The Gudeta Mekonen

  • Home
  • The Gudeta Mekonen

The Gudeta Mekonen the aim of this page is to assist true Ethnic Federalism to Come to Ethiopia
(1)

በአማራ ክልል የተካሄደው የሀገራዊ ምክክሩ የተሳታፊ ልየታ ሙስሊሙን ያላካተተ መሆኑን ተገለፀ!…(ሀሩን ሚድያ ፦ግንቦት 13/2016)የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለሀገራዊ...
21/05/2024

በአማራ ክልል የተካሄደው የሀገራዊ ምክክሩ የተሳታፊ ልየታ ሙስሊሙን ያላካተተ መሆኑን ተገለፀ!

(ሀሩን ሚድያ ፦ግንቦት 13/2016)

የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በፃፈው ደብዳቤ በአማራ ክልል ለብሄራዊ ምክክር ለሚደረገዉ ሂደት የመጀመሪያ ዙር የምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ሰዎች ተለይተዉ ወደ ስራ እንደገቡ በመግለፅ ነገር ግን በተሳታፊ ልይታ ወቅት ሙስሊሙን ያገለለ እና የክልሉን እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ባላወቀው መልኩ የተካሄደ መሆኑን አንስቷል ።

በክልሉ የኃይማኖት ተቋም አባል የሆነዉን የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በማያዉቀዉና ሳያማክሩ የኔ የሚሉትን ብቻ በማሳተፍ የሀገሪቱ ግማሽ አካል የሆነውን ህዝበ ሙስሊሙን በማግለል የሚፈለገዉን መልካም ዉጤት ያመጣል ብሎ እንደማያምን ገልጿል፡፡

ስለሆነም ችግሩ ተወግዶ አሰራሩ ተሻሽለ- ከፍተኛ ምክር ቤቱ የሚሳተፉ ሰዎችን መልምሎ እንዲያቀርብና ሙስሊሙን የሚያሳትፍ ምክክር እንዲሆን እየጠየቅን አሰራሩ ሳይሻሻል ባለበት የሚቀጥል ከሆነ ለሀገራዊ ምክክሩ እዉቅና የማንሰጥና አስራሩን የምንቃወም መሆኑን በጥብቅ እናሳዉቃለን ሲል ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በፃፈው ደብዳቤ ላይ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡

©ሀሩን ሚድያ

17/05/2024

እንዲው ለጠቅላላ እውቀት ያነሳዉት ጉዳይ እንደሆነ ይታወቅልኝ። በእርግጥ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር መስሪያ ቤት የአሜሪካ አምባሳደር በኢትዮጵያ ላስተላለፉት መግልጫ ምላሽ የሰጡት መልስ በእርግጥ የመንግስት አቋም ነው?

Old old old traford
16/05/2024

Old old old traford

12/05/2024

Poor Arsenal and valueless win

አሜሪካ እና አውሮፓ ቁጭ ብሎ በምቾት ውስጥ ሆኖ ቁረጠው ፍለጠው የሚል ዲያስፓራ ሊያበቃለት ነው።
10/05/2024

አሜሪካ እና አውሮፓ ቁጭ ብሎ በምቾት ውስጥ ሆኖ ቁረጠው ፍለጠው የሚል ዲያስፓራ ሊያበቃለት ነው።

ደቡብ አፍሪካ 🇿🇦 የአለም ዋንጫን ያስተናገደች የመጀመሪያ እና ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ነች። ደቡብ አፍሪካ የ2010 የአለም ዋንጫን አስተናግዳለች። እቺ ልጅ ሚቺ ሚንስ ትባላለች። ለደቡብ ...
05/05/2024

ደቡብ አፍሪካ 🇿🇦 የአለም ዋንጫን ያስተናገደች የመጀመሪያ እና ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ነች።
ደቡብ አፍሪካ የ2010 የአለም ዋንጫን አስተናግዳለች።
እቺ ልጅ ሚቺ ሚንስ ትባላለች። ለደቡብ አፍሪካው ሰንዳውንስ የሴቶች ኤፍ.ሲ ትጫወታለች። በ 2011 ተወለደች።

አሁን የሚሊየን ዶላር ጥያቄ፡-
በደቡብ አፍሪካ በ2010 የአለም ዋንጫ ሮናልዲኒሆ የት ነበር? 🤣🤣🤣

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት የክቡር ዶ/ር ሼህ ሓጂ ኢብራሂም ቱፋ የተመራ ልዑክ ወደ ሶማሌ ክልል መዲና ጅግጅጋ በመግባት በሱማሌ እና በአፋር ህዝቦች መሀል ያለ...
03/05/2024

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት የክቡር ዶ/ር ሼህ ሓጂ ኢብራሂም ቱፋ የተመራ ልዑክ ወደ ሶማሌ ክልል መዲና ጅግጅጋ በመግባት በሱማሌ እና በአፋር ህዝቦች መሀል ያለውን ልዩነት በውይይት እንዲፈታ እያደረጉ ያለው ጥረት በእውነቱ የሚደነቅ እና ለሌሎችም የሃይማኖት አባት ጥሩ ምሳሌ የሚሆን ነው።
እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት የክቡር ዶ/ር ሼህ ሓጂ ኢብራሂም ቱፋ ፈጣሪ ትልቅ እድሜ ይስጦት ይህንን ተሞክሮ በሌሎችም ክልሎች ሞክረው እንዲሳካሎት እመኛለው።

አንዱ የማህበረ ቅዱሳን በጀት አሰባሳቢ ይህ ልጅ ነው። ጆሮው ላይ ያለውን ቃሪያ በደንብ ማብላት ያስፈልጋል።
02/05/2024

አንዱ የማህበረ ቅዱሳን በጀት አሰባሳቢ ይህ ልጅ ነው። ጆሮው ላይ ያለውን ቃሪያ በደንብ ማብላት ያስፈልጋል።

27/04/2024
17/04/2024

What I understand now is Arsenal is not a football club, it's a TV series, that's why we the fans will always wait for next season.

Reassign!!!ወዮ ወዮ ድድብና
11/04/2024

Reassign!!!
ወዮ ወዮ ድድብና

Maal jechudhaa? Enyutu kana raawwate?
10/04/2024

Maal jechudhaa?
Enyutu kana raawwate?

30/03/2024

Maalif warrii "Gindabarat" maqaa jijjirachuu dadhabanii
Gion=walisoo
Asabatafarii= ciroo
Alamxenaa = boteeti Jijjiratani jiru.

24/03/2024

Oromoo ta'uufi
Oromoof ta'uun
Garaagara

06/03/2024

Ilmi abbaa Gadaa ሀገር እየመራ¡ አፋን ኦሮሞ እስካሁን የፌደራል የስራ ቋንቋ እና የሀገሪቱ ብሔራዊ ቋንቋ አለመሆኑን ሳስበው አይ ኦሮሞ በል በል ያሰኘኛል።

24/02/2024

: Command Post imposes ban after militiamen brutally killed 8 civilians in , region

Military command post overseeing the state of emergency in the Amhara region has imposed an indefinite ban of all kinds of movement on the main asphalt road between Debre Berhan and Dessie cities after militiamen brutally killed 8 civilians in Shewa Robit on Friday.

A credible source disclosed to Addis Standard that the 8 civilians were en route to Kemise, from Addis Abeba, when they were intercepted and killed by the non-state local militia called Fano in Shewa Robit, North Shewa zone of the Amhara region.

According to the source, five of the eight killed were men and teachers, whereas the three were women domestic workers returning to their families from the Middle east.

Read more: https://addisstandard.com/news-command-post-imposes-ban-after-militiamen-brutally-killed-8-civilians-in-shewa-robit-amhara-region/

The cruel assassination of Abdinasir Muse, a   who was working as an air transport expert in the neighboring  .After the...
19/02/2024

The cruel assassination of Abdinasir Muse, a who was working as an air transport expert in the neighboring .

After the Republic of Somaliland took full control of its airspace, It is reported that Somalia gov't sadly murdered him.

The body of the deceased should be transported to Somaliland and a thorough examination must be conducted.

  Government calls its citizens residing in   to vacate and be vigilant of potential terrorist attacks against ethnic So...
19/02/2024

Government calls its citizens residing in to vacate and be vigilant of potential terrorist attacks against ethnic Somalilanders.

16/02/2024
ይሄ ሰውዬ ስለ ስላም የመስበክ የመናገር ምን ሞራል አለው?
13/02/2024

ይሄ ሰውዬ ስለ ስላም የመስበክ የመናገር ምን ሞራል አለው?

09/02/2024

በነገራችን ላይ አሜሪካን ያለጉዞ ሰነድ ገብተህ ብትያዝ ፖሊሶች መጀመሪያ ያስሩሃል። ከዛን ቀለል አድርገው ከአልሸባብ ወይስ ከሁቲ አማፂ ነው ተልከው የመጣኸው ብለው ይጠይቁሃል።

"ሰው ነኝ ሰውነት ይቀድማል"... ብትላቸው እሱ ደግሞ የየት ሀገር አሸባሪ ድርጅት ነው ብለው ያፋጥጡሃል። በመስቀለኛ ጥያቄ ሲያጨናንቁህ በድንጋጤ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ታጣቂ ነኝ ትላለህ።

በፌስቡክ ዘመቻ ፣ የሚዲያ ጋጋታ አዝምተህ በፕሮፖጋንዳ ጩኸት ህግን መጣስ በፍፁም አትችልም። የሀይማኖት አባት ነኝ ካልክማ ጭራሽ በX-Ray ማሽን የፈንጅ ማቴሪያል ታጥቋል ብለው ያነሱሃል።

ህግ ጥሰህ ስታበቃ ... በንግግር አንጀት ለመብላት መመኮር ፣ አጀንዳ ፈጥሮ መወከብ ፣ የሰውነት ኮታ ለማደል መብቃት በእራሱ መታደል ነው 😃 ... "ሰው ነኝና" ... የሚለው መፈክር የሚሰራው ለዘፈን ብቻ ነው።
Via Finfinne Press

08/02/2024

እንዴት አንድ የሃይማኖት አባት የሰውን ልጅ "ሰው ሁኑ" ብሎ ለመሳደብ ድፍረት አገኘ። መንፈሳዊ አገልጋይ ለዛውም አባት እግዛብሔርን መፍራት አቆመ።

በአቡነ ሉቃስ የሚመራ አማራዊ ሲኖዶስ እንዲቋቋም ጥሪ ቀረበ‼Source: Dawit D.
23/01/2024

በአቡነ ሉቃስ የሚመራ አማራዊ ሲኖዶስ እንዲቋቋም ጥሪ ቀረበ‼

Source: Dawit D.

23/01/2024

መንበረ ጴጥሮስ! ተመሰረተ ምስጋና የዛን ፋኖ ጳጳስ ንግግር አላወግዝም ላላችሁ ጳጳሳት።

ይህ ሚዲያ በውጪ የፋኖ ቃለ አቀባይ ነው። የዛሬው አዘጋገብ ደግሞ ለየት ያለ ነው።
18/01/2024

ይህ ሚዲያ በውጪ የፋኖ ቃለ አቀባይ ነው። የዛሬው አዘጋገብ ደግሞ ለየት ያለ ነው።

12/01/2024

ግብፅ በቀይ ባህር ላይ በተለይ በኤርትራ እና ሱማሌ ድበሮች በኩል ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንድታደርግ መፍቀድ የለብንም። ይህንን የፈቀደ ሀይል የኢትዮጵያ ጠላት ነው።

12/01/2024

የውስጥ ችግራችንን ቶሎ ጨርሰን ለኤርትራ በአንድነት ዝግጅት ማድረግ ያለብን ይመስለኛል።

12/01/2024

እውነት ነው በጦርነት ውስጥ ነው የቆየነው። ድጋሜ ጦርነት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቅ ውድቀት ያመጣል። አንዳንድ ጊዜ ግን ግድ የሚሆንበት ጊዜ አለ። ከኤርትራ ጋር የሚደረግ ጦርነት በተለይ ለኦሮሞ ህዝብ እንደ ቅዱስ ጦነት ነው የማየው። 1983 በኦሮሞ ህዝብ ላይ ክደት ፈፅመው ከህወሃት ጋር በመሆን ሲኒየር አባቶቻችንን የፈጁት እነሱ ናቸው። አሁን ደግሞ ፀረ ኢትዮጵያ አቋሟቸውን በግልፅ እያየን ነው።

09/01/2024

ከሰሞኑ Jawar Mohammed ከደረጀ ሀይሌ ጋር የነበረውን ቃለለጠይቅ ተከትሎ በርካታ ሚዲያዎች እና ግለሰቦች ጋር መነጋገሪያ የነበረው ጉዳይ በአሁኑ ወቅት ያለውን ስርአተ-መንግስት ለመግለፅ የተጠቀመበት “Anocracy” የሚለው ቃል ነበር:: የስርአቱን አምባገነንነት ለመሸፈን ነው ከሚለው አንስቶ የዛሬ 5 አመት በፊት ተብሎ ቢሆን ኖሮ ተገቢ ነበር አሁን ግን አኖክራሲ ሳይሆን የለየለት አምባገነናዊ ስርአት ነው የሚሉ የተለያዩ አስተያየቶች ተሰጥተዋል::
በተለያዩ ሰዎች የተነሱት ጥያቄዎች ላይ የራሴን ጨምሬ ጃዋርን “Anocracy” በእርግጥ አሁን ያለውን ስርአት ይገልፀዋል ወይ የሚል ጥያቄ አንስቼለት ነበር::
ከዚህ በታች የተያያዘው የጃዋር መልስ ነው (ለማጋራት ፍቃዱን አግኝቻለሁ)
👇

"Anocracy” አሁን ላይ ያለውን ስርአት ይገልፀዋል ወይ?
አምባገነናዊ እና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓቶች ከሚለያዩባቸው ነግሮች ውስጥ አንዱ ሀገርን አረጋግቶ (maintaining peace & order) ለማስተዳደር የሚጠቀሙት ዘዴ ነው። ይህም ማለት፣ አምባገነናዊ ሥርዓት በአመዛኙ ጉልበትን (coercion) ሲጠቀም፣ ዲሞክራሲያዊ መንግስት ደግሞ ቅቡልነት (legitimacy) ስላለው በአብዛኛው ሕግን እና ሕዝባዊ ይሁንታን (consent) ይጠቀማል።

አምባገነናዊመንግስት ተቀይሮ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ሳይመሰረት ባለው የሽግግር ጊዜ፣ ሥልጣን ላይ ያለው ግለሰብ/ቡድን ሀገርንአረጋግቶ ለማስተዳደር ምን ዓይነት ዘዴ ነው የሚጠቀመው? የሚለው ወሳኝ ጥያቄ ነው። አምባገነናዊ መንግስት በጉልበት ማስተዳደር የሚችለው የተቀናቃኞቹን አቅም አመናምኖ፣ ፍፁም የጉልበት የበላይነቱን በማረጋገጥ ነው። ያኔ ሕዝቡ ፈርቶና ተስፋ ቆርጦ ይገዛል። ያ አምባገነን ከሥልጣን ሲገረሰስ፣ በአዲስ አምባገነን ወይም ዲሞክራሲያዊ ስርዐት እስኪተካ ድረስ በሽሽግር ወቅት አለመረጋጋት ይከሰታል። ምክንያቱም ሕዝቡን በጭቆና እንዲገዛ ያደረገው ፍርሃት ስለሚገፈፍ መብቱን ለማስከበር የሚንቀሳቀስ ሲሆን፣ በተቃራኒው ደግሞ የመንግስት ጨቋኝ ተቋማት (coercive apparatus) ስለሚዳከሙም ነው። ይህ ሁኔታ ሥርዓት አልበኝነትን (anarchy) ያስከትላል። ስለዚህ ለጊዜው ሥልጣን የያዘው ኃይል ጉልበትን እና ፍቃደኝነትን/ሕግን እያምታታና እያፈራረቀ ይጠቀማል። ሀገሪቱን ወደ ዲሞክራሲ ማሸጋጋር ካሰበ ከጉልበት ይልቅ ፍቃደኝነት ላይ መንተራስን እየጨመረ ይሄዳል። ይህም በሂደት ቅቡልነት አጎናጽፎት በይሁንታ እና በህግ ላይ የተመሰረት ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ያደርጋል።

በተቃራኒው አዲስ አምባገነን መሆን ከፈለገ ደግሞ ከጊዜ ወደጊዜ ወደ ጉልበት እያዘነበለ የፖሊቲካ ምህዳሩን ይበልጥ እያጠበበ ይሄዳል። አንዳንዱ ይሳካለትና የጉልበት የበላይነትን አስፍኖ የተረጋጋ አምባገነናዊ ሥርዓት ይገነባል። ሌላው ደግሞ አምባገነናዊ ሥርዓት ለመገንባት ሲሞክር የጉልበት የበላይነት ማስፈን ይሳነዋል። ይህ ሁኔታ ሥርዓት አልበኝነትን (Anarchy) የበለጠ ያስፋፋል። እናም በሂደት ወደ ዲሞክራሲ ተሸጋግሮ በሕግ እና በሕዝባዊ ቅቡልነት፣ አልያም አምባገነናዊ ሥርዓት መስርቶ በጉልበት የበላይነት መረጋጋትን ማምጣት ያልቻለን ሥርዓት ሊገልፀው የሚችለው “Anocracy” ነው። ይሄም የሚፈጠረው አንድ ሽግግር ወደ ዴሞክራሲም ሆነ ወደ አምባገንነት መለወጥ ሲያቅተው ነው።

የ“Anocracy” ቀጥተኛ ትርጉሙ ግማሽ ዲሞክራሲ፣ ግማሽ አምባገነንነት የሚታይበት የመንግስት ስርዐት ማለት ነው። እንዲህ ዓይነት ሥርዓት በሁለት ምክንያት ሊፈጠር ይችላል። አንደኛው አምባገነናዊ ሥርዓት ከወደቀ በኋላ ቀጥሎ የሚከሰት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ዲሞክራሲያው ሥርዓት ሲሸረሸር (democratic regression) የሚታይ ነው።“Anocracy” ከዲሞክራሲም ሆነ ከአምባገነናዊ ሥርዓቶች የበለጠ ግጭቶች የሚታይበት ነው። ስረዓተ መንግስቱ ( state) የጉልበት የበላይነት (monopoly over the means of violence) ስለሚያጣ ገዢው ቡድንም ሆነ ተቀናቃኞቹም መረን የለቀቀ ጥቃቶችን (uncontrolled violence) ይፈፅማሉ። ሽብር፣ ዘረፋ፣ ግድያ እና ማፈናቀል በሰፋት ይታዩበታል።ዛሬ እንደ ኢትዮጵያ እና ሶሪያ ያሉ ሀገሮች በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ነው ያሉት።
አንዳንዶች አሁን ኢትዮጵያውስጥ ያለው ሥርዓት አውቶክራሲ (autocracy) ነው ሲሉ ሰምቻለው። አውቶክራሲ ማለት በአንድ ግለሰብ ፍፁም የበላይነት የሚመራ የአምባገነናዊ ሥርዓት ነው። ነገር ግን ከላይ ለመግለፅ እንደሞከርኩት አምባገነናዊ ሥርዓት (be it autocratic or oligarchic) የጉልበት የበላይነትን በመጎናፀፍ መረገጋትን አስፍኖ የሚገዛ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ በርግጥም autocracy ለመመስረት ተመኮሮ ነበር:: ነገር ግን ይህ ባለመሳካቱ አሁን anocracy ተፈጥሯል።

በነገራችን ላይ ለህዝብ እና ሀገር anocracy ከአምባገነናዊ ስርዓትም የበለጠ ጎጂ ነው።በአምባገነናዊ ስርዓት ውስጥ ህዝብ ነጻነቱን ቢያጣ እንኳን ቢያንስ ደህንነቱ የተረጋገጠ ነው።በanocracy ውስጥ የሚፈጠረው anarchy ነጻነቱንም ደህንነቱንም ያሳጣዋል። የሀገርን ኢኮኖሚያዊ እና የጸጥታ አቅምም በከፍተኛ ሁኔታ ያዳክማል። በኢትዮጵያም እያስተዋልን ያለው ይሄንኑ ነው።
Via Eyasped Tesfaye

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when The Gudeta Mekonen posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to The Gudeta Mekonen:

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share