Harari Mass Media Agency

Harari Mass Media Agency Harari Mass Media Agency is a public media operating in Harar, Ethiopia.
ገፃችንን በመከተል ትኩስ ዜና እና መረጃዎችን ያገኛሉ።

22/04/2024
በኢፌዴሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዲኤታ የተመራ የልኡካን ቡድን በሀረሪ ክልል የሌማት ትሩፋትና የንግድ ስራዎችን ጎበኘ**************በኢፌዴሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር...
22/04/2024

በኢፌዴሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዲኤታ የተመራ የልኡካን ቡድን በሀረሪ ክልል የሌማት ትሩፋትና የንግድ ስራዎችን ጎበኘ
**************
በኢፌዴሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፍሰሃ ይታገሱ የተመራ የልኡካን ቡድን በሀረሪ ክልል በሌማት ትሩፋት መርሃግብር እና በንግድ ስራዎች እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ጎብኝቷል።

የኢፌዴሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፍሰሃ ይታገሱ እንዳሉት ምልከታው ነጋዴውና ተጠቃሚው የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ለይቶ ለመንግሥት ውሳኔ ለማቅረብና ለፖሊሲም የሚሆን ግብአት ለማሰባሰብ ነው ብለዋል።

ምልከታው በሪፖርት ከሚቀርበው በተጨማሪ መሬት ላይ በተጨባጭ አምራቹ፣ ነጋዴውና ተጠቃሚው ያሉበትን ሁኔታ ለመገምገም ያለመ ነው ብለዋል።

በዚህም በክልሉ በቅዳሜ ገበያ ምርትን በቀጥታ ለሸማቾች በማቅረብ ጥሩ እንቅስቃሴ መመልከታቸውን ጠቁመው በሃማሬሳ የምግብ ዘይት ፋብሪካ የሚቀርቡ ምርቶችንና ያሉ ችግሮችስ ምን ይመስላሉ የሚለውን እንደተመለከቱም ገልጸዋል።

እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት በተለይም ዋጋን ለማረጋጋት የሚያግዝ በመሆኑ ጅምር ስራዎችን ማጠናከርና ማስፋት ይገባል ብለዋል።

የሀረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ሸሪፍ ሙሜ በበኩላቸው እንዳሉት ገበያን ከማረጋጋት አኳያ በሌማት ትሩፋት እንዲሁም በሸማቾችና በዩኒየኖች አበረታች ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

እንዲሁም በበዓል ጊዜያት የሚፈጠሩ የዋጋ ጭማሪዎችን በመቆጣጠር አምራችና ሸማቾችን በቀጥታ በማህበራቶች በኩል እንዲገናኙ ይሰራል ብለዋል።

በጉብኝቱ በከተማዋ የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም እየተከናወኑ የሚገኙ የእንስሳት እርባታ፣ የቅዳሜ ገበያና የተለያዩ የሸማች ማህበራት ማከፋፈያዎች እና በንግድ ስራዎች ላይ ምልከታ ተደርጎባቸዋል።

14 / 08 / 2016

HTV:- Amharic News
21/04/2024

HTV:- Amharic News

Harari TV newsToday news Amharic news

የሀረር ከተማ የአካባቢ ፅዳትና የአረንጓዴ ልማት ስራ ላይ በትኩረት በመስራት የከተማዋን የቱሪዝም መስህብነቷን ለማሳደግ ሁሉም ባለድርሻ አካላቶች የበኩላቸውን አስተዋጾ ሊያደርግ እንደሚገባ ተ...
21/04/2024

የሀረር ከተማ የአካባቢ ፅዳትና የአረንጓዴ ልማት ስራ ላይ በትኩረት በመስራት የከተማዋን የቱሪዝም መስህብነቷን ለማሳደግ ሁሉም ባለድርሻ አካላቶች የበኩላቸውን አስተዋጾ ሊያደርግ እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡
***********************
የሀኪም ወረዳ ነዋሪዎች በከተማው አረንጓዴ ልማት መርሐ ግብር የተተከሉ ችግኞችን ተንከባክበዋል፡፡

ሐረር ከተማን ውብ ፅዱ፤ ለነዋሪዎችዋ እና ለቱሪስቶች ምቹ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ የሚገኝ ሲሆን በሀረሪ ክልል የሀኪም ወረዳ ነዋሪዎችም በከተማው አረንጓዴ ልማት መርሐ ግብር የተተከሉትን ችግኞች ተንከባክበዋል፡፡

የሀረር ከተማ ማዘጋጃ ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ኢሊያስ ዩኒስ ባለፉት አመታት በከተማ በዘርፉ በተሰራው ስራ አበረታች ለውጥ መምጣቱን ገልጸው ማዘጋጃ ቤቱ የመጣውን ለውጥ ለማስቀጠል በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሀኪም ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢብሳ አሊዪ እንደገለፁት በወረዳቸው በየሳምንቱ ሁለት ቀን የአካባቢ ፅዳትና ችግኞችን የመንከባከብ ስራ እንደሚያከናውኑ አውስተው በዛሬው እለትም ከሀማሬሳ እስከ አራተኛ ድረስ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከባቸውን ገልጸዋል፡፡

በሀኪም ወረዳ የተጀመረው የአካባቢ ፅዳት እና ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በዘላቂነት እንዲሰራ የከተማውን ውብ ፅዱና ለነዋሪዎች እና ለቱሪስቶች ምቹ እንዲሆን የማስቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት አበክረው እየሰሩ እንደሚገኙ በመግለፅ ግቡን ለማሳካት የሚመለከታቸ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በአካባቢ ፅዳት እና በከተማው አረንጓዴ ልማት የተተከሉትን ችግኞች የመንከባከብ ስራ ላይ የተሳተፉ የማህበረሰብ ክፍሎች በቀጣይም ስራውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

ዘጋቢ አብዲ ኡስማን
12 8 19

በዝናብ ወቅተ የሚመጣውን የትራፊክ አደጋ ለመከላከል  አሽከርካሪዎች የራሳቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ የሀረሪ ክልል መንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡****************...
21/04/2024

በዝናብ ወቅተ የሚመጣውን የትራፊክ አደጋ ለመከላከል አሽከርካሪዎች የራሳቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ የሀረሪ ክልል መንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡
*****************
ቢሮው በወቅቱ ሊመጣ የሚችለውን የትራፊክ አደጋን ቀድሞ ለመከላከል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላቶች ጋር ውይይት አካሄደዋል፡፡

ከፊታችን የሚመጣውን የክረምት ወቅት ከፍተኛ የዝናብ መጠን የሚዘንብበት መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሜትሮሎጂ ኤጀንሲ ያወጣው መረጃዎች ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሜትሮሎጂ ኤጀንሲ እንዳስታወቀው የዝናብ መጠኑ ከፍ ያለ ስለሆነ የተለያዩ የጎርፍ አደጋዎች ሊከሰቱ የሚችሉ ይህ ደግሞ በትራፊክ እንቅስቃሴ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ተፅእኖ ስለሚኖረው ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አስታውቋል፡፡

በሀረሪ ክልልም ይህ አደጋ ሊከሰት ከሚችልባቸው አካባቢዎች ውስጥ አንዱ በመሆኑ አደጋው እንዳይከሰት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል፡፡

ጉዳዩን አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት የሀረሪ ክልል መንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ ጠይባ አብደላ እንደገለፁት በክረምት ወቅት ሊከሰት የሚችለውን የትራፊክ አደጋ ቀድሞ ለመከላከል በክልሉ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ቢሮአቸው ከሚመለከታቸው ባላድርሻ አካላቶች ጋር በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ለአደጋ ምቹ ሁኔታን ሊፈጥሩ የሚችሉ ችግሮችን በመቅረፍ እና መንገዶችን የማስተካከል ስራ በፍጥነት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

አሽከርካሪዎች በወቅቱ ተገቢ ጥንቃቄ በማድረግ ሊያሽከረክሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ወይዘሮ ጠይባ የትራፊክ አደጋ በንብረት እና በሰው ህይወት ላይ ሊያመጣ የሚችለውን አደጋ ለመከላከል የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት በተገቢው ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ወይዘሮ ጠይባ አክለውም ባስተላለፉት መልዕክት ማህበረሰቡ መንገዶች ለብልሽት እንዳይዳረጉ የተለያዩ ቆሻሻን የጎርፍ መውረጃ ዲች ውስጥ መጣል እንደሌለበት እና ውሃ በትክክል መስመሩን ይዞ እንዲሄድ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ በማሳሰብ ቆሻሻውን በተፈቀደለት መንገድ የማያስወግዱ ግለሰቦች ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረግ አለበት ብለዋል፡፡

የቢሮው ሀላፊዋ በመቀጠልም ማህበረሰቡ በዝናብ ወቅት ሊከሰት ከሚችለው የትራፊክ አደጋ እራሱን መጠበቅ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

በዝናብ ወቅት ሊከሰት የሚችለውን የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ሁሉም ባለድርሻ አካላቶች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ እንደሚገባ ወይዘሮ ጠይባ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ዘጋቢ ዲኔ መሀመድ
13 8 16

Naannoo Harariitti ganna baranaa biqiltuuwwan miliyoona 2.5 dhaabuuf qophiin taasifamaa jiraachuu Itti aantuun Pirezdaan...
21/04/2024

Naannoo Harariitti ganna baranaa biqiltuuwwan miliyoona 2.5 dhaabuuf qophiin taasifamaa jiraachuu Itti aantuun Pirezdaantii naannichaa Aadde Roozaa Umar dubbatan.
*********
Itti aantuun Pirezdaantii fi Hoggantuun biiroo misooma Qonnaa Naanoo Hararii Aadde Roozaa Umar ibsa kannaniin barana Sagantaa ashaaraa magariisaatiin biqiltuuwwan miiliyoona 2.5 dhaabuuf qophiin taasifameera jedhan.

Biqiltuuwwan dhaabaman keessaa miliyoonni 1.7 biqiltuulee firiin isaanii nyaataaf oolan gosa adda addaa akka jiran kan himan yoo tahu, kuniis karoora wabii nyaataa milkeessuuf bu’aa guddaa akka qabu ibsaniiru.

Gama biraatiin biqiltuulee bosonaa jijjiirama haala qilleensaa to'achuu fi kanneen eegumsa biyyee fi bishaanii fooyyessuuf gargaaran qophaa’uu ibsanii jiru.

Yeroo ammaa naannichatti mudraalee xiqqaachaa dhufan deebisuuf biqiltuuleen gargaaraniis akka jiran ibsaniiru.

Naannichatti iddoowwan lolaa fi dhiqama biyyeef saaxilamoo tahan hir’isuu fi milkaa’ina biqiltuuwwan dhaabaman akka qabatuuf misooma sululatiin hojiin gaara hidhuu hojatamuu eeraniiru.

Karaa biraatiin buufataalee biqiltuu iddoo gara garaa keessatti lammiilee hedduudhaaf carraa hojii uumuun akka danda’ame himaniiru.

Sagantaa Ashaaraa magariisaa bara kanaatiin naannichatti biqiltuuwwan miliyoona 2.5 dhaabaman keessaa 70% mukkeen firiin isaanii nyaataa fi bosonaafiis oolan akka tahee fi 30% immoo mukkeen bosonaaf oolan tahuu eeraniiru.

Qophii ashaaraa magariisaa kanaatiif qindeessitoonni, ogeeyyiin qonnaa fi hojjattoonni buufataalee biqiltuu jiran keessatti hojiin sanyii biqiltuu adda addaa diqaaloomsuu fi unkursuu hojjetamaa jiraachuu ibsuun karoora kana milkeessuuf murannoon hojiileen hojjatamaa jiraachuu ibsaniiru.

13 / 08 / 2016

ሀረሪ ሑስኒቤ ዪ አመት 2 ኑቅጣ 5 ሚሊየን ኡንኩራች መብቀልሌ ጠብቲ ዪትከመልቤ ዛልነት ሐረሪ ሑስኒ ሒጋኝ ረኢስ ጊስቲ ሮዛ ኡመር ገለጡ***********ሑስኒዞ ሒጋኝ ረኢስ ዋ ሐራሺነት ኔሮ...
21/04/2024

ሀረሪ ሑስኒቤ ዪ አመት 2 ኑቅጣ 5 ሚሊየን ኡንኩራች መብቀልሌ ጠብቲ ዪትከመልቤ ዛልነት ሐረሪ ሑስኒ ሒጋኝ ረኢስ ጊስቲ ሮዛ ኡመር ገለጡ
***********
ሑስኒዞ ሒጋኝ ረኢስ ዋ ሐራሺነት ኔሮት ኢዳራ መስኡል ጊስቲ ሮዛ ኡመር ዪ አመት ወሪቅ አሻራ ሚሕሪራው ዪነክዛልቤ ዚገለጦኩትቤ 2 ኑቅጣ 5 ሚሊየን ኡንኩራች መብቀልሌ ጠብቲ መትከመልዞ ገለጡ።

ዪበቅሉዛሉ ኡንኩራች ማቤይነቤ 1 ኑቅጣ 7 ሚሊየንቤ ለአይ ኢስበልበላት አይና ቢስሲ ዋ ቢሳያች መኽነዚዩው አቀነኡማ ዪም ሐንጉር ደማናው የቂን ሞሸሌ ላቂ ፋይዳ ዛላነቱው አሴነኑ።

ዪቤ ዲባያም ዪትሜሐርዛል ወሪቅ አሻራ ሚሕሪራቤ ዱውፍ ሃለት ዋ አፈር ዋ ሚይ ቄረሖቱው የጡኝዛል አላያች ቦስና ለፉያች ጠብ ባይቲዚዩው ገለጡ።

አዞኩትዞም አኽኸእ ወቅቲቤ ሑስኒዞቤ ዪትሜሐርቤ ዛል ቢሳያ ኡንኩራች ቢዝሐቤ ዪትረኸብቦዛልነቱም ገለጡ።

አኽኸእ ወቅቲቤ ሑስኒዞቤ ኢስበልበላት ሺርቲያችቤ መስሪ ቂፊኛ ዪናቅሲዛል ኡንኩር መስበትቲ ቂያሱው የሊቅዛል ሲፈቤ ዚኹልቀት ዲነት ቄረሆት ዲላጋ መትደለግዞው አቴወቁ።

ሑስኒዞቤ ዪትረኸብዛሉ ኢስበልበላት ኡንኩር መርከዛች መደኒያችሌ ዲላጋ ነሲብ መኽለቅ መፍረክዞውም ሐፍ አሹ።

ሑስኒዞቤ ዪ አመት ወሪቅ አሻራ ሚሕሪራቤ ዪበቅሉዛሉ 2.5 ሚሊየን ኡንኩራች ኡስጡቤ በቅለቤ 70 ኢጂዞ ጢሚጃ ቦስና ዚኻነሳ በቅለቤ 30 ኢጂዞ ቦስና ለፉ መኽነዞው ገለጡ።

ዪታሹቤ ዛሉ ጠብቲያቹው ዪነክዛልቤ ኡንኩር መርከዝ መስኡላች ዋ ሲነተኛቹም ዪ አመት ሑሉፍ ዛዩ አመታችቤ ሉይ ሲፈቤ ኢስበልበላት ኡንኩራቹው መፍለህ ዲላጋ ዪትደለጊቤ ዛልነቱው ገለጡማ ሑስኒዞቤ ዚትለሐዳ አቡራቤ ዪነጅሒኩት ቁጭነትቤ ዪደልጉቤ ዛሉነቱው አሴነኑ።

13 / 08 / 2016

በሀረሪ ክልል በዘንድሮው አመት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ችግኞች ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የሀረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመር ገለፁ **********የክልሉ ምክት...
21/04/2024

በሀረሪ ክልል በዘንድሮው አመት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ችግኞች ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የሀረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመር ገለፁ
**********

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብርን አስመልክተው እንደገለፁት ዘንድሮው በሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።

ከሚተከሉ ችግኞች መካከልም ከ1 ነጥብ 7 ሚሊየን በላይ የተለያዩ አይነት ፍራፍሬዎች መሆናቸውን ጠቁመው ይህም የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አንፃር ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በሚካሄደው በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአየር ንብረትና የአፈርና ውሃ ጥበቃ የሚያሻሽሉ ሌሎች የደን ዛፎች መዘጋጅታቸውን ገልጸዋል።

እንዲሁም በአሁኑ ወቅት በክልሉ እየተመናመኑ የሚገኙ የፍራፍሬ ችግኞችን እንደሚገኙበትም ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅትም በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የጎርፍ ተጋላጭነትን በሚቀነስና የችግኝ ፅድቀት መጠንን በሚያሳድግ መልኩ የተፋሰስ ልማት ስራ መሰራቱን ጠቅሰዋል።

በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ የችግኝ ጣቢያዎችም ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉንም አንስተዋል።

በክልሉ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከሚተከሉ 2.5 ሚሊየን ችግኞች ውስጥ 70 በመቶው የጥምር ደን ሲሆን 30 በመቶው ደግሞ የደን ዛፍ መሆኑን ገልጸዋል።

እየተደረጉ የሚገኙ ዝግጅቶች በሚመለከት የችግኝ ጣቢያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎችም ዘንድሮ ከወትሮው በተለየ መልኩ የተለያዩ ችግኞችን የማዳቀል ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው በክልሉ የተያዘው እቅድ እንዲሳካ በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

13/8/2016

በሀረር ከተማ የእግረኛ መንገዶችን ለነዋሪዎች ነፃ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ለዜጎች ደህንነትና  ለከተማው ገፅታ አበርክቶው የጎላ  መሆኑን የሐረር ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ********...
20/04/2024

በሀረር ከተማ የእግረኛ መንገዶችን ለነዋሪዎች ነፃ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ለዜጎች ደህንነትና ለከተማው ገፅታ አበርክቶው የጎላ መሆኑን የሐረር ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ።
*****************
በሐረሪ ክልል ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት እየተሰሩ ያሉ የእግረኛ መንገዶችን ነፃ ለማድረግ እየሰራ ያለው የህግ ማስከበር ስራ የሚበረታታ መሆኑንም ገልፀዋል።

በመኪና መንገድ ዳርና ዳር የሚገኙ እግረኛ መንገዶችን በህገ ወጥ በመያዝ የተለያዩ ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎችን ሲያካሂዱ በነበሩ አካላት ላይ ህግን በማስከበር መንገዶቹን ነፃ የማድረግ እርምጃ በክልሉ ደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት እየተወሰደ መሆኑ ይታወቃል።

የሐረሪ ብዙሃን መገናኛ ኤጀንሲ ያነጋገራቸው
የሐረር ከተማ ነዋሪዎች በደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት በኩል እየተሰራ ያለው ህግን የማስከበር ስራ የሚበረታታ መሆኑን በመግለፅ የእግረኛ መንገድ መስፋቱ የትራፊክ ፍሰቱን በማሳለጥ በሰዉ እና በንብረት ላይ ሊደርሱ የሚችሉ የትራፊክ አደጋና ጉዳቶችን ለማስቀረት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

የእግረኛ መንገዶቹ መስፋትና ነፃ መሆናቸው ለተዋበ የከተማ ገፅታም ጥቅም እንዳለው ጨምረው ገልፀዋል።

ህብረተሰቡ ይሄን በመረዳት ከእግረኛ መንገዶች ውጪ መጓዝ ሊያደርስ ከሚችለው አደጋ ራሱን መጠበቅ እንዳለበት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በደንብ ማስከበር ፅህፈት ቤት እየተሰሩ ያሉ የህግ ማስከበር ተግባር ቀጣይነት ያለዉ ሊሆን እንደሚገባ ነዋሪዎቹ ገልፀዋል።

በአብስራ አሰግድ
12 / 08 / 2016

HTV:- ሀረሪ ሲናን ኸበር
20/04/2024

HTV:- ሀረሪ ሲናን ኸበር

Addis Ababa Shewal Eid

በተለያየ ጊዜ ለፍርድ ቤቶች የሚቀርቡ የፍቺ ጥያቄዎችን መጠን  ለመቀነስ ትኩረት ሰቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ*********** በሀረሪ ክልል ለፍርድ ቤቶች የሚቀርብ የፍቺ ጥያቄ መጠን ትኩ...
20/04/2024

በተለያየ ጊዜ ለፍርድ ቤቶች የሚቀርቡ የፍቺ ጥያቄዎችን መጠን ለመቀነስ ትኩረት ሰቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
***********
በሀረሪ ክልል ለፍርድ ቤቶች የሚቀርብ የፍቺ ጥያቄ መጠን ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በክልሉ የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ፈርሃን መሀመድ አስታውቀዋል።

አቶ ፈርሃን ይህን የገለፁት በክልሉ የሚገኙ የኡለማኦች ስብስብ በአዳ ቤት ስለ ጋብቻ ባዘጋጁት መድረክ ባቀረቡት አጠር ያለ ፅሁፍ ነው።

አቶ ፈርሃን እንዳሉት ባለፉት 8 ወራት ብቻ ለመደበኛ ደረጃ ፍርድ ቤቶች 426 የፍቺ ጥያቄዎች ቀርበዋል። ባለፉት 5 አመታት ደግሞ ከ 1,700 በላይ ፍቺዎች ለፍርድ ቤቱ ሲቀርቡ በ10 አመታት ከ3,500 በላይ የፍቺ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

ፍርድ ቤቱ ከቀረቡለት የፍቺ ጥያቄዎች መካከል ከፍተኛ ቁጥር የያዙት ሴቶች ሲሆኑ በአሃዝ 90 በመቶ ይደርሳሉ ብለዋል።

ፍርድ ቤቱ ከቀረቡለት የፍቺ ጥያቄዎች እስከ 75 በመቶ ለሚደርሱት ውሳኔ ሲሰጥ 15 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ፍርድ ቤቶቹ ለማስማማት ጥረት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

ይህ የፍቺ ጥያቄ ከመደበኛ ፍርድ ቤት ውጭ ለክልሉ ሸሪዓ ፍርድ ቤትም ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ ከ200 በላይ ጥያቄዎች መቅረቡን አቶ ፈርሃን መሀመድ ተናግረዋል።በአምስት አመታት ብቻ 1,121ፍቺዎች ቀርበው ውሳኔ ተሰጥቶታል ሲሉም አክለው ገልፀዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የፍቺው ጉዳይ አሳሳቢ በመሆኑ ሊታሰብበት እንደሚገባና መደረኮች በብዛት በማዘጋጀት መስራት ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ የጋብቻ ምንነት፤ በትዳር የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችና መፍትሔዎች የሚሉ ፅሁፎች ቀርበው ውይይት ተካሂዷል።

በመሀመድ አብዱረሂም
12 / 08 / 2016

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ሀዋሳ ከተማ ገቡ********************በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አፈጻጸም ላይ በሚያተኩረው ውይይት ላይ ለመሳተፍ የሀረሪ ክልል ...
20/04/2024

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ሀዋሳ ከተማ ገቡ
********************
በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አፈጻጸም ላይ በሚያተኩረው ውይይት ላይ ለመሳተፍ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ሀዋሳ ገብተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ሀዋሳ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ በየነ በራሳና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ይፋ ከተደረገበት ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ የተሰሩ ስራዎችና የመጡ ለውጦችን አፈጻጸም እንደሚገመገም ከሀረሪ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር በእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ምርትና ምርታማነት ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት እንዲቻል የተቀረጸ ሲሆን፤ መርሀ ግብሩ በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ መደረጉ ይታወቃል።

መርሀ ግብሩ በዋናነት እንቁላል፣ ዶሮ፣ ማር፣ ወተት እና አሣ ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው የልማት መስኮች ናቸው።

12 / 08 / 2016

19/04/2024

HTV:- Oduu Afaan Oromoo TV Hararii Guyyaa 11/08/2016

በሀረሪ ክልል የገበያ የማረጋጋት  ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ ገለፀ፡፡**********************የኑሮ ውድነትን ለማቃለል ከግብርና ምርቶች በ...
19/04/2024

በሀረሪ ክልል የገበያ የማረጋጋት ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ ገለፀ፡፡
**********************
የኑሮ ውድነትን ለማቃለል ከግብርና ምርቶች በተጨማሪ ሌሎች የምግብ ፍጆታ እቃዎች በቅዳሜ ገበያ ስርአት እንዲቀርቡ እየሰራ መሆኑንም አስታውቋል።

የኑሮ ውድነትን ለመከላከል የሀረሪ ክልል መንግስት አምራች አርሶ አደሩ እና ሸማቹ በቀጥታ ተገናኝተው እንዲገበያዩ እና ተጠቃሚም እንዲሆኑ ሰፊ ስራ እየተሰራ ነው ፡፡

ከግብርና ምርት በተጨማሪም ሌሎች ምርቶች ቅዳሜ ገበያ ላይ እንዲቀርቡ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን የሀረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡

በኤጀንሲው የህብረተሰብ ማደራጃ እና ግዢ ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ መሀመድ ዩሱፍ አርሶ አደሩ እና ሸማቹ በቀጥታ እንዲገናኙ ከተደረገ ወዲህ የሽንኩርት እና ቲማቲም ዋጋ መቀነሱን ገልፀዋል፡፡

ለሸማች ማህበራት የሚቀርቡ ሸቀጦች ጋር ተያይዞ አቅርቦት ችግር ያለ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ ችግሩን ለመፍታት በከተማም በገጠርም ዩኒዬን እንዲጠናከር ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

እንደ ክልሉ የኑሮ ውድነቱን ለማቃለል የተጀመረ ስራ ተጠናክረው የሚቀጥል መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ዘጋቢ ትግስት በለጠ
11 8 16

የኮሌራ በሽታን ለመከላከል ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት የአቦከር ወረዳ ጤና ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡*****************በክልሉ ኮሌራ መከሰቱን የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ማስታወ...
19/04/2024

የኮሌራ በሽታን ለመከላከል ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት የአቦከር ወረዳ ጤና ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
*****************
በክልሉ ኮሌራ መከሰቱን የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

በኮሌራ ምክንያት በሚከሰት ተቅማጥ ለሰውነት ጠቃሚ የሆነ ኤሌክትሮ ላይት የሚባሉ ንጥረ ነገሮች ከሰውነት እንዲወጡ በማድረግ ጉዳት ያደርሳል፡፡

በአቦከር ወረዳ ጤና ፅህፈት ቤት ጤና መኮንን የሆኑት ሲስተር ሰብለ ታምሩ በክልሉ በሽታው ከተከሰተ ግዜ ጀምሮ የተለያዩ ግንዛቤ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ያለው የውሃ እጥረት የህብረተሰብ ንፅና አጠባበቅ ላይ ችግር እየሆነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በሽታው አጣዳፊ ተቅማጥ የሚያስይዝ መሆኑን ገልጸው እንደዚህ አይነት ችግር ያጋጠመው ሰው በፍጥነት ወደ ሀኪም ቤት ሄዶ መታከም አለበት ብለዋል፡፡

ህብረተሰቡ በሽታውን ለመከላከል ከመመገቡ በፊት እና በኋላ መፀዳጃ ቤት ከተጠቀመ በኋላ እንዲሁም በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንኪኪ ካደረገና ምግብ ከማዘጋጀት በፊት በአግባቡ እጅ መታጠብ እንዳለበት ጠቁመው ምግብ ሲቀምጥ መክደን አካባቢ እና የግል ንፅህና በመጠበቅ በሽታውን መከላከል እንደዳለበት መክረዋል፡፡

ዘጋቢ ቱራ አያና
11 8 16

19/04/2024

HTV:- ባለ ዕደ- ጥበቡ የሀረር ወጣት

19/04/2024

HTV:-ሐረሪ ቴሌቪዥን የአማርኛ ዜና .. ቀን 11/08/2016

በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶችን በሁሉም ወረዳዎች ለመገንባት የተጀመረውን ስራን በተደራጀ መልኩ ለመፈፀም እየተሰራ መሆኑን በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀ...
19/04/2024

በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶችን በሁሉም ወረዳዎች ለመገንባት የተጀመረውን ስራን በተደራጀ መልኩ ለመፈፀም እየተሰራ መሆኑን በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ።
***************
በሀረሪ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶችን በሁሉም ወረዳዎች ለመገንባት የተጀመረውን ስራን በተደራጀ መልኩ ለመፈፀም እየተሰራ መሆኑን በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ።

አቶ ጌቱ ወዬሳ የፓርቲው ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች ግንባታ ዓላማ የፓርቲውን እይታና ታእማኒነት ለማሳደግ፣ ድርጅታዊ መዋቅርን ለማጠናከር፣ የአባላት ተሳትፎ እና ስልጠናን በተሻለ ሁኔታ ለማመቻቸት፣ ህዝባዊ ዝግጅቶችን ለማስተናገድ ፣ የፓርቲ እሳቤዎችና እሴቶችን ማሳደግ እና ቋሚ ና ዘላቂ መሰረት ለመጣል ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።

በክልሉ ባሉት ሁሉም ወረዳዎች የቅርንጫፍ ፅህፈትቤቶቹ ግንባታ ቀድሞ የተጀመረና በሂደት ላይ ያለ መሆኑን መናገራቸውን ከክልሉ የፓርቲው ማህበራዊ ትስስር ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

አቶ ጌቱ የፓርቲውን አባለትና ደጋፊዎች በተሻለ ሁኔታ ለማሳተፍና በአይነት፣ በእውቀት፣ በጉልበትና በገንዘብ የሚደረገውን ድጋፍ በተገቢው ሁኔታ አቀናጅቶ ለመጠቀም እንዲሁም አጠቃላይ ስራውን በተደራጀ ሁኔታ ለመከታተልና ለመደገፍ ኮሜቴዎች በየደረጃው መደራጀታቸውን አስታውቀዋል።

የሚገነቡት ህንፃዎች ለትውልድ የሚተላለፉ የሃገር ሀብቶች ስለሆኑ ግንባታቸው በተያዘለት ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቅ አባላት ደጋፊዎችና ባለሀብቶች አስፈላጊውን የገንዘብ ፣ የአይነት፣ የእውቀትና የጉልበት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

11 / 08 / 2016

18/04/2024

HTV:-ሐረሪ ቴሌቪዥን ሐረሪ ሲናን ኸበር .. አያም 10/08/2016

18/04/2024

HTV:- Oduu Afaan Oromoo TV Hararii Guyyaa 10/08/2016

18/04/2024

HTV:-ሐረሪ ቴሌቪዥን የአማርኛ ዜና .. ቀን 10/08/2016

በሀረሪ ክልል የአፋር ባህላዊ ቤት ሊገነባ ነው*********በሀረሪ ክልል ሀማሬሳ በሚገኘው የባህል ማዕከል ቅጥር ግቢ የአፋር ባህላዊ ቤት ሊገነባ ነውየሀረሪ ክልል ባህል፣ ቅርስና ቱሪዝም ቢ...
18/04/2024

በሀረሪ ክልል የአፋር ባህላዊ ቤት ሊገነባ ነው
*********
በሀረሪ ክልል ሀማሬሳ በሚገኘው የባህል ማዕከል ቅጥር ግቢ የአፋር ባህላዊ ቤት ሊገነባ ነው

የሀረሪ ክልል ባህል፣ ቅርስና ቱሪዝም ቢሮም የባህል ቤቶችን ለመገንባት የሚያስችል መሬት ለአፋር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስረክቧል።

የሀረሪ ክልል ባህል ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወለዳ አብዶሽ መሬቱን ባስረከቡበት ወቅት እንዳሉት ሀረር የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በሰላም፣ በመቻቻልና በአብሮነት የሚኖሩባት ከተማ ነች።

የአብሮነት ተምሳሌት በሆነችው ሀረር ከተማ የአጎራባች ክልሎች የባህል ማዕከል እንዲገነባ ማድረግ ይህንን አብሮነትን የበለጠ እንዲጠናከር ያደርጋል ብለዋል።

ይህም አንዱ የሌላውን ባህልና እሴት በአግባቡ እንዲያወቅ እና እህትማማችነትና ወንድማማችነት እንዲጎለብት የላቀ ሚና እንዳለው ነው የገለፁት።

የአፋር ክልል የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ አቶ አህመድ አብዱልቃድር በበኩላቸው መሬቱን በይፋ መረከባቸውን በማንሳት ለቀጣይ የአፋር ባህል ቤቶች መገንባትም በህዝቦች መካከል አብሮነትና ትስስር ያሳድጋል ብለዋል።

በብሔር ብሔረሰቦች መካከል የባህል ትስስርን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።

የፕሮጀክቱ ግንባታም በተያዘው የበጀት ለማጠናቀቅ መታቀዱን ገልጸዋል።

10/ 8 2016

Hojiileen abdachiisaan hawaasa abbaa gochuun Magaalaa Harar keessatti hojjatamaa jiran cimee itti fufa: Obbo Ordiin Badr...
18/04/2024

Hojiileen abdachiisaan hawaasa abbaa gochuun Magaalaa Harar keessatti hojjatamaa jiran cimee itti fufa: Obbo Ordiin Badrii.
***********

Pirezidaantiin Naannoo Hararii obbo Ordiin Badrii Magaalaa Hararitti hojiiwwan misoomaa abdachiisaan hawaasa abbaa gochuun hojjetamaa jiran cimee itti fufa jedhan.

Pirezidaantiin naannichaa obbo Ordiin Badrii hojiiwwan ji'a darbe keessa aanoolee magaalichaa keessatti hojjetaman ilaalchisee hoggantoota deeggarsaa fi hordoffiif ramadaman waliin marii taasisaniiru.

Marii kanarratti hojiiwwan aanoolee magaalichaa keessatti hojjetaman gabaasni raawwii hojii dhihaateera.

Pirezidaantiin naannoo Hararii obbon Ordiin Badrii akka jedhanitti hojiileen misoomaa bifa hawaasa magaalattii hirmaachiseen hojjetaman bu’aan qabatamaan argamee jira jedhan.

Keessattuu hojiiwwan misooma magariisaa,qulqullinaa fi miidhagina magaalattii eeguu keessatti hojjetamaa jiraniin magaalaa Harar jiraattotaa fi daawwattootaaf mijjattuu fi Magaalaa filatamtuu gochuun akka danda’amu kan agarsiise ta’uu ibsaniiru.

Hojiin qulqullina magaalaa fi miidhaginaa, balfa gogaa fi xuraawaa gatuu, hojii misooma magariisaa, daldala seeraan alaa, ijaarsaa seeraan alaa, ibsaa fi faaya daandii maddii irratti hojjetamaa turan cimee itti fufuu qaba jedhaniiru.

Qindoomina hoggansaan hojiin bu'a qabeessa ta'e hojjatamuu eeruun, hojiileen kunneen fuulduraafiis cimee itti fufuu akka qabu hubachiisaniiru.

Fuulduraafiis haala idileen dhaabbilee fi aanaaleen ummata abbaa gochuun hojiileen kun itti fufiinsa akka qabaatu taasisuuf tumsi jiraachuu akka qabu hubachiisaniiru.

Keessattuu hojiin eegumsaa fi kunuunsa hambaalee idil-addunyaa Jogolaa hojjatamaa jiru cimee itti fufuu akka qabu akeekkachiisanii jiran.

10/8/2016

ሐረር አሲማ ሸእቢ አውነት ሹኡብቤ የሚህራቤዛል  ኔሮት ዲላጋች ዚቅቲቤ የትኺትላል :- ጌስሲ ኦርዲን በድሪ*********ሐረሪ ሑስኒ ረኢስ ጌስሲ ኦርዲን በድሪ ሐረር አሲማ ሸእቢ አውነት ሹኡ...
18/04/2024

ሐረር አሲማ ሸእቢ አውነት ሹኡብቤ የሚህራቤዛል ኔሮት ዲላጋች ዚቅቲቤ የትኺትላል :- ጌስሲ ኦርዲን በድሪ
*********

ሐረሪ ሑስኒ ረኢስ ጌስሲ ኦርዲን በድሪ ሐረር አሲማ ሸእቢ አውነት ሹኡብቤ የሚህራቤዛል የንቀህቂ ኔሮት ዲላጋች ዚቅቲቤ የትኺትላል ባዪቲቤ ገለጡ።

ረኢስ ኦርዲን በድሪ አሲማዞቤ ዪትረኸብዛሉ ወረዳች ሑሉፍዛያ አሐድ ወሕሪቤ ዚትሜሐሩ ዲላጋች ሺርቲቤ ተኽታተሎት ዋ ሙራቀባሌ ዚትረመዱ ኤመሮታች በህ፣ ሒርጊ አሜሐሩ።

ሒርጊዞ ለአይቤ አሲማቤ ዪትረኸብዛሉ ወረዳችቤ ዚትሜሐሩ ዲላጋቹው ዪነክዛልቤ ሒካሞት ቀረባ።

ሒርጊዞቤ ረኢስ ጌስሲ ኦርዲን በድሪ ዛዮኩትቤ አሲማዞቤ ሸእቢው ዘትሳአዳ ሲፈቤ ዚትደለጉ ኔሮት ዲላጋች ሩኹብ ነቲጃ ተረኸባ ባዩ።

ሉይቤም አሲማዞ ወሪቅ ኔሮት ፣ ኒዝፋ ዋ መትቆመስቲ ዲላጋች ነባሪዞሌ ሙች ዋ ዘያሪሌ ሙሉህ አሲማ ሞሸሌ ዪትፊርኪዛል ዲላጋች ዚትሪአቤው ኢንታ ባዩ።

ሺርቲ ነዛፋ ፣መትቆመስቲ ፣ ደረቅ ዋ ኩእ ቁሻሽ መትኻተርቲ፣ ወሪቅ ኔሮት ዲላጋች፣ ቃኑንቤ ቃጪ ቲጃራ ዋ ቼኸሎት ዋ ኡጋ ጠረፍ ቲሪካች ሺርቲቤ ዚትደለጉ ዲላጋች ዚቅቲቤ መትኼተል ሐልባ ባዩ።

ኤመሮትዞ ተዋሐቦትቤ መድለግዞቤ ነቲጃ ዚሴጀለነት አቴወቁማ ተኼታይቤም ዪትሜሐሩቤ ዛሉ ዲላጋች ዚቅቲቤ ዪትኼተልዛልነት አቀነኡ።

ተኼታይቤም ዋሪነትቤ ሳም ዛለዩ ተእሲሳች ዋ ወረዳች ሸእቢ አውነት ሹኡብ ዋ ዘትሳአዳ ሲፈቤ ዲላጋች ዋሪ ዩኹኑኩት ሞሸ ገረብሌ ጁህዲ ሞሻ ዛልባነት አትሒሳሰቡ።

ሉይቤም ጀጎል አለም ሑቁፍ ቁራስ ቄረሖት ዋ ተፋቀዶት ዲላጋቹም ዚቅቲቤ መትኼተል ሐልባ ባይቲቤ አሴነኑ።

10/8/2016

በሀረሪ ክልል የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ እየተሰሩ የሚገኙ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው- ወይዘሪት ሌንሳ መኮንን የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ**********በሀረሪ ክልል የቱሪዝ...
18/04/2024

በሀረሪ ክልል የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ እየተሰሩ የሚገኙ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው- ወይዘሪት ሌንሳ መኮንን የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ
**********
በሀረሪ ክልል የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ እየተሰሩ የሚገኙ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሪት ሌንሳ መኮንን ገለጹ።

የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሪት ሌንሳ መኮንን በሀረሪ ክልል የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሪት ሌንሳ መኮንን እንዳሉት ሀረር ከተማን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እና ለቱሪስቶች ምቹ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

ከመደመር ትውልድ መፅሐፍ በተገኘ ገቢ እየተገነባ የሚገኘው የሀረር ኢኮ ፓርክ ፕሮጀክትን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የሀረር ኢኮ ፓርክ ግንባታ በዘመናዊና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተካሄደ መሆኑ ገልጸው ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የቱሪዝም ፍሰቱን ለማሳደግ ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።

በጉብኝቱ ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሪት ሌንሳ መኮንን ጨምሮ የክልሉ አመራሮች ተገኝተዋል።

10 / 08 / 2016

በሀረር ከተማ ህዝብን ባለቤት ባደረገ መልኩ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች ስራዋች ተጠናክረው ይቀጥላሉ:- አቶ ኦርዲን በድሪ*************የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በ...
18/04/2024

በሀረር ከተማ ህዝብን ባለቤት ባደረገ መልኩ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች ስራዋች ተጠናክረው ይቀጥላሉ:- አቶ ኦርዲን በድሪ
*************
የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ በሀረር ከተማ ህዝብን ባለቤት ባደረገ መልኩ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በከተማው በሚገኙ ወረዳዎች ባለፈው አንድ ወር በተከናወኑ ስራዋች ዙሪያ ለድጋፍና ክትትል ከተመደቡ አመራሮች ጋር ውይይት አካሂደዋል።

በውይይቱ ላይም በከተማው በሚገኙ ወረዳዎች የተከናወኑ ስራዎች በሚመለከት ሪፖርት ቀርቧል ።

በውይይቱ ላይ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እንዳሉት በከተማው ህዝብን ባሳተፈ መልኩ በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ተገኝቷል።

በተለይም በከተማው የአረንጓዴ ልማትና የከተማ ፅዳትና ውበት ስራዎች ለነዋሪዎቹ ምቹና በጎብኚዎች ተመራጭ ከተማ ለማድረግ እንደሚቻል ያመላከተ ነው ብለዋል።

በጽዳትና ውበት፣በደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ፣በአረንጓዴ ልማት ስራዎች ፣ በህገ ወጥ ንግድና ግንባታ እና የመንገድ ዳር ጌጠኛ መብራቶች ስራዎች ዙሪ የተሰሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለበት ብለዋል።

አመራሩ በቅንጅት በመስራቱ ውጤት ማምጣታቸውን ጠቅሰው በቀጣይም እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።

በቀጣይ በመደበኛነት ባለቤት ተቋማትና ወረዳዎች ህዝብን ባለቤት ባደረገ መልኩ በመንቀሳበስ ስራዎቹን ዘላቂ እንዲሆኑም በማድረግ ረገድ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በተለይም የጁገል አለም አቀፍ ቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ስራዎችም ተጠናክረው መቀጠል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

10 / 08 / 2016

17/04/2024

HTV:-ሐረሪ ቴሌቪዥን ሐረሪ ሲናን ኸበር .. አያም 9/08/2016

17/04/2024

HTV:- የሸዋል ኢድ በአል የመክፈቻ ፕሮግራም ቀን 8 8 16

Address

Red Cross Street
Harar
1331

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Mass Media Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harari Mass Media Agency:

Videos

Share



You may also like