Harari Mass Media Agency

Harari Mass Media Agency Harari Mass Media Agency is a public media operating in Harar, Ethiopia.
ገፃችንን በመከተል ትኩስ ዜና እና መረጃዎችን ያገኛሉ።

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና አስጀመሩ ። *********በክልሉ በሚገኙ በሁሉም የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች ለ 5 ,250 ተማሪዎች ...
10/06/2025

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና አስጀመሩ ።
*********

በክልሉ በሚገኙ በሁሉም የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች ለ 5 ,250 ተማሪዎች ፈተናው እየተሰጠ ይገኛል ።

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና አስጀምረዋል ።

በመርሃ ግብሩ የክልሉ ትምህር ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌቱ ነገዎ እንደገለፁት በክልሉ በሁሉም የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች የስምንተኛ ክፍል መልቀቂያ ክልላዊ ፈተና ለተከታታይ ከዛሬ ጀምሮ ለ 2 ተከታታይ ቀናት መሰጠት መጀመሩን ጠቁመዋል ፡፡

በሚሰጠው ክልል አቀፍ የስምንተኛ ፈተናም 2 , 856 ወንድ እና
2, 394 ሴት በአጠቃላይ 5,250 ተማሪዎች 9 በገጠር
10 በከተማ በ19 ጣቢያዎች እየተከታተሉ እንሚገኙ ጠቁመዋል ፡፡

ተማሪዎች ከዚህ ቀደም ካሉ ውጤቶች የተሻለ እንዲያስመዘግቡ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወኑን የገለፁት አቶ ጌቱ የሞዴል ፈተናዎችን በማዘጋጀት ለተማሪዎች የስነልቦና ትምህርቶችም በመስጠት ተገቢውን ክትትል እና ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱን አብራርተዋል ።

የፈተና አሰጣጡ በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድም ቢሮው ከመምህራን ማህበር ፣ ከጤና ቢሮ ፣ ከፖሊስ እና ከጸጥታ ቢሮ ጋር በቅንጅት እያከናወነ ይገኛል ፡፡

ዘጋቢ :- ገዛኸኝ አራጌ
03 / 10 /17

09/06/2025

የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ የምሽት ስራዎችን ማስፋፋትና ማጠናከር እንደሚያስፈልግ መግባባት ላይ ደርሰናል፦ አቶ ኦርዲን በድሪ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በምሽት  ተመልክተዋል። **********በምልከታው በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮ...
09/06/2025

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተከናወነ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በምሽት ተመልክተዋል።
**********
በምልከታው በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች አፈፃፀም አበረታች መሆናቸውን ጠቁመው ስራዎቹን ከጥራት ባሻገር በፍጥነት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ከቀን ባሻገር በምሽትም መከናወናቸው የስራ ባህልን በእውን መለወጣቸውን ገልፀዋል።

በአሁኑ ሰአት በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ከዚህ ቀደም ከተሰሩ የልማት ስራዎች በተሻለ ጥራት እና ውበት መከናወን እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል ።

በተለይም የከተማዋን ደረጃ በጠበቀ መልኩ እና ለነዋሪዎች ምቹ የእግረኛ መጓጓዣን (ዎክ ዌይ) በጥራት ማከናወን እንደሚገባ ገልፀዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለፁት እየተከናወኑ ያሉ የአረንጓዴ ልማት ስራዎች የአካባቢ ውበት ከማጎናፀፋቸው ባሻገር ለአየር ንብረት እንዲሁም ለአካባቢው ጥላን ማላበስ የሚችሉ መሆን እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

ከተማዋ እየተጓዘችበት ያለውን የልማት ጎዳና ለማሳለጥ ከቀን ባሻገር በምሽትም በስራ ላይ የሚገኙ ሰራተኞችን ተዘዋውረው አበረታተዋል።

በገዛኸኝ አራጌ
2/10/2017

09/06/2025

ሰላም፣ መስሳነትዋ ዚጊሽ ሲቃ ዊጃችቤ ዚትገለጣሳኣ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ተወያዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የንግዱ ማህበረሰ...
09/06/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የንግዱ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር በዞን፣ በክልል እና ከተሞች ደረጃ ከተካሄዱ ውይይቶች የቀጠለ ውይይት ዛሬ በፌዴራል ደረጃ አካሂደናል ብለዋል።

ይኽ መድረክ በየደረጃው የተሰበሰቡ የንግዱ ዘርፍ ጉዳዮች እና ሃሳቦች በሀገር አቀፍ እቅዶች እና የልማት ግቦች ዝግጅት ግብዓት ይሆኑ ዘንድ ለማካተት የተዘጋጀም ነው ሲሉም ገልጸዋል።

2/10/2017

ተኪ ምርቶችን በማምረትና በመገጣጠም የውጭ ምንዛሬን ማዳን መቻሉን አል ሀያት የሶላርና የባትሪ ምርቶች መገጣጠሚያና ማምረቻ አስታወቀ። ***********************************...
09/06/2025

ተኪ ምርቶችን በማምረትና በመገጣጠም የውጭ ምንዛሬን ማዳን መቻሉን አል ሀያት የሶላርና የባትሪ ምርቶች መገጣጠሚያና ማምረቻ አስታወቀ።
*****************************************************

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እንደ ሀገር የኢንደስትሪ አብዮትን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማስፋፋት ስራዎች በልዩ ትኩረት እየተሰሩ የሚገኝ ሲሆን ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየታዪ ይገኛል።

በሐረሪ ክልልም የግብርናውን ዘርፍ ጨምሮ የኢንደስትሪ ተቋማትን በመገንባት፣ ተኪ ምርቶችንከማምረትና የስራ እድልን ከመፍጠር አኳያ ጅምር ስራዎች ተጀምረዋል።

በክልላችን ከተቋቋሙ የኢንዱስትሪ ተቋማት መካከል በሐማሬሳ አካባቢ የሚገኘው አል ሀያት የሶላርና የባትሪ ምርቶች መገጣጠሚያና ማምረቻ አንዱ ነው።

ከሁለት አመታት በፊት የክልሉ መንግስት ባመቻቸላቸው የኢንቨስትመንት እድል በመጠቀም ቦታ ወስደው በ15 ሚሊየን መነሻ ካፒታል ስራ በመጀመር በአሁኑ ሰአት በቂ ምርቶችን እያመረተና ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ራጂህ መሀመድ ይናገራሉ።

በተለይም እንደሀገር የተጀመረውን ባለን ጸጋ ሀገር በቀል ምርቶችን በማስፋፋትና ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በማስቀረት በራስ ምርት ራስን መቻል መርህን ለማሳካት እየሰሩ እንደሚገኝ አብራርተዋል ።

ድርጅቱ ምርቶችን ገጣጥሞ ለገበያ ከማቅረብ በዘለለ የእውቀት ሽግግር ስራ እየሰራ እንደሚገኝና ወጣቶችንም እያሰለጠነ እንደሚገኝ ስራ አስኪያሄጁ አክለው ገልጸዋል።

የሚገጣጠሙት ምርቶች በተለያዩ አማራጮችና አመራጭ የመጠቀም ዘዴን የያዙ መሆናቸውን ያነሱት አቶ ራጂህ ብልሽት ቢያጋጥም እንኳን በቂ መለዋወጫ ያላቸው መሆኑ ደንበኞች ያለስጋት እንዲጠቀሙ ያስችላቸዋል ብለዋል።

ከሶላርና ባትሪ ምርቶች በዘለለ ተጨማሪ የተለያዩ የቴክኖሎጂ በማምረት ለክልሉ ህብረተሰብና ለአጎራባች አካባቢዎችም ተደራሽ የማድረግ ስራዎችን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።

በቀጣይም በክልሉ መሰል ምርቶችን በማምረት ና የስራ እድልን የመፍጠር ጅምር ስራዎች እንዳሉና የክልሉ መንግስትም እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ዘጋቢ:- ሲሳይ ዘርይሁን
02/10/17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ : https://www.youtube.com/

ቴሌግራም: https://t.me/hararimassmediaagency

ፌስቡክ: https://web.facebook.com/mediaharari/

በሀረሪ ክልል በጤና ዘርፍ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት ለመስጠት እየተደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። *********በሕዝብ ተወካዮች ም...
09/06/2025

በሀረሪ ክልል በጤና ዘርፍ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት ለመስጠት እየተደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ።
*********
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፤ማህበራዊ ልማት ፤ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ልኡክ በክልሉ የተመረጡ የጤና ተቋማትን ምልከታ አድርጓል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፤ማህበራዊ ልማት ፤ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ልኡክ በሀረሪ ክልል የተመረጡ የጤና ተቋማትን ምልከታ አድርጓል።

ከተመለከታቸው ውስጥ የሶፊ እና ጅንኤላ ጤና ጣቢያዎች ፣ቡርቃ ጤና ኬላ፣ የደም ባንክ እና የክልሉ የጤና ምርምር ላብራቶሪ ይገኙበታል።

በቋሚ ኮሚቴው የመስክ ምልከታው ቡድን መሪ ወ/ሮ ፈቲያ አህመድ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየተደረገ ያለው ጥረት እና በየደረጃው ካሉ ጤና ተቋማት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል ።

በጤና ተቋማቱ የባለሙያዎች የስራ ተነሳሽነትም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ጠቁመዋል።

ወባን ጨምሮ በሌሎች ወረርሽኞች ላይ እየተሰራ ያለው የቅድመ መከላከል ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል ።

በጅንኤላ ጤና ጣቢያ ላይ ያለው ዘመናዊ አሰራር ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን እንደሆነና በሌሎቹም ተቋማት ማስፋት እንደሚገባ ተናግረዋል።

በሶፊ ጤና ጣቢያ ላይ ያለውን የቦታ ጥበት ችግር መፍትሄ መስጠትና የነፍሰጡር እናቶች ማቆያ ላይ አስፈላጊ ግብአቶች እንዲሟሉ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የደም ባንክ ላይ ያለውን የደም ዕጥረት ለመቅረፍ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን መስራት እና በጎ ፈቃደኞችን ማብዛት ያስፈልጋልም ብለዋል ።

እየተሰራ ያለው የክልሉ ላብራቶሪ በታቀደው ጊዜ ተጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል ።

የአንዳንድ መድሃኒቶች ዕጥረት እና ለደምባንኩ የደም ልየታ ማሽን እና ሌሎችም እንደ ችግር የተነሱ ጥያቄዎችን ቋሚ ኮሚቴው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የሚነጋገርበት መሆኑን ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል ።

የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ አሪፍ መሀመድ እና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በጥንካሬ የተነሱትን ለማስፋትና ትኩረት በሚሹ የተሰጡ አስተያየቶችን እንደ ግብአት ወስደው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አብዲ አሚን የደም ልየታ ማሽን አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው ፤ ቋሚ ኮሚቴው እገዛ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።

2/10/2017

ፓርቹጋል የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች።*********በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው በኔሽንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በፓርቹጋል አሸናፊነት መጠናቀቅ ችሏል።ምሽቱን በተደረገ ተጠባቂ የኔሽ...
08/06/2025

ፓርቹጋል የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች።
*********
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው በኔሽንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በፓርቹጋል አሸናፊነት መጠናቀቅ ችሏል።

ምሽቱን በተደረገ ተጠባቂ የኔሽንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ ስፔን ፖርቹጋልን 2 ለ 1 እየመራች ጨዋታው ወደ ረፍት ቢያመራም ከዕረፍት መልስ ክሪስትያኖ ሮናልዶ አማካኝነት ፓርቹጋል አቻ መሆን ቻለ።

በመጀመሪያው አጋማሽ በስፔን የ 2 ለ 1 መሪነት ቢጠናቀቅም፤ ክርስቲያኖ ሮናልዶ የአቻነቱን ግብ አስቆጥሮ ሀገሩን 2 ለ 2 እንድትሆን አስችሏል።

ሁለቱን የአቻነት ጎሎችን ለስፔን ማርቲን ዙቢሜንዲ እና ሚኬል ኦያዛርባል ግቦቹን ሲያስቆጥሩ፤ ለ ፖርቹጋል ኑኖ ሜንዴዝና ክሪስትያኖ ሮናልዶ አስቆጥሯል።

በዚህም ፖርቹጋል ከ ስፔን ያደረጉት የኔሽንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ መደበኛው 90 ደቂቃና ተጨማሪ 30 ደቂቃም 2 ለ 2 በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠ ፍፁም ቅጣት ምት ፓርቹጋል 5ለ3 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆን ችላለች።

ሁለቱ ክለቦች ከአውን ቀደም በሁሉም ጨዋታ 42 ግዜ የተገናኙ ሲሆን ስፔን 19 ግዜ ስታሸንፍ ፓርቹጋል በ6 ጨዋታ ብቻ ነው ድል የቀናት 17'ቱን ጨዋታ ነጥብ ተጋርተዋል።

በዛሬ ምሽት የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ በ40 ዓመቱና የ5 ግዜ ባላንዶር አሸናፊ ክሪስትያኖ ሮናልዶና በ17 ዓመቱና የዘንድሮ ባላንዶር እጩ ላሚን ያማል መካከል ተደርጎ ቀሮናልዶ አሸናፊነት ተጠናቋል።

በጨዋታው ለሀገሩ ፓርቹጋል አንድ ግብ ማስቆጠር የቻለው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በ88ኛው ደቂቃ እንዲሁም ታዳጊው የእግር ኳስ ኮኮብ ላሚን ያማል በ102ኛ ደቂቃ ተቀይሮ ከሜዳ ወተዋል።

በፋህሚ ዚያድ
01/9/2017

የ5 ግዜ ባላንዶር አሸናፊው ክሪስቲያኖ ሮናልዶና የዘንድሮ ባላንዶር እጩ ላሚን ያማል የዋንጫ ፍልሚያ።*********ከጨዋታው በፊት ሁለቱም ተጫዋቾች ስለሌላው ተጠይቀዋል።የ40 አመቱ ሮናልዶ ...
08/06/2025

የ5 ግዜ ባላንዶር አሸናፊው ክሪስቲያኖ ሮናልዶና የዘንድሮ ባላንዶር እጩ ላሚን ያማል የዋንጫ ፍልሚያ።
*********
ከጨዋታው በፊት ሁለቱም ተጫዋቾች ስለሌላው ተጠይቀዋል።

የ40 አመቱ ሮናልዶ “ይህ ልጅ በጣም በሚረዳው ክለብ እና ብሄራዊ ቡድን ውስጥ ጥሩ ነገሮችን በማድረግ ላይ ይገኛል።

እምቅ ችሎታውን ለማሳየት ጨዋታው ለእሱ ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሮለታል።

"በእንዲህ አይነት ተሰጥኦ ለብዙ አመታት እንድንደሰትበት እባካችሁ ልጁን ጫና ውስጥ አታስገቡት'' በማለት ክሪስትያኖ ተናግሯል።

በፈረንጆቹ ጁላይ 13 18 ዓመት የሚሞላው ያማል በበኩሉ “እሱ የእግር ኳስ ጀግና ነው።

እኔም እንደ ሁሉም ተጫዋቾች ለክርስቲያኖ ትልቅ ክብር አለኝ በማለት ተናግሯል።

በዚህ እድሜ የያማል ችሎታ አስደናቂ ነው።

18 አመት ሳይሞላው የመጨረሻ ጨዋታውን ዛሬ ያደረገ ሲሆን ከስፔን ጋር የአውሮፓ ሻምፒዮንሺፕ፣የአወሮፓ ኔሽንስ ሊግ ዋንጫን እንዲሁም ሁለት የላሊጋ ዋንጫዎችን እና ኮፓ ዴልሬይ ከባርሴሎና ጋር አሳክቷል።

ለባርሴሎና 106 ጊዜ ተጫውቷል፣በዚያን ጊዜ 25 ጎሎችን ሲያስቆጥር ሌላ 18 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቷል።

በአውሮፓ ሻምፒዮና፣ ቻምፒዮንስ ሊግ እና ኔሽንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ላይ ጎል ማስቆጠር የቻለ ሲሆን ሀሙስ ፈረንሳይን 5-4 ባሸነፉበት ጨዋታ ሁለት ጊዜ ጎል ማስቆጠሩ አይዘነጋም።

በኤል ክላሲኮ ሪያል ማድሪድ ላይም አራት ጎሎችን አስቆጥሯል።

ሮናልዶ 18 አመት ሲሞላው ለስፖርቲንግ በ19 ጨዋታዎች 5 ጎሎችን በማስቆጠር 3 አሲስቶችን ብቻ ነው ያስመዘገበው።

በዚህ እድሜው ገና ለፖርቱጋል መጫወት አልያም ትልቅ ዋንጫ ማንሳት አልቻለም።

ሮናልዶ የሊግ ዋንጫ ከማግኘቱ በፊት (ከማንቸስተር ዩናይትድ ጋር) እና 31 ትልቅ አለም አቀፍ ዋንጫን ሲያነሳ 22 አመቱ ነበር።

የሮናልዶ ረጅም ዕድሜ ግን ወደር የለውም።

ያማል በወጣትነቱ ከሮናልዶ የበለጠ ውጤት ያስመዘገበ ቢሆንም እንደ ፖርቹጋላዊው ኮኮብ ሮናልዶ በትልቅ እድሜው ተፅዕኖ ፈጣሪ ለመሆን ጠንክሮ መስራት ይኖርበታል።

ሮናልዶ በ40 አመቱ አሁንም በሳውዲ አረቢያ ሊግም ሆነ በሃገሩ ከፍተኛ የሆነ ግልጋሎቱን በመስጠት ላይ ይገኛል።

ተጫዋቹ በዚህ ክረምት ከአል ናስር ጋር አዲስ ውል ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።

በኔሽንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ ውድድር ጀርመን ላይ ያስቆጠረው 137ኛ ጎሉ ሲሆን 220ኛ ጨዋታውም ነበር።

ይህም በወንዶች አለም አቀፍ እግር ኳስ ሪከርድ ነው።

ክሪስቲያኖ በአጠቃላይ 937 ግቦች አሉት፣በዚህ ሪከርድም ያስመዘገበ ሲሆን በሁለት አመታት ውስጥ 1,000 ለመድረስ በዝግጅት ላይ ይገኛል።

ያማል በተወለደበት ጊዜ እንደ ፈረንጆቹ ጁላይ 2007 ሮናልዶ 46 ዋንጫዎችን አግኝቷል።

ባሎንዶርና ሻምፒዮንስ ሊግ አሸንፏል።

ያማል ትምህርት ከመጀመሩ በፊት የምንግዜም ውድ የእግር ኳስ ተጫዋች ለመሆን በቃ በዚህም ግዜ በ80ሚሊየን ፓውንድ ከዩናይትድ ሪያል ማድሪድን ተቀላቅሏል።

የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በፓርቹጋልና ስፔን መካከል በጀርመን አሊያንዝ አሬና ስታድየም በመደረግ ላይ ይገኛል።

በፋህሚ ዚያድ
01/10/2017

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ የአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ-ጎሮ አደባባይ የኮሪደር ልማት ሥራ ተመለከቱ።*******ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤ...
08/06/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ የአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ-ጎሮ አደባባይ የኮሪደር ልማት ሥራ ተመለከቱ።
*******

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጋር በመሆን የተጠናቀቀውን የአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ-ጎሮ አደባባይ የኮሪደር ልማት ሥራ ዛሬ ተመልክተዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራው 8 ኪሎሜትር የእግረኛ መንገድ፣ 4 ኪሎሜትር የብስክሌት መጋለቢያ፣ የሕዝብ መጸዳጃዎች፣ ደረጃቸውን የጠበቁ ሱቆች፣ በመላው ከተማዋ እንደተገነቡት ያሉ የተለያዩ ዘመናዊ የሕዝብ መገልገያዎች ግንባታን አካትቷል።

ይኽ ለውጥ በከፍተኛ የፍሰት መጨናነቅ በሚታወቀው ከባቢ በእጅጉ ሲፈለግ የነበረውን የፍሰት መሻሻል እና የኑሮ ደረጃ ከፍታ የሰጠ ሆኗል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
1/10/2017

08/06/2025

በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃ አይነቶችና የመረጃ ፍሰት‼️

" ሐሰተኛ መረጃና አሉታዊ ተፅኖን ለመከላከል የመገናኛ ብዙሀን አስተምህሮት እና ንቃትን ማጎልበት ወሳኝ ነው " :- የሚዲያ ባለሞያዎች *********ሐሰተኛ መረጃና አሉታዊ ተፅኖን ለመከላከ...
08/06/2025

" ሐሰተኛ መረጃና አሉታዊ ተፅኖን ለመከላከል የመገናኛ ብዙሀን አስተምህሮት እና ንቃትን ማጎልበት ወሳኝ ነው " :- የሚዲያ ባለሞያዎች
*********

ሐሰተኛ መረጃና አሉታዊ ተፅኖን ለመከላከል የመገናኛ ብዙሀን አስተምህሮት እና ንቃትን ማጎሎበት የላቀ ሚና እንደሚወጣ የሚዲያ ባለሞያዎች ገለፁ።

ማህበራዊ ሚዲያው ካለው ዘርፈ ብዙ ጥቅም ባሻገር በግለሰብና በማህበረሰብ ደረጃም አሉታዊ ተፅኖ የሚያስከትል ለተሳሳተ መረጃዎች ስረጭት የተጋለጠ በመሆኑ መረጃን ከአላማና ትክክለኛነት አንፃር አገናዝቦ መረዳትና ማጣራት እንደሚገባ ተገልጿል።

ማህበራዊ ሚዲያ፣ ሰላም እና የሀገራት ተሞክሮ በሚል ርዕስ በሀረሪ ቲቪ ልዩ ዝግጅት ቆይታ ያደረጉት የሚዲያ ባለሞያዎች ስለ ማህበራዊ ሚዲያ የመረጃ ፍሰት፣ ሐሰተኛ መረጃዎችና የመገናኛ ብዙሐን አስተምህሮን የተመለከቱ ጉዳዮችን አንስተዋል።

ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና መተግበሪያዎች መብዛትና የበይነ መረብ ዕድገት ሳቢያ ማህበራዊ ሚዲያዎች ፈጣንና ሰፊ የመረጃ ማሰራጫና መቀበያ መንገድ እንዲሆኑ ማስቻሉን አስታውሰዋል።

የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ግለሰቦችም መረጃን ለብዙዎች እንዲያሰራጩና እንዲቀበሉ ማስቻሉ እንደ መደበኛ ሚዲያው የመረጃ ትክክለኛነት የማጣራት ሀላፊነትና ተጠያቂነት ያለበት ስርአትን ለመከተል ያልተመቸ መረጃ ሰጪና ተቀባዮችን መፍጠሩ ሐሰተኛ መረጃን ሳይሰራጭ ለመቆጣጠር እንዳይመች ማድረጉን ጠቅሰዋል።

ይህም ከታዳሚዎች ንቃተ መገናኛ ብዙሐን (media literacy) አንፃር ሐሰተኛ መረጃ በሰዎች ግንዛቤና አመለካከት አሉታዊ ተፅኖ የማሳደር አቅሙ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

እንደ ማሳያም ሐሰተኛ መረጃዎቸ በተለያዩ ሐገራት ለፖለቲካዊ አለመረጋጋት፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መንስኤ በመሆን አሉታዊ ተፅኖ ያሳደሩበትን አጋጣሚዎች አንስተዋል።

የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትና ተፅኖን ለመቀነስ የማህበረሰብን ንቃተ መገናኛ ብዙሐን አስተምህሮን ማሳደግ፣ ተጠቃሚዎች የመረጃዎች ይዘትና ትክክለኛነትን ተገቢነት ካላቸው ምንጮች ማጣራትን ጨምሮ መረጃን የማሰራጨት ፋይዳና አላማን በሚገባ ለመገንዘብ ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ ገልፀዋል ።

በሀገራትና አለምአቀፍ ትብብር የማህበራዊ ሚዲያ አበልፃጊ ተቋማቱ መረጃዎች ተጠቃሚዎች ጋር ሲደርሱ በተጋሩበት ብዛት እና ዕይታ መጠን ብቻ በይበልጥ ለሌሎች እንዲደርሱ የማቅረብ ስርአት ( algorithm ) ላይ የተመሰረተው የመረጃ ፍሰትን ከይዘት ትክክለኛነት አንፃር ትኩረት መስጠት የሚቻልበት መፍትሄን እንዲያመጡ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ማህበራዊ ሚዲያው ለበጎ አላማና ጥቅሞች የሚውልበት የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ባለሞያዎቹ በውይይቱ አንስተዋል።

መደበኛ የሚዲያ ተቋማት ከተጣራ መረጃቸው ጋር የማህበራዊ ሚዲያ አማራጭም ያላቸው መሆኑና ነባሩን የመገናኛ ዘዴ ከማህበራዊ ሚዲያና ዘመናዊ መተግበሪያዎች ጋር ማስተሳሰራቸው ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልፀዋል።

ዘጋቢ :- ገዛኸኝ አራጌ
1/10/2017

Address

Red Cross Street
Harar
1331

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Mass Media Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harari Mass Media Agency:

Share