
10/06/2025
የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና አስጀመሩ ።
*********
በክልሉ በሚገኙ በሁሉም የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች ለ 5 ,250 ተማሪዎች ፈተናው እየተሰጠ ይገኛል ።
የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና አስጀምረዋል ።
በመርሃ ግብሩ የክልሉ ትምህር ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌቱ ነገዎ እንደገለፁት በክልሉ በሁሉም የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች የስምንተኛ ክፍል መልቀቂያ ክልላዊ ፈተና ለተከታታይ ከዛሬ ጀምሮ ለ 2 ተከታታይ ቀናት መሰጠት መጀመሩን ጠቁመዋል ፡፡
በሚሰጠው ክልል አቀፍ የስምንተኛ ፈተናም 2 , 856 ወንድ እና
2, 394 ሴት በአጠቃላይ 5,250 ተማሪዎች 9 በገጠር
10 በከተማ በ19 ጣቢያዎች እየተከታተሉ እንሚገኙ ጠቁመዋል ፡፡
ተማሪዎች ከዚህ ቀደም ካሉ ውጤቶች የተሻለ እንዲያስመዘግቡ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወኑን የገለፁት አቶ ጌቱ የሞዴል ፈተናዎችን በማዘጋጀት ለተማሪዎች የስነልቦና ትምህርቶችም በመስጠት ተገቢውን ክትትል እና ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱን አብራርተዋል ።
የፈተና አሰጣጡ በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድም ቢሮው ከመምህራን ማህበር ፣ ከጤና ቢሮ ፣ ከፖሊስ እና ከጸጥታ ቢሮ ጋር በቅንጅት እያከናወነ ይገኛል ፡፡
ዘጋቢ :- ገዛኸኝ አራጌ
03 / 10 /17