Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ

Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ is an Ethiopian entertainment and news website launched in March 2016. The official page of tobiatube247.com

ከሀምሌ ወር አንስቶ ለሙዚቀኞች የሮያሊቲ ክፍያ ሊጀመር ነው አዲስ በወጣው መመሪያ መሰረት ማናቸውም ሚዲያ ለሚያስተላልፈው ሙዚቃ ለሙዚቃው ባለቤቶች ክፍያ መፈፀም ይኖርበታል፡፡መመሪያው የተዘጋ...
04/03/2025

ከሀምሌ ወር አንስቶ ለሙዚቀኞች የሮያሊቲ ክፍያ ሊጀመር ነው

አዲስ በወጣው መመሪያ መሰረት ማናቸውም ሚዲያ ለሚያስተላልፈው ሙዚቃ ለሙዚቃው ባለቤቶች ክፍያ መፈፀም ይኖርበታል፡፡

መመሪያው የተዘጋጀው ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመመካከር እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ይህንን ጉዳይ የአእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እንደሚከታተለውና እንደሚያስፈፅመው ተነግሯል፡፡ የሮያሊቲ ክፍያው ስርአት በቴክኖሎጂ ታግዞ በሶፍትዌር የሚመራ ሲሆን ሚዲያዎች የሚያሰራጩትን ሙዚቃ ወደሶፍትዌሩ የመላክ ግዴታ ይጣልባቸዋል፡፡

በመሆኑም በተሰራጨው ሙዚቃ ልክ ተሰልቶ ለሙዚቀኞቹ የሮያሊቲ ክፍያቸው እንደሚፈፀም ተሰምቷል፡፡ በአዲሱና ከሀምሌ ወር አንስቶ ተግባራዊ በሚሆነው መመሪያ መሰረት አንድ ሙዚቃ በሬዲዮ ወይንም በሌላ ሚዲያ ሲሰራጭ ለሙዚቀኞቹ ሀያ ሳንቲም የሚከፈል ይሆናል፡፡

ከዚህ በላይ ሙዚቀኞቹ ደግሞ ከጠቅላላ ገቢያቸው ላይ ሁለት ፐርሰንት ለመንግስት በግብር መልክ እንደሚከፍሉ መመሪያው አስረድቷል፡፡ ዲጄዎችና ሌሎች መዝናኛ ቦታዎች ለሚያጫውቱት ሙዚቃ ደግሞ በግምትና በድርድር ክፍያ እንዲፈፅሙ የሚገደዱ መሆኑን መመሪያው አስታውቋል፡፡

04/02/2025
የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት  እንዲያስተምሩ ሊገደዱ ነው ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ማኅበረሰቡን ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያስተ...
04/02/2025

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ ሊገደዱ ነው

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ማኅበረሰቡን ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያስተምሩ ወይም እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ዕቅድ መያዙን አስታወቀ።

ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ የሆነበትን መንስዔ በተመለከተ በቀረበ ጥናት ላይ ውይይት ሲደረግ፣ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ላይ ስለተያዘው እቅድ አብራርተዋል።

ላለፉት ዓመታት(እሳቸው በኃላፊነት ከተሾሙ ጀምሮ)፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት በከፍተኛ ደረጃ ዝቅተኛ እንዲሆን ካደረጉ መንስዔዎች መካከል፣ የመምህራን ብቃትና የተነሳሽነት ማነስ ተጠቃሽ መሆናቸው ጠቁመዋል።

ችግሩን በአጭር ጊዜ ለመፍታት እንዲቻል የተለያዩ ተግበራት እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

''የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ'' የሚል መጠሪያ የተሰጠው አሠራር ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ዕቅድ የተያዘ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ "በአራት ዓመት የሚመረቅ ተማሪ፣ የሦስተኛ ዓመት ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ወደ አስተማረው ማኅበረሰበብ ተመልሶ ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት ይሰጥና (ማኅበረሰቡን እንዲያገለግል ይደረግና) እንዲመረቅ ይደረጋል"ሲሉ ተናግረዋል። ይህም ሲሆን የተማሪዎቹ መሠረታዊ ወጪ የሚሸፈን እንደሚሆንም አክለዋል።

ይህ አሰራር ለተማሪዎች ለራሳቸው የተግባር ትምህርት እንደሚሆንና የበለጠ እንዲበስሉ እንደሚያደርጋቸውም ተናግረዋል።

ተማሪዎች የመምህርነትን ሙያ ተላብሰው በዚያው ወደ ሙያው እንዲያመሩ ዕድል በመፍጠር ለጊዜውም ቢሆን በዘርፉ እየቀነሰ የመጣውን ወደ ሙያው የሚገባ የአስተማሪን ቁጥር ለማሳግ እንደሚረዳም ሚንስትሩ አብራርተዋል።

በቅርቡ በመምህራን ላይ በተደረገ ግምገማ ፣ 100,000 የሚደርስ የመምህራን ዕጥረት መኖሩ መታወቁን የተናገሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ አሰራሩ በከፍተኛ ደረጃ ያለውን የመምህራን ዕጥረት እንዲቀንስ የበኩልን እንደሚወጣ አስረድተዋል።

ወደ መምህርነት ሙያ የሚገቡ ሰዎችን ክፍተት ለማስተካከል ከተያዙ ዘርፈ ብዙ የማትጊያ ሥርዓቶች አንዱ፣ መምህራን በአገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ የራሳቸው ድርሻ እንዲኖራቸውና የኑሮ ውድነቱን እንዲቋቋሙ ለማድረግ፣ "የመምህራን ባንክ" ማቋቋም አንዱ እቅድ መሆኑን አንስተዋል።

ባንኩ "በአንድ ዓመት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባዋል ብለን እንጠብቃለን" ያሉት ሚኒስትሩ፣ በ2019 ዓ.ም ደግም በእርግጠኝነት ወደ የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ አሰራር እንደሚገባ ጠቁመዋል።
(ሪፓርተር)

ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት በኢትዮጵያ 43 ጋዜጠኞች ለእስርና እገታ እንደተዳረጉ IMS Good Journals የተሰኘው አለምአቀፍ ተቋም ሪፓርት አመልክቷል። ከታገቱት 3 ጋዜጠኞች መካከልም ...
04/01/2025

ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት በኢትዮጵያ 43 ጋዜጠኞች ለእስርና እገታ እንደተዳረጉ IMS Good Journals የተሰኘው አለምአቀፍ ተቋም ሪፓርት አመልክቷል። ከታገቱት 3 ጋዜጠኞች መካከልም ሁለቱ እስካሁን የደረሱበት አይታወቅም ተብሏል። ሪፓርቱን በዝርዝር ይከታተሉ

“በ43 ጋዜጠኞች ላይ ለእስርና እገታ ተፈፅሟል” የጊዜያዊ አሰተዳደር ማራዘሚያ አዋጅ ፀደቀ

❤️❤️❤️
03/31/2025

❤️❤️❤️

ኢድ ሙባረክ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉእንኳን አደረሳችሁ🙏🙏🙏❤️❤️❤️
03/29/2025

ኢድ ሙባረክ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ
እንኳን አደረሳችሁ
🙏🙏🙏❤️❤️❤️

🤔🤔🤔
03/27/2025

🤔🤔🤔

ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የቴሌኮምና የፋይናንስ ዘርፍን በበለጠ ክፍት እንድታደርግ መጠየቋ ተገለጸ ኢትዮጵያ በተቀመጠላት መርሐ ግብር መሠረት በመጪው የአውሮፓውያን ዓመት...
03/26/2025

ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የቴሌኮምና የፋይናንስ ዘርፍን በበለጠ ክፍት እንድታደርግ መጠየቋ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በተቀመጠላት መርሐ ግብር መሠረት በመጪው የአውሮፓውያን ዓመት መጋቢት ወር የዓለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን፣ የቴሌኮምና የፋይናንስ ዘርፉን አሁን ካለው በበለጠ ክፍት እንድታደርግ ከዓለም የንግድ ድርጅት ተጨማሪ ጥያቄ እንደቀረበለት ተገለጸ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ሰኞ መጋቢት 15 ቀን 2017 ዓ.ም. በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ በድርጅቱ የአባልነቷ ጥያቄ እንዲፀድቅ ከ19 አገሮችና ከዓለም ባንክ ድጋፍ ማግኘቷን ገልጸዋል፡፡ ከዓለም ንግድ ድርጅት ኢትዮጵያ ማሟላት አለባት በሚል የቀረቡ ጥያቄዎችን በተመለከተም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በዚህም መሠረት የቴሌኮምና የፋይናንስ ዘርፉን ኢትዮጵያ የበለጠ ክፍት እንድታደርግ የተለመዱ የድርድር ጥያቄዎች እንደቀረቡላት ጠቅሰው፣ በዋናነት ግን ኢትዮጵያ የበኩሏን ሚና የምትጫወተው ‹‹ኤልዲሲ›› (Least Developed Country) ጋይድ ላይን የሚባል መመርያ ተገን በማድረግ ነው ብለዋል፡፡ ይህ መመርያ ለታዳጊ አገሮች ኢኮኖሚ ወደ ዓለም ንግድ ድርጅት ሥርዓት እንዲገቡ ለማስቻል ተብሎ የተዘጋጀ ልዩ ጥቅም እንዳለ አክለው ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያም ይህንን ልዩ ጥቅም ተግባር ላይ ከማዋል አንፃር የበኩሏን ሚና እንደምትጫወት፣ ነገር ግን በድርጅቱ አንዳንድ ጊዜ ኢትዮጵያ እጅግ በጣም ካላደጉ አገሮች ተርታ የምትመደብ ነች ወይ? አሁን ያለው ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በራሱ እንደዚያ የሚያሳይነው ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች እንደሚነሱ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡

በአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን በዚህ ወር በተካሄደ የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድና ቀጣናን የተመለከተ ባለሙያዎችና የአገሮች የፋይናንስ ሚኒስቴሮች የተገኙበት ጉባዔ ላይ፣ በአኅጉሪቷ ስለሚገኙ እጀግ ውስን የሆነ ዕድገት ያላቸው አገሮች (LDC) የተመለከተ ጥናት በዓለም ካሉ 44 መሰል የዕድገት ደረጃ ካላቸው አገሮች 32 በአፍሪካ እንደሚገኙ የሚጠቀስ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ ግን ኢትዮጵያ አልተካተተችም፡፡

በተለይ ከዓለም የንግድ ድርጅት በኩል በጣም ፈታኝ የሆነ ወይም የማይመለስ አስቸጋሪ ጥያቄ አለመቅረቡን፣ ይሁን እንጂ የጅምላ ንግድ፣ የችርቻሮ፣ የአስመጪና የላኪነት ንግድ ፈቃድ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ቢደረግም ሕጎችን ከማሻሻል አንፃር ክፍተቶች አሉ የሚሉ ጥያቄዎችን እንደቀረው አክለው ገልጸዋል፡፡

የንግድ ዘርፉ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሲደረግ ቅድመ ሁኔታዎች እንደነበሩትና ቅድመ ሁኔታዎቹ እንዲነሱ ጥያቄ ቢቀርብም፣ ይህንን ክፍት ማድረግ የማይቻልበት ምክንያት ማብራሪያ እንደተሰጣቸው አስረድተዋል፡፡

በሌላ በኩል ታሪፍን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ካሳሁን (ዶ/ር) ማብራሪያ ሲሰጡ እንደገለጹት፣ የአገሪቱን ገቢ የማመንጨት አቅም በሚጎዳ መንገድ ድርድር አይደረግም ብለዋል፡፡

ታሪፍን በተመለከተና ከገቢ ጋር የሚያያዝ ጉዳይ
ከገቢዎች ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴርና ከጉምሩክኮሚሽን ጋር ውይይት ተደርጎና ተሠልቶ ስለሚሆን፣ ‹‹ምንም ታሪፍ ዝቅ ብናደርግ ምን ያህል ገቢ እናጣለን የሚለው ተሠልቶ ነው፤›› ሲሉ ካሳሁን (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞ ገቢ ላይ የተወሰነ ተፅዕኖ ቢኖረውም ገቢን አሽመድምዶ አጠቃላይየመንግሥትን እጅ የሚያስር እንዳልሆነ ገልጸው፣ ገቢና ወጪን እኩል ለማስኬድ ኢትዮጵያ በጣም ትጎዳለች የተባለው ጉዳይና እስካሁን የውጭ ባለሀብቶች እንዳይገቡ የተደረገበት ሁኔታ ኢትዮጵያን ምንም እንዳልጠቀማት ያሳያል ብለዋል፡፡

በተለይ በቅርቡ የውጭ ባለሀብቶች ገብተው እንዲሠሩ ክፍት ከተደረገ በኋላ፣ የኤክስፖርት ገቢ በፍጥነት ማደግ መጀመሩን ለአብነትም ባለፈው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በፓርላማ የስምንት ወራት አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት 4.5 ቢሊዮን ዶላር ከኤክስፖርት መገኘቱን መናገራቸውን አስታውሰዋል፡፡

በዚህ መሠረት የኤክስፖርት ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት መደረጉ ጥሩ ነገር የሚያሳይ መሆኑን፣ ኢትዮጵያም የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ስትሆን የሸቀጦች ማራገፊያ ትሆናለች የሚለውን ነገር ገልብጦ ማየት እንደሚጠይቅ አስረድተዋል፡፡

ከ2010 እስከ 2015 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ከ85 ቢሊዮን ዶላር ወደ 205 ቢሊዮን ዶላር ጂዲፒ መሄድ ከተቻለ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አሁን ባለው ሁኔታ በሚቀጥሉት ስድስት ዓመታት 405 ቢሊዮን ዶላር ጂዲፒ እንደሚደርስ ገልጸዋል፡፡

በተለይ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ትንንሽ የአፍሪካ አገሮች ያልፈሩትን ኢትየጵያ የምትፈራው ለምንድነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ የድርጅቱም አባል መሆን ተደማረና ተገማች የገበያ ዕድል ለመፍጠር እንጂ ሌላ ነገር እንደሌለው አክለዋል፡፡

ተደማሪና ተገማች የገበያ ዕድል ለመፍጠር በሚደረግ ሒደት ውስጥ መወዳደር ከተቻለ፣ እንዲሁም ራስን ከዓለም ኢኮኖሚ ጋርየሚናበብ ማድረግ ከተቻለ በውድድር ውስጥ የሚገኙ ውጤቶች እንዳሉ አስረድተዋል።

ጉዳዩም ለቀጣይ ትውልድ የሚጠቅም እንደሆነና ነገር ግን ይህንን በመፍራትና በመዝጋት ውድድር የማይበረታታበት ምክንያት እንዳለ ጠቅሰው፣ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ብትሆን ብዙም የሚያሠጋት ነገር እንደሌለ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስትደራደር አንዱ ጥያቄ የነበረው፣ ( ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ከሆነች የእነሱ ሸቀጣ ሸቀጥ ማራገፊያ ነው የምንሆነው› የሚል እንደሚገኝበት ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ላለመሆን በዘጋችው መንገድ ያገኘችው ምንም ጥቅም እንደሌለ ገልጸው፣ በተለይ ባለፉት ጊዜያት ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ባይደረግ ኖሮ እ.ኤ.አ. 2026 ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ትሆናለች ብሎ ማሰብ እንደማይቻል አክለዋል፡፡

ነገር ግን አሁን ባለው ሁኔታ ስድስተኛውና ሰባተኛው የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር እ.ኤ.አ. በ2025 እንደሚካሄድ ገልጸው፣ እ.ኤ.አ. በ2026 የካቲት ወይም መጋቢት ወር በካሜሩን በሚካሄደው ጉባዔ ኢትዮጵያ አባል ሆነች የሚል የምሥራች እንደሚሰማ አስረድተዋል።

አምስተኛው የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የሥራ ቡድን አባላት ጉባዔ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ መካሄዱን ገልጸው፣ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሠራቻቸውን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ማቅረቧን አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ማመልከቻ በማቅረብ ድርድር የጀመረችው በ1996 ዓ.ም. እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ ከዚህ ቀደም ብሎ ድርጅቱ ሲመሠረት (እ.ኤ.አ. በ1948) ጠቅላላ የንግድና የታሪፍ ስምምነት ወይም

460 ሺህ ፎርጂድ የትምህርት ዶክመንት ወደ ህጋዊ መስመር እንዲገባ ሊደረግ መሆኑ ተጠቁሟል በርካታ የፖለቲካ አመራሮች ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ስላላቸው ዶክመንቶችን የመለየት ሂደት እክል ...
03/26/2025

460 ሺህ ፎርጂድ የትምህርት ዶክመንት ወደ ህጋዊ መስመር እንዲገባ ሊደረግ መሆኑ ተጠቁሟል

በርካታ የፖለቲካ አመራሮች ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ስላላቸው ዶክመንቶችን የመለየት ሂደት እክል ገጥሞታል ተባለ

(መሠረት ሚድያ)- ሕገወጥ እና ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ መስፋፋቱን ተከትሎ በመንግሥት የተወሰዱ እና እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ችግሩን ከመቅረፍ ይልቅ መመርያ በማውጣት ሀሰተኛ ትምህርት ያላቸውን ህጋዊ በማድረጉ ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ምንጮች ተናገሩ።

460 ሺህ ፎርጂድ የትምህርት ዶክመንት ያላቸው ግለሰቦች ሰነዶቻቸው ህጋዊ ወደማድረጉ እየተሄደ መሆኑም ታውቋል።

በመመርያ 990/2016 መሰረት እንዲሁም በኢቲቪ አማካኝነት መስከረም 2016 ዓ/ም ላይ 500 ሺህ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች እንዳሉ ለህዝብ መነገሩ ይታወሳል።

ይሁንና የትምህርት ሚኒስትሩ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ከቀናት በፊት 'እውነት ወይስ ሀሰት?' በሚል በተደረገ አንድ ውይይት ላይ ለቀረበላቸው የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን የተመለከተ ጥያቄ ሲመልሱ ተጣርቶ የተገኘው 40 ሺህ መሆኑን መግለፃቸው ታውቋል።

"ይህ ማለት ከ500 ሺህ ውስጥ 460 ሺህ ፎርጅድ ወይም የተጭበረበረ ትምህርት ህጋዊ እየተደረገ ነው ማለት ነው" በማለት ጉዳዩን ለአመታት ሲከታተሉ የነበሩ እና ለመንግስትም ጥቆማ ሲሰጡ የነበሩ አንድ ግለሰብ ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

"በየግዜው የሀሰተኛ ትምህርት ማስረጃን የማጣራት ጉዳይ እየተጀመረ ይቋረጣል፣ በመንግስት መዋቅር ውስጥ በሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ወደ ስልጣን የመጡ የስራ ሃላፊዎች እና ያለሙያቸው ሙያተኛ የሆኑ ሰራተኞች እስካልተወገዱ ድረስ በሀገራችን የሚስተዋለው የሌብነትና የመልካም አስተዳደር ችግር ይቀረፋል ብሎ ማመን አስቸጋሪ ነው" የሚሉት ግለሰቡ ይህን ሀላፊነት በዋናነት መውሰድ የሚገባው የትምህርት ሚኒስቴር እንኳን የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን ማጣራት ሲገባው በተለያየ ጊዜ መመርያዎችን በማውጣት ፎርጅድን ህጋዊ ማድረጉን ተያይዞታል ብለዋል።

የካቲት 2016 ዓ/ም ላይ የወጣው መመርያ የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ 1152/2011 ባወጣው አዋጅ ላይ በአንቀጽ 40 መሰረት የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ሙሉ በሙሉ ጥሰው ሰርተፍኬት ያገኙትን ህጋዊ ያደርጋል ያሉን ሌላ የሚኒስቴር ቢሮው ምንጫችን ደግሞ አዋጁን ለማስፈጸም የወጣውን መመርያ 5/2004 ላይ ትምህርት ሚኒስቴር ያመጣውን ሳይከተሉ የተማሩትን ህጋዊ ያደርጋል ብለዋል።

"የከፍተኛ ትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በጣም እየተበራከተ መምጣቱን ከቁጥራዊ መረጃ ጋር አያይዞ ለህዝብ ሲገልጽ ቢቆይም በፖለቲካ ውሳኔ በተቋሙ የተጣሩትን ሀሰተኛ ትምህርት ማስረጃ በአሁኑ ሰዓት ህጋዊ ተደርገዋል" ያሉት ስሜ አይጠቀስ ያሉት ምንጫችን ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጣራቱን ስራ የሚሰራው አካል በፖለቲከኞች ጣልቃ ገብነት ስራውን መስራት ካልቻለ የማጣራት ሂደቱን አስቸጋሪ ያረገዋል ብለዋል።

"ይህን የምለው ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች ጭምር ሀሰተኛ ትምህርት እንዳላቸው ፀሀይ የሞቀው ሀቅ በመሆኑ ነው" በማለት ጉዳዩን አብራርተዋል።

የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ከ1995 ጀምሮ እስከ 2014 ዓ.ም መረጃቸውን ለተቋሙ ካስገቡ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ እስካሁን ከተመረቁ 1.1 ሚሊየን ተማሪዎች መካከል ከ100 ሺህ በላይ የሚሆኑት ተማሪዎች ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የያዙ መሆናቸውን ይፋ አድርጎ ነበር።

Meseret Media

አንድ አውቶብስ ሙሉ መንገደኞች የተሰወሩበት ሰሞነኛው እገታመጋቢት 07 ቀን 2017 ዓ.ም (ዶይቼ ቬለ) መነሻውን ከአዲስ አበባ አድርጎ ወደ ደብረማርቆስ ሲያመራ ከነበረው የሕዝብ ማመላለሻ አ...
03/25/2025

አንድ አውቶብስ ሙሉ መንገደኞች የተሰወሩበት ሰሞነኛው እገታ

መጋቢት 07 ቀን 2017 ዓ.ም (ዶይቼ ቬለ) መነሻውን ከአዲስ አበባ አድርጎ ወደ ደብረማርቆስ ሲያመራ ከነበረው የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ታግተዋል የተባሉ ከ50 በላይ ሰዎች እስካሁን የደረሱበት እንደማይታወቅ እየተነገረ ነው።

ኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከገርባ ጉራቻ ከተማ ቅርብ ቦታ ላይ በምትገኘው አደገኛ ስፍራ ተብላ በምትገለጸው አሊዶሮ ተፈጸመ በሚባለው በዚህ የአንድ አውቶብስ ሙሉ ተሳፋሪዎች እገታ እስካሁን የሚታወቀውም ጥቂት ነው። የዞኑ መንግሥት መዋቅርም ጉዳዩን እያጣራሁ ነው ይላል።

ማሩ ሽፌ ይባላል። የዕቃ ጫኝ ከባድ ተሽከርካሪ ሾፌር ነው። ከአዲስ አበባ በጎጃም በማቋረጥ የንግድ ሸቀጦችን ጭኖ ወደ ጎንደር ወሮታ እና አካባቢው መመላለስ የሰርክ ተግባሩ ነው። እንደወትሮው ሁሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስጋት በነገሰበት በዚሁ የአዲስ አበባ ጎጃም መንገድ ላይ ሸቀጦቹን ጭኖ እሑድ መጋቢት 07 ቀን 2017 ዓ.ም. ማልዶ በመነሳት መንገዱን ይጀምራል። ማሩ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገረው በዕለቱ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ፊቼ እና ገርባ ጉራቻን እንዳለፉ ወትሮም ለአሽከርካሪዎች ፈታኝ ስፍራ ተደርጋ በምትታየው የደገም ወረዳዋ አሊዶሮ ላይ አንድ ነገር ይመለከታል።

«እሑድ ቀን 2፡30 ሰአት ነው። መኪኖች ተከታትለው ሲወጡ እኔ አራተኛው ነበርኩ። ሸቀጥ ጭኜ እየተጓዝኩ ነበር። ግዮን ባስ ኤ-30273 ኢት የሚል ታርጋ ያለው ሰዎችን የጫኔ ባስ ፊትለፊት በጥይት የተመታው አባይ ባስ ጥሶ ሲያልፍ ግዮን ባስን ጎማውን መትተው አስቆሙት። ያንን ስንመለከት እኛ ወደኋላ ነው ለመዞር የወሰነው። ከዚያም ፊቼ አካባቢ ዞረን ቆምን። በዓይኔ የተመለከትኩት ግዮን ባስ ውስጥ የነበሩን ተሳፋሪዎች በሙሉ ፀጉራቸውን ያሳደጉ ታጣቂዎች ሲያስወርዱዋቸው ነበር። በሰዓቱ መኪናውን ጥየው እንዳልሄድ የብዙ ሚሊየን ብር ዕቃ ስለጫንኩ መኪናውን እንዳያቃጥሉት ፈርቼ ወደኋላ ለመዞር ወሰንኩ» ይላል ማሩ።

መንገደኞቹ በሙሉ ወደ አማራ ክልል ደብረማርቆስ ከተማ የሚጓዙ ነበሩ ያሉት የዐይን እማኝ ታጣቂዎች መንገደኞቹ ላይ እገታ የፈጸሙት አራት ተሸከርካሪዎች ተከታትለው በሚሄዱበት ወቅት መሆኑን ገልጸዋል። በወቅቱ እገታውን የፈጸሙ ታጣቂዎች ከመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ቢያደርጉም ታጋቾችን ግን ማስጣል እንዳልተቻለ ነው የዓይን እማኙ የተናገሩት።

«ተሳፋሪዎቹን አውርደው እየገፉ ሲወስዷቸው በቅርብ ርቀት እየተመለከትናቸው ነበር» ያሉን አስተያየት ሰጪው የዓይን እማኝ፤ ተሽከርካሪው ከተመታ በኋላ የፀጥታ ሃይሎች አካባቢው ላይ ዘግይተው ቢደርሱም ታጋቾችን ማስጣል ግን እንዳልተቻላቸው አስረድተዋል። የፊት ጎማውን የተመታው መንገደኞች የታገቱበትን ተሸከርካሪ ግን በዚያው ዕለት እሑድ ማታውን የፀጥታ ሃይሎች ባሉበት ማንሳት መቻሉን ገልጸዋል። ከተሽከርካሪው ውስጥ ሾፈርና ረዳቱን ጨምሮ 58 ሰዎች መወሰዳቸውን እንደሚያውቁ የገለጹት አስተያየት ሰጪው አሽከርካሪ «ታግተው ከተወሰዱት መንገደኞቹ መካከል አንዲት የደብረማርቆስ ከተማ ነዋሪ ደውላ 1.5 ሚሊየን ብር መጠየቋና እርዳታ እየተሰባሰበላት» መሆኑን ገልጸዋል።

አስተያየታቸውን የጠየቅናቸው አንድ የፈለገ ጊዮን አውቶብስ ሠራተኛ ማንነታቸውን ሳይገልጹ በድርጅቱ ንብረት አውቶብስ ላይ የድርጊቱን መፈጸም ለዶቼ ቬለ አረጋግጠዋል።

መንገደኞቹን ያሰለቸው የተደጋገመው እገታ

በዕለቱ ከ50 በላይ መንገደኞች ከታገቱበት አውቶብስ በተጨማሪ በርካታ ተሽከርካሪዎች የታጣቂዎች ጥቃት ኢላማ ነበሩ ያሉት የዐይን እማኞች፤ በዚህ አካባቢ በታጣቂዎች እየታገቱ ገንዘብ መጠየቁ የቆየና መንገደኞችን ስጋት ላይ የጣለ፤ አሽከርካሪዎችን ደግሞ ያሰለቸ ጉዳይ እንደነበርም አስታውሰዋል። አሊዶሮ ተብሎ የሚታወቅ ይህ ስፍራ ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ከደባርቅ እና ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተነስተው ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ የነበሩ በርካታ ተማሪዎችን ጨምሮ ከ100 በላይ ሰዎች በታጣቂዎች የታገቱበት ቦታ ነው።

አሁን ተፈጸመ ስለተባለውና የታጋቾች እጣፈንታ በውል ባልታወቀበት ጉዳይ ላይ ዶይቼ ቬለ አስተያየታቸውን እዲሰጡ የጠየቃቸው ለሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከፈለው አደሬ «መረጃውን በማጣራት ላይ ነን» የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

ከእገታው ጋር ተያይዞ በተደጋጋሚ ስሙ የሚጠቀሰው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎቹ በአካባቢው በስፋት እንደሚንቀሳቀሱ ባያስተባብልም በዚህ አካባቢ ተደጋግሞ ስለሚፈጸመው እገታ ማስተባባያ ሲሰጥ ቆይቷል። ኦነሰ በአሁኑ ከአዲስ አበባ ተነስተው ወደ ደብረማርቆስ በመጓዝ ላይ ሳሉ ደገም ወረዳ ውስጥ ታገቱ ስለተባሉ መንገደኞች ግን በመመርመር ላይ መሆኑን ባለፈው ሳምንት በይፋዊ ማኅበራዊ ገጹ ባወጣው አጭር መግለጫ አስታውቋል። የሆነ ሆኖ እስካሁን የተወሰዱበት ስፍራ ያልታወቀው መንገደኞቹ፤ በአካባቢው የተደጋገመው የጸጥታ ችግሩ ሰለባ ስለመሆናቸው ነው የሚነገረው።

ምንጭ:- ዶይቼ ቬለ

ለመቄዶንያ የገቢ ማሰባሰቢያ 800 ሚልዮን ብር ደርሰናል!!!እናመሰግናለን!!ይክበር ይመስገን!!በጽናት እንቀጥላለን!!ያሬድ ሹመቴ
03/25/2025

ለመቄዶንያ የገቢ ማሰባሰቢያ 800 ሚልዮን ብር ደርሰናል!!!
እናመሰግናለን!!

ይክበር ይመስገን!!
በጽናት እንቀጥላለን!!
ያሬድ ሹመቴ

እሳቱ በቁጥጥር ሥር ውሏልበአዲስ አበባ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ሰባራ ባቡር አካባቢ የተፈጠረውን የእሳት አደጋ መቆጣጠር መቻሉን ክፍለ ከተማው አስታውቋል፡፡ ባልታወቀ ምክንያት የ...
03/25/2025

እሳቱ በቁጥጥር ሥር ውሏል

በአዲስ አበባ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ሰባራ ባቡር አካባቢ የተፈጠረውን የእሳት አደጋ መቆጣጠር መቻሉን ክፍለ ከተማው አስታውቋል፡፡

ባልታወቀ ምክንያት የተከሰተው እሳት አደጋ በእሳት አደጋ ሰራተኞች፣ ነዋሪዎች እና በፀጥታ አካላት የተነሳውን እሳት መቆጣጠር መቻሉ ነው የተነገረው።

የእሳት አደጋ መንስኤውን በቀጣይ እንደሚያሳውቅ የገለጸው ክፍለ ከተማው፤ በአደጋው ከንብረት ውጭ በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ አደጋም ጉዳት አለመኖሩን አመላክቷል፡፡

ጉዳዩን ለማስተባበል የተሄደበት ርቀት እንደ ሀገር የገባንበትን ዝቅጠት ያሳያል!ማስተባበያው ወጣቷ የዩኒቨርስቲው ተማሪ አልነበረችም አይለንም፣ ብቻ "ዩኒቨርሲቲው የፋርማሲ ትምህርት ሲሰጥ በ2...
03/24/2025

ጉዳዩን ለማስተባበል የተሄደበት ርቀት እንደ ሀገር የገባንበትን ዝቅጠት ያሳያል!

ማስተባበያው ወጣቷ የዩኒቨርስቲው ተማሪ አልነበረችም አይለንም፣ ብቻ "ዩኒቨርሲቲው የፋርማሲ ትምህርት ሲሰጥ በ2013 የሁለተኛ ዓመት ተማሪ እንዳልነበረው ይገልጻል" ብሎ ለጭብጡ አላስፈላጊ የሆነ ነገር መዞ ክስ ለመመስረት ይዝታል። ለመሆኑ እንደ ተቋም ተማሪዎቹ ሲታገቱ ምን አደረገ?

ኢቢኤስ ላይ የተደረገውን ማስፈራራት ሳይ ትዝ ያለኝ ይህን ዜና በወቅቱ ለ Associated Press ስፅፍ የደረሰብኝ ወከባ ነበር

አንዴ የታገተ ተማሪ የለም፣ ሌላ ግዜ በሙሉ ተለቀዋል፣ ቆይተው ደግሞ ስድት ብቻ ነው የቀሩት እያሉ ጉዳዩን ሲያምታቱ የነበሩት የመንግስት ባለስልጣናት ነበሩ፣ እኛንም ቢሯቸው እየጠሩ ዜና መስራት እንድናቆም ሲጠይቁ ነበር። አሁን ጉዳዩ ቆይቶ ለህዝብ ሲደርስ ደግሞ ሌላ ማስፈራርያ።

በዚህ አካሄዳቸው ልጅቱንም ሊያስፈራሩ ይችላሉ፣ ስለዚህ በቅርብ እንከታተላለን። ልጅቱን ለማገዝም እንቅስቃሴ እናደርጋለን፣ እስካሁን በስልኳ ለማግኘት ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም።

በነገራችን ላይ፣ የእገታ ዜና ሰልችቶን ዜና ሳይመስለን የምናልፍበት እጅግ አሳዛኝ ሁኔታ ተፈጠረ እንጂ በየሳምንቱ የሚታገቱትም እጣ ፈንታቸው ይሄው የልጅቷ ነው። ባለፈው ሳምንት ብቻ ሁለት ሙሉ አውቶቡስ ህዝብ ታግቷል፣ የሁለት አመት ህፃን ልጅን ጨምሮ።
በቃችሁ ይበለን።
(Via Elias Meseret)

ፀሀዩ መንግስታችን ያበሰረው ዜናከዛሬ መጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ጨምሯል።ዝርዝሩ እነኾ:-በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ምርቶች የችርቻ...
03/23/2025

ፀሀዩ መንግስታችን ያበሰረው ዜና

ከዛሬ መጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ጨምሯል።
ዝርዝሩ እነኾ:-

በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ:-

ቤንዚን 112.67
ኬሮሲን 107.93p!
ነጭ ናፍጣ 107.93
ቀላል ጥቁር ናፍጣ 109.22
ከባድ ጥቁር ናፍጣ 106.75 ብር በሊትር የሚሸጥ ይሆናል።

4.2 ሚልየን ብር ቅጣት በአንድ ቀን ብቻፖሊስ ጣብያዎች ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ገንዘብ በመቅጣት ገቢ እንዲያስገቡ መታዘዛቸው ተሰማ - "እያንዳንዱ የፖሊስ ጣብያ በቅጣት የሚያስገባው ...
03/20/2025

4.2 ሚልየን ብር ቅጣት በአንድ ቀን ብቻ
ፖሊስ ጣብያዎች ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ገንዘብ በመቅጣት ገቢ እንዲያስገቡ መታዘዛቸው ተሰማ

- "እያንዳንዱ የፖሊስ ጣብያ በቅጣት የሚያስገባው የገንዘብ ኮቴ ተጥሎበታል፣ በዛሬው እለት ብቻ 4.2 ሚልየን ብር ተሰብስቧል"

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የፖሊስ አባላት ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን ገንዘብ በመቅጣት ገቢ እንዲያስገቡ መታዘዛቸው ታውቋል።

ለመሠረት ሚድያ የደረሰው ጥቆማ እንደሚያሳየው የየክፍለ ከተማው ስራ አስፈፃሚዎች በየጊዜው የፖሊስ አዛዦችን እየሰበሰቡ ገንዘብ በተለይ ከነጋዴዎች እና ድርጅቶች በአስገዳጅ ሁኔታ እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ተላልፎላቸዋል።

"በእያንዳንዱ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ከላይ የተወሰነ ኮታ አለ፣ ያንን በተሰጠን ጊዜ ገደብ ሰብስበን ማስገባት ግዴታችን ነው" ብለው ቃላቸውን የሰጡ አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር በዚህ ምክንያት ፖሊስ መደበኛ ስራውን ጥሎ ቤት ለቤት እና በየድርጅቱ ገንዘብ ሲጠይቅ ይውላል ብለዋል።

ሌላኛው ደግሞ "ገንዘብ ከምንሰበስብባቸው መንገዶች መሃከል ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ገንዘብ መቅጣት፣ አስገዳጅ የህዳሴ ኩፖን ማስገዛት፣ ለኮሪደር ልማት በሚል ከነጋዴዎች መዋጮ መጠየቅ ናቸው ያልተስማማ ካለ የንግድ ፈቃድ እስከመታገድ ይደርሳል" በማለት ሁኔታውን አስረድተዋል።

ከሰሞኑ በርካታ የመንግስት ሚድያዎች ፍሳሽ የለቀቁ፣ መንገድ ያበላሹ፣ እና ያልተፈቀደ ስራ የሰሩ በማለት ድርጅቶች ከአስር ሺዎች እስከ መቶ ሺህ ብሮች እንደተቀጡ መዘገባቸው ይታወሳል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዛሬ ባወጣው አንድ መግለጫ በዛሬው ቀን ብቻ ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን 4.2 ሚልዮን ብር እንደቀጣ አስታውቋል።

ባለስልጣኑ እንዳለው በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 1.3 ሚልዮን ብር፣ በአቃቂ ክ/ከተማ 800 ሺህ ብር፣ በየካ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 500 ሺህ ብር በዛሬው እለት ብቻ ከቅጣት ተሰብስቧል።

ምንጭ:- መሠረት ሚድያ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረ ጃርሶ ወረዳ ልዩ ስሙ "አሊዶሮ መውጫ' በተባለ ሥፍራ ታጣቂዎች መጋቢት 08, 2017ዓ.ም እኩለ ቀን ላይ የአንድ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ተሳፋሪዎችን ...
03/18/2025

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረ ጃርሶ ወረዳ ልዩ ስሙ "አሊዶሮ መውጫ' በተባለ ሥፍራ ታጣቂዎች መጋቢት 08, 2017ዓ.ም እኩለ ቀን ላይ የአንድ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ተሳፋሪዎችን በሙሉ አፍነው መወሰዳቸውን ዋዜማ ሰምታለች።

ታጣቂዎቹ እገታውን የፈጸሙት፣ ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል ሲጓዝ በነበረ "ፈለገ ግዮን" በተሰኘ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ተጓዦች ላይ እንደኾነ ምንጮች ተናግረዋል። ታጣቂዎቹ አፍነው ከወሰዷቸው ተሳፋሪዎች መካከል በርካታ ሴቶች እንደሚገኙበት ምንጮች ገልጸዋል። በዚሁ ሥፍራ በተደጋጋሚ ተመሳሳይ የእገታ ወንጀሎች እንደሚፈጸሙ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ መዘገቡ አይዘነጋም።
[ምንጭ:-ዋዜማ]

 በአፍሪካ ለመኖርያ ምቹ የሆኑ አስር ከተሞች በማለት Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን) ስላወጣው ዘገባ 👇👇ቢዝነስ ኢምፓየርስ አፍሪካ ከአፍሪካ ለኑሮ ምቹ ናቸው ያላቸውን አስር ከተሞች ...
03/18/2025


በአፍሪካ ለመኖርያ ምቹ የሆኑ አስር ከተሞች በማለት Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን) ስላወጣው ዘገባ 👇👇

ቢዝነስ ኢምፓየርስ አፍሪካ ከአፍሪካ ለኑሮ ምቹ ናቸው ያላቸውን አስር ከተሞች ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

እንደ ድረገጹ ዘገባ በመስፈርቶቹ ከተሞቹ ያላቸው የኑሮ ሁኔታ፣ የሚፈልጉትን መገልገያዎች ከማግኘት አንጻር ያላቸው ምቹነት፣ መሰረተ ልማት እና አጠቃላይ የከተሞቹ እንቅስቃሴን መሰረት ያደረገ ነው። በማለት ድህረገፁን ዋቢ በማድረግ አዲስ አበባን በአንደኛ ደረጃ አስቀምጧል ነገር ግን ቢዝነስ ኢምፓየርስ አፍሪካ
ባወጣው ዘገባ አዲስ አበባን በ 8ኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል።

Address

Jersey City, NJ

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tobia Tube/ጦቢያ ቲዩብ:

Videos

Share