Halaale Media Network / ሀላሌ ሚዲያ ኔትወርክ

Halaale Media Network / ሀላሌ ሚዲያ ኔትወርክ የሚዲያ እና የፕሮዳክሽን ድርጅት።

አቶ ማራዶና ዘለቀ በሀዋሳ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሃላፊ እንደመሆናቸው፣ የፓርቲውን ዘለቄታዊነት እና የቅቡልነት ስርዓት በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። በተጨማሪም፣ የህዝብ...
30/01/2025

አቶ ማራዶና ዘለቀ በሀዋሳ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሃላፊ እንደመሆናቸው፣ የፓርቲውን ዘለቄታዊነት እና የቅቡልነት ስርዓት በማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል።

በተጨማሪም፣ የህዝብን ፍላጎት በተግባር የመሟላት፣ የዴሞክራሲ ባህልን የመዳበር፣ እና የፖለቲካ መረጋጋትን የማስፈን ባለሞያዊ ችሎታቸው በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ አጽናኝነት እንዲያተረፍ አስችሏቸዋል።

# # # **1. የፓርቲ አስተዳደር እና ስራ አፈጻጸም**
አቶ ማራዶና የፓርቲውን ውጤታማነት በማረጋገጥ ከአለም ከሚገኙ ታዋቂ ፖለቲከኞች ጋር ሊወዳደሩ ይችላሉ። ለምሳሌ፣ የሲንጋፖር ቀደምት መሪ ሊ ኩዋን ዩ፣ የሀገራቸውን ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ልማት በቅልጥፍና የማስተዳደር ችሎታቸው ታዋቂ ነበር። በተመሳሳይ፣ አቶ ማራዶና የፓርቲውን ዘርፎች በስርዓተ-ፍላጎት አሳታፎ የማስፈጸም አቅም ይህንን ሞዴል ያንጸባርቃል።

# # # **2. የህዝብ ፍላጎት አሟላት እና ተግባራዊ አመራር**
በጃኬንዳ አርደርን እንደምሳሌ ከወሰድን፣ በኒው ዚላንድ የተከሰተውን የተፈጥሮ አደጋ እና የበሽታ ሁኔታ በምትቆጣጠርበት ወቅት ያሳየችው ተግባራዊ እና ርኅራኄ ያለው አመራር ታዋቂ ነች። አቶ ማራዶናም በህዝብ ጥያቄ ላይ በመተማመን፣ ቀልጣፋ መልሶችን በመስጠት የዜጎችን ታማኝነት አስገኝተዋል።

# # # **3. የዴሞክራሲ ባህልን ማጎልበት**
አቶ ማራዶና የሚያሳዩት አመራር ከኔልሰን ማንዴላ ጋር ሊነጻጸር ይችላል። ማንዴላ በደቡብ አፍሪካ የዴሞክራሲ ሽግግርን በሰላማዊ እና አንድነት ያለው አቀራረብ ሲያስተዳድሩ ይታወቃሉ። በተመሳሳይ፣ አቶ ማራዶና የሀዋሳን ፖለቲካዊ መረጋጋት በመርህ የተጠናከረ የዴሞክራሲ ባህል በማሳደግ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።

# # # **4. አለም አቀፍ ትንታኔ**
የአቶ ማራዶና አመራር የሚያስደንቀው በብቃት፣ በተግባራዊነት፣ እና በህዝብ ግንኙነት ውስጥ ያለው ሚዛናዊነት ነው። እንደ አሜሪካዊው ፕሬዝዳንት ፍራንክሊን ሮዘቬልት በ1930ዎቹ የኢኮኖሚ ቀውስ ወቅት ያሳዩትን "አዲስ ስምምነት" ፖሊሲ የሚነሳ ሲሆን፣ አቶ ማራዶናም የህዝብን ተስፋ በማሳደግ እና በተግባራዊ ለውጦች ላይ ትኩረት በማድረግ ተመሳሳይ ውጤታማነት አሳይተዋል።

አቶ ማራዶና ዘለቀ በህዝብ፣ በፓርቲ፣ እና በዴሞክራሲያዊ ሂደቶች ውስጥ ያላቸው አስተዋጽኦ በኢትዮጵያ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ውጤታማ የሚባሉትን ስለሆነ ጀግናው በርታልን።

እንደ አለም አቀፍ መሪዎች ሁሉ፣ የእርሳቸው ስኬት በተግባራዊ አመራር፣ በህዝብ ግንኙነት፣ እና በርኅራኄ የተገነባ ነው።

የህዝብ ልጅ የህዝብ ተወካይ ነው።

የተከበሩ አቶ አብርሃም ማርሻሎ በሲዳማ ክልል የፖለቲካ ንቅናቄን በመምራት ረገድ ላቅ ያለ ጥበብና ብቃት ያሳዩ ጀግና መሪ ናቸው። በፖለቲካዊ አመራራቸው በርካታ ስኬቶችን ብሎም ድሎችን በማስመ...
21/01/2025

የተከበሩ አቶ አብርሃም ማርሻሎ በሲዳማ ክልል የፖለቲካ ንቅናቄን በመምራት ረገድ ላቅ ያለ ጥበብና ብቃት ያሳዩ ጀግና መሪ ናቸው።

በፖለቲካዊ አመራራቸው በርካታ ስኬቶችን ብሎም ድሎችን በማስመዝገብ ለክልሉ ዕድገትና ለህዝቡ ደህንነት የማይተካ አስተዋጽኦ አድርገዋል። በክልሉ ውስጥም ብልፅግናዊ ልዕልናን ከፍ ማድረግ ችለዋል።

አቶ አብርሃም ማርሻሎ በፖለቲካዊ ንቅናቄያቸው የሚመሩትን ህዝብ ተግባር እና በላቀ ብልህነት፤ አመራርነት፤ ሃገርን እና ህዝብን ለማገልገል ባላቸው ልዩ ፍላጎት አመርቂ ውጤት ያስመዘገቡ ብሎም ህዝብ በመንግስት ላይ ያለውን ተስፋን እንዲለመልም በማድረግ ረገድ የሚደነቁ መሪ ናቸው።

በክልሉ የሚገኙ ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ሲዳማ የጋራ ቤታችን ናት ብለው ሰርተው ተረጋግተው ተዋደውና ተዋህደው እንዲኖሩ ከሌሎች ከክልሉ ወንድም/እህት አመራሮች ጋር በመሆን ያላሰለስ ጥረት አድርገዋል እያደረጉም ይገኛሉ።

በተለይም አቶ አብርሃም ማርሻሎ የለውጡ ሃዋሪያ ናቸው። ቢባልም ክብር አቶ አብርሃም ለውጡን በማምጣታቸው ብቻ ሳይሆን ለውጡን ለማስቀጠል የሚከፍሉት መስዋዕትነት የህይወት በመሆኑ በተለይ በሲዳማ ህዝብ ልብ ውስጥ ክብር አቶ አብርሃም የለውጡ ሃዋሪያ ብቻ ሳይሆን፤ የለውጡ አባትም ተብለው ይገለፃሉ።

በክልሉ ውስጥ መረጋጋትን በማስፈንና የህዝቡን አንድነት በማጠናከር ረገድ ያላቸው ሚና ከፍተኛ የሆነው አቶ አብርሃም ፓርቲያቸው ብልፅግና በክልሉ የዲሞክራሲነትን አድማሱን እና ምህዳሩን በማስፋት በክልሉ ፓርቲውን ሉዓላዊ ያደረጉት ሲሆን የተቃዋሚ ፓርቲዎች ቀልብ ስበው ተቃውሞዎቸው መሰረት ላይ እና ስሌት ላይ እንዲሆን እንጂ፤ ንዴት እና ስሜት ላይ እንዳይሆን ስራዎችን በመስራት ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ በሃሳብ እና በርዕዮት የሚመራ ፖርቲ እየመሩ (የተቃዋሚ ፓርቲዎችም) እንቅስቃሴዎች እንዲህው እንዲሆኑ እና በሰላም ሀሳባቸውን እንዲያንፀባርቁ አድርገዋል።

እኚህ ብርቱ መሪ፣ የሲዳማ ህዝብ የፖለቲካ ንቅናቄን በብቃት በመምራት የሚታወቁ ሲሆን ለክልሉ እድገትና፤ ለህዝቡ ብልጽግና የማይታክት ጥረት ያደርጋሉ እያደረጉም ይገኛሉ።

ጥረታቸውም ግብ የመታ የህዝብ የልብ ትርታ ያገኘበት መሆኑ ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ በህዝብ ዘንድ በልዩ ሞገስ እና ክብር እንዲታዩ አስችሏል።

የአመራርነት ብቃታቸውም ምስክር የሆኑ በርካታ የቀድሞ የደቡብ ክልል አመራር እና ሰራተኞች ብሎም የአሁኑ የሲዳማ ክልል እና የለውጡ አመራሮች ክብር አቶ አብርሃም ሲገልፁ ልዩና ብልህ ሰው ቃላትን ተንትኖ ማፅረፅ የሚችል ይሉታል። ሌሎች ደግሞ አቶ አብርሃም ተግባር ሰው ነው ብለውም ይገልፁታል። በክልሉ ውስጥ የተንሰራፋ ያለው ዲሞክራሲ፤ ሰላም፤ ልማት፤ አንድነት ሁሉ በብልፅግናዊ ፊት አውራሪነትን መሰረት የሚፈጸም ሃገር የቁርጥ ቀን ልጅ ይሉታል።

ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ህዝብን በታማኝነትና በትጋት የሚያገለግል ትልቅ መሪ ነው ስንል በምክንያት ነዉ።ህዝባዊ መሪ ነው። በትልቅነቱ ታላቁ ህዝባችንን በእዉቀትና በብልሃት ብሎም በክህሎት...
16/01/2025

ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ህዝብን በታማኝነትና በትጋት የሚያገለግል ትልቅ መሪ ነው ስንል በምክንያት ነዉ።

ህዝባዊ መሪ ነው። በትልቅነቱ ታላቁ ህዝባችንን በእዉቀትና በብልሃት ብሎም በክህሎት የሚመራ ህዝብን የሚያማክል ሥራ ቀን ከሌት በታደሰ አስተሳሰብ የሚሰራ ሀገርን በፅናት እና በሉዓላዊ ዲሞክራሲ ለማቆየት ሁለገብ ሥራዎችን የሚከውን ጀግና ሰው ነው።

ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ በስራው ህዝባዊነቱን የሚያረጋግጥ ለህዝቡ እርካታ እና ዕፎይታ ወደር የለሽ ልፋትን የሚለፋ የህዝብ ልጅ ነዉ።

ሀገራዊ ተልዕኮን ከግብ ለማድረስ ሲዳማ ክልልን የዲሞክራሲ እና የብልፅግና ቀጠና እና ቀለም ተብላ እንድትጠራ ለሃገርችን ሉዓላዊነት የሚተጋ ለሁለንተናዊ የህዝባችንን ኑሮ ምቹነትና ጤናማነት የሚጨነቅ ግላዊ ሳይሆን ህዝባዊ፤ ውስናዊ ሳይሆን ብዙሃዊነት ያረጋገጠ ምርጥ መሪ ነው።

ሀገር ወዳድ ዜጋን በማፍራት ለሀገር ክብርና ለህዝቦች ሁለንተናዊ የእኩልነትና የልማት ተሳትፎ የጋራ ተጠቃሚነት የሚተጋ ሰው ነው።

የብሔር ብሔረሰቦች ነፃነትን በማስፈን በሃገራቸው የማይደራደሩ ጀግኖችን ሰብስቦ ያበቃ ሰው ሲሆን ከወጣትነት ጀምሮ ከወረዳ እስከ ክልል በተለያየ የአመራርነት ቦታዎች በጥበብና በብስለት ብሎም በእዉቀትና በክህሎት ሀገርን ከታች እስከ እላይ የመራ የዘመናች ድንቅ ሰው አብርሃም ማርሻሎ ነው።

በሀገር ፍቅር የተጠማን ዜጋ በማፍራት፤ የሠላም አምባሳደር ወጣቶችን በማደራጀት፤ ዘርፈ ብዙ ሥራ በማሰራትና የወጣቶች የልብ ጎደኛ፤ ለሥራ ፈላጊ ዜጎች የስራ ዕድል አመቻችቶ ቀልጣፋ ወጣቶችን ለሀገር ኩራት በማብቃት የተሰጠዉንና የጣለበትን ሃላፊነት በብቃት የሚወጣ ድንቅ ሀገር ወዳድ የሆነ ኢትዮጵያዊ መሪ ነው።

ከአጎራባች ክልሎች እና ዞኖች ጋር ሠላማዊ የዲሞክራሲ ባህልን የጋራ ብልፅግና እንዲፈጠር የተጋ ለብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት እና ነፃነት መረጋገጥ የሰራ የዘመናዊ ፖለቲካ አሰራርን የሚከተል ትልቅ ትንሽ የሚያከብር ከሁሉ የተወዳጀ መሪ ነው።

በፈጠነ ተደራሽነት ፤ በሰከነ ንግግር የሚታወቁት ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ የግጭት ሰባሪ የሰላም ምህዳር እና የዲሞክራሲ ባህል ማህንዲስ የእውነት ለእውነት የቆመ በሀቅ እና ፈሪሃ እግዚአብሔር በተሞላ በቅን ልብ ህዝብን የሚያገለግል ድንቅ ሰው ነው።

ኢትዮጵያዊነትን ለማፍረስ የሚሰሩትን ከልክ አብዝቶ የሚያወግዝ ፍፁም በኢትዮጵያነቱን የሚኮራ ኢትዮጲያዊነቱን የሚወድ ህዝብን በማታለል ጠባብ ጎሳኝነትን እና ወገንተኝነትን ተላብሰው ለሚመላለሱ ጭልምተኞችን የሚሰባብርን የአንድነት አባት የኢትዮጵያነት ጠባቂ ናቸው።

የስራውን ስኬት በማሳየት በህዝብ የተወደደ ጨለምተኛ ጠባብ ጎሰኝኞችን በአስተማሪ ምክር እና ፍቅር የመለሰ የዲሞክራሲ አባት ነው።

ጠባብ ጎሰኝነት እና ጠባብ ብሔርተኝነት ከኢትዮጵያዊነት እንደማይበልጥ ዘውትር መናገር ቅድምት ተግባራችን የሆኑት ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ኢትዮጲያን በኢትዮጵያዊነት አቅም በመምራት እና በማብልፀግ መሆኑ ታሪክ እየሰራ ይገኛል።

ክብር አቶ አብርሃም ማርሻሎ የህዝብ ልጅ እና የኢትዮያዊነት ካባ ተዋዳጅ መልካም መሪ ነው።

02/11/2024
በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ወንዶገነት ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ህንፃ ግንባታ በዛሬው እለት በይፋ ተጀምሯል።በህንፃው ግንባታ ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ የሰ...
23/10/2024

በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ወንዶገነት ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ህንፃ ግንባታ በዛሬው እለት በይፋ ተጀምሯል።

በህንፃው ግንባታ ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፃዲቁ ባጢሶ የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አበበ ይታደጉ እና የከተማዉ አመራሮች እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

 ከዚህ በፊት በተወዳጅ ስራዎቻቸዉ የምናዉቃቸዉ እዉቅ የሲዳምኛ ሙዚቃ አቀንቃኞች አርቲስት ሹሙሎ ሹንዴ ፣ አርቲስት ትብለጥ ተከስተ እና አርቲስት መለሰ ዌና በጋራ በመሆን Ninkeho የተሰኘ...
07/09/2024



ከዚህ በፊት በተወዳጅ ስራዎቻቸዉ የምናዉቃቸዉ እዉቅ የሲዳምኛ ሙዚቃ አቀንቃኞች አርቲስት ሹሙሎ ሹንዴ ፣ አርቲስት ትብለጥ ተከስተ እና አርቲስት መለሰ ዌና በጋራ በመሆን Ninkeho የተሰኘ ምርጥ የሲዳምኛ ሙዚቃ ይዘዉ ቀርበዉልናል።

እኛም በተወዳጅ አርቲስቶቻችን የተሰራዉን Ninkeho የተሰኘዉን ሙዚቃ ዛሬ ከጠዋቱ 5:00 ሰአት በሲዳምኛ ሙዚቃዎች መገኛ Sidaama Music Tube የቴሌግራም ቻናል ላይ ይዘንላችሁ እንቀርባለን።

Share በማድረግ ለወዳጆ ያድርሱ ቻናላችንን ያልተቀላቀላችሁ ከታች የሚገኘዉን ሊንክ በመንካት ይቀላቀሉ።

👉 T.me/SidaamaMusic_Tube

"ሰሞኑ በሲዳማ ቡና የደጋፊዎች ማህበር ስራ አስፈፃሚዎች መሀከል በተፈጠረው አለመግባባት/ግጭት በግሌ አዝኛለሁ" "ለ2017 ዓ.ም የዉድድር ዘመን በተጫዋቾች ዝዉዉርም ሆነ በተለያዩ መንገዶች ...
04/08/2024

"ሰሞኑ በሲዳማ ቡና የደጋፊዎች ማህበር ስራ አስፈፃሚዎች መሀከል በተፈጠረው አለመግባባት/ግጭት በግሌ አዝኛለሁ"

"ለ2017 ዓ.ም የዉድድር ዘመን በተጫዋቾች ዝዉዉርም ሆነ በተለያዩ መንገዶች ቅድመ ዝግጅት እያደረግን ባለንበት ወቅት ይህ መሆኑ የክለቡን ማህበረሰብ ያሳዘነ ጉዳይ ሲሆን ሁለቱንም አካላት በቅርቡ በመሰብሰብ አወያይቼ ወደመፍትሄዉ የምናመራ ይሆናል። ከእዛ በስተቀር የትኛውም አካል የክለቡን ስም ከሚያጎድፍ ማንኛውም ተግባር እንዲቆጠብ አሳስባለሁ"

"ሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ የጥቂት ግለሰቦች ሳይሆን የመላው የሲዳማ ህዝብ ነዉ። እኛም በተሰጠን ኃላፊነት ለክለቡ የሚጠቅሙ በርካታ የሪፎርም ስራዎችን እየሰራን እንደምንገኝ እየገለፅኩ በቅርቡ ለክለቡ ደጋፊዎች ይፋ የምናደርግ ይሆናል"

"ከእንግዲህ ማንም በክለቡ ስም የግሉን ፍላጎት የሚያሟላበት አሰራር በእኔ ዘመን የማይኖር ሲሆን ለክለቡ የማይበጁ መወገድ ያለባቸዉን በማስወገድ መቀጠል የሚገባቸዉን በማስቀጠል ህጋዊ አሰራር የተከተለ መንገድ ብቻ በመተግበር ለሲዳማ ቡና ከፍታ የምንሰራ ይሆናል። ለዚህም የክለቡ ደጋፊ ከየትኛውም ጊዜ በላይ ከክለቡ ጎን በመሆን ለሲዳማ ቡና በሚበጁ ተግባራት ላይ እንዲሳተፍ ስል አደራ እላለሁ"

በግል ጉዳይ በአሁን ሰአት ከሀገር ዉጪ ከሚገኘዉ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ የቦርድ ሰብሳቢና የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ከሆነው ከአቶ Alemayehu Timotewos ጋር በስልክ ባደረኩት ቆይታ ስለ ክለቡ ካነሳቸዉ ነጥቦች ዉስጥ ቀንጨብጨብ አድርጌ ያቀረብኩት ነዉ።

✍️ Biruk Hanchacha

23/07/2024
የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ለታዳጊዎች የሚሆን የስፖርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ።የሲዳማ ክልል ርዕስ መስተዳድር የተከበሩ አቶ ደስታ ሌዳሞ ለታዳጊ...
20/07/2024

የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ለታዳጊዎች የሚሆን የስፖርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ።

የሲዳማ ክልል ርዕስ መስተዳድር የተከበሩ አቶ ደስታ ሌዳሞ ለታዳጊ ስፖርተኞች የስፖርት ቁሳቁስ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን ከፕሬዝዳንቱ የተበረከቱትን የስፖርት ቁሳቁሶች የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ኃላፊ የተከበሩ አቶ ካሱ አሩሳ በትላንትናው እለት ፍፃሜዉን ባገኘው በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ሲካሄድ የሰነበተዉ የ2016 ዓ.ም የሲዳማ ክልል ከ15 እና 17 ዓመት በታች የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ ዉድድር ላይ ተገኝተዉ አበርክተዋል።

የክልሉ መንግስትም ሆነ የክልሉ ፕሬዝዳንት ለስፖርቱ ትኩረት በመስጠት እየሰሩ የሚገኙት ስራ ይበል የሚያሰኝ ሲሆን በብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ዉስጥ አልፎ የክልሉን እግር ኳስ በኢትዮጵያ ደረጃ ከፍ ብሎ እንዲደመጥ ካደረገዉ ከክልሉ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጎን በመሆን ይበልጡን በስፖርቱ ላይ ዘርፈብዙ ስራ እንደሚሰሩ እምነቴ ነዉ።

ከሌሎች የልማት ስራዎች ጎን ለጎን ለስፖርቱ እድገት ትኩረት ለሰጡት ለክልላችን መንግስት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ትልቅ አክብሮት እና ምስጋና አለኝ።

እንዲሁም ከፕሬዝዳንታችን ጎን በመሆን ለታዳጊዎች የድጋፍ ስራ ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከተዉ ለርዕስ መስተዳድር ጽ/ቤት ሀላፊ የተከበሩ አቶ Kassu Arussa ትልቅ አክብሮት እና ምስጋና አለኝ።

በተጨማሪም ለፌዴሬሽኑ እዚህ መድረስ ብዙ ሚና ለተጫወተዉ ለሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ አንበሴ አበበ እና አባላቶቹ ትልቅ አድናቆት እና ምስጋና አለኝ።

የርዕስ መስተዳደር ጽ/ቤት ለክልሉ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዘላቂ ድጋፍ እንደሚያደርግ እና የክልላችንን እግር ኳስ ትልቅ ደረጃ ላይ በተባበረ ክንድ እንደሚያደርሱት እምነቴ ነዉ።

በርቱልን !!🙏

✍️ Biruk Hanchacha

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች በነገዉ እለት ይከናወናሉ።በርካታ ሀገር አቀፍ ዉድድሮችን ተረክቦ በስኬት በሚያካሂደው በሲዳማ ክልል እግ...
13/06/2024

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች በነገዉ እለት ይከናወናሉ።

በርካታ ሀገር አቀፍ ዉድድሮችን ተረክቦ በስኬት በሚያካሂደው በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስተናጋጅነት በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች በነገዉ እለት በሀዋሳ አርተፊሻል ሜዳ ይካሄዳሉ።

በዚህም መሰረት ከጠዋቱ 3:00 ኢትዮ ኤሌትሪክ ከ መቻል እንዲሁም ከጠዋቱ 5:00 ሰአት ኢትዮጵያ ቡና ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታቸዉን የሚያካሂዱ ይሆናል።

በነገው እለት ብርቱ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ በሚጠበቀው የታዳጊዎች አጓጊ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ላይ ከፍተኛ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸዉ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በተገኙበት የሚካሄድ ሲሆን ይህን አጓጊ የእግር ኳስ ፍልሚያ በሀዋሳ ከተማ እና አከባቢዋ የምትገኙ የእግር ኳስ ቤተሰቦች መታችሁ እንድትመለከቱ ሲል የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥሪዉን እያስተላለፉ በተጨማሪም ይህንን የነገ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ተስፋዎች መፍለቂያ የሆነዉን ዉድድር በሀዋሳ ከተማ እና አከባቢዋ የምትገኙ አሰልጣኞች ፣ ኤጀንቶች ፣ ተጫዋቾች እና የስፖርት ጋዜጠኞች በሀዋሳ አርተፊሻል ሜዳ በጠዋቱ በመገኘት እንድትታደሙ ሲል መልእክቱን ያስተላልፋል።



T.me/SidamaFootballFederation

መልካም ዜና በሲዳማ ክልል ለሚትገኙ ከ15 ዓመት በታች የእግር ኳስ ፕሮጀክቶች የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በየአመቱ የተለያዩ የውስጥ ውድድሮችን እንደሚያከናውን ይታወቃል እያደረገም ይ...
08/06/2024

መልካም ዜና በሲዳማ ክልል ለሚትገኙ ከ15 ዓመት በታች የእግር ኳስ ፕሮጀክቶች

የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በየአመቱ የተለያዩ የውስጥ ውድድሮችን እንደሚያከናውን ይታወቃል እያደረገም ይገኛል።ዘንድሮ ለማድረግ ካቀዳቸው ውድድሮች ውስጥ አንዱ በሲዳማ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ከ15 ዓመት በታች ለሆኑ በሴትም እና በወንድም ፕርጀክቶች የእግር ኳስ ውድድር ማዘጋጀት ሲሆን ፌዴሬሽኑ ከሲዳማ ክልል ስፖርት ኮምሽን ጋር በመተባበር ከፊታችን ባሉት ሳምንታት ውስጥ ለማስጀመር ዝግጅቱን ጨርሷል።

በመሆኑም በክልሉ ውስጥ የሚትገኙ ከ15 ዓመት በታች የወንድና የሴት ፕሮጀክቶች ፌዴሬሽኑ በቅርብ ቀን ውድድር ማካሄድ ስለሚጀምር በቂ ዝግጅት ያደረጋችሁ፣ለውድድሩ ትጥቅ የሚታሟሉ፣ እንዲሁም እስከዛሬ እየሰራችሁ የቆያችሁትን ሪፖርት ማቅረብ የሚትችሉ ከሰኞ ሰኔ 3 ጀምሮ በፌዴሬሽኑ ፅ/ቤት በመገኘት እንዲትመዘገቡ ፌዴሬሽኑ ያሳውቃል።እንዲሁም መመዝገቢያ እና መወዳደሪያ በነፃ መሆኑን እናሳውቃለን።

© የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የሲዳማ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር አራርሶ ገረመው ላይ ቅሬታ በማቅረብ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ አሳስቧል።ሀላሌ ሚዲያ ኔትወርክ ግ...
06/06/2024

የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የሲዳማ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር አራርሶ ገረመው ላይ ቅሬታ በማቅረብ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ አሳስቧል።

ሀላሌ ሚዲያ ኔትወርክ
ግንቦት 29/2016 ዓ.ም ሀዋሳ ፣ ሲዳማ ፣ ኢትዮጵያ

የሲዳማ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር አራርሶ ገረመው አፊኒ የተሰኘ መፅሀፍ ፅፈዉ እንዳሳተሙ እና ይህም መፅሀፋቸዉ በኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እንደተመዘገበላቸዉ በትላንትናው እለት በማህበራዊ ትስስር ገፃቸዉ ገልፀዉ የነበረ ሲሆን በገለፃቸዉም በአፊኒ መፅሀፋቸዉ ላይ የፃፉት የአፊኒ ስርዓት ፈጣሪ ተደርገዉ በኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እንደተመዘገቡም አክለዉ ገልፀዉ ነበር።

ሆኖም ግን በዛሬው እለት የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ይዞታ በወጣው መግለጫ "አፊኒ -የሲዳማ ብሔር ድንቅ ባህላዊ ዕሴት ነው እንጂ የግለሰቦች የፈጠራ ውጤት አይደለም !" ያለ ሲሆን አክሎም "አፊኒ - የሲዳማ ብሔር ለዘመናት ግጭቶችን ለመፍታት፣ ዕርቅን ለማውረድ ፣ ማህበራዊ ፊትህን ለማስፈን ከጥንት ዘመን ጀምሮ ሲገለገልበት የቆዬ ባህላዊ እሴት: የማህበረሰቡ የፈጠራ ውጤት እና ድንቅ የሀገር በቀል ዕውቀት እንጂ የአንድ ግለሰብ የፈጠራ ውጤት አይደለም ፣ልሆንም አይችልም::" ብሏል። በተጨማሪም በመግለጫው "ይኸን ድንቅ ባህል ማንም ቢሆን ስለ አፊኒ መጽሐፍ ሊጽፍ፣ሊመራመር፣ሊተውን......ወዘተ ይችላል ፤ ይህ ተግባር ዕሴቱን ለመጭው ትውልድ ለማስተላለፍ የበኩሉን ድርሻ ስለሚያበረክት የሚበረታታም ነው።" ያለ ሲሆን "ከዚህ ባለፈ ከጥንት ዘመን ጀምሮ ስወርድ ስዋረድ የመጣውን የብሔሩን የባህላዊ ዕሴት የኔ የፈጠራ ውጤት ነው ለማለት የሚችል አካል ፣ግለሰብ ወይንም ቡድን ካለ በየትኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የለሌው ድርጊት ነው።" ብሏል።

ቢሮዉ አክሎም "በመሆኑም የህዝቡን ዕሴትና ቅርስ የሆነውን "አፊኒ" ን በተመለከተ በማወቅም ይሁን በግንዛቤ ማጣት ከኢትዮዽያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የተሰጠው ዕውቅና እንዲታረም ቢሮው ጥብቅ ክትትል በማድረግ ውጤቱን ለሕዝብ የሚያሳውቅ ይሆናል::" ያለ ሲሆን "ይህ ካልሆነ ወይም በአስቸኳይ እርምት ካልተወሰደ ቢሮው በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን ሕጋዊ እርምጃ በመውሰድ የሕዝቡን የዕሴቱን ባለቤትነት መብት ለማስመለስ የሚገደድ መሆኑን ጭምር እንገልፃለን::" ብሏል።

ሀላሌ ሚዲያ ኔትወርክ በጉዳዩ ዙሪያ የሚኖሩ መረጃዎችን እየተከታተለ የሚያቀርብላችሁ መሆኑን ከወዲሁ ይገልፃል።


የእዉነት ድምፅ !!

Address

Hawassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halaale Media Network / ሀላሌ ሚዲያ ኔትወርክ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share