Ethio Review ኢትዮ ሪቪው

  • Home
  • Ethio Review ኢትዮ ሪቪው

Ethio Review ኢትዮ ሪቪው Welcome To Ethio Review . please leave us a comment on any that you enjoy!

13/04/2024

ዘመቻውን ተቀላቀሉ!ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ከእስር እንዲፈታ የሚጠይቅ ዘመቻ ጀመረዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከአራት ወራት በፊት የታሰረው ጋዜጠኛ Bel...
24/03/2024

ዘመቻውን ተቀላቀሉ!

ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ከእስር እንዲፈታ የሚጠይቅ ዘመቻ ጀመረ

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከአራት ወራት በፊት የታሰረው ጋዜጠኛ Belay Manaye ከእስር እንዲፈታ የሚጠይቅ ዘመቻ ጀመረ።

“የኢትዮ ኒውስ” ዩትዩብ ዜና ማሰራጫ መሥራቹ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር የዋለው ከአራት ወራት በፊት ኅዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም ነበር። ጋዜጠኛዉ በቁጥጥር ስር ከዋለ ወራቶች ቢቆጠሩም፤ እስከዛሬ ፍርድ ቤት አልቀረበም፤ የታሰረበት ምክንያት አልተገለፀም፤ ምርመራም አልተደረገበትም።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ የታሰረው፤ „በአማራ ክልል ያለውን ግጭት አስመልክቶ በሠራው ዘገባ ነው ተብሎ ቢታመንም የታሰረበት ምክንያት አልተገለጸለትም“ብሏል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በአማራ ክልል ለተፈጠረው ግጭት “ሌሎች ሰባት ጋዜጠኞችን በዘፈቀደ አስሮ ጥቂቶችንም ከእስር ፈትቷል” ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ይፋ ባደረገዉ መግለጫ አስታዉቋል።

“የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ያሰሯቸዉን ጋዜጠኛ በላይ ማናዬን እና ሌሎች ሁለት ጋዜጠኞችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ” አምነስቲ ዘመቻውን አስመልክቶ በድረ ገጹ ይፋ ባደረገዉ መልዕክት አሳስቧል።

የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር የተደነገገዉን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አስታከዉ “ፕሬሱን እና ሰላማዊ ተቃውሞዎችን ለማፈን ተጠቅመውበታል” ሲል አምነስቲ ከሷል።

አምነስቲ ሰዎች በድረ ገጹ የተጋራውን የደብዳቤ ቅጂ ወይም በራሳቸው የጻፉትን ድብዳቤ ተጠቅመው ዘመቻውን እንዲቀላቀሉ ጠይቋል።

ጭንቅና መከራው ሲበዛ ሀገሩን ጥዬ ለመሰደድ ተገድጃለሁ !ህዝብ ራሱን ከመንግስት የሚጠብቅበት፣ ሽሽትና ፍርሀቱም አላስጥል ብሎት በመንግስት ተገዳይና ተሳዳጅ ህዝብ ያለበት ሀገር..... ሀገረ...
24/03/2024

ጭንቅና መከራው ሲበዛ ሀገሩን ጥዬ ለመሰደድ ተገድጃለሁ !
ህዝብ ራሱን ከመንግስት የሚጠብቅበት፣ ሽሽትና ፍርሀቱም አላስጥል ብሎት በመንግስት ተገዳይና ተሳዳጅ ህዝብ ያለበት ሀገር..... ሀገረ- ኢትዮጵያ !
ሀገርንና ህዝብን አስቦ መስራት፣ ሙያና ፀጋን በተግባር ማዋል፣ ከሰከረ ፖለቲካ ውጪ በመርህ መስራት፣ ያለ ገዥው ፓርቲ ማለም፣ በግርድና ከሚያገለግሉት ተገዥ ካድሬዎች ሃሳብ መቃረን፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ከባድ ወንጀል ተደርጓል። ብዙ መከራና ስቃይም አምጥቷል።
በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የአመታት ቆይታዬ ስለ ተሳዳጁ የአማራ ህዝብ ጉዳይ ከሚገድዳቸው ወዳጆች ጋር ብዙ ለመታገል ሞክረናል። ከወለጋ እስከ አጣዬ ከማይካድራ እስከ ቤንሻንጉል ግልፅ ጦርነቶች እስከ ስውር ደባዎቹ ብዙ ለመስራት ሞክረናል።
ነገሩ ግን አልጋ በአልጋ አልነበረም። ብዙ ፈተና ብዙ ምክርና መከራ፣ ብዙ እንግልትና ወከባንም እያመጣ እሱን ማውራትም ሌላ መከራ እየደቀነ ውጠነው ኖረናል።
አሁን ግን ከአፈናና ወከባው መብዛት ባሻገር ሁኔታዎች እጅግ በመበለሻሸታቸው ሀገር ጥለን መሰደድ ምርጫ ሆነ።
በዝርዝር ጉዳዮችና በተሻለ ስራ ወደ ህዝባችን እንመለሳለን !
እንዳልካቸው አባቡ አየለ !

የአድዋ ባዶ እግር ሩጫ ተሳታፊዎች በአሁኑ ወቅት አዘጋጁ ጋዜጠኛ ብስራት መንግስቱን ጨምሮ በርካታ የሚዲያ ባለሙያዎች የተካተቱበት የሩጫው ተሳታፊዎች በፀጥታ አካላት ወደ ላዛሪስት ፖሊስ  ጣቢ...
02/03/2024

የአድዋ ባዶ እግር ሩጫ ተሳታፊዎች በአሁኑ ወቅት አዘጋጁ ጋዜጠኛ ብስራት መንግስቱን ጨምሮ በርካታ የሚዲያ ባለሙያዎች የተካተቱበት የሩጫው ተሳታፊዎች በፀጥታ አካላት ወደ ላዛሪስት ፖሊስ ጣቢያ ተወስደዋል!!! ፕሮግራሙ ሕጋዊ ፍቃድ እንደነበረውም የሚታወቅ ሲሆን አዘጋጁም በዚሁ ዝግጅት ተደጋጋሚ ፈተናዎችን ተጋፍጧል!

Am alive   The former ETV (EBC) Jornalistas
20/12/2023

Am alive

The former ETV (EBC) Jornalistas

አማራነት ወንጀል አይደለም   እኛ በግፍ የታሰርነው አማራዎች  ህፃናት አላረድንም ።ነፍሰጡር እናት ሆዷን አልሰነጠቅንም ።ህዝብ አልጨፈጨፍንም ።ሴት ተማሪዎችን አግተን አልሰወርንም ።ባንክም ...
31/10/2023

አማራነት ወንጀል አይደለም

እኛ በግፍ የታሰርነው አማራዎች ህፃናት አላረድንም ።ነፍሰጡር እናት ሆዷን አልሰነጠቅንም ።ህዝብ አልጨፈጨፍንም ።ሴት ተማሪዎችን አግተን አልሰወርንም ።ባንክም አልዘረፍንም ። ህዝብም አላፈናቀልንም ። ወንጀላችን ህፃናትን አትረዱ ፤ነፍሰጡሯን እናት አትሰንጥቁ ፤ የአማራን ህዝብ አትጨፍጭፉ፤ያገታችኋቸውን አማራ ሴቶች ተማሪዎችን መልሱ ፤ በዳቦ ስም ባንክ አትዝረፉ ፤የአማራ ህዝብ አታፈናቅሉ ብለን ለአማራ ህዝብ ስለ እውነት በመቆማችንና አማራ ሆነን መፈጠራችን ብቻ ነው ።

አርቲስት ዬርዳኖስ አለሜ ከቂሊንጦ እስር ቤት ዛሬ ያስተላለፈው መልክት !!

   !   በሰላማዊ የነፃነት ታጋዮች ላይ እየደረሰ ያለው  የፍትሕ እጦት፣ የሰብዓዊ መብት ገፈፋ እና ያለ ጥፋታቸው መታሰራቸው የመብት ረገጣ መሆኑን በመግለጽ በአስቸኳይ ከግፍ እስር እንዲለ...
31/10/2023


!
በሰላማዊ የነፃነት ታጋዮች ላይ እየደረሰ ያለው የፍትሕ እጦት፣ የሰብዓዊ መብት ገፈፋ እና ያለ ጥፋታቸው መታሰራቸው የመብት ረገጣ መሆኑን በመግለጽ በአስቸኳይ ከግፍ እስር እንዲለቀቁ " እኔም እጠይቃለሁ ፤ ለምን ?! " የበይነ መረብ ዘመቻው ዛሬ በይፋ ተጀምሯል ፣ይቀላቀሉ !

ለዘመቻው የተዘጋጀው ፕሮፋይል ይሄ ስለሆነ ፤ ፕሮፋይል ምስልዎን በመቀየር ፣ጽሁፎችን በመጻፍ፣ ምስሎችን በማጋራት ሃሳብዎን ያንፀባርቁ !!

" እኔም እጠይቃለሁ ፤ ለምን ?! "

ማሰር መሸነፍ ነው።
17/09/2023

ማሰር መሸነፍ ነው።

ጋዜጠኛ  Yehualashet Zerihun በፌደራል ፖሊሶች ተይዞ ተወሰደ        ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን ዛሬ ከቀኑ 7:40 ላይ ባልዳራስ ኮንዶሚኒየም ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በ7 የፌደራል...
12/09/2023

ጋዜጠኛ Yehualashet Zerihun በፌደራል ፖሊሶች ተይዞ ተወሰደ

ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን ዛሬ ከቀኑ 7:40 ላይ ባልዳራስ ኮንዶሚኒየም ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በ7 የፌደራል ፖሊስ አባላት ተይዞ ሜክሲኮ የቀድሞው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ወደሚገኘው ጊዜያዊ ማቆያ ቦታ ተወሰደ ። ባለቤቱ የታሰረበት ቦታ ሄዳ የጠየቀችው ሲሆን በምን ምክንያት እንደታሰረ እንዳላወቀና ለጥያቄም እንዳልቀረበ ገልጾላታል ።

Tewodros Teklearegay

የማቀርበውን የሙዚቃ ስራ ሰርዤአለሁ !    | እኔ ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ ጳጉሜ 6 በሸራተን አዲስ ለአዲስ ዓመት ዋዜማ የሙዚቃ ስራዬን ለማቅረብ ተፈራርሜ የተዘጋጀሁ ቢሆንም ይህን ስራ በመሰ...
05/09/2023

የማቀርበውን የሙዚቃ ስራ ሰርዤአለሁ !

| እኔ ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ ጳጉሜ 6 በሸራተን አዲስ ለአዲስ ዓመት ዋዜማ የሙዚቃ ስራዬን ለማቅረብ ተፈራርሜ የተዘጋጀሁ ቢሆንም ይህን ስራ በመሰረዜ የሚያስከፍለኝ ዋጋ ቢኖርም ከሁሉም በላይ በቃሏ የምመራላት ቤትክርስትያን ሀይማኖት አባቶቼን ትዕዛዝ በመቀበል የማቀርበውን የሙዚቃ ስራ ሰርዤአለሁ !

ለውድ አድናቂዎቼ እንዲሁም የፕሮግራሙ አዘጋጆች ይቅርታ እየጠየኩ በሌላ ዝግጅት እንደማስደስታችሁ እና እንደምንገናኝ ስገልፅላችሁ በታላቅ አክብሮት እና ምስጋና ነው!

ኩኩ ሰብስቤ

ይህቺ የOMN ዘገባ እኔን ጨምሮ አንዳንድ ሰዎች ያቀረቡትን ትችት ተከትሎ የተሰጠች የመልስ ምት ትመስላለች። ቀሽም መልስ። ይህቺው እንደመልስ ምት የተወረወረችው ዜና በራሷ ከOMN ኩሽና እን...
22/08/2023

ይህቺ የOMN ዘገባ እኔን ጨምሮ አንዳንድ ሰዎች ያቀረቡትን ትችት ተከትሎ የተሰጠች የመልስ ምት ትመስላለች። ቀሽም መልስ። ይህቺው እንደመልስ ምት የተወረወረችው ዜና በራሷ ከOMN ኩሽና እንዴት ክሽን ብላ እንደተሰራች ለማወቅ የምትከብድ አይደለችም። ፈጠራ አልቆባቸዋል። ማስመሰልም ጥበብን ይጠይቃል። የብሄር ስም ለጥፈህ የመሰረትከው ሚዲያ ማንነትህንና ስራህን በሚገባ ይናገራልና ወዲህ መቧጠጥ ወዲያ መላላጥ አያስፈልግም። ጋዜጠኝነት ትወና አይደለም። ገጸባህሪ ፈጥረህ የምትጫወተው ቲያትር አይደለም። ፕሮፖጋንዳም ከሆነ ትልቅ እውነት ይዞ ትንሽ ቅመም የሚጨምሩበት ክህሎት ነው። ዝም ብሎ በደረቁ ውሸት መጋት ጋዜጠኝነት ሳይሆን ጋጠወጥነት ነው።

ስለእዉነት ፆምን ፍቺ አሳቦ አይከብድም  ለአራጅ እና ሰዉ በላ መንግስት ለሚያደላ መከላከያ ህዝቡን ለመፍጀት ብትሉት ጥሩ ነበር
22/08/2023

ስለእዉነት ፆምን ፍቺ አሳቦ አይከብድም ለአራጅ እና ሰዉ በላ መንግስት ለሚያደላ መከላከያ ህዝቡን ለመፍጀት ብትሉት ጥሩ ነበር

ከዚህ በታች ያለው ፅሁፍ ሰሞኑን በፀጥታ ሃይሎች የታፈነው ታዋቂው የፊልም ዳይሬክተር እና የጉማ ሽልማት መስራች ዮናስ አባት ጋሽ ብርሃነ መዋ በፌስቡክ ገፁ ላይ የከተበው ነው::ከብርሃነ መዋ...
12/06/2023

ከዚህ በታች ያለው ፅሁፍ ሰሞኑን በፀጥታ ሃይሎች የታፈነው ታዋቂው የፊልም ዳይሬክተር እና የጉማ ሽልማት መስራች ዮናስ አባት ጋሽ ብርሃነ መዋ በፌስቡክ ገፁ ላይ የከተበው ነው::

ከብርሃነ መዋ
ሰኔ 4 ቀን 2015
ዮናስ ብርሃነ መዋ የኢትዮፊልም ዋና ስራ እስፈጻሚና የጉማ ፊልም ሽልማት መስራችና ዳይሬክተር

እስር-ፍች-እስር

በጉማ ፊልም ሽልማት 7ተኛ ዙር ዝግጅት ወቅት ለኔ ለአባቱ በተደጋጋሚ በፖለቲካ ስለመታሰሬ ጉዳይ
“ በሃይለ ስላሴ ጊዜ ታሰርክ፣ በደርግ ጊዜ ታስርከ፣ በኢሃዲግ ጊዜ 2 ጊዜ ታስርክ፣ ከንግዲህ ፖለቲካ ውስጥ ብትገባ እኔው አራሴ አስርሃለሁ” ብሎኝ ነበር። ዮናስ ብርሃነ መዋ

ምክሩን ሰምቸ ብቀዘቅዝም፡ ሲታሰር ትዝ ያለኝ ይህ ነበር። አንደሱ ፖለቲካ ውስጥ የሌለም፣ ሙያውን ለማሳደግ ሲጥርም ያላግባብ ሊታሰር አንድሚችል ሳየው፡፡

የጉማ ፊልም ሽልማት የፕሮግራሙ መስራችና ዳይሬክተር በሰኔ 2 ቀን በፕሮግራሙ ማጠናቅቂያ ላይ በፖሊስ ለእስር ተዳርጓል።

ይህን ጉዳይ በሚመለከት በተለያየ መንገድ ስጋታችሁን፡ አጋርነታችሁን፡ ብሶታችሁን፣ ንዴታችሁን፣ ለገለጻችሁ፣ እንዳንድ ማብራሪያዎችን ለጠየቃችሁ ወዳጆች፣ ባለሞያዎችና ቤተሰቦች። በራሴ አና በቤተሰቡ ስም ታላቅ ምስጋናየን አቀርባለሁ። የሆነውንና ትክክለኝውን ነገር እንድትረዱት አንደሚከተለው እቅርቤዋልሁ።

እርብ ሰኔ 2 ቀን
ከምሽቱ 5፡30 ሰአት የጉማ ፕሮግራም ተጠናቀቀ
ሌሊቱ 6፡00 ሰአት ዮናስና ባለቤቱ ሳምራዊት(ሊሊ) ወደ ቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ተወሰዱ
ከለሊቱ 6፡00 ሰአት ሳምራዊት(ሊሊ)ስትለቀቅ ዮናስ ታሰረ
ቅዳሜ ሰኔ 3 ቀን
ከጥዋቱ 3፡00 ሰአት ዮናስ ፍርድ ቤት ተወሰደ
ከጥዋቱ 4፡00 ሰአት ዮናስ ዳኛ ፊት ሳይቀርብ ወደ እስር ቤት ተመለሰ
ከጥዋቱ 4፡30 ሰአት ዮናስ ወደ ፍርድ ቤት አንደገና ተመለሰ
ከጥዋቱ 5፡30 ሰአት ዮናስ በ 5ሽህ ብር ዋስትና እንዲፍታ ተወሰነ
ከቀኑ 7፡15 ሰአት ዋስትና ተከፈለ የፍች ፎርማሊቲ ተሟላ
ከቀኑ 7፡20 ፍርድ ቤቱ ከእስር እንዲፈታ የሰጠውን የመፍቻ ጽሁፍ ትእዛዝ ለፖሊስ መመሪያው ደርሶ እንደሚለቀቅ ተነገረን
ከቀኑ 7፡20 እስክ 8፡15 የፍርድ ቤቱ ትእዛዝ ለፖሊስ ገቢ ሆኖ እንደሚለቀቅ እና የሃላፊዎች መቅረብ እንድንጠባበቅ ተነግሮን በተስፋ ስንጠባበቅ ቆየን
ከቀኑ 8፡15 ወደቤተሰብ ሊቀላቀል ሲሄድ በፖሊስ መምሪያው ሚኒ ባስ መኪና እንዲገባ ተገዶ ወዴት እንደሚሄድ ሳይነገረን ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት በተለምዶ 3ኛ ተብሎ ወደ የሚጠራው ቦታ ተወሰደ (አዲዮስ የፍርድ ቤት ትዛዝ)
ከቀኑ 9፡00 ሰአት ዮናስን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ተረክቦት ታሰረ
እቃ ገባለት ሰኞ ጠዋት ፍርድ ቤት እንደሚቀርብ ተነገርን።

እኔ ብርሃነ መዋ፡ የዮናስ አባት ሃሙስ ስኔ አንድ ቀን ከአሜሪካ አዲስ አበባ ገባሁ፤ በማግሰቱ አርብ የልጀና የስራ ባልደረቦቹ ዝግጅት የሆነውን ጉማ ለመታደም። እንደ አባት ለአግሩ የሙያ እድገት ያበረከተውን ላደንቅለት፣ አገሩ ስታመሰግነው ለማዳመጥ፣ ያጋጠመኝ ግን ሲመሰገን ስይሆን ሲታስር ማየት ሆነ።

ጥፋት ያጠፋ አይቀጣ፣ ወንጅል የሰራ አይጠየቅ የሚል ግብዝነት የለኝም። እሱ ባላረገውና ሌሎች መብታችን ነው ብለው ባደረጉት ድርጊት ምክንያት ተጠርጣሪ ተደርጎ ለስር ሲዳረግ ማየት ግን ቅስም ይሰብራል ተስፋን ያጨልማል።

በ1996 በህገመንግስት ውይይት በሰነዘርኩት ሃሳብ መነሻነት ጥርስ ተነክሶብኝ የጋዜጣ ድርጅቴ እንደምክንያት ተወስዶ አዘጋጁና እኔ በባለቤትነት አንድ ወር ታስረን በዋስ ተፈታን፣ ከጣቢያው ስንወጣ ወዲያው ተገደን በሌላ መኪና ወደ ሌላ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደን ታሰርን። የቅዳሜው ክስተት በኔ የደረሰን አሮጌ አሰራር አስታወሰኝ።ባሁኑ ጊዜ ይህ መሆኑ እንዴት? የሚል ጥያቄ ጫረብኝ እንጅ አልገረመኝም።

ሁሌም በኢትዮጵያ ተስፋ አልቆርጥምና በልጀ የዮናስ ብርሃነ መዋ ጉዳይ ላይ የተጀመረው ምርምራ አግባብ አለመሆኑ ተረጋግጦ ይለቀቃል የዋስትና መብቱም ይከበርለታል ብየ ተስፋ አድርጋለሁ።

የመንግስት ባለስልጣናቱ ከህዝብ ጋር በዚህ መልኩ በቲውተር ገፃቸዉ ዘቅጠዉ ይስተዋላል ።
10/06/2023

የመንግስት ባለስልጣናቱ ከህዝብ ጋር በዚህ መልኩ በቲውተር ገፃቸዉ ዘቅጠዉ ይስተዋላል ።

ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው እና ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ለዘሐበሻ የደረሰው መረጃ ያስረዳል።
14/04/2023

ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው እና ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ለዘሐበሻ የደረሰው መረጃ ያስረዳል።

አቤል ገብረኪዳን (Ab Bella ) በ3000 ብር ዋስ እንዲፈታ ፍ/ቤት ፈቅዶ ነበር።ፖሊስ እንደተለመደው እና እንደሚጠበቀው ይግባኝ ጠይቋል!5 ቀናት የት እንዳቆየ መረጃ አምጣ ቢባልም ዛሬም...
09/03/2023

አቤል ገብረኪዳን (Ab Bella ) በ3000 ብር ዋስ እንዲፈታ ፍ/ቤት ፈቅዶ ነበር።

ፖሊስ እንደተለመደው እና እንደሚጠበቀው ይግባኝ ጠይቋል!

5 ቀናት የት እንዳቆየ መረጃ አምጣ ቢባልም ዛሬም መረጃውን ይዞ ያልቀረበው ፖሊስ ለይግባኝ ግን ፈጥኗል። ዋስትና አስፈቅጄ ከችሎት ወጥቼ ቢሮዬ ሳልደርስ ተመለስ ይግባኝ ቀርቧል ተብያለሁ።
ከሰሞኑ ልምድ አንጻር ዋስትና ሲፈቀድም እንኳ ስራዬ ገና ሀ ብሎ እየተጀመረ እንደሆነ ይገባኛል!! እንግዲ ፖሊስ ደንበኞቻችንን ይዞ በሄደበት ሁሉ እየተከተሉ መሟገት እንጂ ምን ማድረግ ይቻላል?!

ሁላችሁም ሼር አድርጉ!!!!ጋዜጠኛ አቤል ገብረ ኪዳን  በፌስቡክ ስሙ    በፖሊሶች ተወስዷል። ለምን እንደተወሰደ ለምን እንደሆነ ምንም መረጃ የለም።ይሄ ወንድማችን ቤተ ክርስቲያን ችግር ላይ...
01/03/2023

ሁላችሁም ሼር አድርጉ!!!!

ጋዜጠኛ አቤል ገብረ ኪዳን በፌስቡክ ስሙ በፖሊሶች ተወስዷል። ለምን እንደተወሰደ ለምን እንደሆነ ምንም መረጃ የለም።

ይሄ ወንድማችን ቤተ ክርስቲያን ችግር ላይ በነበረችበት ጊዜ አጀንዳውን ቤተ ክርስቲያን አድርጎ ስለ ቤተ ክርስቲያን ሲሟገት ሲጽፍ ሲያነቃን በርካታ ሃሳቦችን ሲያካፍለን የነበረ ሲሆን፣ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የድል በዓል ስለሆነው ዓድዋም የተለያዩ ሳቅ አዘል እና ኢትዮጵያዊነትን አዘል ጽሑፎችን ሲያጋራን ነበረ። እናም ለወንድማችን ድምጽ እንድንሆን አሁንም አጀንዳችን ቤተ ክርስቲያን እንድትሆን አደራ ልላችሁ እወዳለሁ። ወንድማችንን ፍቱልን!!!

የአማራዉን አጀንዳ ለማስቀየር በአማራ ክልል ''ኢትዮጵያ ታምርት'' የንቅናቄ መድረክ እየተካሔደ ነው ሲል የፊንፊኔዉ ሚዲያ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በገፁ አስፍሯል ።
25/02/2023

የአማራዉን አጀንዳ ለማስቀየር በአማራ ክልል ''ኢትዮጵያ ታምርት'' የንቅናቄ መድረክ እየተካሔደ ነው ሲል የፊንፊኔዉ ሚዲያ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በገፁ አስፍሯል ።

ከታሪክ የተጣላ መንግስት ሲመራህ ዛሬ በነፃነት እንዲቀመጥ ያረጉትን ጀግና እንኳን በሙሉ አፉ መጥራትና በፓስተሩ ማረግ ያሳፍረዋል ።  ምኒልክ ዛሬም ንጉስ ነዉ
24/02/2023

ከታሪክ የተጣላ መንግስት ሲመራህ ዛሬ በነፃነት እንዲቀመጥ ያረጉትን ጀግና እንኳን በሙሉ አፉ መጥራትና በፓስተሩ ማረግ ያሳፍረዋል ።

ምኒልክ ዛሬም ንጉስ ነዉ

 #ሚኒሊክ ዛሬም ንጉስ ነዉ
24/02/2023

#ሚኒሊክ ዛሬም ንጉስ ነዉ

በአድዋ ላይ ውይይት ለታሪክ የሚቀመጥ ፎቶ !! አምባሳደር ዲና ምን አስገርሟቸው ይሆን ?
24/02/2023

በአድዋ ላይ ውይይት ለታሪክ የሚቀመጥ ፎቶ !!
አምባሳደር ዲና ምን አስገርሟቸው ይሆን ?

በሀይማኖትና በብሄር ሽፋን የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኞችን በመታገል ወጣቱ አንድነቱንና አብሮነቱን እንዲያጠናክር ያስፈልጋል ይላል ማጣፊያዉ ያጠረዉ መንግስት ወጣቶችን ሰብስቦ ፕሮፓጋንዳዉንና ስልጣኑን...
24/02/2023

በሀይማኖትና በብሄር ሽፋን የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኞችን በመታገል ወጣቱ አንድነቱንና አብሮነቱን እንዲያጠናክር ያስፈልጋል ይላል ማጣፊያዉ ያጠረዉ መንግስት ወጣቶችን ሰብስቦ ፕሮፓጋንዳዉንና ስልጣኑን እንዳያጣ ለመለማመጥ ዛሬ በማዘጋጃ አዳራሽ በጠራዉ ስብሰባ ።

What is goingnon in Addis Ababaከጦር ሀይሎች- 22- መገናኛ- ሲኤምሲ መንገድ ዝግ ነው!!
24/02/2023

What is goingnon in Addis Ababa

ከጦር ሀይሎች- 22- መገናኛ- ሲኤምሲ መንገድ ዝግ ነው!!

07/01/2023

ተፈቷል

የሃቅ አሳዳሪዋ። ለህሊናዋና ለሰውነት ቋሚ ተሰላፊ። የፍትህ አምበል! ብርቱ እንስት ጋዜጠኛ መምህርና የፓለቲካ ተንታኝ!  የእኛ ሰው መስኪላታ !!!       (ሸጋ ነገር ለሰው)
29/12/2022

የሃቅ አሳዳሪዋ። ለህሊናዋና ለሰውነት ቋሚ ተሰላፊ። የፍትህ አምበል! ብርቱ እንስት ጋዜጠኛ መምህርና የፓለቲካ ተንታኝ! የእኛ ሰው መስኪላታ !!!

(ሸጋ ነገር ለሰው)

ከ 80 በላይ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችን በግፍ ያባረረው Addis Media Network-AMN የስራ ቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል።
22/12/2022

ከ 80 በላይ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችን በግፍ ያባረረው Addis Media Network-AMN የስራ ቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል።

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Review ኢትዮ ሪቪው posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Review ኢትዮ ሪቪው:

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share