Geez Media ግእጽ ሚድያ

Geez  Media ግእጽ ሚድያ ዓወት ንሓፋሽ awet NHafash

16/09/2020

“በሽኸት/አብዓላ ከተማ የተፈፀመው ድርጊት አሳፋሪ፣ ሃላፊነት የጎደለውና ፍፁም ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው”ሲሉ የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ነብዩ ስሑል ሚካኤል ገለፁ።
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

ሽኸት ከተማ የመቻቻል፣ የመፈቃቀርና የአንድነት ከተማ እንጂ የብሄር ነጋዴዎች፣ ሴረኞችና ቁማርተኞች እንደሚመኙት የመለያያና የግጭት ከተማ አይደለችም።

ቅድምያ ለሰላም፣ ለመቻቻልና ለአብሮ መኖር ይሁን፤ አጥፊዎችም በአፋጣኝ ለፍርድ ይቅረቡ።

ለሟቾች ዘለአለማዊ እረፍት፤ ለቤተሰብ ደግሞ መፅናናትን እመኛለሁ ሲሉ ሃላፊው ገለፀዋል።

ኢትዮጵያ ነባሮቹን የ10፣ የ50 እና የ100 የብር ኖቶች የሚተኩ አዲስ የገንዘብዓይነቶችና አዲሱን የ200 ብር ኖት ይፋ አደረገችአዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ ...
14/09/2020

ኢትዮጵያ ነባሮቹን የ10፣ የ50 እና የ100 የብር ኖቶች የሚተኩ አዲስ የገንዘብ
ዓይነቶችና አዲሱን የ200 ብር ኖት ይፋ አደረገች
አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ ነባሮቹን የ10፣ የ50
እና የ100 ብር ኖቶች ዓይነቶችን ሙሉ ለሙሉ በመተካት ለግብይት የሚሆን
አዲስ የብር ኖት መጠቀም እንደምትጀምር ይፋ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር
ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።
ነባሮቹን የብር ኖቶች ከሚተኩት በተጨማሪ በዛሬው ዕለት የ200 ብር ኖት ይፋ
እንደሆነ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በፌስቡክ ገፃቸው ባወጡት
መረጃ የገለፁት።
የ5 ብር ኖት ባለበት ቀጥሎ፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ወደ ሣንቲም የሚለወጥ
ይሆናል ተብሏል።
እነዚህ አዲስ የገንዘብ ዓይነቶች ለሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎች የሚደረግን ድጋፍ፣
ሙስናን እና የኮንትሮባንድ ሥራዎችን ለመቀልበስ እንደሚረዱ ተጠቁሟል።
እንዲሁም የፋይናንስ ተቋማት የገንዘብ እጥረትን ለመቋቋም እንዲችሉም
ያግዛል ነው የተባለው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲሶቹ የገንዘብ ዓይነቶች ላይ የተካተቱ መለያዎች
አመሳስሎ ገንዘብ ለማተም የሚደረጉ ሕገ ወጥ ጥረቶችንም ለማስቀረት
እንደሚያግዙ ገልፀዋል።
አዲስ የታተሙት የብር ኖቶቹ በአካላቸው ላይ የሚገኙ የደህንነት መጠበቂያ
ምልክቶች ያሉባቸው ናቸው።
እነዚህን ያላሟሉ ወይም ተመሳስለው የተዘጋጁ ገንዘቦች የያዙ ወይም
የሚጠቀሙ ግለሰቦች ካጋጠሙ ለፀጥታ አካላት መጠቆም እንደሚገባ
ተነግሯል።
በአሁኑ ወቅት የአዲሶቹ የብር ኖቶች አብዛኛው የህትመት ሥራ ተገባዶ
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ግምጃ ቤት እንደሚገኝ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የስርጭት ስርዓት እና ዕቅድ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በሚመለከታቸው አካላት
አማካኝነት እንደሚተገበር ተጠቁሟል።
በገንዘብ ቅያሬው ሂደት የጸጥታ ማስከበር አካላት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖራቸው
የተገለፀ ሲሆን፥ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ከማህበረሰቡ ጋር
በመተባበር ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ እንደሚያስፈፅሙ ተነግሯል።
ለዚህም ከብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት፣ ከብሔራዊ የመረጃ እና ደህንነት
አገልግሎት እና ከፌደራል ፖሊስ የተውጣጣ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሞ፤ ሂደቱን
በበላይነት ያስተባብራል።
እንዲሁም የክልል መንግሥታት ተመሳሳይ ኮማንድ ፖስት አቋቁመው ሥራውን
እንዲያከናውኑ ይጠበቃል።
የገንዘብ ቁጥሮቹ በሚያጎላ መሳሪያ ሲታዩ ከጥቁር ወደ አረንጓዴ ፍሎረሰንት
ቀለም እንደሚለወጡ ብሄራዊ ባንክ አስታውቋል።
ለአይነ ስውራንም የእውቅና ምልክት ያለው ሲሆን የብሩን ዋጋ በእጅ ዳሰሳ
ማወቅ የሚችሉበት የደህንነት መጠበቂያ ያለው ነው።
በተመሳሳይ ገንዘቡ ወደ ላይ ወይንም ወደታች ሲዞር የሚንቀሳቀስ ደማቅ
የቀለም ፍንጣቂ የደህንነት መጠበቂያ ምልክት እንዳለውም ነው ተነግሯል።
የብር ኖቱ ሲዳሰስ የመጎርበጥ ስሜት እንዲሁም የኖቱ ዋጋ ይታያል።
የሚሽከረከር ደማቅ ቀለም ኮኮብ አዲስ የደህንነት መጠበቂያ ክር፤ በክሩ
ውስጥም NBET፣ ኢብባ እና ገንዘቡ አይኖቶች ተፅፈው ይገኙበታል ነው
የተባለው።
ገንዘቡ ወደ ብርሃን አቅጣጫ ተደርጎ ሲታይ በላይ ላይ ከሚገኘው ምስል ፊት
ለፊት ተመሳሳይ ደብዛዛ ውሃ መልክ ያለው ምልክት እንደሚታይ ተጠቁሟል።
የብር ኖቶቹ በብርሃን አቅጣጫ ሲታዮ ኳስ መሳይ ምልክት ከኖቶቹ በስተኋላ
ካለው ተመሳሳይ ምልክት ጋር በፍፁም ትይዩ ሆነው በአንድ ቦታ ላይ ያርፋሉ።
እንዲሁም አንበሳው ምስል ራስ ላይ አልትራቯዮሌት ጨረር ሲበራበት ወደ ቢጫነት የሚለወጥ ፍሎረሰንት ምልክት አለው ተብሏል።

27/06/2020

በቦሌ ክ/ከተማ የመብራት ኃይል ሠራተኞች ነን በሚል ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አስተላላፊ የሆነ ትራንስፎርመር በክሬን ጭነው ለማምለጥ ሲመክሩ በአካባቢው ነዋሪዎች ጥርጣሬ ለፖሊስ በተሰጠ ጥቆማ እሰከጫኑበት ክሬን እጅ ከፍንጅ ሊያዙ መቻላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ ፡፡
በተለያዩ አካባቢዎች የመብራት ኃይል ሰራተኞች ነን በሚል ማጭበርበሪያ
ከመስሪያ ቤቱ እውቅና ውጭ ህብረተሰቡ በሚጠቀምበት የኤሌክትሪክ ኃይል
ላይ የተለያዩ ወንጀሎችን የሚፈጽሙ ግለሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከቱ
ስለሆነ ህብረተሰቡ ለኤሌክትሪክ ኃይል ንብረቶች ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርግ
ተጠቆመ፡፡
በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ሐያት ቁ.1 በሚባል አካባቢ ሠኔ 19/2012 ዓ.ም
ከቀኑ 9፤30 አካባቢ ለ80 አባወራዎች አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውን
ትራንስፎርመር ከመስሪያ ቤቱ ዕውቅና ውጭ ኮድ3ኢ.ት84535 በሆነ ክሬን
ተሸከርካሪ ታግዘው በመስረቅ ለማምለጥ ሲመክሩ በአካባቢው ነዋሪ ጥርጣሬ
ለፖሊስ በተሰጠ ጥቆማ እጅ ከፍንጅ ሊያዙ መቻላቸውን በቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ
መምሪያ የወንጀል መከላከልና የማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገልግሎት ም/
ዳይሬክቶሬት የሆኑት ኮማንደር ያሲን ሁሴን ለአዲስ ፖሊስ ገልዋል፡፡
ግለሰቦቹ በኃላፊያቸው ታዘው ትራንስፎርመር ለመቀየር መምጣታቸውን
ቢናገሩም በኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የምስራቅ አዲስ አበባ
ዲስትሪክት የኮንስትራክሽንና ሜንቴናንስ ኃላፊ አቶ ሱልጣን ሰርሞሎ ግለሰቦቹን
መሥሪያ ቤቱ እንደማያውቃቸውና ከመሥሪያ ቤቱ የታዘዙ ቢሆኑ እንኳን የትዕዛዝ
ደብዳቤ መያዝ እንደነበረባቸው ገልጸው ለማነኛውም ትዕዛዝ ሰጥቶናል
እንድንሰራ ያሉትንም ሓላፊ ከፖሊስ ጋር በጋራ እንደሚያጣሩት በበኩላቸው
አስረድተዋል ፖሊስ የምርመራ ሂደቱን ለመቀጠል ተጠርጣሪዎቹንና
በእግዚቢትነት የተያዙ ንብረቶችን በቁጥጥር አውሎ ምርመራ መጀመሩን
የገለጹት ኮማንደር ያሲን ሁሴን በመብራትና በሌሎች የመሰረተ ልማት
አውታሮች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ለመከላከል ህ/ተሰቡ ከፖሊስ ጋር
በመቀናጀት አካባቢውን መጠበቅ እንዳለበትና የመብራት ኃይል ሰራተኞች ነን
በሚል የሚመጡ ግለሰቦች ሲያጋጥሙት ህጋዊ ሰራተኞች ስለመሆናች
በአግባቡ ማረጋገጥ ይኖርበታል ሲሉ ኃላፊው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን

አሳዛኝ ዜናየራያ ቆቦ ዋና አስተዳዳሪ ና የገጠር ወረዳ አስተዳደርና ፀጥታ ፅ/ቤት ሀላፊ መንገሻ ሞላ ዛሬ ራያ ቆቦ ሮቢት በጥይት ተገድለዋል ። አመራሮቹ ከሰሜን ወሎ ወልድያ ለስራ ጉዳይ ሂደ...
01/06/2020

አሳዛኝ ዜና
የራያ ቆቦ ዋና አስተዳዳሪ ና የገጠር ወረዳ አስተዳደርና ፀጥታ ፅ/ቤት ሀላፊ መንገሻ ሞላ ዛሬ ራያ ቆቦ ሮቢት በጥይት ተገድለዋል ። አመራሮቹ ከሰሜን ወሎ ወልድያ ለስራ ጉዳይ ሂደው ሲመለሱ መንጀሎ ከተባለ ቦታ ላይ ትርፍ የጫነ ባጃጅ በማግኘታቸው ከመኪና ወርደው ለምን ትርፍ ትጭናለህ ብለው በሚያነጋግሩበት ወቅት ከባጃጁ ውስጥ የነበረ ተሳፋሪ በያዘው መሳሪያ እንደገደላቸው ነው የደረሰኝ መረጃ ።
የአመራሮቹም አስከሬን በቆቦ ካቶሊክ ገዳም ሲስተሮች ህክምና ጣቢያ ለምርመራ ገብቷል። የዚህን ጉዳይ ዝርዝር ተጨማሪ መረጃ ተከታትለን እናቀርባለን ነፍስ ይማር

29/05/2020

የሃይማኖት በዳዳ ገዳይ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገለጸ
********************
በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የተገደለችሁ የወጣት ሃይማኖት በዳዳ ገዳይ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ፡፡
የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪ የሆነውና በ20ዎቹ እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ ደግነት ወርቁ የተባለ ወጣት ነው የ27 ዓመቷን ሃይማኖት በዳዳ ሕይወት ያጠፋው ብሏል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፡፡
ትናንት ምሽት 1 ሰዓት ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት ባካሄደው ክትትል ነው በቁጥጥር ስር የዋለው፡፡
ቀን ከሌሊት በተካሄደው በዚህ ክትትል የተያዘው ወጣቱ ደግነት ወርቁ ከሟች ጋር ምንም ዓይነት ትውውቅ እንዳልነበራቸው ትናንት እስከ እኩለ ሌሊት በተደረገ ምርመራ የወንጀሉን ዝርዝር ለፖሊስ አስረድቷል፡፡
ግለሰቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪ እንደነበርና የኤች አይ ቪ ኤድስ መድኃኒት ለማግኘት ምርምር ላይ ስለሆንኩ የጥቁር አንበሳ ሐኪሞች ይረዱኝ በማለት ወደ ግቢው በተለያዩ ጊዜያት ይመላለስ እንደነበር ዘርዝሯል፡፡
ከዚያም በግንቦት 17 ቀን 2012 እንደልማዱ ለዚሁ ጉዳይ እንደመጣ ገንዘብ እንደተቸገረና ቢላዋ ይዞ በግቢው ውስጥ ከሚገኙ ቢሮዎች በአንዱ ላፕቶፕብወይም ሞባይል ካገኘ ሰርቆ ሽጦ ለመጠቀም ሲዟዟር የሟች ክፍል ክፍት በመሆኑ መግባቱን አስረድቷል፡፡
ሟች ሞባይሏን እንድትሰጠው ጠይቋት እምቢ ስትለው መታገላቸውንና ከዚያም በያዘው ስለት ወግቷት ንብረቱን ይዞ መውጣቱን ተናግሯል፡፡
ፖሊስ ከሟች ጋር የቅርብ ግንኙነት የነበራቸው 12 ተጠርጣሪዎችን ይዞብተጨማሪ ምርመራ ማድረጉን የግድያ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክቶሬት ለኢቲቪ ገልጿል፡፡
ለፖሊስ ምርመራ ትልቅ አቅም የሆነው የሟች ወላጅ አባት ከሳምንት በፊት ለልጃቸው የሰጧት የ5 ሺ ብር ቼክ ነው፡፡
ገዳዩ በወቅቱ የሟችን ላፕቶፕና ሞባይል ፓስፖርት መታወቂያና ይህንን ቼክ ወስዶ ስለነበር ቼኩን የካ አካባቢ በአንድ ባጃጅ ተሳፍሮ አሽከርካሪውን መታወቂያ ስላልያዝኩ በአንተ መታወቂያ ይህንን ብር አውጣልኝ ብሎት የባጃጅ ሹፌርም መልኩን አስተውሎ ስለነበር ምርመራው ከዚህ እንደጀመረ ፖሊስ
ገልጿል፡
ኮሚሽኑ በወቅቱ የሆስፒታሉ ሴኩሪቲ ካሜራ አፕዴት ሳይደረግ ከአገልግሎት ውጪ መሆኑንና የጥበቃ ሰራተኞችም ቢላዋ ተይዞ እስከሚገባ ፍተሻቸውብአጋላጭ መሆኑንም ጠቁሟል፡፡

አሁን በስራ ላይ ያለውን የገንዘብ ኖት እንዲለውጥ የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበርለመንግስት መጠየቁን አስታውቋል፡፡ ማህበሩም በአሁኑ ወቅት ከ 113 ቢሊዮን ብር በላይ ከባንክ ስርዓቱ ውጭ መሆኑን...
20/05/2020

አሁን በስራ ላይ ያለውን የገንዘብ ኖት እንዲለውጥ የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር
ለመንግስት መጠየቁን አስታውቋል፡፡ ማህበሩም በአሁኑ ወቅት ከ 113 ቢሊዮን ብር በላይ ከባንክ ስርዓቱ ውጭ መሆኑን አስታውቋል፡፡
Capital Magazine
ኣዳዲስ ና ፈጣን መረጃ እንዲደርስዎት ፔጁን ይደዱ like

20/05/2020

ትራምፕ አሜሪካ በቫይረሱ በተያዙ ሰዎች ቁጥር ቀዳሚ መሆኗ 'ክብር' ነው አሉ
የአሜሪካው ፕሬዝዳነት ዶናልድ ትራምፕ አገራቸው በኮሮናቫይረስ መያዛቸው በተረጋገጡ ሰዎች ብዛት ከዓለም ቀዳሚ መሆኗ "ክብር" ሊያሰጣት እንደሚገባ
ተናገሩ።
ዋይት ሐውስ ውስጥ በሰጡት መግለጫ ላይ "ይህንን ነገር በተለየ መልኩ ነው የምመለከተው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ "የተገኘው ውጤት እንደ ጥሩ ነገር ነው የማየው። ምክንያቱም ይህ የምናደርገው ምርመራ ከሁሉም የተሻለ መሆኑን ያሳይል" ብለዋል።
የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ በሚያወጣው መረጃ መሰረት በአሜሪካ በአሁኑ ጊዜ 1.5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ቫይረሱ የተገኘባቸው ሲሆን 92 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ በወረርሽኙ ህይወታቸውን አጥተዋል።
የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአሜሪካ ከተከሰተ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰኞ ዕለት ባካሄዱት የካቢኔ ስብሰባቸውን ያካሄዱት ፕሬዝዳንቱ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት አገራቸው በበሽታው በተያዙ ሰዎች ቁጥር ቀዳሚ የሆነችው ከየትኛውም አገር በበለጠ ምርመራ በማድረጓ መሆኑን አመልክተዋል።
ጨምረውም "በርካታ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ሲኖረን በአንድ መልኩ እንደ መጥፎ ነገር አላየውም ምክንያቱም ምርመራችን የተሻለ መሆኑን ስለሚያመለክት" ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጨምረውም የተገኘው ውጤትን "እኔ እንደ ክብር ምልክት ነው የማየው። በአውነትም የከብር ምልክት ነው። የተገኘው ውጤት በመመርመር እና በተለያዩ የህክምና መስኮች ላይ የተሰማሩት ባለሙያዎች ላከናወኑት ሥራ የተገኘ ውጤት ነው" ብለዋል።
የተቀናቃኛቸው ዲሞክራቲክ ፓርቲ ብሔራዊ ኮሚቴ ግን ከሪፐብሊካን ፓርቲ የመጡትን ፕሬዝዳንት በዚህ ንግግራቸው ተችቷቸዋል።
ፓርቲው በፕዊትር ገጹ ላይ እንዳሰፈረው በአሜሪካ 1.5 ሚሊዮን የኮቪድ-19
ህሙማን መገኘታቸው የሚያስከብር ሳይሆን "የአመራሩን ፍጹም ውድቀት"
የሚያመለክት ነው ብሏል።
የአሜሪካ መንግሥት የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል ባወጣው መረጃ መሰረት በመላው አገሪቱ በ12.6 ሚሊዮን ሰዎች ላይ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ተደርጓል።
BBC

20/05/2020

# Update # Covid19 # ትግራይ # ግንቦት_12
ሕዘውን ካብ ጁቡቲ መፂኡ ኣብ መወሸቢ ዘነበረ ሹፌር ኮሮና ቫይረስ ተረኪብዋ ኣሎ::እዚ ሲዒቡ ድማ ብቲ ቫይረስ ዝተለከፉ ሰባት 13 በፂሖም ኣለው::
ብጥይት ተወቂዑ ኣብ icu ዝነበረ ሓውና ፅቡቅ
ለውጢ ስለዘርአየ ካብ icu ወፂኡ ኣብ ደቂሱ ሕክምና ዝከታተለሉ ክፈሊ ኣትዩ ኣሎ::
(በኣካል ሕዚ ባዕለይ ሪኤዬ ኣለኩ)
# ሕዝውን ንጠንቀቅ
# ናይ ሕሾት ዜና ካም ምስርጫው ንቆጠብ
— with Rigat Bishaw and 2 others .

20/05/2020
20/05/2020

ሓበሬታ!
መንግስቲ ኢትዮጵያ ሓድሽ ናይ ገንዘብ ገደብ ኣዊጁ ኣሎ:: ብዙይ መሰረት ዝኮነ ግለሰብ ካብ ባንኪ ብመዓልቲ 100ሸሕ ጥራሕ ኣብ ውሽጢ ወርሒ ግን ልዕሊ 500ሺሕ ከውፅእ ኣይክእልን:: ንነጋዳይ ኣብ ምዓልቲ 200 ሽሕ ዘውፅእ ዝክእል እንትከውን ኣብ ወርሒ ግን ልዕሊ 1ሚልዮን ምውፃእ ኣይክኣልን::

19/05/2020

ካብ ጁቡቲ መጽዩ ኣብ መወሸቢ ዝነበረ ሰብ ብ ኮረና ምትሓዙ ተረጋጎጹ ኣሎ
ንጠንቀቅ, ሰላምታና ብሩሑቅ,ኢድና ንተሓጸብ

ሓበሬታ''''''''''''''''''ካብ ዓዲግራት ናብ ዓድዋ ዝወስድ መንገዲ ኣብ ከባቢ ዓሎቃ ( ሙጉላት )ዓብዪ ደንጎላ ፀዲፉ መንገዲ ተዓፅዩ ሹፌራት መካይን መሕለፊ ሲኢንና ይብሉኣለዉ ። ዝ...
19/05/2020

ሓበሬታ
''''''''''''''''''
ካብ ዓዲግራት ናብ ዓድዋ ዝወስድ መንገዲ ኣብ ከባቢ ዓሎቃ ( ሙጉላት )
ዓብዪ ደንጎላ ፀዲፉ መንገዲ ተዓፅዩ ሹፌራት መካይን መሕለፊ ሲኢንና ይብሉ
ኣለዉ ። ዝምልከተኩም ኣካላት ምትሕብባር ንኽትገብሩ ንላቦ ።
11/09/2012 ዓ.ም

18/05/2020

ግዕዝ ሚዲያ ድምፂ ውፁዕ ህዝቢ !!
ፍትዋት ተኸታተልቲ ግዕዝ ሚዲያ እዚ ሚዲያ ንሓደ ዓመት ተዓፅዩ ዝፀንሐ እንትኸውን ኣብ ቀረባ እዋን ሓቃውን ሚዛናውን ሓበሬታ ሒዝና ናባኹም ክንመፅእ ኢና።
ግዕዝ ሚዲያ ንቐዳምነት

Address

Mekelle

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Geez Media ግእጽ ሚድያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share