Ethio Tinsae Media

Ethio Tinsae Media Ethio Tinsae Media (ETM) ኢትዮ ትንሣኤ ሚዲያ
(2)

መምህር ሰሎሞን ሀይሌመምህር ዮሐንስ ለማመምህር ዮናስ ፍቅረበክርስቲያን ካውንስሊንግ ሁለተኛ ዲግሪ (MTH) በመመረቃችሁ ኢትዮ ትንሣኤ ኤዲቶሪያል አባላት የተሰማንን ልባዊ ደስታ እንገልጻለን:...
07/03/2024

መምህር ሰሎሞን ሀይሌ
መምህር ዮሐንስ ለማ
መምህር ዮናስ ፍቅረ

በክርስቲያን ካውንስሊንግ ሁለተኛ ዲግሪ (MTH) በመመረቃችሁ ኢትዮ ትንሣኤ ኤዲቶሪያል አባላት የተሰማንን ልባዊ ደስታ እንገልጻለን::

እንኳን ደስ አላችሁ!

ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም
ኢትዮ ትንሣኤ ሚዲያ

Photo Credit to Photo Me

ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫበስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ...
06/06/2024

ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቅዱሳን አበው ሐዋርያት ትውፊት በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባውን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በርካታ አጀንዳዎችን በመቅረጽ ውይይት ሲያካሄድ ሰንብቷል፡፡

ምልዓተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት፣ ለመንፈሳዊ ዕድገትና ለምእመናን ደኅንነት ትኩረት በመስጠት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡

በዚሁ መሠረት፡-

፩.በቅድስት ቤተ ክርስቲያንና በሀገራችን መንግሥት መካከል ሊኖር ስለሚገባው መልካም የሥራ ግንኙነት በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሚመካከር የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ልዑክ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፤

፪.በመላው ሀገራችን በተፈጠሩ ግጭቶች፣ አለመግባባቶችና የሰላም ዕጦት በርካታ የሰው ሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት እንደቀጠለ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን በእጅጉ አሳዝኗል፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከግጭትና ከጥፋት ድርጊት ተቆጥበው የተፈጠረውን አለመግባባትና ግጭት በውይይትና በምክክር እንዲፈቱ እና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንኦት ጥሪውን ያቀርባል፤

፫.በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት ምክንያት ለፈረሱ የቤተ ክርስቲያናችን ይዞታዎች የከተማ አስተዳደሩ ምትክ ቦታ በመስጠትና ቤተ ክርስቲያናችን ወደ መልሶ ማልማት እንድትገባ ድጋፍ በማድረግ፤ በተለይም ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በፈረሰው የጽርሐ ምኒልክ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃ ምትክ በከተማ አስተዳደሩ ሙሉ ወጭ ተጨማሪ ምድር ቤትና የቦታ ስፋት ያለው B+G+4 ሕንፃ ገንብቶ ለማስረከብ ቃል በመግባትና የቤተ ክርስቲያናችን የበላይ ኃላፊ አባቶች በተገኙበት የመሠረት ድንጋይ እንዲጣል ማድርጋቸውን ቅዱስ ሲኖዶስ ከምስጋና ጋር የተቀበለው ሲሆን በተሰጠን ምትክ ቦታ ላይም የከተማው ፕላን በሚፈቅደው መሠረት የመልሶ ማልማት ሥራው እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

፬.የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት አዋጅ መረዳት እንደሚቻለው ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክርና በውይይት ለመፍታት የተቋቋመ መሆኑን ተረድተናል፡፡ ይሁን እንጅ ሀገረ መንግሥትን ከመመሥረት ጀምሮ በአስታራቂነትና በሰላም ግንባታ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ለሆነችው እናት ቤተ ክርስቲያን እስከአሁን ድረስ በይፋ የቀረበ የተሳትፎ ጥሪ ሳይኖር ኮሚሽኑ የተሳታፊ ልየታንና አጀንዳ መረጣ አጠናቆ ወደ ምክክር ትግበራ እየገባ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን ቅር አሰኝቷል፡፡ በመሆኑም የቤተ ክርስቲያኒቱ ተሳትፎና አጀንዳ የማቅረብ መብቷ እንዲረጋገጥ ከኮሚሽኑ ጋር በመነጋገር ጉዳዩን ተከታትሎ ለፍጻሜ የሚያበቃ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡

፭.የብፁዓን አባቶች የዝውውርና የአህጉረ ስብከት ሥያሜን አስምልክቶ የቀረቡ ጥያቄዎችን ምልዐተ ጉበኤው ተመልክቶ ተገቢውን ውሳኔ አሳልፏል፤

፮.የሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በረቂቅ አዋጁ ሊሻሻሉ ይገባቸዋል ብሎ ያመነባቸውን የማሻሻያ ሐሳቦች በማዘጋጀት ለሚመለከተው መንግሥታዊ ተቋም እንዲላክና ረቂቅ አዋጁ ከመጽደቁ በፊት የተሰጡት የማሻሻያ ሐሳቦች በረቂቁ ስለመካተታቸው ክትትል የሚያደርግ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡

፯.በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ ተመሥርቶ አባታዊ ምክርና ተግሣጽ ማስተላለፍ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው መሆኑ ቢታወቅም በሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተፈጠሩ አለመግባባቶች የተከሰቱትን ወቅታዊ ችግሮች አስመልክቶ እየተላለፉ ያሉ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ መልእክቶችን ቅዱስ ሲኖዶስ የማይቀበላቸውና በጥብቅ የሚቃወማቸው መሆኑን እየገለጸ ወደፊት እንዲህ ዓይነት ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጸም ለማድረግ ይቻል ዘንድ ወጥ የሆነ የመግለጫ አሰጣጥና የትምህርተ ወንጌል ተልእኮ ሕገ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምልዐተ ጉበኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

፰.ግብረ ሰዶማዊነትና የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በሕገ ተፈጥሮም ሆነ በሰው ልጅ የሰብዓዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው፣ ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር መለኮታዊ ፈቃዱ በተገለጠባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ፈጽሞ የተከለከለ፣ በቀኖናተ ቤተ ክርስቲያን፣ በፍትሕ መንፈሳዊና በፍትሐ ብሔር ድንጋጌዎች፣ በሥነ ልቦና ደንቦች የተወገዘ፣ ሥነ አእምሮዊ ሚዛንን የሚያዛባ፣ ግለሰባዊ ማንነትን፣ ቤተሰባዊ ሕይወትን፣ ማኅበራዊ ትሥሥርን የሚጎዳ ተግባር በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ እያወገዘ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና የግብረ ሰዶማዊነትን ኃጢአት በተመለከተ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አቋም በሚገልጽ መልኩ ራሱን ችሎ ዓለም አቀፋዊ ይዘቱን ባገናዘበ ሁኔታ ዝርዝር መግለጫ እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

፱.በደቡብ የሀገራችን ክፍል የቤተ ክርስቲያኒቱን አብነት ትምህርት ከማስፋፋትና ከፍ ያለ መዐርግ ከመስጠት አንፃር የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዝጊቲ ደብረ ሰላም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን የአራቱ ጉባኤያት ማስመስከሪያ ትምህርት ቤት እንዲሆን በቀረበው ጥናት መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ ለምሥክር ጉባኤ ቤቱ ዕውቅና በመስጠት ወደ ትግበራ እንዲገባ ወስኗል፡፡

፲.ከሀገራችን ውጭ ባሉ አህጉረ ሰብከት መደበኛ አገልግሎት ለመስጠት የሚላኩ አገልጋዮች በክፍሉ ሊቀጳጳስ ሲጠየቅ በሙያ ብቃታቸው፣ በምግባራቸውና በመንፈሳዊነታቸው የተመሰከረላቸው አገልጋዮች ከሁሉም አህጉረ ስብከት በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አቅራቢነት በውድድር እየተለዩ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲላኩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

፲፩.የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ የዐሥር ዓመት መሪ ዕቅድ በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲገባ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ በዚሁም መሠረት ለአፈጻጸሙ ያመች ዘንድ በባለሙያዎች ተዘጋጅቶ የቀረበውን መዋቅራዊ አደረጃጀት በማጽደቅ በሕገ ቤተ ክርስቲያኑና በቃለ ዓዋዲው ተካቶ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

፲፪.በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተዘጋጅቶ የቀረበውን የ2017 ዓ.ም. ዓመታዊ በጀት በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

በአጠቃላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራ ላለፉት ተከታታይ ቀናት በመንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየትና ተገቢውን ውሳኔ በማስተላለፍ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት በጸሎት አጠናቅቋል፡፡ መሐሪና ሁሉን ቻይ የሆነ እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን፣ ፍቅሩንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ግንቦት ፳፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ኢትዮጵያ አዲስ አበባ
©የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት

🎁የምሥራች🎁🌐ከኢትዮጵያ ውጪ ለምትኖሩ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ--------------------------'ሐዲስ ኪዳን ለሕፃናት' የተሰኘውን ተወዳ...
05/23/2024

🎁የምሥራች🎁

🌐ከኢትዮጵያ ውጪ ለምትኖሩ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ
--------------------------
'ሐዲስ ኪዳን ለሕፃናት' የተሰኘውን ተወዳጅ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ስብስብ ሙሉውን መጽሐፍ በስስ ቅጂ (Soft Copy) እነሆ ብያለሁ።

መጽሐፉ፡-
📍140 ገፅ ሲሆን፣ በሙሉ ቀለም የተዘጋጀ ነው።
📍አንድ ታሪክ በአንድ ገፅ ያልቃል፤ ታሪኩን አጉልቶ የሚያሳይ ስእልም በቀጣዩ ገፅ አለው።
📍ከ4-12 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ ልጆች ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
📍ወላጆች፣ ቤተሰቦች፣ ጓደኞች የሆናችሁ ራሳችሁ ልታነቧቸው፣ ለልጆችም ልታነቡላቸው፣ ልታስነብቧቸው ትችላላችሁ።

የአንድ የስስ ቅጂ ዋጋ
• 9 የአሜሪካ ዶላር
• 7 ፓውንድ
• 12 የካናዳ ዶላር
• 8 ዩሮ
• 5 ኩዬት ዲናር ነው።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሒሳብ ቁጥር 1000146133979 ላይ የከፈሉበትን ደረሰኝ እዚህ👉 https://t.me/Ze1619 ቴሌግራም ላይ ከላኩ በኋላ
ይህንን ሊንክ ይጫኑታል
https://drive.google.com/file/d/1FJq1GpfWKRHx2kgSvWtUOz08biaQQi9a/view?usp=drive_link
ከዚያም የሚመጣልዎትን ‹Request access› ሲልኩ መጽሐፉን የሚያገኙበት ፈቃድ ይደርስዎታል፡፡

[በቅርቡ፡- 'ብሉይ ኪዳን ለሕፃናት' የተሰኘውን ተወዳጅ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ስብስብ ሙሉውን መጽሐፍ በስስ ቅጂ (Soft Copy) አቀርባለሁ።]
Share በማድረግ ሌሎች ያድርሱ፡፡

🧲ከመጽሐፉ ላይ ለቅምሻ የሚሆኑ 10 ገፆችን
በዚህ ቴሌግራም 👉https://t.me/Ze1619 ላክልኝ ለሚሉ እጋብዛለሁ!

© የኮፒራይት መብትን ያክብሩ፣ ያስከብሩ!

-------------
ስለመጽሐፉ
ከስመ ጥሩ ካህን ቀሲስ ታድሮስ ማላቲ ላቅ ያለ ጠቀሜታ ያላቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትረካዎች ባማረ ሁኔታ ተጠናቅረው በዚህ መጽሐፍ ቀርበዋል፡፡
ይህ መጽሐፍ ከሕፃናት ጀምሮ እስከወላጆች እንዲሁም በወጣቶች ሃይማኖታዊ ትምህርት ላይ አደራና ሓላፊነት እስካለበት ማንኛውም ሰው ድረስ ሐዲስ ኪዳንን እና በውስጡ የተካተቱትን እጅግ ወሳኝ ታላላቅ ክስተቶች በአስደናቂ ሁኔታ የያዘ በሁሉም እድሜዎች ለሚገኙ ሁሉ የሚጠቅም ነው፡፡
ይህ የከበረ መጽሐፍ አማርኛው ለሁሉም በሚገባ መልኩ የተዘጋጀና በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ በደስታ እንድንጓዝ የሚጋብዝ ሲሆን ለበርካታ ቀጣይ ትውልዶችም ትልቅ ዋጋ ያለው ሐብት ነው፡፡

የመጽሐፉ መግቢያ
የተወደዳችሁ አንባቢዎች፤ ይህ በእጃችሁ ያለው መጽሐፍ ከልጆቻችሁ ጋር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪኮችን በቀላሉ በየዕለቱ እንድታነቧቸው ሆነው የተዘጋጁት የሁለቱ ተከታታይ መጻሕፍት (ብሉይ እና ሐዲስ ኪዳን) አንዱ ክፍል ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሁሉም ዕድሜዎች ለሚገኙ ለሁሉም ሰዎች መረዳትን የሚሰጥ መለኮታዊ ጥበብን ያስተላልፋል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስን በእምነት መንፈስ የሚያነበው ሁሉ እግዚአብሔርን ለማወቅ ይጥራል፤ እግዚአብሔር ለሁሉም የሰው ዘር ያለውን የተትረፈረፈ ፍቅርም በሕይወቱ ይለማመዳል፡፡
1. ልጆቻችሁ ጥቅሶቹን እንዲያውቋቸው፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉት ብዙዎቹ ጥቅሶች አልተለወጡም፡፡
2. ለልጆቻችሁ፣ ይህን መጽሐፍ ዕለት ተዕለት በምትጠቀሙበት ቋንቋ አንብቡላቸው፤ ልጆቻችሁም በቀላሉ ሊከተሏችሁ ይችላሉ።ልጆቻችሁ ሲያድጉም ማብራሪያዎች ያሉበትን ይህን መጽሐፍ ራሳቸው እንዲያነቡት ፍቀዱላቸው፤ በዚህም ልጆቻችሁ በሂደት መጽሐፍ ቅዱስን ያለረዳት ማንበብ ይችላሉ፡፡
-----------
ቀሲስ ታድሮስ ያዕቆብ ማላቲ የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ካህን ሲሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ አንድምታ (ኮሜንታሪ) መጻሕፍትን በመጻፍ የታወቁ ሊቅ ናቸው።
----------
ዘኤልያስ ወልደ ሚካኤል Zealias Wolde Michael

“ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ" (ማር.4÷24) *********************************ከብፁዕ አቡነ አብርሃም የደቡብ አፍሪካ ጉዞ መሰረዝ ጋር  ተያይዞ የሐሰት ዜና በመሰራጨት ላይ ...
05/10/2024

“ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ" (ማር.4÷24)
*********************************

ከብፁዕ አቡነ አብርሃም የደቡብ አፍሪካ ጉዞ መሰረዝ
ጋር ተያይዞ የሐሰት ዜና በመሰራጨት ላይ ይገኛል።
*********************************

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ጆሐንስበርግ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተበት ፳፭ኛ ዓመት በዓል ላይ ለመገኘት፣ ቅዳሴ ቤቱን ለማክበርና በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትን ለመባረክ እንዲሁም ምዕመናንን ለማስተማር ዛሬ ማለዳ ከቅዱስነታቸው ጋር ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመጓዝ መርሐ ግብር ይዘው እንደነበር ይታወቃል።

ይሁን እንጂ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ካለባቸው ተደራራቢና አስቸኳይ ሥራዎች አንጻር ለአሥር ቀናት ከጽሕፈት ቤታቸው ርቀው መቆየት በጠቅላይ ጽ/ቤቱ የዕለት ተዕለት ሥራዎች ላይ ክፍተት እንዳይፈጠር በመስጋታቸው እንዲሁም ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊውና ምክትል ሥራ አስኪያጁ በሌሉበት በቢሮኘቸው በሌሉበት ሁኔታ ለበርካታ ቀናት ከጠቅላይ ጽሕፈቱ ርቀው ከተጓዙ ሥራዎች ስለሚበደሉ ቀደም ሲል ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊያደርጉት የነበረውን ሐዋርያዊ ጉዞ ከቅዱስነታቸው ጋር በጥሞና በመወያየት ለመሰረዝ ተገደዋል።

ይሁን እንጂ እውነታው ይኸው ሆኖ ሳለ በአንዳንድ ማኅበራዊ ገጾች ፈጽሞ እውነትነት በሌለው መንገድ ብፁዕነታቸው ወደ ኤርፖርት እንዳይሔዱ እንደተከለከሉና ፓስፖርታቸው እንደተያዘ በማስመሰል የሚሰራጨው ዜና ፍፁም መሰረተ ቢስና የሐሰት ዜና ነው።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ከታቀደው ሐዋርያዊ ጉዞ ለመቅረት የተገደዱት በተደራራቢ ሥራ ምክንያት መሆኑንና የብፁዕነታቸው ፓስፖርትም ለጉዞ ሲባል ቀደም ብሎ ከሚመለከተው አካል መጥቶ በልዩ ጽሕፈት ቤቱ ጉዳይ አስፈጻሚ እጅ የሚገኝ መሆኑን እንገልጻለን። የቤተ ክርስቲያን ልጆች ምእመናንና የቤተ ክርስቲያናችን ወዳጆችም በአንዳንድ መንፈሳዊ ኃላፊነት በማይሰማቸው ማኅበራዊ ገጾች የሚሰራጨው መረጃ የሐሰት መሆኑን እንዲያውቁና ራሳቸውን ከሐሰተኛ መረጃዎች እንዲጠብቁ ለማሳሰብ እንወዳለን።

የዜናው ምንጭ
የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ኢትዮ ትንሣኤ ሚዲያ
ግንቦት ፪ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም (2024)

እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና አደረስዎ!
04/25/2024

እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና አደረስዎ!

*** አይናቸውን ለማብራት 400 ሺህ ዶላር ያስፈልጋል ***ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር ግማሽ ሚሊዮን (500ሺህ) ብር፣ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ 100ሺ ብር በመስጠት ጀምሯል  ደጋግ ኢትዮጵያውያኖች የ...
04/25/2024

*** አይናቸውን ለማብራት 400 ሺህ ዶላር ያስፈልጋል ***

ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር ግማሽ ሚሊዮን (500ሺህ) ብር፣
ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ 100ሺ ብር በመስጠት ጀምሯል ደጋግ ኢትዮጵያውያኖች የአቅማችሁን በማድረግ የትዕግስት ሶስት መንታ ልጆች የአይን ብርሃናቸው እንዲመለስ የበኩላችንን እናድርግ።

ሼር በማድረግ እንጀምር!

አካውንታቸው ይህው እባካችሁ
ሼር አድርጉት

* СВЕ 1000622473872
* Dashen Bank 5563671317021
* Abyssinia bank 91613069
* ኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ 1023500172828
* አዋሽ ባንክ 013471254339600

ትግስት ካሳ ቀፀላ

ስልክ
* 0911868306
* 0911137097

go fund me
* https://gofund.me/42557274

ይህን ሼር ማድርግ መልካም ነገር መስራት ነውና እባካችሁ ሼር አድርጉላቸው

ማሳሰቢያ:-በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ለሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን የተላለፈ ጥብቅ መመሪያ:-ሀገረ ስብከቱ እኔ የማላውቀውና ህገ ወጥ ጉባኤ በመሆኑ ማህበረ ካህናትም ማህበረ ምዕመናንም እንዳት...
04/16/2024

ማሳሰቢያ:-

በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ለሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን የተላለፈ ጥብቅ መመሪያ:-

ሀገረ ስብከቱ እኔ የማላውቀውና ህገ ወጥ ጉባኤ በመሆኑ ማህበረ ካህናትም ማህበረ ምዕመናንም እንዳትገኙ ብሏል::

አቡነ ንብሎ   | እንኳን ለጻዲቁ አባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።የዘማሪት ሕይወት ወልዴ አዲሱን « አቡነ ንብሎ ለገብረ ሕይወት»  የተሰኘውን...
03/12/2024

አቡነ ንብሎ

| እንኳን ለጻዲቁ አባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።

የዘማሪት ሕይወት ወልዴ አዲሱን « አቡነ ንብሎ ለገብረ ሕይወት» የተሰኘውን አዲስ ዝማሬ በማኀቶት የዩቲዩብ ቻናል ላይ ተለቋል። ያደምጡት ዘንድ ግብዣችን ነው::

👉 https://youtu.be/YXEbsNVBKN0?si=IY5s1YMqkqDeKlvi

❤️ አዲስ ዝማሬ “ አቡነ ንብሎ “ ዘማሪት ሕይወት ወልዴ ​⁠@-mahtot

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በበዓለ ሢመታቸው ያስተላለፉት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ +++++በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!• ብፁዕ አቡነ አብርሃም፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት...
03/03/2024

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በበዓለ ሢመታቸው ያስተላለፉት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ +++++

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
• ብፁዕ አቡነ አብርሃም፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
• ብፁዕ አቡነ ሄኖክ፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤
• የተከበራችሁ የመንግሥት ከፍተኛ ባለ ሥልጣናት፤
• የተከበራችሁ አምባሳደሮችና ኮር ዲኘሎማቶች፤
• የተከበራችሁ የቤተክርስቲያናችን የየመምሪያውና የየድርጅቱ ኃላፊዎች፤
• ክቡራን ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፤
• ክቡራን የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፤
• የሰንበት ት/ቤት ወጣት ልጆቻችን፤
• በአጠቃላይ በዚህ ዓውደ ምሕረት የተገኛችሁ ክቡራንና ክቡራት በሙሉ፤

ፈተናዎች ቢበዙብንም ምሕረቱን ከኛ ያላራቀ እግዚአብሔር እንኳን ለዐሥራ አንደኛው በዓለ ሢመተ ክህነት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
‹‹ወይእዜኒ ተመየጡ ኀቤየ ወአነሂ እትመየጠክሙ፡- ‹‹አሁንም ወደኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደናንተ እመለሳለሁ›› (ዘካ. ፩-፫)

ቅዱስ መጽሐፍ ታላቁ የዓለማችን መጽሐፍ ነው፤ በዕድሜም በብዛትም በዓለም ውስጥ የሚተካከለው የለም፤ ቅዱስ መጽሐፍ በዓለም ውስጥ በብዙ ቋንቋ የተተረጐመና ብዙ አንባቢና ተከታይ ያለው ብቸኛው የዓለማችን ታላቅ መጽሐፍ ነው፡፡

የቅዱስ መጽሐፍ ይዘት በጥቅሉ ሲታይ በእግዚአብሔርና በሰው መካከል የነበረው ያለውና የሚኖረው ግንኙነትን የሚገልጽ ነው። የግንኙነቱ ሁናቴ ሲታይ ደግሞ ቀጥ ያለ ሳይሆን ብዙ ፈተና ያስተናገደ ጎርባጣና ጠመዝማዛ እንደሆነ በግልጽ ያመለክታል። በረጅሙ ግንኙነት እግዚአብሔር ፍጡሩን እየተከታተለ በምሕረትና በፍቅር ሲጎበኝ አንዳንዴ ደግሞ ሲቀጣም ሲገሥጽም ይታያል፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ ሰዎች የእግዚአብሔርን ጥሪ ተቀብለው እንደ ቃሉ ለመኖር ሲጣጣሩ፣ ነገር ግን በአብዛኛው እንዳልተሳካላቸው፣ በዚህም ጉዳታቸው እየከፋ እንደሄደ እናስተውላለን፡፡ ሆኖም እግዚአብሔር ሰውን ለመመለስ መጣራቱን አቋርጦ እንደማያውቅ ተጽፎአል፡፡ ‹‹አሁንም ወደኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደእናንተ እመለሳለሁ›› የሚለው ጥሪውም ይህንን ያስረዳል፡፡ ጥቅሱን በትክክል ስናጤነው ሰዎች ከእግዚአብሔር የመኮብለል ዝንባሌያቸው ያየለ እንደሆነ፣ በአንጻሩ ደግሞ የእግዚአብሔር ጥሪ የማያቋርጥ እንደሆነ የሚያስረግጥ ነው፤ ቀድሞም ሆነ ዛሬ የምናየው ሐቅም ይኸው ነው።

ከዚህ አንጻር በዘመናችን ያለው ሁኔታም ስንመለከት ከበፊቱ ብዙም የተሻለ ሆኖ አናገኘውም፤ ይልቁንም በጣም የተዛባና ለእግዚአብሔር ቁጣ የተጋለጠ ሆኖ እናየዋለን፤ ያለንበት ዘመን ለእግዚአብሔር ክብርን የነሣ፤ ከፍቅርና ከአንድነት የራቀ፣ ራስ ወዳድነትና በቃኝ አለማለትን የወረረው፤ በዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ የተዋጠ ትውልድ የታየበት ዘመን ነው፡፡ የዘመናችን ትውልድ ከተግባር ይልቅ አስመሳይ ሆኖ መታየትን፣ ከቅድስና ይልቅ ነውረ ኃጢአትን፤ ከትሕትና ይልቅ ትዕቢትን የተለማመደ፣ ለሃይማኖትም ሆነ ለማኅበረ ሰብዕ ጤናማ ህላዌ ያልተመቸ ትውልድ እንደሆነ በግልጽ የሚታይ ነው፡፡ ይህ አደገኛ አዝማሚያ በማስተዋል ካልታረመ ሂዶ ሂዶ የእግዚአብሔርን ቁጣ ማስከተሉ አይቀርምና እንደ እግዚአብሔር ጥሪ ወደእሱ ብንመለስ ይሻላል፡፡

• ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣
• ክቡራን የበዓሉ ተሳታፊዎች፡-

እኛ የሃይማኖት አባቶችም አልጫ የሆነውን የዘመናችንን ትውልድ በትጋት አስተምረን በቆራጥነት ገሥጸንና መክረን ወደ እግዚአብሔር ካልመለስነው ከቁጣው አንድንም፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ እንዳስተማረን አስተምረነው የማይመለስ ከሆነ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል። እኛ ባለማስተማራችን የሚጎዳ ትውልድ ካለ ግን እኛ የደሙ ተጠያቂዎች መሆናችንን በማያሻማ ሁኔታ ተገልጾአልና ነው። የኛ ኃላፊነት እስከዚህ ድረስ ከባድ መሆኑን ባንዘነጋውም እንደዓለሙ በልዩ ልዩ ደካማ አስተሳሰቦችና ተግባራት እየተሰናከልን መሆናችን የአደባባይ ምሥጢር ከሆነ ውሉ አድሮአል፡፡

ዓለም ሲሳሳት ከመገሠጽ ይልቅ አብሮ ማጨብጨብ ተለማምደናል። ባናጨበጭብም ዝምታን መርጠናል። ነገር ግን ኃላፊነቱን የተረከብነው ጥፋት ሲፈጸም ዝም ብሎ ለማየት አልነበረም። ከዓለሙ ጋር አብሮ ለማጨብጨብ ወይም አድማቂ ለመሆንም አልነበረም፡፡ ከቅዱስ ወንጌሉ መሠረተ ሐሳብ ፍንክች ሳንል የእውነት፣ የፍትሕ፣ የሰላም፣ የፍቅር፣ የዕርቅ፣ የይቅርታ፣ የአንድነትና የስምምነት ጠበቃ መሆናችንን ማሳየት ነበረብን፡፡ ሰውን ሁሉ በእኩልነት በመቀበልና የሁሉም እኩል አባቶች መሆናችንን በተግባር ማስመስከር ይገባን ነበር። የተዛባውን በማረም ትውልዱን ለማዳን ያደረግነው ጥረት የሚያረካ እንዳልሆነ ታዛቢው ሁሉ አይቶብናል፡፡ ያም በመሆኑ ሁኔታው እኛንም ቤተ ክርስቲያንንም ለፈተና ለመዳረግ እየዳዳ ነው። በመሆኑም በዚህ ክሥተት የእግዚብሔር ቁጣ የለበትም ለማለት አንደፍርም። በዓለሙ ብልሹ አሰራርም ተሳታፊ ከመሆን አላመለጥንም፡፡ ክሱን፣ አቤቱታውን፣ ሰውን ከሥራ እያፈናቀሉ ፍትሕ ማዛባቱን፣ በደምብ ተለማምደነዋል። ደመወዛችሁ ይብቃችሁ የሚለውን አምላካዊ መርሕ ዘንግተን የዚህ ዓለም ንዋይ እያሸነፈን ነው። ግን ዓለምን ልናሸንፍ እንጂ በዓለም ልንሸነፍ አልተጠራንም።

በዚህ ምክንያት የብዙ ምእመናን ልብ ወደኋላ እንዲያፈገፍግ ምክንያት እንዳንሆን መጠንቀቅ ይገባናል። በዚህ ሁሉ የእግዚአብሔር ቁጣ በእኛና በሕዝባችን በሀገራችንና በዓለማችን እንዳይገለጥ እነሆ አሁንም ቃሉ ተመለሱ እያለ ነውና እንመለስ። እየተዛባ ያለው ሁሉ መስተካከል ይችላል። በሃይማኖት የማይቻል ነገር እንዳለ የሚያስብ ካለ ሃይማኖት የሌለው እሱ ነው።

• ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣
• ክቡራን የበዓሉ ተሳታፊዎች፡-
እኛ የሃይማኖት አባቶች ከሌላ የምንዋሰው ንግግርና አስተምህሮ የለንም። ዐሠርቱ ቃላትን ማክበርና መተግበር፤ ማስተማርና ማሥረጽ በቂያችን ነው፡፡ ምክንያቱም ከዐሠርቱ ቃላት የበለጠ ሌላ ሕግ በዓለም ስለሌለ ማለት ነው። ቢኖርም ከሱ የተኮረጀ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ የኛ አስተምህሮ አትግደል እንጂ ግደል ሊሆን አይችልም። የኛ ተግሣጽ አትስረቅ፣ አትዋሽ፣ የሌላውን አትመኝ፣ አታመንዝር የሚል እንጂ በተመሳሳይ የፆታ ጋብቻ ወደ ነውረ ኃጢአት ተሠማራ የሚል ትምህርት መቼውም ቢሆን ከቶ ሊኖረን አይችልም፡፡

እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ከዚህ ውጭ ከዘመኑ የወሬ ሱሰኛ መሣሪያን እየተበደርን ከቅዱስ ወንጌሉ ጋር የሚጣረስ ንግግርና አስተምህሮ ማስተላለፍ ለምን አስፈለገ? ይህ ለኛ ኃሣር እንጂ ክብር ሊያስገኝልን አይችልም። ከእንደዚህ ያለ ድርጊትም መራቅ አለብን። የኛ ደንበኛና ዘላለማዊ ፖለቲካ ቅዱስ ወንጌል ነው። ዘላለማዊውን ትተን ጊዜያዊውን፣ መለኮታዊውን ትተን ሰዋዊውን አንከተል፡፡ ይህ ለኛ የሞራል ዝቅጠት ያስከትልብናል። ሕዝቡም እግዚአብሔርም ከኛ የሚጠብቁት ትክክለኛውን ቃለ ቅዱስ ወንጌል ማስተማር ነው። ለዓለሙ ፖለቲካ ግን የራሱ ባለቤቶች አሉለት፡፡ እኛ በፖለቲከኞች ላይ ያለን ሥልጣንና መብት ማስተማርና መምከር ነው። ያም ሆኖ አንዱን በመደገፍ ሌላውን በመንቀፍ ሳይሆን ሁሉም እኩል ልጆቻችን መሆናቸውን አውቀን በፍቅር በመመልከት ነው፡፡ ሲጋጩብንም የማስታረቅና የማቀራረብ፤ የመምከርና የማሳመን እንጂ ወደ አንዱ ተለጥፎ ሌላውን ዘልፎ መናገር የቆምንለት ቅዱስ ወንጌል አይፈቅድልንም፡፡

ፓለቲከኞችም ባልዋሉበትና ባልተፈቀደላቸው፣ ሌላው ቀርቶ የተቋቋሙበት ሕገ መንግሥቱ እንኳ የማይፈቅድላቸውን በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ ጣልቃ እየገቡ የግል ፍላጎትና ዓላማ ለማስፈጸም መሞከር ፍጹም ስሕተት ነው። ተቀባይነትም የለውም። ለቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይሆን ለራሳቸው ለፖለቲከኞቹም አይበጅም፡፡ ሁሉም ድንበሩን ጠብቆ በጋራ ጉዳዮች ላይ በፍቅርና በመከባበር ተመካክሮና ተግባብቶ መሥራት ያሻል። በዚህ መንፈስ ቤተ ክርስቲያንና መንግሥት ተናበው ቢሠሩ በሀገር ላይ ሰላም ይሰፍናል፣ ልማት ይፋጠናል፣ ዕድገት ይመዘገባል፤ ስለዚህም በዚህ ዙሪያ ሁላችንም ከምር ልናስብበት ይገባል።

• ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣
• ክቡራን የበዓሉ ተሳታፊዎች፡-
በዛሬው ዕለት እያከበርነው ያለ በዓለ ሢመተ ክህነት ዓላማው የተሰጠንን ተልእኮ በማሰብ ለተሻለ መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የመነቃቃትና የመነሣሣት መንፈስ ለመፍጠር ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ባለፉት ዓመታት ያጋጠሙንን ፈተናዎች በመለየት፣ በቀጣዩ እንዳይደገሙ ነቅተንና ተግተን መሥራት ያስፈልጋል፡፡ ባለፉት ዓመታት እጅግ በጣም አስቀያሚ ነገሮችና ፈተናዎች በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ተከሥተዋል፤ አሁንም አልቆሙም፡፡

በየአካባቢው መብቱ ተነፍጎ በቀየው እንዳይኖር በልዩ ልዩ ምክንያት እየተፈናቀለ ያለውን ሕዝባችን ለማጽናናትና ለመደገፍ በአንድነት መቆም ይገባናል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ልጆችዋን የመንከባከብ፣ የመጠበቅና ዕንባቸውን በማበስ ፍትሕንና ርትዕን የማንገሥ ኃላፊነት አለባት። ይህንን ኃላፊነት በአስተውሎት ልትወጣው ይገባል፡፡ በመሆኑም መጪው ጊዜ ቤተ ክርስቲያን በውስጧ ያለውን ውጣ ውረድ በማስተካከል መልክ የምታስይዝበት፣ የተፈናቀሉ ልጆችዋን የምታጽናናበትና የምታግዝበት እንዲሁም ለፈተና የተጋለጡ ልጆቻችን ሁሉ የዜግነት፣ የሃይማኖትና የሰብአዊ መብታቸው እንዲከበር ሰላም ፍቅር፣ ፍትሕ፣ አንድነት በሀገር እንዲነግሥ ሁሉም ድንበሩን ጠብቆ ሕዝቡን የሚያገለግልበት ዓመት እንዲሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ በርትተን መሥራት አለብን፡፡ ይህንን ብናደርግ በእውነትም ወደ እግዚአብሔር ተመልሰናል ማለት ነው። እኛ ከተመለስን እሱም ወደኛ መመለሱ አይጠረጠርም። ስለዚህ አሁንም ወደ እሱ እንመለስ፡፡

በመጨረሻም፤
በሀገራችን ላይ ይልቁንም በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ያለው ድባብ እጅግ በጣም አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱ ለማንኛችንም ግልፅ ነው፡፡ በመሆኑም ካህናትና ምእመናን በሃይማኖት ጸንተው እንዲቆሙ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እጃቸውን እየዘረጉ የሚገኙ ሁሉ ቤተ ክርስቲያን ጠላታቸው አይደለችምና እጃቸውን እንዲያነሡ፣ መንግሥትም ለቤተ ክርስቲያን የሕግ ከለላና ጥበቃ እንዲያደርግ በእግዚአብሔር ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

መልካም በዓለ ሢመት ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን!!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ፤
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም፣ ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

እንኳን ለ128ኛው የዐድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ!!!
03/02/2024

እንኳን ለ128ኛው የዐድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ!!!

ከሃያ በላይ የአብነት ተማሪዎች ከነመምህራቸው፤ መነኮሳትም ተገደሉ+++(አደባባይ ሚዲያ፤ ማርች 1/2024፤ የካቲት 22/2016 ዓ.ም):- ሰሜን ሜጫ ብራቃት ከተማ ልዩ ቦታው ጋፊት ገብርኤል...
03/01/2024

ከሃያ በላይ የአብነት ተማሪዎች ከነመምህራቸው፤ መነኮሳትም ተገደሉ
+++
(አደባባይ ሚዲያ፤ ማርች 1/2024፤ የካቲት 22/2016 ዓ.ም):-
ሰሜን ሜጫ ብራቃት ከተማ ልዩ ቦታው ጋፊት ገብርኤል በሚባል ቦታ
ከሃያ በላይ የአብነት ተማሪዎች ከነመምህራቸው በመንግሥት ወታደሮች መገደላቸውን ምንጮች ለአደባባይ ተናግረዋል።

የካቲት 20 ቀን 2016 ዓ.ም ከሌሊቱ 6:30 እስከ 8:00 በተፈጸመው ግድያ ዕድሜያቸው ከ11 ዓመት እስከ 18 ዓመት ናቸው ያሉ የቤተ ክርስቲያን ተማሪዎች አረመኔነት በተሞላበት መልኩ የተገደሉ ሲሆን ከተገደሉት መካከል
1) ስብሐት
2) ገብረ ኢየሱስ
3) ዘርዓ ዳዊት
4) ናሁ ሠናይ
5) ቃለ ጽድቅ
6) በዕውቀት
7) እንዳልካቸው
8) ኤፍሬም
የሚባሉ ተማሪዎች ይገኙበታል ተብሏል። ከአካባቢው በመንግሥት ታጣቂዎች የተያዙ ካህናት እንዳሉም ታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ለመንበረ ፓትርያርኩ በጻፈው ደብዳቤ በሀገረ ስብከቱ ሥር በሚገኙ የተለያዩ አድባራትና ገዳማት ብዙ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን ገልጿል:: ታሕሣሥ 2/2016 ዓ.ም በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት በማቻከል ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር በሚገኘው የዋሻ አምባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም እመምኔት እማሆይ ወለተ ማርያም ገላው ታፍነው መወሰዳቸው ተገልጿል።

በተመሳሳይ መልኩም በአዋበል ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር በሚገኘው በመካነ ቅዱሳን ጣቢት ቅ/ጊዮርጊስ አንድነት ገዳም ላይ በተፈጸመ ጥቃት አባ ገ/ሥላሴ ታመነ የተባሉ አባት ሲገደሉ ዲ/ን ዮሐንስ ለማ ላይ ደግሞ ከፍተኛ የአካል ጉዳት መድረሱን ሀገረ ስብከቱ አስተውቋል። ከዚህም በተጨማሪ የተለያዩ ንብረቶች መዘረፋቸው ተገልጿል::

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እየተፈጸሙ ባሉ የተቀናጁ ጥቃቶች ገዳማት፣ በየገዳማቱ ውስጥ ያሉ መነኮሳት፣ በገጠር አብያተ ክርስቲያናት የሚያገለግሉ ካህናትና ዲያቆናት እንዲሁም አብያተ ክርስቲያናት ዒላማ ተደርገው እየተገደሉና ንብረቶችም እየወደሙ ይገኛሉ።

በቅርቡ በዝቋላ አቦ ገዳማ ባሉ አባቶች ላይ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል መፈጸሙ ይታወቃል።
ኢትዮ ትንሣኤ ሚዲያ
የካቲት 22/2016 ዓ/ም

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ...
02/06/2024

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል።

ብፁዕነታቸው ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ እውቅና ወደ ሀገረ ስብከታቸው በመሄድ የአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል፣ የከተራና የጥምቀት በዓላትን ከመንፈስ ልጆቻቸው ጋር ያከበሩ ሲሆን ለአዳጊ ሕጻናትም ማዕረገ ዲቁና መስጠታቸው ይታወቃል።

ብፁዕነታቸው በአሁኑ ሰዓት ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያው ይገኛሉ ሲሉ መረጃ ሰጭዎቻችን አድርሰውናል።

MK

የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ የበረከት ጥሪ::የኮለምበስና አካባቢው ምዕመናን በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ::ሁላችሁም ተጋብዛችኃል::
12/02/2023

የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ የበረከት ጥሪ::

የኮለምበስና አካባቢው ምዕመናን በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ::

ሁላችሁም ተጋብዛችኃል::

በአሁኑ ሰዓት:-የዘማሪት ህይወት ወልዴ የመዝሙር አልበም ምርቃት::አራት ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ
10/29/2023

በአሁኑ ሰዓት:-

የዘማሪት ህይወት ወልዴ የመዝሙር አልበም ምርቃት::

አራት ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ

10/29/2023

ኑ አብረን እግዚአብሔርን እናመስግን!!!

10/25/2023

+++ ጥቅምት 18 ቀን 2016 ዓ.ም +++

እርስዎም በክብር ተጋብዘዋል!

አድራሻ:- አራት ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ዩንቨርስቲ አዳራሽ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

10/22/2023

ጥቅምት 18 ቀን 2016 ዓ.ም!

እርስዎም በክብር ተጋብዘዋል!

አድራሻ:- አራት ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ዩንቨርስቲ አዳራሽ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ቅዱስ ሲኖዶስ ለውጭ አሁጉረ ስብከት ወጥ የሆነ መመሪያ እንዲያወጣ ብፁዕ አቡነ ሙሴ ጠየቁ።ብፁዕ አቡነ ሙሴ የምዕራብ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት  ሊቀ ጳጳስ በ፵፪ኛው ዓለም አቀፍ የሰበካ መን...
10/21/2023

ቅዱስ ሲኖዶስ ለውጭ አሁጉረ ስብከት ወጥ የሆነ
መመሪያ እንዲያወጣ ብፁዕ አቡነ ሙሴ ጠየቁ።

ብፁዕ አቡነ ሙሴ የምዕራብ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በ፵፪ኛው ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ
ላይ የሀገረ ስብከታቸውን ሪፖርት አቅርበዋል።

ብፁዕነታቸው በሪፖርታቸው ባለፉት ሦስት ዓመታት
በኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ባለመቻላቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤዎች ሳይሳተፉ መቅረታቸውን ገልጸው በቅርቡ ደግሞ ቋንቋና ፖለቲካን ምክንያት በማድረግ በሀገረ ስብከታችን በተፈጠረውን ችግር ምክንያት ምዕመናን እንዳይለያዩ በቅርበት ለመቆጣጠርና ምክር ለመስጠት በዚያ ለመቆየት ተገድጃለሁ ብለዋል።

በግንቦት 2015 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ ለስብሰባ መምጣታቸውን የገለጹት ብፁዕነታቸው በትግራይ ክልል በተፈጠረው ችግር ምክንያት በሀገረ ስብከታችን ስር በቆዩ ሦስት አብያተ ክርስቲያናትና በቅርቡ በእኛ ሥር የቆየን አንድ ቤተክርስቲያን ጨምረው በህገ ወጥ መንገድ ተሹመናል የሚሉ መነኮሳት ቋንቋና ፖለቲካን ምክንያት በማድረግ ወስደዋቸዋል ብለዋል።

አሁን የተወሰዱት አብያተ ክርስቲያናት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥር ይተዳደሩ የነበሩ መሆናቸውን የገለጹት ብፁዕነታቸው ቅዱስ ሲኖዶስ መተዳደሪያ ወይም መመሪያ በማዘጋጀት ተቋማዊ ሕልውናቸው እንዲረጋገጥ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።

በሀገረ ስብከታቸው በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደነበር የገለጹት ብፁዕ አቡነ ሙሴ በዚያው አገር ተወልደው ያደጉ 45ዲያቆናትና 4 ቀሳውስትን ለማዕረገ ክህነት ማብቃታቸውን ገልጸዋል።

በአሁኑ ጊዜ በሀገረ ስብከታቸው ሥር የሚገኙ ምዕመናን ለሁለት ተከፍለው እንደሚገኙ በሪፖርታቸው የገለጹት ብፁዕነታቸው ግማሾቹ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እና ከቅዱስ ሲንዶስ ጋር መሆናቸውን በመግለጽ ላይ የሚገኙ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ ተለይተናል በማለት ከህገ ወጥ ተሿሚዎቹ ጋር ወግነዋል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በውጭ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ችግር እየተፈጠረ ስለሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ወጥ የሆነ መመሪያ በማጣትና አህጉረ ስብከቱ ለሚገኙባቸው መንግሥታት በማሳወቅ ችግሩን ከመሰረቱ ሊፈታው ይገባል በማለትም ሪፖርታቸውን አጠቃለዋል።

በመጨረሻም ብፁዕነታቸው በአውስትራሊያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥር የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት በየ ዓመቱ እንደሚደረገው ሁሉ ለሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ገቢ የሚደረግ ገንዘብ እንዲልኩልኝ በተደጋጋሚ ያቀረብከት ጥያቄ ምላሽ ሊያገኝ ባለመቻሉ ከግል ገንዘቤ ለበረከት የሚሆን ሁለት ሺህ የአሜሪካ ዶላር ገቢ አድርጌያለሁ ብለዋል።

ዘገባው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው

10/17/2023

“እንደ ተሰጠን መጠን ይህ አገልግሎት ስላለን አንታክትም" 2 ቆሮ 4፥21

ጥቅምት 18 ከቀኑ 6:30ጀምሮ!

በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ አዳራሽ ብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፤ መምህራነ ወንጌል ፤ ዘማርያን እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት "ከስም ሁሉ በላይ" የተሰኘው አዲስ የዘማሪት ህይወት ወልዴ የመጀመሪያ የምስጋና መዝሙር አልበም ይመረቃል::

እርስዎም መጥተው አብረን እንድንመርቅ በታላቅ አክብሮት ተጋብዘዋል::

"ከስም ሁሉ በላይ!"

*********** ጥቅምት 18 ቀን 2016 ዓ/ም *********
10/02/2023

*********** ጥቅምት 18 ቀን 2016 ዓ/ም *********

09/22/2023

መስከረም 16 ቀን 2016 ዓ/ም

እርሶዎም ተጋብዘዋል:-
09/20/2023

እርሶዎም ተጋብዘዋል:-

**** በቨርጅንያ እና አካባቢው ለምትኖሩ የቀረበ ጥሪ! ***ይምጡና የ2016 ዓ/ም መስቀል ደመራ በዓልን ከእኛ ጋር ያክብሩ!
09/14/2023

**** በቨርጅንያ እና አካባቢው ለምትኖሩ የቀረበ ጥሪ! ***

ይምጡና የ2016 ዓ/ም መስቀል ደመራ በዓልን ከእኛ ጋር ያክብሩ!

ስልጤ ቅባት....ተበዳይ ዝም ሲል በዳይ ከሳሽ ሆኖ መጥቷል።***ኦርቶዶክሳውያንን በጭካኔ ቀጥቅጠው፣የንግድ ተቋማቸውን ዘርፈው ፣መኖሪያ ቤታቸውን አፍርሰው እና አቃጥለው ፣ታቦታቱን እና ምዕመ...
09/13/2023

ስልጤ ቅባት....ተበዳይ ዝም ሲል በዳይ ከሳሽ ሆኖ መጥቷል።
***

ኦርቶዶክሳውያንን በጭካኔ ቀጥቅጠው፣የንግድ ተቋማቸውን ዘርፈው ፣መኖሪያ ቤታቸውን አፍርሰው እና አቃጥለው ፣ታቦታቱን እና ምዕመኑን አሳደው ምጻተኛ ካደረጉ በኃላ

"ሰው ተገደለብን፣ቁስለኛ በዛብን፣በድግምት የሚሰቃዩ ተማሪዎቻችን ዕረፍት አጡ "ብለው ገፊዎች ተገፊ ነን ለማለት በየሚዲያዎቻቸው እየለፉ ነው።

ወዳጄ....ይህ ዓለም እንደዚህ ነው። ገርፎ መጮኹን በደንብ ያውቅበታል። ግፈኞች ዳኛ ምስኪኖችን ተከሳሽ ማድረግ ህግ ሆኗል። የስልጤ አክራሪ ኃይል ደግሞ ይህን በደንብ መስሎታል።

የመሐመድ ልጅ ከታመመች የመሐመድ አምላክ ያድናት እንጅ ለመሐመድ ልጅ ህመም ቅድስት ቤተክርስቲያንን ኃላፊነት ትወስድ ዘንድ የወሰነባት ማን ነው?

ሙስሊሞች የሚመሩት የስልጤ ዞን ጸጥታ መዋቅር በወሰደው እርምጃ ለሞቱት እና ለተጎዱ ሰዎች ምዕመናንን በህይወት እና በንብረት ዋጋ ይከፍሉ ዘንድ የተወሰነው በየትኛው ስሌት ነው?

ለማንኛውም ብዙዎች የስልጤ ቅበት ከተማ ላይ ዝምታ ስላሳዩ አሁን በዳዩች ከሳሽ ሆነው መጥተዋል።

ተበድለናል ለማለት በሃሮን ሚዲያ ያለመሸማቀቅ ጥቁር ውሸት እና የአሳዳጅነታቸውን እርካታ እየለፈለፉ የነበሩ ሰዎችን ንግግር በማስረጃ እና አመክንያ እንገልጣለን።

© Kune Demelash kassaye -Arba Minch

እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ አደረሳችሁ እያልን እግዚአብሔር ቢፈቅድ እና ብንኖር ጥቅምት 18  ቀን 2016 ዓ. ም እንገናኝ::
09/02/2023

እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ አደረሳችሁ እያልን እግዚአብሔር ቢፈቅድ እና ብንኖር ጥቅምት 18 ቀን 2016 ዓ. ም እንገናኝ::

Address

2472 Centerville Road
Herndon, VA
20171

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Tinsae Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Tinsae Media:

Videos

Share

Ethio Tinsae Media

ይህ በምስረታ ላይ የሚገኘው የEthio Tinsae Media (ETM) ኢትዮ ትንሳኤ ሚዲያ ኦፊሻል የFacebook ገፅ ነው፡፡ በርካታ ሚሊዮን የሚቆጠር ተከታይ ያላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እያደገ የመጣውን የማህበራዊ ሚዲያ በንቃት ተፅዕኖ በመፍጠር ረገድ በግል ከሚደረገው አስተዋፅዖ በተጨማሪ በተደራጀ መልኩ አገልጋዮች በጋራ የሚያደርጉት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ በመሆኑም መሰረታቸውን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አድርገው በማህበራዊ ሚዲያ እየተንቀሳቀሱ ያሉትን የሚዲያ ጥረት ይበልጥ ለማገዝ በቤተክርስቲያኗ ልጆች ይህ ETM ሚዲያ በምስረታ ላይ ይገኛል፡፡ በETM ሀይማኖታዊ፣ ማህበራዊ፣ ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖማዊና ሀገራዊ ጉዳዮች በስፋት ይዳሰሱበታል፡፡ ሁላችሁም ሀገር ወዳድ ኢትዮጲያውያን ይህን ሚዲያና መሰል ተቋማትን በማበረታታትና ገንቢ አስተያየት በመስጠት በጋራ እንድንረባረብ ETM ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ይህን ጥሪ ለሎችም በማዳረስ አገልግሎቱን በጋራ እናሳድግ፡፡ ለኢትዮጵያ እና ለቤተክርስቲያናችን አንድነት አበክረን እንሰራለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ የYouTube ቻናሉን Subscribe እና ይህንን የFacebook ገፅ follow የበማድረግም አገልግሎቱን ይደግፉ ። Ethio Tinsae Media


Other News & Media Websites in Herndon

Show All