ ጸንቶ የሚኖር፣ በባሕርዩ የማይመረመር ሲሆን በፍጥረቱ የሚታወቅ፣ መባርቅትን በነፀብራቅ ብልጭታ የሚበታትነው፣ ውሀዎችን በረቂቅ ደመና አካል የሚቋጥር፣ ሲወድቁ የሚፍገመገሙትን የሚደግፍ፣ ሐሰተኞችን ወደ ዕውቀት የሚመልስ፣ ከወንዶችና ከሴቶች ከሽማግሌዎችና ከሕፃናት ለሱ ብቻ ምስጋና (መመለክ) የተገባው።

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በማመን #ቀን #የሚነበብ #የሚጸለይ የፍጹም ደስታ መልአክ የሚሆን #የሊቀ #መላእክት #ቅዱስ #ገብርኤል #ድርሳን።

የጸሎቱ ኃይል ከሕዝበ ክርስቲያኑ ሁሉ ጋር ለዘለዓለሙ ይኑር አሜን።

ወንጌላዊው ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ የመላእክት አለቃ ስለሚሆን ስለ ቅዱስ ገብርኤል እንዲህ ብሎ ተናገረ። እግዚአብሔር አምላክ ከሌሎች ስነ ፍጥረት በተለየ ሰውንና መላእክትን ስሙን እንዲቀድሱ ክብሩን እንዲወርሱ ፈጥሮአቸዋል።

ቅዱሳን መላእክትን በየወገናቸውና በየማዕረጋቸው አንድ አድርጐ ዓሥር ሊቃነ መላእክትን ሾመ እነዚህም ቅዱሳን የሚሆኑ ዓሥር አለቆች በብርሃን ድንኳኑ ዙሪያ እና በዙፋኑ ፊት ይቆማሉ፤ ከዚያም ግሩም በሚሆን በመለኮት የእሳት አትሮንስ አካባቢ ይዞራሉ።

ከነዚህም የአለቆች አለቃ፥ የሆነ የመላእክትን ምስጋና ወደ እግዚአብሔር የሚያሳርግ፥ ሣጥናኤል የሚባል መልአክ ነበር።

ይህም ርጉም ከሀዲ መልአክ ፍጡር መሆኑን እያወቀ ከእርሱ ጋር ያሉትን መላእክት “እኔ የሁሉ ፈጣሪ ስለሆንኩ ‘ስቡሕ ክቡር ታላቅ’ ተብሎ መመስገን ይገባኛልና ከኔ በቀር ሌላ ልታመሰግኑ አይገባችሁም” አላቸው። በዚህ ጊዜ በመላእክት ዘንድ ሽብር ጸና በሦስት ተከፈሉ። እሊህም፦

-“አዎን አንተ ፈጠርከን” ያሉ /የሳጥናኤልን ፈጣሪነት ያመኑ/
-“ምን አንተ ትፈጥረናለህ እኛ ፈጠርንህ እንጂ ያሉ” [እና]
-“ፈጥሮን ይሆን አልፈጠረን ይሆን” ብለው የተጠራጠሩ ናቸው።

ሳጥናኤልም ይህንን የትዕቢት ቃል በተናገረ ጊዜ በቅጽበት ከመንበሩ ወደቀ፣ ከክብሩም ተዋረደ፣ የሱ ተከታዮች የሆኑ መላእክትም ከማዕረጋቸው ተሻሩ።

ይህ ሁኔታ በተከሰተ በዚያን ጊዜ የሰላሙ መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም “እኛ ሁላችን መላእክት በፍቅርና በሃይማኖት፣ እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በንጽሕና ሆነን በያዝነው ሥርዓታችን እንጽና!” ብሎ በታላቅ ቃል በመናገር የመላእክትን ሠራዊት እንደ በጐ አርበኛ ጸጥ አድርጐ አረጋጋቸው፤ በዚህ ምክንያት ‘መልአከ ሰላም’ /የሰላም መልአክ/ ተብሏል።

ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ተገልጦ የፈጠራቸው እሱ መሆኑን በጨለማ መካከል “ብርሃን ይሁን” ብሎ አዞ ትእዛዝ ሰጠ፤ ይህም እውቀት ሆናቸውና “ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ” ብለው ፈጣሪያቸው እግዚአብሔርን በአንድነቱ በሦስትነቱ አመስግነውታል።

የሰላሙ መልአክ የቅዱስ ገብርኤልን ቃል ከሰሙ በኋላ ቅዱሳን መላእክትም አሸናፊ እግዚአብሔርን “ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብለህ ትመሰገናለህ የጌትነትህም ምስጋና በሰማይና በምድር የመላ ነው” እያሉ አመሰገኑ /ኢሳ. 6፥3፣ ራዕ.4፥8/። ሥርዓትን ያወቀና ትእዛዙንም የተቀበለ በየማዕረጉ ጸንቶ ቆየ፤ የገብርኤልን ቃል ያልሰማና ትእዛዙንም ያልተቀበለ ግን ከማዕረጉ ወርዶ ከዲያብሎስ ጋር ወደቀ።

ይህ መልአክ ሳጥናኤል በካደ ጊዜ መላእክትን በእምነት እንዳፀናቸው በቃሉም እንዳረጋጋቸው በጸናች በቀናች በኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖት ከበጎ ምግባር ጋር ያጽናን ጠላቶቻችንን ከእግራችን በታች ይጣልልን ፍጹም ሰላምን ያድለን።

ልመናው አማላጅነቱ ከሁላችንም ጋር ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን።

ምንጭ፦
ትንሿ ድርሳነ ገብርኤል እና መልክአ ገብርኤል፣ መጋቤ ብሉይ ያሬድ ካሣ፣ ገጽ 12 – 16፣ 1999 ዓ.ም

01/26/2025

" ኢትዮጵያ ውስጥ ምሕረት ጠፍቷል "

-ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን
የርዕሰ አድባራት ወገዳማት ጣና ቂርቆስ ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር መምህር

Address

Lancaster, PA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ermiyas Girma - ዘማሪ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ermiyas Girma - ዘማሪ:

Videos

Share