Wolaita Press Agency

Wolaita Press Agency Naqqasha Pullituwa
(1)

የሁምቦ ወረዳ አስተዳደር ለ50 አቅም ደካሞችና 480 በላይ ወላጅ አጥ ተማሪዎች የመማርያ ቁሳቁስ፣ አልባሳትና የተለያዩ ድጋፍ አድርጓል ወላይታ ሶዶ፣ መስከረም 09/2016 ዓ.ም በወላይታ ዞ...
20/09/2023

የሁምቦ ወረዳ አስተዳደር ለ50 አቅም ደካሞችና 480 በላይ ወላጅ አጥ ተማሪዎች የመማርያ ቁሳቁስ፣ አልባሳትና የተለያዩ ድጋፍ አድርጓል

ወላይታ ሶዶ፣ መስከረም 09/2016 ዓ.ም በወላይታ ዞን ሁምቦ ወረዳ ከሁሉም ቀበሊያትና ታዳጊ ማዘጋጃዎች ለተወጣጡ ለ50 አቅም ደካሞችና ወላጅ አጥ 480 በላይ ተማሪዎች የመማርያ ቁሳቁስ፣ አልባሳትና የተለያዩ ድጋፍ ተደርጓል።

የሁምቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፀጋዬ ቀልታ በዛሬው ዕለት የሚደረገው ድጋፍ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አካል መሆኑን ገልጸው፣ በወረዳው በክረምት ወራት በረካታ ማህበረሰብ ክፍል ተጠቃሚ ያደረገ ሥራ በሁሉም ትኩረት መስኮች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በጎ ሥራ ከፍተኛ የአእምሮ እርካታ የሚሰጥ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በዛሬው ዕለትም አንድም ተማሪ በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ እንዳይቀሩ ያለመ ተግባር ተከናውኗል ብለዋል።

በጎ ፍቃድ አገልግሎት በክረምት ወራት ብቻ ሳይሆን በበጋም እንዲሁም ባህል ሆኖ እንዲቀጥል እየተሰራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

የወላይታ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ም/ኃላፊና ወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ደረጀ በወረዳው በጎ ፍቃድ አገልግሎት የተሰሩ ሥራዎች በጣም ተስፋ ሰጪና ለሌሎች አካባቢዎች ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።

ወላጅ አጥና የአቅም ደካማ ቤተሰብ ልጆች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ከትምህርት ገበታ እንዳይቀሩ ለማድረግ የተሰራው ሥራ እጅግ በጣም ጥሩ በመሆኑ ወረዳውን አመስግነው፣ ይህ ተግባር የአእምሮ እርካታ የሚሰጥና ከፈጣር ዘንድም ዋጋ ያለው ተግባር ነው ብለዋል።

የሁምቦ ወረዳ ዋና የመንግሥት ተጠሪና የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አመኑ ጎአ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚመራ ዐቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ ተዋቅሮ ተግባሩን መምራቱን ገልጸዋል።

አቶ አመኑ አክለውም በሁሉም ቀበሊያት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በትኩረት መሰራቱን ጠቁመው፣ በዝህም በረካታ ወጣቶች መሳተፋቸውን ጠቁመዋል።

በዛሬው ዕለትም የመማርያ ቁሳቁስ እጥረት ላለባቸው ተማሪዎች የተለያዩ የመማርያ ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉን ጠቁመው በቀጣይም በጎ ፍቃድ አገልግልት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።

"ጊፋታ" የወላይታ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነ የህዝብ በዓል ነውጊፋታ አሮጌው ዓመት የሚሸኝበትና አዲስ ዓመት የሚቀበሉት የዘመን መለወጫ በዓል ትልቅ ቦታ ተሰጥቶ ከሚከበሩት በዓላት አንዱ ...
19/09/2023

"ጊፋታ" የወላይታ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነ የህዝብ በዓል ነው

ጊፋታ አሮጌው ዓመት የሚሸኝበትና አዲስ ዓመት የሚቀበሉት የዘመን መለወጫ በዓል ትልቅ ቦታ ተሰጥቶ ከሚከበሩት በዓላት አንዱ ሲሆን በየአመቱ ጊፋታ ይከበራል።

በዓሉ ለማህበረሰቡ ያለው ፋይዳ የተለየ ሲሆን በተለይ የተኮራረፉት የተጣሉትና የተጋጩት ብሎም ደመኞች ጥላቸውን ይዘው ወደ አዲሱ አመት እንዳይሸጋግሩ ጥላቻና ኩርፊያ በፍቅር ተተክቶ ሰላምና ፍቅር እንዲሰፍን ሚናው ወደር የለውም።

በዓሉ ሁለት አላማዎችን ያነገበ ሲሆን በዋናነት አሮጌውን ዓመት በሰላም ላሸጋገረው ቤተሰብን ጎረቤትን አከባቢውንና አገርን በሙሉ ጠብቆ ላቆየው አምላክ እግዚአብሔር ምስጋና ውዳሴ ክብርና አድናቆትን የሚያቀርቡበት በዓል ነው።

በሌላ በኩል አዲሱ አመት የሰላም የደስታ የፍቅር የስኬት የድል እና የመተሳሰብ አመት እንዲሆን ለፈጣሪ እግዚአብሔር ፀሎት የሚያደርሱበት እና የሚማጽኑበት በዓልም ጭምር ነው።

ጊፋታ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ አእዋፋትና የቤት እንስሳትም ጭምር በጋራ የሚያከብሩት በዓል ነው፡፡ ምክንያቱም በጊፋታ ሰዎች በሬ አርደው ሥጋ እየበሉና እየጠጡ በዓሉን ሲያከብሩ የሰማይ ወፎችም ቅንጥብጣቢው ስለሚደርሳቸው ነው፡፡

በበዓሉ ወቅት ለቤት እንስሳት ከወትሮ በተለየ ሁኔታ የበዓል ወቅት እስከሚጠናቀቅ ድረስ የሚመገቡት በአሞሌ (aduwaa) የተለወሰ ልዩ ሳርና የእህል ዓይነት ይዘጋጃል፡፡ በመሆኑም ጊፋታ ለፍጥረት በሙሉ የደስታና የአዲስ ህይወት ጅማሮ እንደሆነም ይታመናል፡፡

የጊፋታን በዓል መቃረብ የሚያበስሩ የሰዎች የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ደግሞ በየቤቱ እና በየገበያ ቦታዎች የሚሰሙ የወንዴ እና ሴቴ (Adiyaanne Indde karaabiyaa) ድምጾች፣ በየአካባቢው የሚሰሙ ባህላዊ ዘፈኖች፣ ሰዎች እርስ በርስ ″እንኳን ከጨለማ ወደ ብርሃን በሰላም አሻገረህ (Hashshu Xumaappe Poo’uwaa Saro Pinnasa) እየተባባሉ መመራረቅ ከብዙ በጥቂቱ የሚታዩ ናቸዉ፡፡

የወላይታ ህዝብ በአከባቢው መኖር ከጀመረ ወዲህ ሲወርድ ሲዋረድ ዛሬን የደረሰው ጊፋታ በዓል ዘንድሮም ካለፋት ጊዜያት በተለየ መልኩ በድምቀት ሊከበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቋል።

ዮ ዮ ጊፋታ!! Yoo yoo gifaataa !!

የሁሉም ዜጎች አሻራ ያረፈበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አራተኛው የውሃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ፦ አቶ ሳሙኤል ፎላየወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ አራ...
10/09/2023

የሁሉም ዜጎች አሻራ ያረፈበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አራተኛው የውሃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ፦ አቶ ሳሙኤል ፎላ

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ አራተኛው ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን አስመልክተው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ኢትዮጵያዊያን ከድህነት ለመውጣት የሚያደርጉትን እልህ አስጨራሽ ትግል እውን ማድረጊያና የሀገርቱን ዜጎች ማንኛውም ሁኔታና ልዩነት ሳይገድባቸው በአስተሳሰብና በተግባ አንድ ያደረገ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑን በውል እንገነዘባለን።

በመሆኑም እንደ ገዢ ፓርቲም ሆነ እንደ መንግስት በዋናነት ትኩረት ከተሰጣቸው ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ውስጥ ታላቁ የህዳሴ ግድብ አንዱ ነው፡፡ ግድቡ ለኢትዮጵያዊያን ያለው ትርጉም ከፍ ያለና የላቀ ነው፡፡

ኢትዮጵያዊያን ህዳሴ ግድብ ከድህነት መውጫ መንገዶች አንዱና ዋነኛው መሆኑን በመገንዘብ በአስተሳሰብ፣ በዕውቀትና በገንዘብ ያልተቆጠበ ተሳትፏቸውን እያደረጉ ይገኛሉ።

የአገሪቱን ኢኮኖሚ ወደ አንዱስትሪ ስለሚያሸጋግር ዜጎቿ ከዕለት ጉርሳቸው ቀንሰው ይህንን የሀገር አለኝታ የሆነውን ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ ከጊዜ ጋር እልህ ውስጥ በመግባት ሥራው ቀንና ሌሊት ሥራው እየተከናወነ ይገኛል። ይህ በኢትዮጵያዊያን ልብ ውስጥ ያለ የሁሉም ዜጎች አሻራ ያረፈበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሆኑ ማሳያ ነው፡፡

ግድቡ ለዜጎች ብሔራዊ ኩራት ከመሆኑም ባሻገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያና ፖለቲካዊ ፋይዳው ከፍተኛ ነው።

ህዳሴ ግድባችን የመተባበርና የአንድነት ዕሴት ያጎለበተ ፤ እርስ በእርስ ያለንን ግንኙነት ያጠናከረ እንዲሁም አይበገሬነትና የይቻላል መንፈስን ቀተግባር ያሳየንበትን ጭምር ነው፡፡

የግድቡ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ከተቀመጠበት እለት ጀምሮ የኢትዮጵያ ህዝብ ያለምንም የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ልዩነት ሳያግደው ሁሉም ዜጋ ከልጅ እስከ አዋቂ ያሳየው ድጋፍ፣ የሃገራችን ብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ያሳዩት ተነሳሽነት እና በግድቡ ዙሪያ የፈጠሩት አንድነት ከመቼውም ጊዜ በላይ እንድንቀራረብ እና በጋራ እንድንረባረቡ ማድረጉ ከማድረጉም ቀላይ ብሄራዊ መግባባትን በመፍጠር በየትኛውም ዘርፍ ለተያያዝናቸው አጀንዳዎች ትልቅ እና የገዘፈ ብሄራዊ አቅም ፈጥሮልናል፡፡

ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያለምንም የውጭ ድጋፍም ሆነ ብድር በራሳችን አቅም ተጠናክረን ግድቡን እዚህ ደረጃ ላይ ማድረሳችን ለአፍሪካም ሆነ ዓለም ላይ ላሉ ሃገራት በራሳቸው አቅም ህዝባቸውን አስተባብረው ማደግ እንደሚችሉ ቀተግባር ያሳየ የሰንደቅ ዓላማ ፕሮጀክታችን ነው፡፡ በመጨረሻም የታላቁ ህዳሴ ግድብ 4ኛ ዙር ውሃ ሙሌት በሠላም በመጠናቀቁ በድጋሚም እንኳን ደስ አላችሁ እያልኩኝ በቀሪ ምዕራፎችም ፕሮጀክቱ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን በጽናት የዘለቀው ሁለንተናዊ ድጋፋችሁና አብሮነታችሁ አይለየን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

በወላይታ ዞን በባይራ ኮይሻ ወረዳ የሚገኝ ሰው ሰራሽ ታሪካዊ  ይህ ሰው ሰራሽ   ከወላይታ ሶዶ ከተማ በ30 ኪ ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ታሪካዊ ስፍራን ነው።ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የተፈጥሮ...
16/08/2023

በወላይታ ዞን በባይራ ኮይሻ ወረዳ የሚገኝ ሰው ሰራሽ ታሪካዊ

ይህ ሰው ሰራሽ ከወላይታ ሶዶ ከተማ በ30 ኪ ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ታሪካዊ ስፍራን ነው።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስዕብ ቦታዎች እንዳሉት ይታወቃል። በዋናነት ሰው ሰራሽ የመስዕብ ቦታዎች በተለያየ ጊዜ ለተለያየ አላማ ተብሎ የተሰሩ ስሆኑ በወቅቱ ለታለመለት አላማ ከዋሉ በኃላ ለቀጣይ ትውልድ የታሪክ ቦታና ቅርስ ከመሆኑም አልፎ በወቅቱ የነበሩ የአባቶቻችን ጥበብና ለአላማ ያላቸውን ፅናት የሚያሳይ ሆኖ ለዘመናት ይቆያል።

ከዚህም አልፎ ለአካባቢው የገቢ ምንጭ ሆኖ ሲያገለግሉም እናያለን። ከእነዚህ ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስዕብ ቦታዎች አንዱ የሆነውና #በባይራ #ኮይሻ #ወረዳ በሴሬ ባላካ ቀበሌ ፑላሳ አምባ ላይ የሚገኘውን አንድ ታሪካዊ #ዋሻ እናስተዋውቃለን።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ በሴሬ ባላካ ቀበሌ በፑላሳ አምባ መንደር ከባህር ወለል #በ2,302 ሜትር ከፍታ ስፍራ ላይ የሚገኘው ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስዕብ ቦታ የሆነው #የአሩጂያ #ዋሻ ታሪካዊ ቦታ ነው።

ይህ ዋሻ ከክርስቶስ ልደት በፊት የተቆፈረ እንደሆነና ዋሻው የተሰራበት የአሰራር ጥበብና በውስጡ ያሉ ክፍሎች እጅግ በጣም የሚደንቅ ናቸው።

በወቅቱ የነበሩ ሰዎች ልጆቻቸውንና ከብቶቻቸውን ከጠላት ለመጠበቅ፣ በጦርነት ድልን ለማግኘትና ለአደን ምቹ ቦታዎችን ለማግኘት በሚል ዓላማ የተሰራ እንደሆነ የታሪክ አዋቅዎች ይናገራሉ።

በአሩጂያ ንጉሰ ነገስታት ዘመን የነበሩ አባቶች ድንጋይን ከድንጋይ ጋር በማጋጨት እሳት አውጥቶ የተለያዩ የዱር እንስሳትን ቀንድ በመጠቀም የቆፈሩት ይህ አሩጂያ ዋሻ እጅግ ማራኪያ በርካታ ታሪኮችን ጠቅልሎ የያዘ እንደሆነ ይነገራል።

ይህ የአሩጂያ ዋሻ ሶስት መግቢያ በር ያሉት ስሆን በመሃል ያለው ትንሹ እንደ መስኮት እንደሚያገለግልና አንዳንደ ጠላትን አስቀድሞ ለመከላከል ይረዳ ዘንድ ውሻ እንደ ሚታሰር አባቶች ይናገራሉ።

ወደ ውስጥ ስንገባ ከ300 ሰው በላይ መያዝ የሚችል ሰፊ ሳሎን ያለው ስሆን በሁሉም አቅጣጫ የተለያዩ ክፍሎች አሉት። በጣም የሚገርመው በዚህ ዋሻ ውስጥ #ከ30-40 ደቂቃ መንገድ መጓዝ የሚያስችል ሁለት መግቢያዎች ያሉት ስሆን፣

የመጀሪያው ወደ አፋ ወረዳ ወደ ሚባልበት ስፍራ የሚወስድ እንደሆነና ሌላኛው ደግሞ አሁንም ወደ አፋ ወረዳ እንደሚያስወጣ የታሪክ አዋቅ አባቶች ይናገራሉ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ የሚገኘውን የአሩጂያ ሰው ሰራሽ ዋሻ እስከ ቦታው ድረስ በመሄድ እንድትጎበኙና በታሪካዊ አሰራር እንዲትደነቁ ተጋብዛቿል በማለት የባይራ ኮይሻ ወረዳ ማህበራዊ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ዘግቧል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ ህብረተሰብ አቀፍ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ በሁሉም ቀበሌ በተደረገው የፅዳት ዘመቻ የአካባቢው ነዋሪዎች፣  የልማታዊ ሴፊቲኔት ባለሙያዎች እና የመንግስት ስራ ኃላፊዎች ተሳትፈ...
11/08/2023

በወላይታ ሶዶ ከተማ ህብረተሰብ አቀፍ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ

በሁሉም ቀበሌ በተደረገው የፅዳት ዘመቻ የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የልማታዊ ሴፊቲኔት ባለሙያዎች እና የመንግስት ስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

ፅዳት እና ውበት የስልጣኔ መገለጫ መሆናቸውን የሰራ ተሳታፊዎች አስረድተዋል።

በዘመቻ መልክ በአንድነት ወጥቶ ማፅዳት የባለቤትነት ስሜትን እንደሰጣቸው በመግለፅ ለከተማው ውበት ፣ ሰላም እና ልማት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ አስታውቀዋል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ የእለቱ የአየር ሁኔታ ቅዝቃዜ ፣ ካፋያ እና ብርዱ ሳይበግራቸው የፅዳት ዘመቻው እስከአሁን እያካሄዱ ይገኛሉ።

ለስራው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን በማቅረብ እና ከተፈቀደላቸው ቦታ ውጪ ግንባታ ያደረጉ፣ የግንባታ እና የንግድ ቁሳቁሶችን ያከማቹ አካላትን የማረም ስራ በህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ እየተሰራ ነው።

የወላይታ ሶዶ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት።

የህዝቦች አብሮነትና አንድነት ይበልጥ እንዲጠናከር ከከፋፋይ አጀንዳ ተላቀን አንዳች ለሌላችን ድርና ማግ፤ ዋልታና ማገር መሆን ይገባናል።ጨለማን የሚገፈው ብርሃን ነው፡፡ ድካምን የሚያቀለው እ...
07/08/2023

የህዝቦች አብሮነትና አንድነት ይበልጥ እንዲጠናከር ከከፋፋይ አጀንዳ ተላቀን አንዳች ለሌላችን ድርና ማግ፤ ዋልታና ማገር መሆን ይገባናል።

ጨለማን የሚገፈው ብርሃን ነው፡፡ ድካምን የሚያቀለው እረፍት ነው፡፡ ጥላቻን የሚያስወግደው ፍቅር ነው፡፡ ቂምንና ቁርሾን ማስወገድ የሚቻለው ደግሞ በይቅር ባይነት ነው፡፡

ሰሞኑ በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ ጥላቻን ያነገቡ መረጃዎች ለዘመናት የቆየውን የህዝቦች አብሮነትንና እሴቶች ለመሸርሸር ታልሞና ታቅዶ እየተሰራጨ ያለ ቢሆንም ህዝብን ከህዝብ ጋር ለማጋጨት መሞከር ወንጀለኛ እንጂ ጀግና አያስብልም፡፡

ታዋቂው የጥቁሮች ሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በአንድ ወቅት እንዲህ ሲል መናገሩ ይታወቃል፤ "Darkness cannot drive out darkness; only light can do that. Hate cannot drive out hate; only love can do that". “ጨለማን በጨለማ ሳይሆን በብርሀን፤ ጥላቻንም በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር” ልንቀይር እንደምንችል ያሳያል፡፡

ታዲያ እውነታው ይህ ከሆነ እኛ እየሆንን ያለነው የትኛውን ነው? ጥላቻን በጥላቻ ወይስ ጥላቻን በፍቅር? ማንም ሊረዳው የሚገባው እውነታ ግን ጥላቻ የበለጠ ሰውን ከሰው እያራራቀ ወዳልተፈለገ መንገድ ይመራል እንጂ ሰላምና አንድነትን ከቶውንም ቢሆን አምጥቶ አያውቅም፡፡

ስለዚህ በሰዎች ዘንድ የቱንም ያህል ክብራችንን የሚነካ ማንነታችንን የሚያጠለሽ ነገር እንኳ ቢፈጠር ክፉን በክፉ መመለስ ሳይሆን መጥፎውን በደግነት ቀይረን እኛነታችንን የበለጠ በመልካምነት ልናሳይ ይገባናል፡፡ የጽንፈኛ ኃይሎች መጠቀሚያ እንዳንሆን ራሳችንን እንጠብቅ፡፡

አንዳንድ ጽንፈኞች በማህበራዊ ሚዲያ በህዝቦች መካከል ያለው የእርስ በእርስ ትስስርን ለማጠላሸት፣ ወንድማማችነትና እህተማማችነት ለመከፋፈል የሚያሰራጩትን በጋራ መታገልና መቃወም ያስፈልጋል፡፡

ጥላቻን በጥላቻ፤ ስድብን በስድብ ሳይሆን በፍቅርና በመተሳሰብ ማሸነፍ ይገባል፡፡ የህዝቦች አብርነትና አንድነት ከጥንት ጀምሮ አባቶቻችን እንደሰርገኛ ጤፍ ህብር ፈጥረው ያመጡት በጥቂት ሴረኞችና የፌስቡክ አርበኞች የሚሻክር አይደለም፡፡

ብልጽግና ፓርቲ ወንድማማችነትን መተክሉ አድርጎ ሲነሳ የሁሉም ችግሮች ማሰሪያ ውል እንደሆነ ስለሚያምን ነው፡፡ ማናቸውም ለፍትህ እና ለነፃነት የሚዳርጉ ትግሎች ፍሬያማ የሚሆኑትም በወንድማማችነት ዕሴት ውስጥ ብቻ ነው፡፡

የወንድማማችነት ዕሴት ባለበት ሁሉ አንዱ ሌላውን መረዳት አለ፤ ሆኖም ይህ እሴት በተሸረሸረ ቁጥር ደግሞ የሌላውን ሕመምና ፍላጐት መረዳት ከባድ ያደርገዋል፡፡

ሠላም እንዳያያዛችን ሁኔታ የሚወሰን እንጂ በየትኛውም ዓለም ስለተፈለገ ብቻ የሚገኝ ማህበራዊ ሀብት አይደለም፡፡ የመጠፋፋትና የመከፋፈል ስንክ-ሳሮች በብልጽግና ህክምና ይፈወሳሉ፡፡ ለዚህ ደግሞ እያንዳንችን የራሳችንን ድርሻ መወጣት ይኖርብናል፡፡

አዲሱ "የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል" ሠላሙ የሰፈነበት፣ ህብረቱ እንደብረት የሚጠነክርበት፣ ፍቅር የሚጎለብትበት፣ ፍትህ የሚሰፍንበት፣ ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚረጋገጥበት፣ አብሮነትና ወንድማማችነት የሚጸናበት፣ መተሳሰብና አብሮነት የሚታይበት፣ አግላይነት እና ጽንፈኝነት ከሥር መሠረቱ የሚነቀልበትና የሚጠፋበት፣ እውነት የሚነግስበት እና ኢትዮጵያዊነት የሚያጸናበት እንዲሆን ሁሉም የበኩሉን አስተዋፆኦ ማበርከት ያስፈልጋል እንላለን፡፡

ውቢቷ የወላይታ ሶዶ ከተማ አሁናዊ ገጽታ በፎቶ፤
30/07/2023

ውቢቷ የወላይታ ሶዶ ከተማ አሁናዊ ገጽታ በፎቶ፤

Welcome to Wolaita s**o እንኳን ወላይታ ሶዶ ደህና መጡወላይታ ሶዶ ባሁኑ ጊዜ በፈጣን እድገት ላይ የሚትገኝ ምርጥ ከሀገራችን ከተሞች አንዱዋ ነች።ከተማዋ ለኑሮ እጅግ ተስማሚ ና...
23/07/2023

Welcome to Wolaita s**o እንኳን ወላይታ ሶዶ ደህና መጡ

ወላይታ ሶዶ ባሁኑ ጊዜ በፈጣን እድገት ላይ የሚትገኝ ምርጥ ከሀገራችን ከተሞች አንዱዋ ነች።

ከተማዋ ለኑሮ እጅግ ተስማሚ ናት። አየሯ ወይና ደጋ ሆኖ ለመኖርም ሆነ ለመስራት እጅግ በጣም አመቺ ከተማ ናት።
ወላይታ ሶዶ ባለሰባት በር ከተማ ነች።

ኢትዮጵያን ለማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች በነፃነት የሚጓጓዙበት ባለሰባት በር መንገዶችም⏬

1. ከዎላይታ ሶዶ-ዋካ-ታርጫ-ጭዳ-ጅማና ከጭዳ- አመያ- ቦንጋ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ያላት

2. ከዎላይታ ሶዶ- ሠላምበር- ሳውላ-ቡልቂ-ላስካ ኮንክሪት አስፋልት ያላት እና ከዎላይታ ሶዶ- ሠላምበር- ሳውላ-ጅንካ አማራጭ መንገድ ያላት

3. ከዎላይታ ሶዶ- ሁምቦ-አርባምንጭ- ካራት-ጂንካ-ሳላማጎ-ሚዛን አማን የሚያገናኝ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ያላት

4. ከዎላይታ ሶዶ-ባደሣ-ሞሮቾ-ዲላ-ሞያሌ -ናይሮቢ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ያላት (ከዎላይታ ሶዶ-ባደሣ-ሞሮቾ-ሐዋሳ)

5. ከዎላይታ ሶዶ- ቦዲት-ሾኔ- ሀላባ ቁሊቶ- ሻሼመኔ- ዝዋይ- አዲስ አበባ (ከዎላይታ ሶዶ- ቦዲት-ሾኔ- ሀላባ ቁሊቶ- ሻሼመኔ-ሐዋሳ)

6. ከዎላይታ ሶዶ-አረካ-ሆሳዕና -ወራቤ -ቡታጅራ -ሰበታ አስፋልት መንገድ ያላት ናት።

7 .ዎላይታ ሶዶ- ጉልጉላ -ሆብቻ- ዲላ ጌዲኦ- ሞያሌ- ኬኒያ

በእነዚህ በሮች አማካኝነት ስፈልጉ ምርትዎን ማስገባት አሊያም ማስወጣት መብትዎ በእጅዎ ነው። በአጭር ጊዜ ትርፋማ የመሆን እድል በጣም ሰፊ ነው። ይህንን ደግሞ ወደ ከተማዋ ስመጡ በተግባር የሚያዩት ነገር ነውና ይምጡ ይጎብኙ ያትርፉ ይኑሩበት።

አሁን ላይ በሀገራችን ታዋቂ የሆኑ ግለሰቦች የአይን ማረፍያ ሆናለች። ለአብነትም ያክል ሌዊ ሆቴል እና ሪዞርት ሥራ ጀምሯል። ቀጥሎ ሻለቃ ኃይለ ገብረስላሴም ባለስድስት ኮከብ ሆቴልና ሪዞርት ግንባታውን የተጠናቀቀ ስሆን በቅርቡ ሥራ ይጀምራል።

ሌሎች ባለሀብቶችም በውብቷ ወላይታ ሶዶ የእንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው እየሰሩ ይገኛሉ። እናም እርስዎም ይምጡና እንቨስት ያድርጉ ራስዎትን ይለውጡ ሀገርንም ይለውጡ!!!

ከህዝብ አንጻር የወላይታ ህዝብ ራሱን በኢትዮጵያዊነት የሚያይ ስለሆነ ከበርካታ የሀገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ጋር አብሮ የኖረ ህዝብ ነው።

እነዚህ ብሄር ብሄረሰቦች ለአንድም ሰከንድ እንኳን በጎሪጥ ያዬ የለም። እናም የወላይታ ህዝብ ፍቅር ማርኳቸው ሙሉ ኑሯቸውን እዛው ያደረጉት እጅግ በጣም ብዙ ናቸው።

ባጠቃላይ የወላይታ ህዝብ ሥራ ወዳድ ህዝብ ስለሆነ እዛው እንቨስት በማድረግዎ ምንም ጸጸት አይሰማዎትም። ይምጡ ይጎብኙ ያትርፉ ይኑሩ።

ኑ Invest In Wolaita, Ethiopia🙏
ሰላም ለሀገራችን🙏🇪🇹

የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎትን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተሰራ ነውየሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የሰነ...
19/05/2023

የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎትን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተሰራ ነው

የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎት አስታውቋል።

የፌዴራል እና የክልል የሰነድ ማረጋገጥና መመዝገብ ባለድርሻ አካላት የምክክር ጉባኤ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አለምአንተ አግደው፣ የሰነድ ማረጋገጥና ምዝገባ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ደጋቶ ኩምቢ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ እና ቋሚ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ደጋቶ ኩምቢ፥ የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎት አሰጣጥን ተዓማኒ፣ ቀልጣፋ እና አስተማማኝ ለማድረግ በቅንጅት እተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ እና ኦንላይን ለማድረግም እቅድ ተይዞ ስራ መጀመሩን ጠቅሰው፥ አሁን ላይ 80 በመቶ የሚሆነውን አገልግሎት ከሰው ንክኪ ነጻ በማድረግ ብልሹ አሰራርን መቆጣጠር መቻሉንም ነው የተናገሩት።

የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አለምአንተ አግደው በበኩላቸው፥ የሰነዶች ማረጋገጥና ምዝገባ አገልግሎት ለፍትህ ዘርፉ ውጤታማነት ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።

ዜጎች በመተማመን ላይ የተመሰረተ የንግድ፣ የውል እና ሌሎች ጤናማ ስምምነቶች እንዲኖራቸው አገልግሎቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም አስረድተዋል።

ስለሆነም አገልግሎቱ በዘርፉ የሚስተዋሉ የሰነድ ማጭበርበር ወንጀሎችን ለመቀነስ ወጥነት ያለው እና ቀልጣፋ ስርዓት መዘርጋት ይጠበቅበታል ነው ያሉት ።

በዞኑ ለወጣቶች የተለያዩ ስራ አማራጮችን በመጠቀም በተለያዩ ዘርፎች የስራ ዕድል እየተፈጠረላቸው እንደሚገኝ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ገለጹዋና አስተዳዳሪው ይህን የገለጹ...
25/04/2023

በዞኑ ለወጣቶች የተለያዩ ስራ አማራጮችን በመጠቀም በተለያዩ ዘርፎች የስራ ዕድል እየተፈጠረላቸው እንደሚገኝ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ገለጹ

ዋና አስተዳዳሪው ይህን የገለጹት የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአቶ እርስቱ ይርዳው የተመራው ቡድን በወላይታ ዞን በግብርና ዘርፍ ተደራጅተው ውጤታማ የሆኑ ኢንተርፕራይዞችን መስክ ምልከታ ባደረጉበት ወቅት ነው።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ወጣቶች መንግስት ያመቻቸላቸውን የስራ አማራጮችን በመጠቀም ስራን ፈጥረን እንስራ ብለው ተደራጅተው ወደ ስራ እየገቡ መሆናቸውንም አስረድተዋል።

በዛሬው ዕለት በዳሞት ሶሬና በሶዶ ዙሪያ ወረዳ በመስክ ምልከታ ያየናቸው ወጣቶች በግብርና ዘርፍ ተደራጅተው የሚሰሩ የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ናቸው ብለዋል።

ዋና አስተዳዳሪው ወጣቶች ስራን ቁጭ ብለው ከመጠበቅ ይልቅ የስራ አማራጮችን በመጠቀም ያላቸውን ጊዜያቸውን፣ ጎልበታቸውንና ዕውቀታቸውን በመጠቀም ወደ ስራ ከገቡ እንደነዚህ ወጣቶች ሥራ በመፍጠር ሀብት ማፍራት እንደሚቻል ፤በቀላሉ ህይወታቸውን መቀየርና መለውጥ እንደሚችሉም አስረድተዋል።

በሶዶ ከተማ ኤግዞዳስ ፋርም አልሚዎች ትንሽ ገንዘብ ቆጥበው ዛሬ ላይ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እያንቀሳቀሱ እንደሚገኙም በመስክ ጉብኝት መረጋገጡንም ተናግረዋል።

መጽናት፣ መታገስና መጠንከር ለለውጥና ለውጤት ያበቃል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ሰው ይቻላል ብሎ ከሰራ ራሱንና ሀገሩን መለወጥ እንደሚቻልም ጠቅሰዋል።

በዞኑ ቀላል የማይባል የተማረ የሰው ሀይል መኖሩን በመጠቀስ በየአካባቢው ሊለሙ የሚችሉ ወል መሬቶችን በመለየትና ተደራጅተው ውጤታማ የሆኑ ወጣቶች ተሞክሮ በማስፋት ወደ ስራ እንዲገቡ ይሰራልም ብለዋል።

የዞኑ የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች መምሪያ ኃላፊ አቶ ማንደፍሮ ግርማ በበኩላቸው በዞኑ ለወጣቶች ሥራ ዕድልን ለመፍጠር በግብርና ልማትና በሌሎችም ዘርፎች ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በዞኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ55 ሺህ በላይ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ ስራ ዕድል መፈጠሩን በመገለጽ ከዚህም ከ26 ሺህ በላይ ዜጎች የቋሚ ስራ ዕድል የተፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ከዩኒቨርስቲ እና ከኮሌጅ የተመረቁ ወጣቶች ቅዲሚያ በመስጠት እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

በዳሞት ሶሬ ወረዳና በሶዶ ዙሪያ ወረዳ በሰብል ልማት ተደራጀተው ወደ ስራ የገቡ ወጣቶች ኤክስፖርት የሚሆን የወላይታ ቀይ ቦሎቄ እያለሙ ይገኛሉ ብለዋል።

ከወጣቶች አኳያ ያለው የአመለካከት ችግር ለመቅረፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እየተሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች መንግስት ባዘጋጀው የስራ አማራጮችን በመጠቀም ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

እኛ ወጣቶች ስራን መመረጥ የለብንም ያሉት ወጣቶች ስራን ሳንመርጥ ከሰራን መለወጥና በኢኮኖሚም ተጠቃሚ መሆን እንችላለን ብለዋል።

30_40_30 የፍራፍሬ ፕሮጀክት በወላይታ ዞን ሁምቦ ወረዳ"የአርሶአደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለፍራፍሬ ልማት በተሰጠው ትኩረት አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል" አቶ ፀጋዬ ቀ...
22/04/2023

30_40_30 የፍራፍሬ ፕሮጀክት በወላይታ ዞን ሁምቦ ወረዳ

"የአርሶአደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለፍራፍሬ ልማት በተሰጠው ትኩረት አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል" አቶ ፀጋዬ ቀልታ

የሁምቦ አስተባባሪዎች 30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ያለበት ደረጃ በፋንጎ ሎሜ ቀበሌ በመገኘት ጎበኙ።

በጉብኝት ወቅት የሁምቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፀጋዬ ቀልታ 30-40-30 ፕሮጀክት አንድ አርሶአደር በ3 አመት ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ችግኝ የሚተከልበትና አርሶአደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ የሚያስችል ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ፀጋዬ አክለውም በወረዳው በተመረጡ አከባቢዎች የተሻሻሉ፣ በቅርብ ጊዜ የሚደርሱና ብዙ ምርት መስጠት የሚችሉ የሙዝ ችግኝ መንግሥት በማቅረብ እንዲተከል መድረጉን ጠቁመው 30-40-30 ፕሮጀክት ከግብ እንዲደርስ በሁሉም አካባቢዎች የተተከሉ ችግኞችን በተገቢው እንክብካቤ በማድረግ የአርሶአደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰጠው ትኩረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳሰቡ ።

የአርሶአደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለፍራፍሬ ልማት ትኩረት ተሰጥተው መሰራት አለበት ያሉት አቶ ፀጋዬ የሀገርን ዕድገት ለማረጋገጥና ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ግብርና ማዘመን የማይተካ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።

በሁሉም ዘርፍ የአርሶአደሩን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለሁሉም ዘርፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥተው እየተሰራ መሆኑን ጭምር ዋና አስተዳደሩ ገልጸዋል።

የሁምቦ ወረዳ ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ አመኑ ጎአ የብልፅግና ጉዞ ለማፋጠን ግብርና ማዘመን ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ የአርሶአደሩን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በወረዳችን የተጀመረው 30-40-30 ፕሮጀክት ከግብ ለማድረስ በትኩረት መሰራት አለበት ብለዋል።

አቶ አመኑ አክለውም አንድ አርሶ አደር 1 መቶ የአትክልትና ፍራፍሬ በሶስት ተከታታይ ዓመታት 30-40-30 የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል በየአካባቢዉ የአትክልትና ፍራፍሬ መንደር በመፍጠር አርሶ አደሩ ኑሮዉ የሚደጉምበት ነው ብለዋል።

የሁምቦ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት አቶ ተገኝ ታደመ የወረዳው መንግሥት ለግብርው ዘርፈ ትኩረት መሰጠቱን በመጠቆም፣ ከዚህ መካከል የተሻሻለና በአጭር ጊዜ የሚደርሱ የሙዝ ዘሮች ለአርሶአደሮች ማድረስና የተሻለ ምርት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ ቀዳሚው መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ተገኝ አክለውም በወረዳው የፍራፍሬ መንደር ተለይተው እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በየአካባቢው የተተከሉት የሙዝ ችግኞች በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝና ፍሬ እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

በግብርናው የአርሶአደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተገኝ በቀጣይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የአከባቢው አርሶአደሮች በ30_40_30 ፕሮጀክት አመርቂ ውጤት ማግኘታቸው እጅግ ደስተኛ ማደረጋቸውን በመግለጽ ለውጤታማነት የወረዳው መንግስት እያደረገ ላለውን ድጋፍ ከፍ ያለ እውቅና በመስጠት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በጉብኝቱ ላይ የሁምቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፀጋዬ ቀልታ፣ የሁምቦ ወረዳ ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ አመኑ ጎአ፣ ም/አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተገኝ ታደመ እና ረዳት የመንግሥት ተጠሪ አቶ ደነቀ ጊታ መገኘቱን ከወረዳው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ከሀገራችን አልፎ በአለም ደረጃ አካባቢያችን እንዲታወቅ ያደረገውን የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለቡን ለመታደግ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ ቀረበየወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ ለመደገፍ ልዩ ...
18/04/2023

ከሀገራችን አልፎ በአለም ደረጃ አካባቢያችን እንዲታወቅ ያደረገውን የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለቡን ለመታደግ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ

የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ ለመደገፍ ልዩ ገቢን ለማሰባሰብ ያለመ ንቅናቄ መድረክ በጉተራ አድራሽ ተካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙ የወላይታ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነ የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ ያጋጠመውን የፋይናንስ ችግር ለመቅረፍ ልዩ ገቢ አሰባሰብ ስራ ትኩረት መሰጠት እንደሚገባም አመላክተዋል።

ከህዝቡ ማንነትና ደም ጋር የተዋሃደው ድቻ ክለብ እስከሚወደቅ ድረስ መጠበቅ የለብንም ያሉት አቶ ዮሐንስ ክለቡን በዘላቂነት ለመታደግ አመራሩ ግንባር ቀደም ሚናውን ሊወጣ ይገባልም ብለዋል።

ክለብ በዞኑ ህዝብና መንግስት የተቋቋመው ነው ያሉት አቶ ዮሐንስ የክለቡ ባለቤት የሆነው ህዝብ አቅም የቻለውን መደገፍ እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል።

የልዩ ገቢ አሰባሰብ ንቅናቄ እስከ መንደር ድረስ በማውረድ በዘላቂነት ለመደገፍ እያንዳንዱ አካል ክለቡን በስሙ ብቻ ከመደገፍ ባለፈ የራሱን ድርሻ ብወጣ ክለቡን በዘላቂነት መደገፍ እንደሚቻልም አስገንዝበዋል።

ድቻ ከክለብ በተጨማሪ ለወጣቶች ስራ ዕድል የፈጠረ ነው ያሉት አቶ ዮሐንስ ክለቡ በመኖሩ ምክንያት ከአከባቢ አልፎ ለሀገር የሚበቁ ተጫዎቾችን አፈርቷልም ብለዋል።

በየአካባቢው የወላይታ ስም ከፍ ብሎ እንዲጠራ ኩራት የሆነው ክለብ በበጀት እጥረት ምክንያት በየጊዜው የሚገጠሙ ችግሮችን ለመቅረፍ የመፍትሔ አቅጣጫዎችንና ስትራቴጂ የሆነ ዕቅድ እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።

ሁሉንም ህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ በአጭር ጊዜ ልዩ ገቢ ተሰብስቦ ክለቡን መታደግ እንዳለብንም አሳስበዋል።

ስፖርት በስነልቦና ላይ የተመሠረተ ነው ያሉት አቶ ዮሐንስ ክለቡ ውጤት ማምጣት የሚችለው አስፈላጊውን ሁሉ አቀፍ ድጋፎችንና ሞራል በማቅረብ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ደጋፊዎች የፋይናንስ አቅሙን የሚያሳድጉ፣ የሚያስተባብሩ እና የሚያበረታቱ ሊሆኑ ይገባልም ብለዋል።

የወላይታ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መስፍን ዳዊት በበኩላቸው ፈተናዎችንና ችግሮችን ለማሸነፍ ፅናትና ወኔ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል።

የወላይታ ህዝብ ለድቻ የሚሰጠው ስም ልዩ ነው ያሉት አቶ መስፍን ህዝቡ ለድቻ የሚያስፈልገው ሁሉ አቀፍ ድጋፍና ሞራል ማድረግ እንደሚገባም አመላክተዋል።

በየወሩ ከመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ የሚቆርጥ ገንዘብ በአግባቡ መሰብሰብ ከቻልን ቋሚ የድቻ ገቢ እንዲሆን ያደርገዋልም ብለዋል።

የተወዘፉ ዕዳዎችን በአግባቡ ማስመለስና መሰብሰብ እንደሚገባም አመላክተዋል።

በመድረኩ የዞኑ አጠቃላይ አመራር፣ የወረዳና ከተማ አስተዳዳሪዎች፣ የመንግስት ዋና ተጠሪዎችና የክለቡ ቦርድ አባላት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

በረከት ወርቁ "በረከት ገበሬዋ" በአባላ አባያ ወረዳ በአባያ ጉርቾ ቀበሌ በጎርፍ ከቤትና ንብረት ለተፈናቀሉ ዜጎች  ድጋፍ አደረገችድጋፉ የተደረገው በብላቴ ወንዝ ሙላት ምክንያት በቀበሌው ለ...
17/04/2023

በረከት ወርቁ "በረከት ገበሬዋ" በአባላ አባያ ወረዳ በአባያ ጉርቾ ቀበሌ በጎርፍ ከቤትና ንብረት ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ አደረገች

ድጋፉ የተደረገው በብላቴ ወንዝ ሙላት ምክንያት በቀበሌው ለተፈናቀሉ አጥቢና ነፍሰ ጡር እናቶችና ህጻናት የአልሚ ምግብ፣ የወተትና ሌሎች ድጋፎችን በራስ ተነሳሽነት አድርጋለች።

የአባላ አባያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል መና የህዝቡን ጉዳትና መፈናቀል በመረዳት በረከት ላሳየችው በጎነትና ፍቅር አመስግነው በአባያ ጉርቾ ቀበሌ ብቻ የተፈናቀሉት ከ671 በላይ አባወራ ከ5 ሺህ 8 መቶ በላይ የቤተሰብ አባላት በመፈናቀላቸው ከተፈናቃይ ቁጥር አንጻር እየተደረገ ያለዉ ድጋፍ በቂ አይደለም አለመሆኑንም ተናግረዋል።

ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉት አሁንም በማይመች ሁኔታ ውስጥ ያሉና ወደፊትም ከፍተኛ የወባ ስጋት የተጋረጠባቸውና ተያይዞ የመጣ በድርቅ ምክንያት የሚራቡ ወገኖች መኖራቸውን የገለጹት አቶ ሳሙኤል ሌሎችም ነጋዴዎች፣ ኢንቨስተሮች፣ ድርጅቶችና ግለሰቦች የበረከትን መልካምነት ትምህርት ወስደው ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

በረከት ወርቁ በወላይታ ዞን በእርሻ ኢንቨስትመንት ከተሰማሩ ባለሀብቶች አንዷ ስትሆን ድጋፉን ያደረግኩት ለተጎጂዎች ከጎናቸው መሆኔንና ወደፊትም ከእነርሱ ጋር እንደምሆን ለማረጋገጥና ፍቅር ለመግለጽ ነው ስትል ተናግራለች።

"ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው፤ ሰዉ ለመርዳት ባለሀብት መሆን አይጠበቅም።" ያለችው ኢንቨስተሯ አቅም ያለው ሁሉ በመደገፍ እነዚህን ወደ ቤታቸው እንዲገቡ እንዲያደርጉ አሳስባ በአካባቢው ያሉ ነጋዴዎችና ኢንቨስተሮች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቃለች።

ድጋፍ የተደረገላቸው እናቶችም ደስታቸውን ገልጸው ድጋፉ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ስለፍቅር የበጎ ድራጎት ማህበር በአሉን ምክንያት በማድረግ ለአቅደ ደካሞች ድጋፍ አደረገ፡፡የዎላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ አቶ ተመስገን አለማየሁ በተገኙት የበጎ አድራጎት ስራው የተከናወነ ሲሆን...
15/04/2023

ስለፍቅር የበጎ ድራጎት ማህበር በአሉን ምክንያት በማድረግ ለአቅደ ደካሞች ድጋፍ አደረገ፡፡

የዎላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ አቶ ተመስገን አለማየሁ በተገኙት የበጎ አድራጎት ስራው የተከናወነ ሲሆን ስለፍቅር የበጎ ድራጎት ማህበር የጀመረውን ጥረት እንደሚገደግፉ አስታውቀዋል፡፡

ከንቲባው አቶ ተመስገን የትንሳኤን በአል የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍ ማህበር ከሁሉም የሚጠበቅ እና አርአያነት ያለው ተግባር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ስለፍቅር የበጎ ድራጎት ማህበር ስላደረገው ቅን ተግባር በዎላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ስም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

በድጋፍ ላይ የዎላይታ ሶዶ ከተማ የመንግስት ተጠሪ አቶ ጀገና አይዛ በመገኘት በፍፅም አባታዊ ፍቅር ለተቸገሩ ወገኖች ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ስለፍቅር የበጎ ድራጎት ማህበር በዎላይታ ሶዶ ከተማ ብቻ ሳይወሰን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ቦረና ድረስ በመሄድ ድጋፍ ማድረጋቸውን ወጣት ዳጊ አሉላ ገልጿል፡፡

የትንሳኤ በአልን የተቸገሩ ወገኞችን ለመደገፍ ባደረጉት ጥረት በሀገር ውስጥ እና በውጭ የሚኖሩ በጎ አድራጊዎች ላደረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋና ያቀረበው ወጣት ዳጊ በቀጣይም አጠናከረው እንደሚቀጥሉ ተናግሯል፡፡

በእለቱ ከአንድ መቶ በላይ አካል ጉዳተኞች ፣ አረጋዊያን እና የደሀደሀ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡

በሰጡትም ሀሳብ ለተደረገላቸው መልካምነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

በአረካ ከተማ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ በሚገመት ውጭ እየተገነባ ያለው አረካ ፉጦ መሻገሪያ ድልድይ
11/04/2023

በአረካ ከተማ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ በሚገመት ውጭ እየተገነባ ያለው አረካ ፉጦ መሻገሪያ ድልድይ

"ባህር ዛፍ ከጥቅሙ ይልቅ በምርትና ምርታማነት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ ስለሆነ ከእርሻ ማሳ አካባቢ የመንቀል ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት" አቶ ፀጋዬ ቄልታበወላይታ ዞን ሁምቦ ወረዳ...
11/04/2023

"ባህር ዛፍ ከጥቅሙ ይልቅ በምርትና ምርታማነት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ ስለሆነ ከእርሻ ማሳ አካባቢ የመንቀል ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት" አቶ ፀጋዬ ቄልታ

በወላይታ ዞን ሁምቦ ወረዳ በሁሉም አካባቢዎች ከእርሻ ማሳ አካባቢ የመንቀል ሥራ ተጠናክሮ ቀጥለዋል።

የሁምቦ ወረዳ አስተባባሪዎች በአምፖ ኮይሻ ቀበሌ በመገኘት ባህረ ዛፍ የመንቀል ሥራ አበረታቱ።

የሁምቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፀጋዬ ቄልታ ባህረ ዛፍ እርሻ ማሳ አካባቢ መትከል ምርትና ምርታማነት ከመቀነስ አልፈው በዘላቂነት የአፈር ልምነት ስለሚቀንስ ከዚህ በፊት የተተከለውንም ከእርሻ ማሳ አከባቢ የመንቀል ሥራ በሁሉም አካባቢዎች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

አቶ ፀጋዬ አክለውም በተላይ ውሃ_ገብ አካባቢ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው፣ በዓመት ሦስት ጊዜ በሚቻልበት መስኖ አካባቢ ባህረ ዛፍ መትከል ከግለሰቡ አልፈው አካባቢው የሚጎዳና ውሃውንም የሚቀንስ መሆኑን ገልጸዋል።

ባህረ ዛፍ ከጥቅሙ ይልቅ በምርትና ምርታማነት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ ስለሆነ ከእርሻ ማሳ አካባቢ የመንቀል ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያሳሰቡት ዋና አስተዳደሩ፣ አርሶአደሮች ከአመራርና ከባለሙያዎች የሚሰጠውን ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ መረባረብ እንዳለባቸው በአጽንኦት አሳሰቡ።

የሁምቦ ወረዳ ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ አመኑ ጎአ አርሶ አደሩ በየጊዜዉ የአፈር ለምነት እንድቀንስና ምርትና ምርታማነት ላይ አደጋ የደቀነዉን የባህር ዛፍን ከእርሻዉ ማሳ ላይ በማንሳት በሌሎች ሰብሎች ልተካ ይገባል ብለዋል።

አቶ አመኑ አክለውም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣዉ የባህር ዛፍ ተከላ ከጥቅሙ ጉዳቱ የሚያመዝን እንደሆነ አርሶ አደሩ ተገንዝበዉ ከእርሻው እና ከምንጮች ዳር የማስወገዱን ሥራ አጠናክረዉ ልቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።

የሁምቦ ወረዳ ም/አሰተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተገኝ ታደመ የሀገራችን ኢኮኖሚ ጀርባ አጥንት የሆነዉ ግብርናችን ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያሳደረ ያለውን ባህር ዛፍ ከማሳ አካባቢ የመንቀል ሥራ በሁሉም አካባቢዎች በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ተገኝ አያይዘውም አርሶ አደሩ የባህር ዛፉ በተወገደባቸዉ አካባቢዎች በተለያዩ ሰብሎች፣ አትክልት እና ፍራፍሬ ችግኞች በመተካት ምጣኔ ሀብታዊ ተጠቃሚነትን በተሻለ ምርትና ምርታማነት ልደግፍ እንደሚገባ አመላክተዋል።

የአካባቢው አርሶ አደሮችም ባህር ዛፍ በተለያዩ ሰብሎች ላይ የሚያደርሰውን በአይን እንዳዩና ተጎጅ መሆናቸውን በመግለፅ በቀጣይም ከእርሻ ማሳ አካባቢ የመንቀል ሥረሠ አጠናክሮ እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

በወላይታ ዞን የ2015 ዞናዊ የበልግ አዝመራ ንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ነውየወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ የዘንድሮዉን ዞናዊ የበልግ አዝመራ ንቅናቄ መድረክ  እያካሄደ ይገኛል። ንቅናቄው ...
16/03/2023

በወላይታ ዞን የ2015 ዞናዊ የበልግ አዝመራ ንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ነው

የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ የዘንድሮዉን ዞናዊ የበልግ አዝመራ ንቅናቄ መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

ንቅናቄው "በበጋ መስኖ ልማት የተመዘገበውን ስኬት በበልግ እናስቀጥላለን" በሚል መሪ ቃል ነው እየተካሄደ ያለው።

በመድረኩ የ2015 ምርት ዘመን የበልግ ዕቅድና የአፈፃፀም አቅጣጫ ላይ ዉይይት ተካሄዶ ቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

በበልግ ንቅናቄው መድረኩ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ፣ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በየነን ጨምሮ ሌሎች የዞን አጠቃላይ አመራር፣ የሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳዳሪዎች እና ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች እየተሳተፉ ናቸዉ።

ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ "ሊንክ ኢጁኬሽን ኢትዮጵያ" እያደረገ ላለው ድጋፍ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ አመሰገኑበዞኑ ሴት ተማሪዎች በኢኮኖሚ ችግር ከ...
14/03/2023

ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ "ሊንክ ኢጁኬሽን ኢትዮጵያ" እያደረገ ላለው ድጋፍ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ አመሰገኑ

በዞኑ ሴት ተማሪዎች በኢኮኖሚ ችግር ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩና እንዳያቋረጡ "ሊንክ ኢጁኬሽን ኢትዮጵያ" እያደረገ ላለው ድጋፍ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ምስጋና አቅርበዋል።

ሊንክ ኢጁኬሽን ኢትዮጵያ ከወላይታ ዞን ሴቶችና ህጻናት ጉዳዮች እና ትምህርት መምሪያ ጋር በመሆን "የሴቶች ቀን" ምክንያት በማድረግ ህገወጥ የህጻናት ዝውውር፣ ፆታዊ ጥቃት፣ ያለዕድሜ ጋብቻ ላይ ያተኮረ ውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ሴቶች በትምህርታቸው በቁ፣ ብሩህ እይታ ያላቸውና ወደፊቱም ጥሩ መሪዎች እንዲሆኑ መደገፍ ያስፈልጋል ብለዋል።

መንግስት ሴቶች ትምህርታቸው አጠንክረው እንዲማሩ አቅዶ በምሰራበት ወቅት ላይ ድርጅቱ ክፍተቱን በመሙላት ሲሰራና ሲደግፉ እንደቆየም አስታውቀዋል።

በዚህም በዞኑ ከ61 ሺህ በላይ ሴት ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስና ሌሎች ሁሉ አቀፍ ድጋፍ እያበረከተ በመሆኑ ልዩ እውቅና ይሰጣል ብለዋል።

አመራሩም ድርጅቱ እያበረከተ ያለውን ድጋፍ በቅርበት በመከታተልና በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን እያስቀመጠ መምራት እንዳለበትም አሳስበዋል።

ህብረተሰቡ ህገወጥ ህጻናት ዝውውርና ፍልሰትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ፎላን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት መስሪያ ቤቶች ኃላፊዎች፣ ድርጅቱ የሚደግፋቸው ወረዳና ከተማ አስተዳዳሪዎች እና ጉዳዮ የሚመለከታቸው ተወካዮ እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የሥልጠና ጥሪ ማስታወቂያበወላይታ ዞን በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤትየተመዘገባችሁና ወደ ሳውዲ አረቢያ በህጋዊ መንገድ መንግስ ባመቻቸው መን...
11/03/2023

የሥልጠና ጥሪ ማስታወቂያ

በወላይታ ዞን በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤትየተመዘገባችሁና ወደ ሳውዲ አረቢያ በህጋዊ መንገድ መንግስ ባመቻቸው መንገድ ስልጠና ወስዳችሁ ለምስራት ፍቃደኛ የሆናችሁ የመጀመሪያ ዙር ስልጠና የምትገቡ ሴት ድግሪ ሙሩቃን በሙሉ፤

ወደ ሳወዲ አረቢያ በመላክ ለሥራ ፈላጊዎች የሥራ ስምሪት ለማመቻቸት በዚህ ሳምንት በሁሉም አካባቢዎች ምዝገባ ማድረጋችን ይታወሳል፡፡

በዚህ መሠረት ከዚህ ቀጥሎ የሚከተሉትን ቅደም ተከተሎችን ቅድሚያ በመስጠት ዝግጅት በማድረግ፡-

ከሰኞ 04/07/2015 ከ2፡30 ጀምሮ

1. በወላይታ ሶዶ ከተማ በሶዶ ፖሊ ቴክ/ና ሙያ ኮሌጅ በመምጣት መመዝገብ ይኖርባቸዋል፣
2.የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች በገጠርም ሆነ በከተማ ሴት የድግሪ ምሩቃን።

3. ሥልጠናዉ የምቆየዉ ለ21 ቀን መሆኑና የቆይታ ቀናት፣ የትራንስፖርትና ቀለብ በሙሉ ከሠልጣኙ ወጣት መሆኑን እንዲያዉቁ መልዕክት ማስተላለፍ፤

4. ለምዝገባ ስመጣ መመዝገቢያ አንድ ሠልጣኝ 500/ አምስት መቶ የኢት/ያ ብር ይዘዉ ይመጣሉ።

5. በተጨማሪም ዋናዉን የትምህርት ማስረጃ (Original) ዶክመንት እና የማይመለስ 1 ኮፒ ይዘዉ መምጣት አለባቸዉ፡፡

ከሥራ ዕ/ፈተ/ኢንተርፕ/ች ልማት መምሪያ

የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በወላይታ ዞን እየተሰራ ያለውን የተለያዩ ፕሮጀክቶች ጎበኙየህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በወላይታ ዞን እየተሰራ ያለውን የተለያዩ ፕሮጀክቶች ጎብኝተዋል።...
11/03/2023

የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በወላይታ ዞን እየተሰራ ያለውን የተለያዩ ፕሮጀክቶች ጎበኙ

የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በወላይታ ዞን እየተሰራ ያለውን የተለያዩ ፕሮጀክቶች ጎብኝተዋል።

በክቡር አቶ መለሰ መና የተመራው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በወላይታ ዞን በበሌ ሀዋሳ ከተማ የሚገኘውን ኦሞ ሰው ሰራሽ ሀይቅ፣ በኦሞ ሰውሰራሽ ሀይቅ ላይ የሚገነባውን የሮማንና ሀይለማርያም ፋውንዴሽን እና የኢሊኮፕተር ማረፊያና በጉኑኖ ከተማ የሚገነባውን የከተማ ውስጥ ለውስጥ አስፓልት መንገድ ግንባታ ሂደትን ተዟዙረው ተመልክተዋል።

በጉብኝቱ የኢፌዴሪ ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እንድሪያስ ጌታን ጨምሮ ከተለያዩ የወላይታ ዞን በህዝብ ተመርጠው በፌደራልና በክልል የህዝብ ተወካይ የምክር ቤት አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።

የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል ይገባል:- ክብርት ካሰች ኤልያስየህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የወላይታ ዞን ...
09/03/2023

የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል ይገባል:- ክብርት ካሰች ኤልያስ

የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የወላይታ ዞን የምክርቤት ዋና አፌ ጉባኤ ክብርት ካሰች ኤልያስ አሳሰቡ።

የወላይታ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው።

የምክርቤቱ ዋና አፌ ጉባኤ ክብርት ካሰች ኤልያስ 4ኛ ዙር 10ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በይፋ መከፈቱን አብስረዋል።

የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ከአስፈጻሚ መስሪያቤቶች ጋር የውል ስምምነት ከተፈራረመ በኃላ ወደ ተግባር መገባቱን አስረድተዋል።

የኦዲት ግኝት ገንዘብ ለማስመለስ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናና ውይይት የተደረገ ቢሆንም የተፈለገው ውጤት ያልተመዘገበ መሆኑንም ገልጸዋል።

በዞኑ በስፋት የሚታየውን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊትን ለማስወገድ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን የገለጹት ክብርት ካሴች በህብረተሰቡ ዘንድ አሉታዊ ተዕጽኖ እያሳደረ ያለው ጎጂ ልማዳዊ ድርጊትን ለማስወገድ እየተደረገ ያለው ጅምር ስራዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመቅረፍ ታስቦ እንዲተገበር የታቀደው በበጀት ችግርና በተለያዩ ምክንያቶች የህዝቡን ፍላጎት ባማከል መልኩ አለመከናወኑን አንስተዋል።

ከህዝብ የሚነሱ ጥያቄዎች በአግባቡና በተገቢዉ ምላሽ እንድያገኙ ምክር ቤቶች በመንግስትና በህዝብ መካከል ድልድይ በመሆናቸዉ ይህንን ሀላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ዋና አፈ-ጉባኤ አሳስበዋል።

ምክርቤት አባላት ለጉባኤው በተዘጋጁ አጀንዳዎች ላይ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ ገንቢ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ አሳስበዋል።

የወላይታ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል የወላይታ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።ምክር ቤቱ የስድስት ወር አፈጻጸም በመገ...
09/03/2023

የወላይታ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል

የወላይታ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።

ምክር ቤቱ የስድስት ወር አፈጻጸም በመገመገም እና ሌሎች ተያዥ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

በጉባኤው የዞን አጠቃላይ አመራር፣ አጠቃላይ የምክር ቤት አባላት፣ የወረዳና ከተማ አስተዳዳሪዎች፣ የሀይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ሴቶች ህብረብሄራዊ አንድነታቸውን በማጠናከር ለጋራ ዓላማ በጋራ መሰለፍ አለባቸው፦ ወ/ሮ እታገኝ ኃ/ማርያም የወላይታ ዞን ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት ከደቡብ ክልል ግብርና ቢሮ ጋር በመሆን ለሞዴል ሴ...
08/03/2023

ሴቶች ህብረብሄራዊ አንድነታቸውን በማጠናከር ለጋራ ዓላማ በጋራ መሰለፍ አለባቸው፦ ወ/ሮ እታገኝ ኃ/ማርያም

የወላይታ ዞን ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት ከደቡብ ክልል ግብርና ቢሮ ጋር በመሆን ለሞዴል ሴቶች የ45 ቀን ዳሮ ጫጩት ድጋፍ አድርጓል።

በድጋፍ ቦታ የተገኙ የወላይታ ዞን አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ እታገኝ ኃ/ማርያም ባስተላለፉት መልዕክት ሴቶች በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ መስኮች ተጠቃሚነታቸው እየጎላ መምጣቱን ገልጸዋል።

የሴቷን ህይወት በሚለውጡ ጉዳይች ላይ አጠናክረን መስራት ያስፈልጋል ያሉት ወ/ሮ እታገኝ ለዚህም ሁሉ አቀፍ ድጋፍ ከሁሉም እንደሚጠበቅበትም አበክሮ አንስተዋል።

"ምግብን ከጎሮዬ፣ ጤናዬን ከምግቤ" ንቅናቄ ብዙሃን ሴቶች በማሳተፍ ሁሉም እንዲያመርቱ መደረጉ የዋጋ ለውጥ እስከሚመጣ ድረስ ውጤት መምጣቱን ገልጸዋል።

በሀገር ደረጃ የተጀመረው "በሌማት ትሩፋት" ላይ ሴቶች የበኩላቸውን ኃላፊነት በመወሰድ ለተግባራዊነቱና ለውጤታማነቱ ጥረት ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ጠንካራ አባላት እንዲኖር የሊግ አደረጃጀቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል።

ሊግ፣ ፌዴረሽንና ማህበር ሴቷን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ጉዳዮች ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ያሳሰቡት ወ/ሮ እታገኝ ለዚህም ተቀናጅተውና ተናብበው መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የሴቶች ግንባር ቀደም መሪነት እውን ለማድረግ በተግባር የሚገለፅ ስራ ማከናወን እንደሚገባ ያመለከቱት ወ/ሮ እታገኝ በዓላማ ጽናት እና በቁርጠኛ ትግል መፈጸም እና ማስፈጸም ያስፈልጋል ነው ያሉት፡፡

የብልጽግና ጉዞአችን በተሟላ መልኩ ተፈጻሚ ሊሆን የሚችለው፣ ሴቶችን በንቃት ሲሳተፉና በሂደቱም ተጠቃሚነታቸው ሲረጋገጥ እንደሆነም አስገንዝበዋል።

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ ጽ/ቤት የ2015 የስድስት ወራት ዕቅድ ክንውን አፈጻጸምን የዘርፉ አመራሮች በተገኙበት እየተገመገመ ነው።

የኢትዮጵያ አየርመንገድ የሴቶች ቀንን በማስመልከት ሙሉ በሙሉ በሴቶች የሚመራ በረራ አደረገየኢትዮጵያ አየር መንገድ የሴቶች ቀንን በማስመልከት ሙሉ በሙሉ በሴቶች የሚመራ በረራ አደረገ።በአየር...
08/03/2023

የኢትዮጵያ አየርመንገድ የሴቶች ቀንን በማስመልከት ሙሉ በሙሉ በሴቶች የሚመራ በረራ አደረገ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሴቶች ቀንን በማስመልከት ሙሉ በሙሉ በሴቶች የሚመራ በረራ አደረገ።

በአየር መንገዱ የዓለም የሴቶች ቀን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው እና የአየር መንገዱ የቦርድ ሰብሳቢ ግርማ ዋቄ በተገኙበት ተከብሯል።

አየርመንገዱ ወደ ዛንዚባር የሚያደረገውን በረራ ከዋና አብራሪዋ ጀምሮ ረዳት አብራሪ፣ የበረራ አስተናጋጆች እና ቴክኒሽያኖች ሴቶች ናቸው።

ከዚህም ባለፈ የአየር ትራፊክ፣ የበረራ ደህነነትና የጭነት ቁጥጥር፣ የበረራ መለኪያ እስከ አውሮፕላኑ መነሻ ድረስ ሙሉ በሙሉ በሴቶች የተመራ ነው።

ይህ ሴቶች ያላቸው አቅም ሳይገደብ ማህበረሰብን ማነፅ የሚችል አቅም እንዳላቸው ማረጋገጫ መሆኑን የአየርመንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል።

የአለም የሴቶች ቀንን በማስመልከት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በየዓመቱ በሴቶች የተመሩ በረራዎችን ሲያደርግ ይህ ለ7ኛ ጊዜ ሲሆን በረራው የአየርመንገዱ የመጀመሪያ ሴት አብራሪ በሆኑት ካፒቴን አምሳል ጓሉ የተመራ ነው።

አስደሳች ዜና በዎላይታ ሶዶ ከተማ የዳቦ  እና ዱቄት ፋብሪካ በይፋ ምርቶችን ተደራሽ ማድረጉ ተገለፀ።በ3 ማእከላት ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ  የዎላይታ ሶዶ ዳቦ እና ዱቄት ፋብሪካ ምርቶች ለተጠቃ...
08/03/2023

አስደሳች ዜና

በዎላይታ ሶዶ ከተማ የዳቦ እና ዱቄት ፋብሪካ በይፋ ምርቶችን ተደራሽ ማድረጉ ተገለፀ።

በ3 ማእከላት ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ የዎላይታ ሶዶ ዳቦ እና ዱቄት ፋብሪካ ምርቶች ለተጠቃሚዎች እየቀረቡ ይገኛል።

የዳቦ እና ዱቄት ፋብሪካው ምርቶች ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በብቃት የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ለ10 ቀናት ስልጠና የወሰዱ ወጣቶች የስራ እድል ተፈጥሯል።

በተመጣጣኝ የገበያ ዋጋ በአራዳ ፣ መርካቶ እና መሀል ቀበሌ በተዘጋጀ የመሸጫ ማእከል ዳቦ በመሸጠት ላይ ነው።

በቀጣይም የተደራሽነት አድማስን በማስፍት አዳዲስ የሽያጭ ማእከላትን ለመክፈት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።

"አድዋ በአራቱም ማዕዘናት የሚገኙ ብሄር ብሔረሰቦች በአንድ ልብ መክረው ለአገራቸው የተዋደቁበት ታላቅ የድል በዓል ነው"፡- አቶ ዮሐንስ በየነWolaita Press Agencyእንኳን ለጥቁር ...
02/03/2023

"አድዋ በአራቱም ማዕዘናት የሚገኙ ብሄር ብሔረሰቦች በአንድ ልብ መክረው ለአገራቸው የተዋደቁበት ታላቅ የድል በዓል ነው"፡- አቶ ዮሐንስ በየነ
Wolaita Press Agency
እንኳን ለጥቁር ህዝቦች ኩራት ለሆነዉ ለታላቁ የአድዋ ድል 127ኛ ዓመት የመታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

የአድዋ ድል የህብረ ብሔራዊ አንድነታችን ማህተብ፣ የነፃነት አርማና ምልክት፣ የድል አድራጊነታችን ምስክር፣ የኩራታችን ምንጭ የሆነና በአራቱም ማዕዘናት የሚገኙ ብሄር ብሔረሰቦች በአንድ ልብ መክረው ለአገራቸው የተዋደቁበት ታላቅ የድል በዓል ነው።

ይህ ታላቅ ድል በዓልን ለ127ኛ ጊዜ ስናከብርና ስንዘክር የአባቶቻችንን ጀግንነትንና ወኔን ተላብሰን ለአንድ ዓላማ በጋራ መቆም አለብን፡፡

የዐድዋ ድል በጥቁርና በነጭ መካከል የነበረውን የተበላሸ ትርክት የቀየረ፣ የጥቁር ህዝቦችን ማንነት ያስመሰከረ ገድል ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያን መንካት የሚያስከትለው መዘዝ ምን እንደ ሆነ አስተምሮ ያለፈ ደማቅ ሐውልት ነው፡፡

የዓድዋን የድል በዓል ስናከበር አሁን በዘመናችን ያለውን ድህነት፣ ኋላ ቀርነት፣ ዘረኝነት፣ ጎጠኝነትና የመሳሰሉትን የብልጽግና እንቅፋቶች በመዋጋት ጠንካራ የሥራ ባህልን በማዳበር ነገሮችን ሁሉ በስሜት ሳይሆን በስሌት በማከናወን የሀገራችንን ብልጽግና ማረጋገጥ ይገባናል።

አድዋ አባቶቻችንና እናቶቻችን መከፋፈልና ግለኝነትን ትተው ተከባብረውና ተፈቃቅረው እንደሰርገኛ ጤፍ ህብር ፈጥረው፤ በህብር ማሸነፍን ጥበብ ተላብሰው ያረጋገጡት የአይበገሬነት ክብረ ወሰን ማሳያ ነው፡፡

እኛ ኢትዮጵያውያን በጋራ መታገል እና በጋራ ድል መቀዳጀት ልምድ ያለን ህዝቦች መሆናችንን የአድዋ ድል ትልቅ ታሪካዊ ማሳያ ነው።

አባቶቻችን በክብር ያስረከቡንን የነፃነት ሀገር አሁን ያለው ትውልድ አንድነቷን ሊሸረሽሩ ከሚችሉ ነገሮች በመራቅ እና ለልዩነት ቦታ ባለመስጠት አንድነቷን አስጠብቆ ዘመኑ ለሚጠይቀው ትግል በፅናት በመሰለፍ ሰላሟ የተረጋገጠና ልማቷ የተፋጠነ ሀገር መገንባት ይኖርበታል።

አባቶቻችን ልዩነቶቻቸውን ወደ ኋላ ትተው ለሀገራቸው አንድነት ተዋድቀዋል። በአለም አደባባይ የአይደፈሬነት ተምሳሌት የጥቁር ህዝቦች ኩራት የተሰኘውን ቋሚ ቤተመዘክር አውርሰውናል።

ዛሬ አድዋን የምናከብረው ከጀግኖች አባቶቻችን ብልሀትን፣ አርቆ አስተዋይነትን እና ከጥቃቅን ጊዜያዊ ፍላጎቶቻችን ባሻገር ሀገርን በማስቀደም በሚኖረን የጋራ ትልሞቻችን ላይ ትኩረት ማድረግ ሊሆን ይገባል።

የዓለም ታሪክ የሚነግረን እውነት ቢኖር እርስ በእርስ በመገፋፋት ጥፋት እንጂ ብልጽግናም ሆነ ሀገራዊ አንድነት ማምጣት እንደማይችል የሚጠቆም በመሆኑ አንዳችን ለአንዳችን ዋልታ እና ማገር፣ ድርና ማግ መሆን ያስፈልጋል፡፡

አድዋን ስናከብር አንድነታችንን በማጠናከር ለመጪው ትውልድ የይቻላልና የአሸናፊነትን መንፈስን ማጎናጸፍ ይገባናል፡፡ ሁላችንም የየግል ኃላፊነታችንን ከተወጣን ድህነትም ድል የሚሆንበትና ብልፅግናችንን የምናረጋግጥበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡፡

የሀገራችንን ነጻነት በደም እና በአጥንታቸው ጠብቀዉ ለዛሬ ያበቁ የጀግኖች አባቶቻችንን ገድል በመከተል የአድዋን የመደመር እሳቤ ይዘን የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ማረጋገጥ ይኖርብናል።

ዮሐንስ በየነ
የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ
የካቲት፤2015 ዓ.ም

በወላይታ ዞን የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈጻጸም ዞናዊ የግምገማ መድረክ መካሄድ ጀመረበወላይታ ዞን ያለፉት የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች ዞናዊ አፈጻጸም ግም...
23/02/2023

በወላይታ ዞን የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈጻጸም ዞናዊ የግምገማ መድረክ መካሄድ ጀመረ

በወላይታ ዞን ያለፉት የስድስት ወራት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች ዞናዊ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

መድረኩን በንግግር የከፈቱት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ባለፉት ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ያተኮረ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።

በ2015 ግማሽ ዓመት የነበሩ ጥንካሬዎችን በማጽናትና በማስፋት ጉድለቶችን በማረም አመራሩ ለቀጣይ ተልዕኮ ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በየነ በበኩላቸው የአመራር ሚዘና ስርዓት መሠረት የአመራር ማጣራትና ማብቃት ስራ እንደሚሰራም አስታውቀዋል።

የአመራሩ ውጤታማነት፣ የተግባር አንድነትና ልልነት ቀጣይ መቅረፍ እንደሚገባም ያሳሰቡት አቶ ዮሐንስ መድረኩ የዕለት ተዕለት ተግባራት ዕቅድ አፈጻጸምን መነሻ ያደረግ እንደሆነም አስረድተዋል።

መድረኩ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን ፓርቲያችን በምርጫ ወቅት ለህዝቡ ቃል የገባቸው ጉዳዮች መካከል ያልተከናወኑ ጉዳዮችን በመለየት ቀጣይ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሶ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ፣ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በየነ ጨምሮ ሌሎች የዞኑ አጠቃላይ አመራር እና የወረዳና ከተማ አስተባባሪ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

በከፍተኛ ቁጭት የተጀመረው የበጋ ስንዴ የአርሶ-አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ ነው፦ አቶ መስፍን ዳዊትበወላይታ ዞን ዞናዊ በበጋው መስኖ የለማ የስንዴ ምርትን በኮምባይነር የመሰብሰ...
20/02/2023

በከፍተኛ ቁጭት የተጀመረው የበጋ ስንዴ የአርሶ-አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ ነው፦ አቶ መስፍን ዳዊት

በወላይታ ዞን ዞናዊ በበጋው መስኖ የለማ የስንዴ ምርትን በኮምባይነር የመሰብሰብ ሂደት በሁምቦ ወረዳ አምፖ ኮይሻ ቀበሌ ተጀምሯል፡፡

በምርት የመሰባሰብ ሂደት ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የዞኑ ም/አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ዳዊት በወላይታ ዞን በበጋ መስኖ 1650 ሄክታር ከለማው ማሳ ከ57 ሺህ ኩ/ል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።

አምና የበጋ መስኖ ስንዴ ለማስጀመር በአርሶ-አደሩ ዘንድ የአመለካከት ችግር መኖሩን የጠቆሙት አቶ መስፍን ዘንድሮ ከአርሶ-አደሩ ጋር መግባባት ላይ በመድረስ ወደ ተግባር መገባቱን አስረድተዋል።

ምርትን ያለብክነት ለመሰብሰብ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በዘመናዊ ማሽን እንዲሰበሰብ እየተደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

አርሶ-አደራችን የተሻለ ቴክኖሎጂን እንዲጠቀም በማድረግ ጉልበቱን በመቆጠብ ምርትና ምርታማነቱን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አስረድተዋል።

በአርሶ-አደሩ ዘንድ የማልማት ፍላጎቱን መጨመሩን አቶ መስፍን ገልጸው ይህም አርሶ-አደሩን በቁጭት ውስጥ እንዲገባ አድርጎታልም ብለዋል።

በወረዳው አራት ዘመናዊ የመስኖ አውታሮች መኖራቸውን የጠቆሙት የሁምቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀገና አይዛ በአራቱም መስኖ ሳይት የለማው በበጋ መስኖ ስንዴ የተሻለ ምርት መገኘቱን ተናግረዋል።

የለማው ስንዴ በክላስተር በኮምባይነር እንዲሰበሰብ መደረጉ የአካባቢውን አርሶ አደሮች ምርትን ከብክነት እንዴት ማዳን እንደሚቻል ያስተማረም ነው ብለዋል።

የወረዳው ም/አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አመኑ ጎኣ በበኩላቸው ዘንድሮ በበጋ መስኖ ስንዴ ከ255 ሄ/ር በላይ በዘር መሸፈኑንና ከ8 ሺህ 400 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።

በዘንድሮ በጋ መስኖ ስንዴ የተሻለ ምርት እንደሚያገኙ የተናገሩት አርሶ-አደሮቹ በሄክታር ከ30-33 ኩ/ል ምርት እንደሚያገኙም ተናግረዋል።

የዘር አቅርቦት ችግር መኖሩን የገለጹት አርሶ-አደሮቹ በቀጣይ ጊዚያት ወጥ ያለ ዘር ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ጠይቀዋል።

"በወላይታ ዞን የሕዝበ ውሳኔው ሂደት ደኅንነቱ ተጠብቆ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል" አቶ አክሊሉ ለማበወላይታ ዞን ነገ ጥር 29/2015 ዓ.ም የሚካሄደው ሕዝበ ውሳኔ ደኅንነቱ ...
05/02/2023

"በወላይታ ዞን የሕዝበ ውሳኔው ሂደት ደኅንነቱ ተጠብቆ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል" አቶ አክሊሉ ለማ

በወላይታ ዞን ነገ ጥር 29/2015 ዓ.ም የሚካሄደው ሕዝበ ውሳኔ ደኅንነቱ ተጠብቆ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ገለጹ።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ የሕዝበ ውሳኔ ቅድመ ምርጫ ሂደቱ በተሰካ ሁኔታ መከናወኑን ጠቁመዋል።

በተለይም ደግሞ የሕዝበ ውሳኔ የምርጫ ሂደቱን በሚመለከትም ለኅብረተሰቡ የማስገንዘብ ሥራ በስፋት ሲካሄድ መቆየቱንም ነው የገለጹት።

ለሕዝበ ውሳኔ ምርጫው በ8 የተለያዩ ምርጫ ማዕከላትና ከ1 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲደራጁ መደረጉን ጠቁመው አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ ሰው የምርጫ ካርድ መውሰዱን ተናግረዋል።

ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበርም በሁሉም የምርጫ ማዕከላትና ጣቢያዎች የምርጫ ማስፈጸሚያ ቁሳቁስ ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል።

የሕዝበ ውሳኔ ሂደቱም ሰላምና ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው የጸጥታና የፍትህ አካላት ሥምሪት መሰጠቱን ጠቁመዋል።

ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የህዝበ ውሳኔ ሂደቱ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ሚና እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል።

ለሕዝበ ውሳኔ ምርጫ ለመሳተፍ የመራጭነት ካርድ የወሰዱ ግለሰቦችም ካርዳቸውን እንዲጠቀሙበት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ደራሼ) በነገው ዕለት የሕዝበ ውሳኔ ምርጫ ይካሔዳል።

#ኢዜአ

Address

Addis Abeba
S**o
S**O

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Press Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category


Other TV Channels in S**o

Show All