Ethio Tinsae Media

Ethio Tinsae Media Ethio Tinsae Media (ETM) ኢትዮ ትንሣኤ ሚዲያ

02/10/2025

* ፆመ ነነዌ*

“ምንተ እንከ ንረሲከ ወየኃድገነ ባሕር ይትሃወክ ባሕር ወይትነሣእ ማዕበል ዓቢይ”
"ባሕሩ ከእኛ ፀጥ እንዲል ምን እናድርግብህ" ትን/ ዮናስ ምዕ 1 ቁ 11

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከምትፈፅማቸው ከ ፯ቱ አፅዋማት አንዱ የሆነው ፆመ ነነዌ ይባላል::
ፆመ ነነዌ :- የተባለው የነነዌ ሰዎች በኃጢአት ምክንያት የመጣባቸውን የእግዚአብሔር ቁጣ ፣ ከጳጳስ እስከ ንጉሥ ፤ ከልሂቅ እስከ ደቂቅ እንስሳትም ጭምር እንዲፆሙ በአዋጅ ታዞ የተፆመ ፆም ስለሆነ ነው::

ነነዌ :- ጥንታዊ ከተማ ስትሆን ምድር ካሏት ከዓራቱ አፍላጋት/ወንዞች/ መካከል አንዱ ጤግሮስ ወንዝ ዳር የምትገኝ በናምሩድ የተመሠረተች /ዘፍ 10: 11-12/ ለአሦር መናገሻ የነበረች እና ሰናክሬም ብዙ ሕንፃዎች የሰራባት በእንግሊዘኛው /Nineveh/ በአሁኑ Modern day city of Mosul in North Iraq/ ሞሱል የምትባል ከተማ ነበረች:: ነች::

የነነዌ ሰዎች ግፍ እና ክፋት ቅድመ እግዚአብሔር በመድረሱ ምክንያት አምላካችን ሳይመክር የማይገስፅ ፣ ሳይናግር የማያደርግ ፣ ትዕግሥቱ ብዙ ፣ ቸርነቱ ለዘለዓለም ነውና የነነዌ ሰዎች ከጥፋታቸው ተመልሰው ንሥሐ ይገቡ ዘንድ የአማቴ ልጅ ወደሆነው የስሙ ትርጉም ርግብ ከመ የዋህ ወደ ተባለው ወደ ነቢዩ ዮናስ ቃል መጣ::
ትንቢተ ዮናስ 1 ቁ 2
“ተነስተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ::ክፋታቸውም ወደ ፊቴ መጥቷልና በእርሷዋ ላይ ስበክ::”
ነቢዩም ከአምላኩ የተሰጠውን ትዕዛዝ በማስተሀቀር ከእግዚአብሔር ሀሳብ ይልቅ የራሱን ሀሳብ አስቀድሞ ፣ ሀሰተኛ ነቢይ ላለመባል ፣ ካምላኩ ትዕዛዝ ይልቅ የራሱን ክብር አስበልጦ፣ ያስከበረውን፣ ነቢይ ያስባለውን፣ የሚወደውን፣ አምላኩን ትቶ፣ የነገረውን ላለመናገር፣ ያዘዘውን ላለመፈፀም፣ ኢዯጴ ወርዶ ገንዘብ ከፍሎ ወደ ተርሴስ በመርከብ ተሳፈረ::
ነቢዩ ሲሳፈር ኃይሉ ደክሞ፣ ተሰላችቶ፣ ጸሎቱን ትቶ፣ ካምላኩ ጠፍቶ፣ ራሱን ደብቆ፣ እውነትን አንቆ ነውና መርከቧ ውስጥ ሲገባ ዝሎ ነበር : : እንደ ገባም ከባድ እንቅልፍ ወሰደው::

ብዙም ሳይቆይ ከእንቅልፉም ሳይነቃ መርከቧ ማዕበል ተነሳባት:: አውሎ ነፋስም ነፈሰባት:: የእግዚአብሔር ቁጣ አናወፃት:: በውስጧ የተሳፈሩት ተጨነቁባት::ኡኡታ በዛባት::ዋይታ እና እሪታ ቀለጡባት:: ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚል ትንባሌ ተሰማባት ::

ይገርማል! አንድ ሰው ግን አይሰማም አይለማም፣ አያለቅስምም፣ አይጮህም፣ አይለምንም :: ሰው እያለቀሰ ብዙዎች በጭንቀት ተውጠው ብቻውን የተኛ ብቸኛ ሰው :: ዓቢይ ንዋም ላይ ያለ :: በከባድ እንቅልፍ የተወሰደ።
ተኝተው ዋይታ ጩኸት የማይሰማቸው፣
የሕዝብ ለቅሶ የማይጨንቃቸው፣
እውነትን የሚሸሹ፣
ሀቅን የሚንገሸገሹ፣
እግዚአብሔርን የሚዋሹ ዛሬም ከባድ እንቅልፍ ላይ ያሉትን ቤት ይቁጠራቸው:: እውነትን በሀሰት ቅድስናን በርኩሰት ሃይማኖትን በፍቅረ ንዋይ የለወጡትን ነቢያተ ሃሰትንማ እዚህ ታሪክ ውስጥ አንጨምራቸውም :: እነሱ ከዲያብሎስ ናቸው::

ነቢዩ ዮናስ ግን፣ የዋሁ ዮናስ ግን፣ ሁሉን አውቆ አንድ ነገር የተዘነጋው የእግዚአብሔር ነቢይ "እግዚአብሔር ሁሉም ሥፍራ መገኘቱ " የተሸፈነበት ሰው:: መፅሀፍ “ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ
ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ” እንዳለ (መዝ: ዳዊ 139 ፥ 7)። ከአምላኩ ሸሽቶ ተኝቶ ነበር:: ብዙም ሳይቆይ ግን ከእግዚአብሔር የሸሸው ዮናስ ከከባድ እንቅልፉ በተጨነቁት የመርከቧ ተሳፋሪዎች ቅስቀሳ እንዲነሳ ሲደረግ፤ ደነገጠ፣ ነገር ተለውጧል :: ሁሉም ነገር ከሰዎች ዓቅም ብላይ ሆኗል:: የሚደብቅበት ጥግ የሚሸሽበት ጫካ የሚሄድበት ሀገር የለውም :: በውቅያኖስ ተከቦ ነፍስ ውጪ ንፍስ ግቢ ጭንቀት :: ከሞት ጋር ግብ ግብ:: ከመልዓከ ሞት ጋር ትንቅንቅ:: ያስፈራል። በሚያየው ነገር ሁሉ ይሄ ነገር የመጣው በኔ ምክንያት ነው የሚል ውሳኔ ወዲያው ወደ አዕምሮው ገባ:: ጥፋቱ ገባው:: ዳዊት :- "ለስሒት መኑ ይሌብዋ " እንዲል ስሕተቱን ያላስተዋለው ዮናስ ጥፋቱን በማዕበል ውስጥ አያት:: በእግዚአብሔር ቁጣ ውስጥ አስተዋላት:: የሸሸው ቦታ ድረስ የተከተለውን አምላኩን ሥራ አየና ባሕሩ ጸጥ እንዲል ጥፋቱ እንዲቆም ምን እናድርግ ባሉት የሰዎቹ ጥያቄ ውስጥ : “እኔ ጣሉኝ!” ይሚል ድምፅ ለራሱ ተሰማው:: ራሱ በራሱ ላይ ወስኖ " የወደደከውን አድርገሀልና እናመሰግንሃለን" እስኪሉ ድረስ በሚያስገርም ሁኔታ ከጥልቁ እንዲወድቅ ሆነ::

ነገር ግን በሥህተቱ ሊያስተምረው፣ በነፍሱ ላያጠፋው፣ ትዕዛዙን እዲያደርስ አስቀድሞ ነቢዩን የዋሁን የወደደው የመረጠው አምላክ ሳይተወው በጥልቁ ውስጥ እንዲያመሰግን አፉን ለምስጋና ሳይዘጋ፣ አንደበቱን ሳይከለክል፣ በከርሰ አንበሪ ሆድ ውስጥ ሳያሟሟው፣ ነፍሱን ከሥጋው ሳይለየው፣ እስትንፋስ ሰጥቶ በዓሳ አሳፍሮ ነነዌ ጠረፍ ላይ ወርውሮ የአንድ ቀን መንገድ በእግሩ አስጉዞ "ነነዌ ትገለበጣለች" ብሎ እንዲሰብክ አደረገው::

"በልዎ ለእግዚአብሔር ግሩም ግብርከ"
"እግዚአብሔር ሥራህ ድንቅ ነው በሉ"
የነነዌ ሰዎችም የነቢዩን ቃል ሰምተው ከገቢረ ኃጥዕ ወደ ገቢረ ፅድቅ፤ ከርኩሰት ወደቅድስና ተመልሰው መዓቱ በምህረት ቁጣው በትዕግስት ተመልሶላቸው ንስሐ ገብተው ከቁጣው ዳኑ:: የእሳት ምልክት አይተው የምህረቱ ደጅ ተከፈተላቸው:: የነደደው እሳት የዛፍ ቅጠል በልቶ ማስጠንቀቂያ ሰጥቶ ተመለሰ:: ምክንያቱም “አንኳኩ ይከፈትላችሁአል፤ እሹ ታገኛላችሁ፤ ለምኑ ይሰጣችሁአል” የማቴዎስ ወንጌል ምዕ 7፥ 7 (ቀሪውን ትን/ ዮናስ ከምዕ 4 እስመ ፍፃሜ ምዕራፍ ያንብቡ)።

የትምህርቱ ምስጢር:-
ዮናስ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ አንበሪ ማደሩ:-
ጌታችን ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሠ መቃብር የማደሩ ምሳሌ፤
ነቢዩ በሦስተኛው ቀን ከዓሳው ሆድ ውስጥ መውጣቱ:-
ጌታም በሶስተኛው ከሙታን የመነሳቱ ምሳሌ፤
የነነዌ ሰዎች ንስሐ መግባታቸው እና መመለሳቸው:-
በንስሐ የማይመለስ ኃጢአት አለመኖሩ፤
ነቢዩ እንደ ስሙ የዋህ ርግብ እንደሆነ ሁሉ:-
እናንተም እንደ ዮናስ ቅኖች የዋሆች ሲል፤
በአንደኛው ጥሪ እና ትዕዛዝ እንቢ ብሎ ቢሸሽም በሁለተኛው ግን ከስህተቱ ተምሮ ከአምላኩ እንዳልተለያየ ክብሩም እንዳልጎደለ :-
እናንተም ብትሳሳቱ የዋህ ከሆናችሁ፣ እውቀት ከጎደላችሁ፣ ከስህተታችሁ ከተመለሳችሁ ሁለተኛ እድል እንደሚሰጥ ለማስተማር ነው፤

"ወኩሉ ዘተፅህፈ ለተግሳፀ ዚአነ ተፅህፈ እንዲል መፅሀፍ ""መፃህፍት ለኛ በህይወተ ሥጋ በቁመተ ሥጋ ላለነው ለምክር እና ለተግሣፅ ይሆኑን ዘንድ ተፅፈዋልና ነው። ይቆየን

የቅድስት ሥላሴ በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን!!!
የበረከት ፆም ያድርግልን!
ቨርጅንያ ቅድስት ሥላሴ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን
የካቲት 01 ቀን 2017 ዓ/ም

02/09/2025

መልካም ሰንበት!

በወቅታዊ ጉዳይ ከቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠ መግለጫ______በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ  የነገረ መለኮት ፣ የነገረ ቤተ ክርስቲያን፣ የታ...
12/26/2024

በወቅታዊ ጉዳይ ከቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠ መግለጫ
______
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮት ፣ የነገረ ቤተ ክርስቲያን፣ የታሪክ፣ የቅኔያትና የጥንታዊ የቤተ ክርስቲያን መሠረተ ትምህርት የሚራቀቅበትና የሚመሠጠርበት ዓለም አቀፍ ጥናትና ምርምር የሚደረግበት ብቸኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ ዩኒቨርሲቲና የልሕቀት ማእከል ነው።

ይህ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ደቀመዛሙርት ዘመኑን የዋጁ፣ በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ፣ እየሠራ ነው። ይህንን መልካም ተግባር የበለጠ ለማዘመን ተቋሙም ዓለም አቀፋዊ ደረጃቸውን የጠበቁ በቂ የመማርያ ክፍሎች፣ የቤተመጻሕፍት፣ የተማሪዎች ማረፊያ፣ የምርምር ማእከላት፣ ዘመናዊ አዳራሾች፣ ዓለም አቀፋዊ ጉባዔያት ማከናወኛና የእንግዳ መቀበያዎች በማስፈለጋቸው ከፍተኛ ራእይ ሰንቆ መጠነ ሰፊ የማስፋፊያ ሥራዎች እያከናወነ ነው።

ይህ የሕንጻ የማስፋፊያ ሥራ የመሠረት ድንጋይ ከማስቀመጥ ጀምሮ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ የሥራ አመራር አካላት በየጊዜው በቦታው በመገኘት የግንባታውን ሒደት በመከታተል እያበረታቱ ይገኛሉ።

ሰሞኑን ዩኒቨርሲቲው እያስገነባ ያለውን B+G+8 ሕንጻ በተመለከተ በአንድም በሌላም በተለያዩ አካላትና ሚዲያዎች የተመለከተናቸው የቤተ ክርስቲያንን ክብር የማይመጥኑ፣ ሐሰተኛና ያልተጣሩ፣ የተዛቡ ዘገባዎች ተሰራጭተዋል። እነዚህ ዘገባዎች የቤተ ክርስቲያንን የውስጥ ጉዳይ በማኅበራዊ ሚዲያ በመደለል ከቅድስት ቤተክርስቲያን ክብር ይልቅ ለራሳቸው ጥቅም የሚሯሯጡ ወገኖች ዘመቻ ውጤቶች ናቸው። በሚዲያ ዘመቻው የተናፈሱ ወሬዎች የሚያደናግሩ፣ ብዥታ የሚፈጥሩ በመሆናቸው የዩኒቨርሲቲው ምሩቃን፣ ደቀ መዛሙርት፣ የዩኒቨርሲው ወዳጆች እንዲሁም ለቤተ ክርስቲያን ከሚቆረቆሩ ማኅበራት መምህራንና ምእመናን ምላሽ እንድንሰጥ በልዩ ልዩ መልኩ እየጠየቃችሁን መሆኑን እያስታወስን ስለተቆርቋሪነታችሁ የአበው አምላክ ያክብርልን እንላለን።

ዩኒቨርሲቲው የቤተ ክርስቲያንን ችግር ፈቺ አካል እንጂ ተጨማሪ ችግር ፈጣሪ መሆን ስለሌለበት በተለይም ለሀገራችን እና ለቤተ ክርስቲያናችን ፈታኝ በሆነው በዚህ ወቅት በየሚዲያው የእሰጣገባ ምላሽ መወራወር ለቤተ ክርስቲያኒቱና ለዩኒቨርሲቲው የማይመጥን፣ የምእመናንና የሊቃውንትን ጊዜ የሚያባክን፣ በመከራ ውስጥ ባለችው ቤተ ክርስቲያን ሌላ መከራ የሚጨምርና ለጠላት በር የሚከፍት በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ነገሮችን ሁሉ በትዕግስት ለማለፍ እየሠራ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው የሕንጻ ግንባታ ሒደትና አፈጻጸሙን በተመለከተ ጥያቄ ላላቸው አካላት ግልጽ ለማደረግ በሕጋዊ መንገድ በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ በተመደቡ ብፁዕ ጳጳስ ከሚመሩት አጣሪ ጋር በሙሉ ትብብርና በግልጸኝነት እየሠራ ይገኛል። ውጤቱም ተጠናቆ ውሳኔ ሲያገኝ ይፋ የሚደረግ ይሆናል።

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተዳደራዊ የሥራ ሒደትና የአሠራር አለመግባባቶችን ለሚዲያ ፍጆታ ብቻ በማዋል፣ ሰድቦ ለሰዳቢ በመስጠት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክብር የማይመጥኑ ተግባራት ሲፈጸሙ ማየት የተለመደ ተግባር እየሆነ መጥቷል። ዩኒቨርሲቲው በፍጹም በዚህ የቤተ ክርስቲያንን ክብርና ዝና የማይመጥን ተግባር ውስጥ ገብቶ የመዳከር ተነሣሽነትና ፍላጎት የለውም። በሰሞኑ የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ዩኒቨርሲቲውን ከሚመሩት ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ/ ፕሬዝዳንት ጀምሮ የዩኒቨርሲቲውን ማኅበረሰብና የቤተ ክርስቲያንን ክብር የማይጠብቁና ያልተጣሩ ሐሰተኛና የተዛቡ መረጃዎች ተሰራጭተዋል። ዩኒቨርሲቲው ለተሰራጩት የሐሰት ወሬዎች ሁሉ በማስረጃ የተደገፈ ምላሽ መስጠት ይችላል። ነገር ግን ለሐሰት ወሬዎቹ የሚሰጠው ምላሽ ጥያቄ ላላቸው አካላት ግልጽ ለማደረግ የተጀመረው የማጣራት ሥራ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ስለሚኖረው የማጣራት ሒደቱ እስከሚጠናቀቅ ይቆይ ብለናል።

ዩኒቨርሲቲው የተጀመረው የማጣራት ሥራ ተጠናቅቆ በወሳኙ አካል (በቋሚ ሲኖዶስ) ውሳኔ ሲያገኝ ውጤቱን በይፋ ያሳውቃል። ነገር ግን ማናቸውም የዩኒቨርሲቲውን ስም የሚያጎድፍ ሐሰተኛ ወሬ በሚያሰራጩ አካላት ላይ የሕግ ክፍላችን የዩኒቨርሲቲውን ሰላም ለማስጠበቅ ሕጋዊ መንገዶችን ለመሔድ የሚገደድ መሆኑን በአጽንኦት ለማሳሰብ እንወዳለን።

ከሕንጻ ግንባታ ሥራ ጋር ተያይዞ ማንኛውም ጥያቄና አስተያየት አለኝ የሚል አካል ካለ ዩኒቨርሲቲው በግልጽ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሓላፊዎች ለማስረዳት ዝግጁ መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ እንወዳለን።

ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ታኅሣሥ ፲፯ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም

12/22/2024

መልካም ዜና:-

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአፋን ኦሮሞ ቴሌቭዥን የሙከራ ስርጭቱን ጀመረ
*****
(EOTC-AO ታህሳስ 13, 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ)
***
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምቱ ምልዓተ ጉባኤ በአፋን ኦሮሞና በሌሎችም ቋንቋዎች የሚሰራ ቴሌቭዥን በአዲስ መልክ እንዲደራጅ መወሰኑ የሚታውስ ነው።

በዚሁ ውሳኔ መሰረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአፋን ኦሮሞ ቴሌቪዥን መገናኛ ብዙኃን የሙከራ ስርጭት ጀምሯል።

ስርጭቱን ማግኘት ለምትፈልጉ
𝐅𝐫𝐞𝐪𝐮𝐞𝐧𝐜𝐲 𝟏𝟏𝟓𝟒𝟓
𝐬𝐲𝐦𝐛𝐨𝐥 𝐫𝐚𝐭𝐞 45000
𝐏𝐨𝐥𝐚𝐫𝐢𝐳𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 : 𝐇
𝐅𝐄𝐂: 𝟓:𝟔

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቻይና ምድር የመጀመሪያዋን ደብር ሰየመችቤተ ክርስቲያኗ በቻይና ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ በከፈተችው ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ አከናውናለች::ብፁ...
12/09/2024

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቻይና ምድር የመጀመሪያዋን ደብር ሰየመች
ቤተ ክርስቲያኗ በቻይና ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ በከፈተችው ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ አከናውናለች::

ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በቻይና የመጀመሪያውን አንድ ኢትዮጵያዊ ዲያቆን ሾመዋል
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቻይና የመጀመሪያዋን ደብር መሰየሟ ተገለጸ።
በቻይና በቻይና ምድር የተከፈተው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን “ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም” የሚል ስያሜ እንደተሰጠውም የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት መረጃ ያመለክታል።
ሐዋርያዊ አገልግሎት ቻይና የገቡት ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ አዲስ የተከፈተችውን ቤት ክርስቲያን ከሰየሙ በኋላ ሥርዓተ ቅዳሴ በመፈጸም ምዕምናንን ማቁረባቸውም ተነግሯል።

በተጨማሪም ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በቻይና የመጀመሪያውን አንድ ኢትዮጵያዊ ዲያቆን መሾማቸውም ነው የተገለጸው።
በዕለቱም ከቻይና የተለያዩ ክፍላተ ግዛት የተሰባሰቡ ምዕመናን፣ ቻይናውያን እና ትውልደ ቻይናውያን በሥርዓተ ቅዳሴው ላይ መሳተፋቸውም ተነግሯል።
ከሥርዓተ ቅዳሴው በኋላ በቻይና የሚገኙት በፅዕ አቡን ያዕቆብ ለቀጣይ አገልግሎት ወደ ሀገሪቱ መዲና ቤይጂንግ ከተማ ማቅናታቸውም ነው የተገለጸው።

@አል አይን

ታላቅ የምስራች !!!በመላው ዓለም በዲሲ ሜሪላንድ ቨርጂንያ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ልጆች እንኳን ደስ አላችሁ። በዋሽንግተን ዲሲ ሀገረ ስብከት የደብረ...
09/11/2024

ታላቅ የምስራች !!!

በመላው ዓለም በዲሲ ሜሪላንድ ቨርጂንያ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ልጆች እንኳን ደስ አላችሁ።

በዋሽንግተን ዲሲ ሀገረ ስብከት የደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ወቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ሀብተማርያም የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን በሰሜን አሜሪካ በቨርጂንያ ስቴት በፌርፋክስ ግዛት ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን በብዛት በሚገኙበት በመሀል ኸረንደን ከተማ በተመሰረተ በጥቂት ጊዜ ለበርካታ ምዕመናን መጽናኛ ሊሆን የሚችል:-
👉 በ10635 SF ላይ ያረፈ ግዙፍ ህንጻ
👉 ከ250 በላይ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ያለው
👉 ከ20 በላይ ልዩ ልዩ ክፍሎች ያሉት
👉 ደብሩን በልማት ተጠቃሚ ሊያድርግ የሚችል ለተለያየ
የማህበረሰብ አገልግሎት (community service)
የሚውል ሁለገብ አዳራሽ ያለው
👉 ከ550 ሰው በላይ መያዝ የሚችል ቤተመቅደስ
👉 ለዋሽንግተን ዳላስ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ በ2 ማይል ርቀት ላይ የሚገኝ
👉 ለማንኛውም ሜትሮ ተጠቃሚ አመቺ ቦታ
👉 ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ከኢትዮጵያ ወደ ሰሜን አሜሪካ ለሀዋርያዊ አገልግሎት ሲመጡ ማረፊያ የሚሆን ታላቅ ህንጻ በ2,750,000 የአሜሪካን ዶላር ገዝተን በዛሬው እለት ጳጉሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ም የቁልፍ ርክክብ አደረግን። ይህን ያደረገ እግዚአብሔር ይመስገን። ወንጌለ መንግስቱ የሚሰበክበት ፣ ብዙሃን የሚጽናኑበት ፣ ቅዱስ ቁርባንን የሚቀበሉበትና ትውልድ በሃይማኖትና በፈሪሃ እግዚአብሔር የሚታነጽበት ያድርግልን።

የደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ወቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ሀብተማርያም የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን በርካታ የነገረ መለኮት ሊቃውንት የአብነት መምህራን በርካታ አገልጋዬች ፣ ሰ/ትቤትና ጠንካራ ማኅበረ ምዕመናን ወምዕመናት ያሉበት ደብር ነው።

ከዚህ ቀደም በኪራይ በነበረው ቦታ በደብሩ ባሉ ሊቃውንት ስብሀተ ማህሌት ፣ ጸሎተ ሰዓታት ፣ ስርአተ ቅዳሴ ፣ ትምህርተ ወንጌል፣ የህጻናትና የወጣቶች መንፈሳዊ ትምህርት በስፋት ሲሰጥበት ቆይቷል። ወደፊት በተለየና በተጠናከረ መልኩ ይህንኑ አገልግሎት በሰሜን አሜሪካ ተወልደው ለሚያድጉ ህጻናትና ወጣቶች ዘመኑን በወጀ መልኩ የአማርኛና የእንግሊዝኛ የመጽሀፍ ቅዱስና የአብነት ትምህርት ፣ ኢትዮጵያዊ ባህል ፣ ትውፊት ቋንቋና ግብረ ገብ እንዲሁም የማህበረሰብ አገልግሎት (community service) በተደራጀና በተጠናከረ መልኩ ለመስጠት የሚያስችል በቂ ስፍራ ስላገኘን አምላከ ቅዱሳን ልዑል እግዚአብሔርን በእጅጉ እናመሰግናለን።

ሕንፃውን ለመግዛት ባደረግነው የገንዘብ ማሰባሰብ በገንዘባችሁ የተሳተፋችሁ ፣ በጸሎታችሁ ያገዛችሁን ፣ በሃሳባችሁ የረዳችሁን በአስጨናቂውና በመከራው ሰዓት ከእኛ ጋር የነበራችሁትን ሁሉ ልዑል እግዚአብሔር በጤና በእድሜ በሀብት በበረከት ይጠብቅልን በማለት ከፍ ያለ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

"ኵሎ ዘፈቀደ ገብረ እግዚአብሔር ፣ እግዚአብሔር የወደደውን ሁሉ አደረገ" (መዝ.134/135÷6)

ደብረ ከርቤ ቅ/ማርያም ወቅ/ሚካኤ ወአቡነ ሀብተማርያም የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን። ኸረንደን ቨርጂንያ።

2472 Centreville Rd, Herndon, VA, 20171
ረቡዕ ጳጉሜ ፭ ቀን ፳፻፲፯ (2024) ዓ.ም

መምህር ሰሎሞን ሀይሌመምህር ዮሐንስ ለማመምህር ዮናስ ፍቅረበክርስቲያን ካውንስሊንግ ሁለተኛ ዲግሪ (MTH) በመመረቃችሁ ኢትዮ ትንሣኤ ኤዲቶሪያል አባላት የተሰማንን ልባዊ ደስታ እንገልጻለን:...
07/03/2024

መምህር ሰሎሞን ሀይሌ
መምህር ዮሐንስ ለማ
መምህር ዮናስ ፍቅረ

በክርስቲያን ካውንስሊንግ ሁለተኛ ዲግሪ (MTH) በመመረቃችሁ ኢትዮ ትንሣኤ ኤዲቶሪያል አባላት የተሰማንን ልባዊ ደስታ እንገልጻለን::

እንኳን ደስ አላችሁ!

ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም
ኢትዮ ትንሣኤ ሚዲያ

Photo Credit to Photo Me

ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫበስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ...
06/06/2024

ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቅዱሳን አበው ሐዋርያት ትውፊት በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባውን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በርካታ አጀንዳዎችን በመቅረጽ ውይይት ሲያካሄድ ሰንብቷል፡፡

ምልዓተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት፣ ለመንፈሳዊ ዕድገትና ለምእመናን ደኅንነት ትኩረት በመስጠት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡

በዚሁ መሠረት፡-

፩.በቅድስት ቤተ ክርስቲያንና በሀገራችን መንግሥት መካከል ሊኖር ስለሚገባው መልካም የሥራ ግንኙነት በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሚመካከር የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ልዑክ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፤

፪.በመላው ሀገራችን በተፈጠሩ ግጭቶች፣ አለመግባባቶችና የሰላም ዕጦት በርካታ የሰው ሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት እንደቀጠለ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን በእጅጉ አሳዝኗል፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከግጭትና ከጥፋት ድርጊት ተቆጥበው የተፈጠረውን አለመግባባትና ግጭት በውይይትና በምክክር እንዲፈቱ እና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንኦት ጥሪውን ያቀርባል፤

፫.በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት ምክንያት ለፈረሱ የቤተ ክርስቲያናችን ይዞታዎች የከተማ አስተዳደሩ ምትክ ቦታ በመስጠትና ቤተ ክርስቲያናችን ወደ መልሶ ማልማት እንድትገባ ድጋፍ በማድረግ፤ በተለይም ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በፈረሰው የጽርሐ ምኒልክ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃ ምትክ በከተማ አስተዳደሩ ሙሉ ወጭ ተጨማሪ ምድር ቤትና የቦታ ስፋት ያለው B+G+4 ሕንፃ ገንብቶ ለማስረከብ ቃል በመግባትና የቤተ ክርስቲያናችን የበላይ ኃላፊ አባቶች በተገኙበት የመሠረት ድንጋይ እንዲጣል ማድርጋቸውን ቅዱስ ሲኖዶስ ከምስጋና ጋር የተቀበለው ሲሆን በተሰጠን ምትክ ቦታ ላይም የከተማው ፕላን በሚፈቅደው መሠረት የመልሶ ማልማት ሥራው እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

፬.የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት አዋጅ መረዳት እንደሚቻለው ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክርና በውይይት ለመፍታት የተቋቋመ መሆኑን ተረድተናል፡፡ ይሁን እንጅ ሀገረ መንግሥትን ከመመሥረት ጀምሮ በአስታራቂነትና በሰላም ግንባታ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ለሆነችው እናት ቤተ ክርስቲያን እስከአሁን ድረስ በይፋ የቀረበ የተሳትፎ ጥሪ ሳይኖር ኮሚሽኑ የተሳታፊ ልየታንና አጀንዳ መረጣ አጠናቆ ወደ ምክክር ትግበራ እየገባ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን ቅር አሰኝቷል፡፡ በመሆኑም የቤተ ክርስቲያኒቱ ተሳትፎና አጀንዳ የማቅረብ መብቷ እንዲረጋገጥ ከኮሚሽኑ ጋር በመነጋገር ጉዳዩን ተከታትሎ ለፍጻሜ የሚያበቃ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡

፭.የብፁዓን አባቶች የዝውውርና የአህጉረ ስብከት ሥያሜን አስምልክቶ የቀረቡ ጥያቄዎችን ምልዐተ ጉበኤው ተመልክቶ ተገቢውን ውሳኔ አሳልፏል፤

፮.የሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በረቂቅ አዋጁ ሊሻሻሉ ይገባቸዋል ብሎ ያመነባቸውን የማሻሻያ ሐሳቦች በማዘጋጀት ለሚመለከተው መንግሥታዊ ተቋም እንዲላክና ረቂቅ አዋጁ ከመጽደቁ በፊት የተሰጡት የማሻሻያ ሐሳቦች በረቂቁ ስለመካተታቸው ክትትል የሚያደርግ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡

፯.በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ ተመሥርቶ አባታዊ ምክርና ተግሣጽ ማስተላለፍ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው መሆኑ ቢታወቅም በሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተፈጠሩ አለመግባባቶች የተከሰቱትን ወቅታዊ ችግሮች አስመልክቶ እየተላለፉ ያሉ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ መልእክቶችን ቅዱስ ሲኖዶስ የማይቀበላቸውና በጥብቅ የሚቃወማቸው መሆኑን እየገለጸ ወደፊት እንዲህ ዓይነት ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጸም ለማድረግ ይቻል ዘንድ ወጥ የሆነ የመግለጫ አሰጣጥና የትምህርተ ወንጌል ተልእኮ ሕገ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምልዐተ ጉበኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

፰.ግብረ ሰዶማዊነትና የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በሕገ ተፈጥሮም ሆነ በሰው ልጅ የሰብዓዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው፣ ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር መለኮታዊ ፈቃዱ በተገለጠባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ፈጽሞ የተከለከለ፣ በቀኖናተ ቤተ ክርስቲያን፣ በፍትሕ መንፈሳዊና በፍትሐ ብሔር ድንጋጌዎች፣ በሥነ ልቦና ደንቦች የተወገዘ፣ ሥነ አእምሮዊ ሚዛንን የሚያዛባ፣ ግለሰባዊ ማንነትን፣ ቤተሰባዊ ሕይወትን፣ ማኅበራዊ ትሥሥርን የሚጎዳ ተግባር በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ እያወገዘ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና የግብረ ሰዶማዊነትን ኃጢአት በተመለከተ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አቋም በሚገልጽ መልኩ ራሱን ችሎ ዓለም አቀፋዊ ይዘቱን ባገናዘበ ሁኔታ ዝርዝር መግለጫ እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

፱.በደቡብ የሀገራችን ክፍል የቤተ ክርስቲያኒቱን አብነት ትምህርት ከማስፋፋትና ከፍ ያለ መዐርግ ከመስጠት አንፃር የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዝጊቲ ደብረ ሰላም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን የአራቱ ጉባኤያት ማስመስከሪያ ትምህርት ቤት እንዲሆን በቀረበው ጥናት መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ ለምሥክር ጉባኤ ቤቱ ዕውቅና በመስጠት ወደ ትግበራ እንዲገባ ወስኗል፡፡

፲.ከሀገራችን ውጭ ባሉ አህጉረ ሰብከት መደበኛ አገልግሎት ለመስጠት የሚላኩ አገልጋዮች በክፍሉ ሊቀጳጳስ ሲጠየቅ በሙያ ብቃታቸው፣ በምግባራቸውና በመንፈሳዊነታቸው የተመሰከረላቸው አገልጋዮች ከሁሉም አህጉረ ስብከት በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አቅራቢነት በውድድር እየተለዩ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲላኩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

፲፩.የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ የዐሥር ዓመት መሪ ዕቅድ በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲገባ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ በዚሁም መሠረት ለአፈጻጸሙ ያመች ዘንድ በባለሙያዎች ተዘጋጅቶ የቀረበውን መዋቅራዊ አደረጃጀት በማጽደቅ በሕገ ቤተ ክርስቲያኑና በቃለ ዓዋዲው ተካቶ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

፲፪.በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተዘጋጅቶ የቀረበውን የ2017 ዓ.ም. ዓመታዊ በጀት በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

በአጠቃላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራ ላለፉት ተከታታይ ቀናት በመንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየትና ተገቢውን ውሳኔ በማስተላለፍ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት በጸሎት አጠናቅቋል፡፡ መሐሪና ሁሉን ቻይ የሆነ እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን፣ ፍቅሩንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ግንቦት ፳፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ኢትዮጵያ አዲስ አበባ
©የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት

🎁የምሥራች🎁🌐ከኢትዮጵያ ውጪ ለምትኖሩ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ--------------------------'ሐዲስ ኪዳን ለሕፃናት' የተሰኘውን ተወዳ...
05/23/2024

🎁የምሥራች🎁

🌐ከኢትዮጵያ ውጪ ለምትኖሩ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ
--------------------------
'ሐዲስ ኪዳን ለሕፃናት' የተሰኘውን ተወዳጅ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ስብስብ ሙሉውን መጽሐፍ በስስ ቅጂ (Soft Copy) እነሆ ብያለሁ።

መጽሐፉ፡-
📍140 ገፅ ሲሆን፣ በሙሉ ቀለም የተዘጋጀ ነው።
📍አንድ ታሪክ በአንድ ገፅ ያልቃል፤ ታሪኩን አጉልቶ የሚያሳይ ስእልም በቀጣዩ ገፅ አለው።
📍ከ4-12 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ ልጆች ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
📍ወላጆች፣ ቤተሰቦች፣ ጓደኞች የሆናችሁ ራሳችሁ ልታነቧቸው፣ ለልጆችም ልታነቡላቸው፣ ልታስነብቧቸው ትችላላችሁ።

የአንድ የስስ ቅጂ ዋጋ
• 9 የአሜሪካ ዶላር
• 7 ፓውንድ
• 12 የካናዳ ዶላር
• 8 ዩሮ
• 5 ኩዬት ዲናር ነው።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሒሳብ ቁጥር 1000146133979 ላይ የከፈሉበትን ደረሰኝ እዚህ👉 https://t.me/Ze1619 ቴሌግራም ላይ ከላኩ በኋላ
ይህንን ሊንክ ይጫኑታል
https://drive.google.com/file/d/1FJq1GpfWKRHx2kgSvWtUOz08biaQQi9a/view?usp=drive_link
ከዚያም የሚመጣልዎትን ‹Request access› ሲልኩ መጽሐፉን የሚያገኙበት ፈቃድ ይደርስዎታል፡፡

[በቅርቡ፡- 'ብሉይ ኪዳን ለሕፃናት' የተሰኘውን ተወዳጅ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ስብስብ ሙሉውን መጽሐፍ በስስ ቅጂ (Soft Copy) አቀርባለሁ።]
Share በማድረግ ሌሎች ያድርሱ፡፡

🧲ከመጽሐፉ ላይ ለቅምሻ የሚሆኑ 10 ገፆችን
በዚህ ቴሌግራም 👉https://t.me/Ze1619 ላክልኝ ለሚሉ እጋብዛለሁ!

© የኮፒራይት መብትን ያክብሩ፣ ያስከብሩ!

-------------
ስለመጽሐፉ
ከስመ ጥሩ ካህን ቀሲስ ታድሮስ ማላቲ ላቅ ያለ ጠቀሜታ ያላቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትረካዎች ባማረ ሁኔታ ተጠናቅረው በዚህ መጽሐፍ ቀርበዋል፡፡
ይህ መጽሐፍ ከሕፃናት ጀምሮ እስከወላጆች እንዲሁም በወጣቶች ሃይማኖታዊ ትምህርት ላይ አደራና ሓላፊነት እስካለበት ማንኛውም ሰው ድረስ ሐዲስ ኪዳንን እና በውስጡ የተካተቱትን እጅግ ወሳኝ ታላላቅ ክስተቶች በአስደናቂ ሁኔታ የያዘ በሁሉም እድሜዎች ለሚገኙ ሁሉ የሚጠቅም ነው፡፡
ይህ የከበረ መጽሐፍ አማርኛው ለሁሉም በሚገባ መልኩ የተዘጋጀና በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ በደስታ እንድንጓዝ የሚጋብዝ ሲሆን ለበርካታ ቀጣይ ትውልዶችም ትልቅ ዋጋ ያለው ሐብት ነው፡፡

የመጽሐፉ መግቢያ
የተወደዳችሁ አንባቢዎች፤ ይህ በእጃችሁ ያለው መጽሐፍ ከልጆቻችሁ ጋር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪኮችን በቀላሉ በየዕለቱ እንድታነቧቸው ሆነው የተዘጋጁት የሁለቱ ተከታታይ መጻሕፍት (ብሉይ እና ሐዲስ ኪዳን) አንዱ ክፍል ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሁሉም ዕድሜዎች ለሚገኙ ለሁሉም ሰዎች መረዳትን የሚሰጥ መለኮታዊ ጥበብን ያስተላልፋል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስን በእምነት መንፈስ የሚያነበው ሁሉ እግዚአብሔርን ለማወቅ ይጥራል፤ እግዚአብሔር ለሁሉም የሰው ዘር ያለውን የተትረፈረፈ ፍቅርም በሕይወቱ ይለማመዳል፡፡
1. ልጆቻችሁ ጥቅሶቹን እንዲያውቋቸው፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉት ብዙዎቹ ጥቅሶች አልተለወጡም፡፡
2. ለልጆቻችሁ፣ ይህን መጽሐፍ ዕለት ተዕለት በምትጠቀሙበት ቋንቋ አንብቡላቸው፤ ልጆቻችሁም በቀላሉ ሊከተሏችሁ ይችላሉ።ልጆቻችሁ ሲያድጉም ማብራሪያዎች ያሉበትን ይህን መጽሐፍ ራሳቸው እንዲያነቡት ፍቀዱላቸው፤ በዚህም ልጆቻችሁ በሂደት መጽሐፍ ቅዱስን ያለረዳት ማንበብ ይችላሉ፡፡
-----------
ቀሲስ ታድሮስ ያዕቆብ ማላቲ የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ካህን ሲሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ አንድምታ (ኮሜንታሪ) መጻሕፍትን በመጻፍ የታወቁ ሊቅ ናቸው።
----------
ዘኤልያስ ወልደ ሚካኤል Zealias Wolde Michael

“ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ" (ማር.4÷24) *********************************ከብፁዕ አቡነ አብርሃም የደቡብ አፍሪካ ጉዞ መሰረዝ ጋር  ተያይዞ የሐሰት ዜና በመሰራጨት ላይ ...
05/10/2024

“ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ" (ማር.4÷24)
*********************************

ከብፁዕ አቡነ አብርሃም የደቡብ አፍሪካ ጉዞ መሰረዝ
ጋር ተያይዞ የሐሰት ዜና በመሰራጨት ላይ ይገኛል።
*********************************

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ጆሐንስበርግ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተበት ፳፭ኛ ዓመት በዓል ላይ ለመገኘት፣ ቅዳሴ ቤቱን ለማክበርና በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትን ለመባረክ እንዲሁም ምዕመናንን ለማስተማር ዛሬ ማለዳ ከቅዱስነታቸው ጋር ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመጓዝ መርሐ ግብር ይዘው እንደነበር ይታወቃል።

ይሁን እንጂ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ካለባቸው ተደራራቢና አስቸኳይ ሥራዎች አንጻር ለአሥር ቀናት ከጽሕፈት ቤታቸው ርቀው መቆየት በጠቅላይ ጽ/ቤቱ የዕለት ተዕለት ሥራዎች ላይ ክፍተት እንዳይፈጠር በመስጋታቸው እንዲሁም ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊውና ምክትል ሥራ አስኪያጁ በሌሉበት በቢሮኘቸው በሌሉበት ሁኔታ ለበርካታ ቀናት ከጠቅላይ ጽሕፈቱ ርቀው ከተጓዙ ሥራዎች ስለሚበደሉ ቀደም ሲል ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊያደርጉት የነበረውን ሐዋርያዊ ጉዞ ከቅዱስነታቸው ጋር በጥሞና በመወያየት ለመሰረዝ ተገደዋል።

ይሁን እንጂ እውነታው ይኸው ሆኖ ሳለ በአንዳንድ ማኅበራዊ ገጾች ፈጽሞ እውነትነት በሌለው መንገድ ብፁዕነታቸው ወደ ኤርፖርት እንዳይሔዱ እንደተከለከሉና ፓስፖርታቸው እንደተያዘ በማስመሰል የሚሰራጨው ዜና ፍፁም መሰረተ ቢስና የሐሰት ዜና ነው።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ከታቀደው ሐዋርያዊ ጉዞ ለመቅረት የተገደዱት በተደራራቢ ሥራ ምክንያት መሆኑንና የብፁዕነታቸው ፓስፖርትም ለጉዞ ሲባል ቀደም ብሎ ከሚመለከተው አካል መጥቶ በልዩ ጽሕፈት ቤቱ ጉዳይ አስፈጻሚ እጅ የሚገኝ መሆኑን እንገልጻለን። የቤተ ክርስቲያን ልጆች ምእመናንና የቤተ ክርስቲያናችን ወዳጆችም በአንዳንድ መንፈሳዊ ኃላፊነት በማይሰማቸው ማኅበራዊ ገጾች የሚሰራጨው መረጃ የሐሰት መሆኑን እንዲያውቁና ራሳቸውን ከሐሰተኛ መረጃዎች እንዲጠብቁ ለማሳሰብ እንወዳለን።

የዜናው ምንጭ
የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ኢትዮ ትንሣኤ ሚዲያ
ግንቦት ፪ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም (2024)

እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና አደረስዎ!
04/25/2024

እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና አደረስዎ!

*** አይናቸውን ለማብራት 400 ሺህ ዶላር ያስፈልጋል ***ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር ግማሽ ሚሊዮን (500ሺህ) ብር፣ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ 100ሺ ብር በመስጠት ጀምሯል  ደጋግ ኢትዮጵያውያኖች የ...
04/25/2024

*** አይናቸውን ለማብራት 400 ሺህ ዶላር ያስፈልጋል ***

ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር ግማሽ ሚሊዮን (500ሺህ) ብር፣
ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ 100ሺ ብር በመስጠት ጀምሯል ደጋግ ኢትዮጵያውያኖች የአቅማችሁን በማድረግ የትዕግስት ሶስት መንታ ልጆች የአይን ብርሃናቸው እንዲመለስ የበኩላችንን እናድርግ።

ሼር በማድረግ እንጀምር!

አካውንታቸው ይህው እባካችሁ
ሼር አድርጉት

* СВЕ 1000622473872
* Dashen Bank 5563671317021
* Abyssinia bank 91613069
* ኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ 1023500172828
* አዋሽ ባንክ 013471254339600

ትግስት ካሳ ቀፀላ

ስልክ
* 0911868306
* 0911137097

go fund me
* https://gofund.me/42557274

ይህን ሼር ማድርግ መልካም ነገር መስራት ነውና እባካችሁ ሼር አድርጉላቸው

ማሳሰቢያ:-በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ለሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን የተላለፈ ጥብቅ መመሪያ:-ሀገረ ስብከቱ እኔ የማላውቀውና ህገ ወጥ ጉባኤ በመሆኑ ማህበረ ካህናትም ማህበረ ምዕመናንም እንዳት...
04/16/2024

ማሳሰቢያ:-

በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ለሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን የተላለፈ ጥብቅ መመሪያ:-

ሀገረ ስብከቱ እኔ የማላውቀውና ህገ ወጥ ጉባኤ በመሆኑ ማህበረ ካህናትም ማህበረ ምዕመናንም እንዳትገኙ ብሏል::

አቡነ ንብሎ   | እንኳን ለጻዲቁ አባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።የዘማሪት ሕይወት ወልዴ አዲሱን « አቡነ ንብሎ ለገብረ ሕይወት»  የተሰኘውን...
03/12/2024

አቡነ ንብሎ

| እንኳን ለጻዲቁ አባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።

የዘማሪት ሕይወት ወልዴ አዲሱን « አቡነ ንብሎ ለገብረ ሕይወት» የተሰኘውን አዲስ ዝማሬ በማኀቶት የዩቲዩብ ቻናል ላይ ተለቋል። ያደምጡት ዘንድ ግብዣችን ነው::

👉 https://youtu.be/YXEbsNVBKN0?si=IY5s1YMqkqDeKlvi

❤️ አዲስ ዝማሬ “ አቡነ ንብሎ “ ዘማሪት ሕይወት ወልዴ ​⁠@-mahtot

Address

Herndon, VA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Tinsae Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Tinsae Media:

Videos

Share

Ethio Tinsae Media

ይህ በምስረታ ላይ የሚገኘው የEthio Tinsae Media (ETM) ኢትዮ ትንሳኤ ሚዲያ ኦፊሻል የFacebook ገፅ ነው፡፡ በርካታ ሚሊዮን የሚቆጠር ተከታይ ያላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እያደገ የመጣውን የማህበራዊ ሚዲያ በንቃት ተፅዕኖ በመፍጠር ረገድ በግል ከሚደረገው አስተዋፅዖ በተጨማሪ በተደራጀ መልኩ አገልጋዮች በጋራ የሚያደርጉት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ በመሆኑም መሰረታቸውን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አድርገው በማህበራዊ ሚዲያ እየተንቀሳቀሱ ያሉትን የሚዲያ ጥረት ይበልጥ ለማገዝ በቤተክርስቲያኗ ልጆች ይህ ETM ሚዲያ በምስረታ ላይ ይገኛል፡፡ በETM ሀይማኖታዊ፣ ማህበራዊ፣ ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖማዊና ሀገራዊ ጉዳዮች በስፋት ይዳሰሱበታል፡፡ ሁላችሁም ሀገር ወዳድ ኢትዮጲያውያን ይህን ሚዲያና መሰል ተቋማትን በማበረታታትና ገንቢ አስተያየት በመስጠት በጋራ እንድንረባረብ ETM ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ይህን ጥሪ ለሎችም በማዳረስ አገልግሎቱን በጋራ እናሳድግ፡፡ ለኢትዮጵያ እና ለቤተክርስቲያናችን አንድነት አበክረን እንሰራለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ የYouTube ቻናሉን Subscribe እና ይህንን የFacebook ገፅ follow የበማድረግም አገልግሎቱን ይደግፉ ። Ethio Tinsae Media