Harari Mass Media Agency

Harari Mass Media Agency Harari Mass Media Agency is a public media operating in Harar, Ethiopia.
ገፃችንን በመከተል ትኩስ ዜና እና መረጃዎችን ያገኛሉ።

14/06/2025
ከዝናብ ወቅት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ችግሮችን ለመቀነስ ፕሮጀክቶች በጥራት እና በፍጥነት መጠናቀቅ እንደሚገባ የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት  ገለጹ።******************...
14/06/2025

ከዝናብ ወቅት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ችግሮችን ለመቀነስ ፕሮጀክቶች በጥራት እና በፍጥነት መጠናቀቅ እንደሚገባ የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት ገለጹ።
*****************************

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት በክልሉ በግንባታ ላይ ያሉ አራት የመንገድ ፕሮጀክቶችን እና በመገንባት ላይ ያለውን አዲስ የመኪና መነሀሪያን ጎብኝተዋል።

ፕሮጀክቶቹ በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኙ መሆኑን በጉብኝቱ ወቅት ማብራሪያ የሰጡት የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢብሳ መሀመድ ገልጸው በቅርቡ ተጠናቀው ለህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ክፍት እንዲሆኑ ቢሮው የሚያደርገው ጥረትና ክትትል አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ ተጠቁሟል።

ፕሮጀክቶቹ የክረምት ወቅት በመሆኑ በተያዘላቸው ጊዜና በፍጥነት እንዲጠናቀቁ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አዲስ እየተገነባ ያለው የመኪና መነሀሪያን የጎበኙት የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ መናሀሪያ ላይ በቀዳሚነት መሰራት ያለበት በዙሪያው ያለው የግድቡ ስራ መሆን አለበት ብለዋል።

ከአጂብ እስከ ሰላም አደባባይ መንገድ ፕሮጀክት መጓተት ለሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እያጋለጠው ነው ብለዋል።

ፕሮጀክቱ ክልሉን ለሌሎች ተጨማሪ ወጪዎች እንዳያጋልጥ ትኩረት ሊሰጠው ይገባልም ብለዋል።

ከገስት ሃውስ ወደ ሀረር ቢራ መንገድ ያለው ፕሮጀክት የመንገዱን መብራት እና አረንጓዴ መብራት በፍጥነት ማከናወን እንደሚገባ አባላቱ ተናግረዋል።

እንዲሁም የገንደ ፌሮ መንደር እና ሚአይ ገጠር መንደርን የሚያገናኘው የመንገድ ፕሮጀክት በፍጥነትና በጥራት ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ከእንደራሴ እስከ ጁኒየር መካከል ያለው መንገድ በተቻለ ፍጥነት አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች ተሟልቶለት የግንባታ ሂደቱ መከናወን አለበት ብለዋል።

የቋሚ ኮምቴ አባላቱ እነዚህ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲጠናቀቁ ቁጥጥርና ክትትል እንዴት እየተሰራ ነው በሚለው ላይ ሃሳባቸውንና ጥያቄያቸውን አቅርበዋል።

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብሳ መሀመድ ከአባላቱ ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን ፕሮጀክቶቹን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት የሚሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

በአንዳንድ ፕሮጀክቶች ሂደት ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ግንባታና የኢትዮ ቴሌኮም ሥራዎች ፈታኝ እንደሆኑባቸው ገልጸዋል።

በተጨማሪም ኮንትራክተሮች ወደ ስራ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ ተጨማሪ በጀት የጠየቁ ሲሆን በአጂብ እና ሰላም አደባባይ መካከል ያለው ፕሮጀክትም ከፍተኛ ተጨማሪ በጀት ተጠይቋል ብለዋል ።

ስራዎቹ ወቅቱን የጠበቀና ጥራት ባለው መልኩ እየተሰሩ ናቸው ብለዋል።

በመጨረሻም የኢኮኖሚ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጅብሪል መሀመድ በገንደፌሮ መንደር የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በአፋጣኝ ሊጠናቀቁ ይገባል ብለዋል።

የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲተገበሩና እየተጀመሩ ያሉ ፕሮጀክቶች ለሌሎች የበጀት ችግሮች እንዳይጋለጡ ቁጥጥርና ክትትል እንዲደረግ አቅጣጫ በማስቀመጥ ጉብኝቱን አጠቃለዋል።

ዘጋቢ :-አብዲ ኡስማን
07/10/17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ : https://www.youtube.com/

ቴሌግራም: https://t.me/hararimassmediaagency

" የሃይማኖት ተቋማት ሰላም፣ ፍቅር እና አብሮነትን በማስተሳሰር ረገድ አበርክቶአቸው የላቀ ነው " :- አቶ ቶፊቅ መሀመድ *********የሃይማኖት ተቋማት ሰላም ፣ ፍቅር እና አብሮነትን በ...
14/06/2025

" የሃይማኖት ተቋማት ሰላም፣ ፍቅር እና አብሮነትን በማስተሳሰር ረገድ አበርክቶአቸው የላቀ ነው " :- አቶ ቶፊቅ መሀመድ
*********

የሃይማኖት ተቋማት ሰላም ፣ ፍቅር እና አብሮነትን በማስተሳሰር ረገድ አበርክቶአቸው የላቀ ነው ሲሉ የሀረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ ገለፁ።

የሐረሪ ክልል አራተኛውን ሀገር አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ እንዲያዘጋጅ መመረጡ የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው እለት የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዋንጫ ሀረር ከተማ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጓል ።

በመድረኩ ያነጋገርናቸው የሀረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ እንደገለፁት ክልሉ 4ተኛውን የሀይማኖት ተቋማት ኮንፍረንስ ለማዘጋጀት መመረጡን ገልፀዋል።

ይህም ለሀረር መልካም አጋጣሚ መሆኑን የገለፁት ሀላፊው ሀረር የምትታወቅበትን የሰላም የመቻቻል እሴቷን ለሌሎች ለማሳየት እድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።

የሃይማኖት ተቋማት ሰላምን፣ ፍቅርን እና አብሮነትን በማስተሳሰር ረገድ አበርክቶአቸው የላቀ መሆኑን ገልፀው በክልሉ ሰላም ለማደፍረስ የሚተጉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አስታውቀዋል።

ኮንፍረንሱም በተሳካ ሁኔታ በክልሉ እንዲካሄድ ዝግጅቶች ከወዲሁ መጀመራቸውን በመግለፅ ባለድርሻ አካላትም የበኩላቸውን ሀላፊነት ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

በእለቱ በክልሉ የሚገኙ የሀይማኖት አባቶች ባስተላለፉት መልእክት የኮንፍረንሱ አላማ በሀገራችን አንዳንድ አካባቢዎች እየታየ ያለው አለመግባባት እንዲቆምና በየአካባቢው ዘላቂ ሰላም እንዲኖር ለማስቻል መሆኑን ገልፀዋል።

ሀረር የምትታወቅበትን የሰላም ተምሳሌትነቷም ዘላቂ ለማድረግ ሁሉ በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ አስታውቀዋል።

የሀይማኖት ተቋማት ና የሀገር ሽማግሌዎች የእርቅና የሰላም መልእክተኞች እንደመሆናቸው የተሰጣቸውን ሀላፊነት እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል ።

አራተኛው የሀይማኖት ሀገር አቀፍ ኮንፍረንስ ከሐምሌ 28 - 29 ለሁለት ቀናት በሀረር ከተማ የሚካሄድ ይሆናል።

ሦስተኛው የሃይማኖት ጉባኤ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ "ሃይማኖቶች ለሰላም፣ ለመከባበር እና ለአብሮነት" በሚል መሪ መልዕክት በባሕርዳር ከተማ መካሄዱ ይታወቃል።

ዘጋቢ :- ይድነቃቸው ጌታቸው
07/10/17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ : https://www.youtube.com/

ቴሌግራም: https://t.me/hararimassmediaagency

14/06/2025

የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽኑ የነገዋን ኢትዮጵያ የምንሰራበት ትልቅ ሀብት የያዘ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
********
የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን የነገዋን ኢትዮጵያ የምንሰራበት እና የምንገነባበት ትልቅ ሀብት የያዘ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ኤግዚቢሽኑ ልጆች የነገ ማንነታቸው እንዲሰራ እና የነገ መሻታቸው እውን እንዲሆን የሚያደርግ ነውም ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ክፍል ዛሬ በይፋ ተከፍቷል።

ኤግዚቢሽኑ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የኢትዮጵያ ምላሽ፣ ግብርና፣ የውኃ ኃይል እና ኢነርጂ፣ ኤሮኖቲክስ እና አቪየሽን ላይ ያተኮሩ አምስት የዐውደ ርዕይ ምድቦችን የያዘ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሳይንስ ሙዚየም ሕንጻ ከሁለት ዓመት ገደማ በፊት ተገንብቶ በጊዜያዊ ኤግዚቢሽን መመረቁን አስታውሰዋል።

ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ከፍተኛ ሀብት መጠየቁን ጠቁመው በጣም ጠቃሚ ነገር የያዘ መሆኑንና ነገን የምንሰራበት ሙዚየም እዚህ ነው ያለው ሲሉ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያውያን ነገን መስራት ነገን መለወጥ ከፈለጉ ልጆቻቸውን ወደ ኤግዚቢሽኑ ስፍራ ሊያመጧቸው እንደሚገባም አመልክተዋል።

ልጆች በሙዚየሙ ያሉ ነገሮችን በተግባር በማየት የነገ ማንነታቸውን መስራት እና የነገ መሻታቸውን እውን ማድረግ ይችላሉ ሲሉም ገልጸዋል።

ኤግዚቢሽኑ ለልጆች ታላቅ በረከት ይዞ መጥቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልጆች ቴክኖሎጂን በሚገባ እንዲጠቀስሙና አልፎም ፈጣሪ እንዲሆኑ በር የሚከፍት ነው ብለዋል።

ወላጆች ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ለልጆች ትልቅ ዕድል መሆኑን ተገንዝበው ወደ ስፍራው ይዘዋቸው እንዲመጡ እና መልካም ዘርን እንዲዘሩባቸው አስገንዝበዋል።

ይህንን እያየ ያደገ ልጅ ጥበብ እና እውቀትን በማዳበር ነገ ሀገሩን የሚጠብቅ፣ ሀገር የሚያበለጽግ፣ ሀገር የሚያለማ እና ሀገር የሚያጸና ይሆናል ሲሉም ተናግረዋል።

እንደ ኢዜአ ዘገባ መምህራን፣ ተመራማሪዎችና ነገን መስራት የሚፈልጉ ሰዎች በሙሉ ኤግዚቢሽኑን እንዲጎበኙ ጥሪ አስተላልፈዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቋሚ ኤግዚቢሽኑ ግንባታ ድጋፍ ላደረጉ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል።

7/10/2017

በከተሞች የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ ነው፦ ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ********የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያዘጋጀው ምዕራፍ ሁለት 20 ኛው ‘ስለኢትዮጵያ’ የውይይት መድረ...
14/06/2025

በከተሞች የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ ነው፦ ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ
********

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያዘጋጀው ምዕራፍ ሁለት 20 ኛው ‘ስለኢትዮጵያ’ የውይይት መድረክ "መሰረተ ልማት ስለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ አስተዳደር ተካሂዷል።

ውይይቱን የመሩት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ መንግስት በሁሉም ዘርፎች የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋት የሚያስችሉ ቁልፍ የሆኑ ተግባራትን እየከወነ ይገኛል ብለዋል።

መሰረተ ልማቶች ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ስኬት ከፍተኛ አበርክቶ እንዳላቸው የገለፁት ወ/ሮ ጫልቱ ለዘርፉ እድገት በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።

ዜጎች ለመሰረተ ልማት አውታሮች የሚያደርጉትን ጥበቃና እንክብካቤ ማጠናከር እንዳለባቸውም አመልክተዋል።

የመሰረተ ልማት አውታሮች ለሀገረ መንግስት ግንባታ ካላቸው ጠቀሜታ አንፃር መንግስት ለዘርፉ እድገት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው "የትራንስፖርት መሰረተ ልማት እድገት" በሚል ርዕስ ባቀረቡት ሃሳብ ከትራንስፖርት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው ስራዎች ለሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ አበርክቶ እንዳላቸው ገልፀዋል።

በዚሁም መንግስት የዘርፉን ተደራሽነት ለማስፋት ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ በዘርፉ የዜጎችን ተጠቃሚነትን ያሻሻለ ለውጥ ተመዝግቧል ብለዋል።

ለትራንስፖርት ዘርፉ አስቻይ የሆነ የመንገድ መሰረተ ልማትን ለማስፉት በተሰጠው ትኩረት 26 ሺ ኪ.ሜ የነበረው የመንገድ መሰረተ ልማት ሽፋንን ባለፉት 6 አመታት ወደ 175ሺ ኪ.ሜ ማሳደግ መቻሉን ገልፀዋል።

በቀጣይም የትራንስፖርት ዘርፉን ለማዘመን እየተካሄዱ ያሉ ተግባራት ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በበኩላቸው ለቴሌኮምና ዲጂታል መሰረተ ልማቶች በተሰጠው ትኩረት በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ከ92 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚና ከ52 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ደግሞ የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

በቀጣይም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ትኩረት እንደተሰጣቸውም ገልፀዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ድኤታ ዶክተር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ "የሀይል አቅርቦት እድገትና የኢነርጂ መሰረተ ልማት" በሚል ርዕስ ባቀረቡት ሃሳብ ከለውጡ ወዲህ የኢነርጂ መሰረተ ልማትን ለማስፋት ያስቻሉ ስራዎች መካሄዳቸውን ገልፀዋል።

የታዳሽ ኢነርጂ ተደራሽነትን ማስፋት፣ አማራጭ የሀይል ምንጮችን ማሳደግ፣ የኢነርጂ ብቃትን ማሻሻልና መሰረታዊ የሆኑ የሀይል አቅርቦትን ማሻሻል ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን ጨምረው ገልፀዋል።

በውይይት መድረኩ ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፣ የኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ድኤታ ዶክተር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀርን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

ዘጋቢ፦ሄኖክ ግርማ
07/10/17

አገልግሎቱ ማህበራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተጀመረዉን ስራ እያገዘ ነው-ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ ሮዛ ኡመርየማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድን አገልግሎት ፣መንግስስት ማህበራዊ ብልፅግናን ...
14/06/2025

አገልግሎቱ ማህበራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተጀመረዉን ስራ እያገዘ ነው-ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ ሮዛ ኡመር

የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድን አገልግሎት ፣መንግስስት ማህበራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የጀመረዉን ስራ እያገዘ እንደሚገኘ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ ሮዛ ኡመር ገለፁ።

የሐረሪ ክልል የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ቦርድ በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድን እየተሰጡ የሚገኙ አገልግሎቶችን ገምግሟል።

በውይይቱ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር እንደለገፁት የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ማህበረሰቡ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት እንዲያገኝ እያስቻለ ነው።

በተለይ ከፍለው መታከም የማይችሉ አቅመ ደካማ ዜጎች አስፈላጊውን የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ በማስቻል አበርክቶው የጎላ መሆኑንም ገልፀዋል።

ይህም መንግስት ማህበራዊ ብልፅግናን በማረጋገጥጥ ጤናማ፣አምራች እና ተወዳዳሪ የሆነ ትውልድን ለማፍራት እያደረገው የሚገኘውን ጥረት እያገዘ እንደሚገኝ አክለዋል።

የማህበረሰብ የጤና መድህን አገልግሎት የጤና ተቋማት አቅምና የሚሰጡትን አገልግሎት እያሳደገ እንደሚገኝመ ጠቁመዋል።

ማህበራዊ ብልፅግናንን ለማረጋገጥ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት አበርክቶው የጎላ በመሆኑ በክልሉ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንዲገኝም ጠቁመዋል።

በክልሉ በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት የተመዘገበውን ስኬት በውጤት አጅቦ ለማስቀጠል ርብርብ እንደሚደረግም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ ጠቁመዋል።

7/10/2017

የሀረሪ ቋንቋ በሁሉም ትምህርት ቤቶች  በሚፈለገው ልክ እንዲሰጥ በትኩረት  መሰራቱን የሀረሪ ክልል  ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።*******የሀረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በሀረሪ ክልል...
14/06/2025

የሀረሪ ቋንቋ በሁሉም ትምህርት ቤቶች በሚፈለገው ልክ እንዲሰጥ በትኩረት መሰራቱን የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
*******
የሀረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ አካሄደዋል ።

የሀረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ አካሂደዋል።

በግምገማው ላይ የቢሮውን የ 2017 በጀት አመት አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ዘካሪያ አብዱለዚዝ በክልሉ በከተማና ገጠር በሁሉም ትምህርት ቤቶች የሀረሪ ቋንቋ ትምህርት በምፈለገው ልክ እንዲሰጥ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን ገልፀዋል።

በአንድ አንድ ት/ቤቶች ይታይ የነበረውን የሀረሪ ቋንቋ መምህራን እጥረት መቀረፍ የተቻለ መሆኑን ገልፀዋል።

የተማሪዎችን መማሪያ መፅሀፍት ለማዳረስም እየተሰራ መሆኑን አቶ ዘካሪያ አክለው ገልፀዋል።

ትውልድን በስነ ምግባርም ጭምር ለማነጽ ግብረ ገብ ትምህርትንም እንዲማሩ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ወጣቱ ወደ መምህርነት ሞያ መቀላቀል ፍላጎት መጥፋት እና ያሉ መምህራኖችም ወደ ሌላ የስራ መስክ መፍለስ የዘርፉ ተግዳሮት መሆኑን በሪፖርቱ ቀርበዋል።

የቀረበውን ሪፖርት መሰረት በማድረግ አስተያየታቸውን የሰጡት የሀረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አሚና አብዱልከሪም ባለፉት ጊዜያት ቢሮው በትምህርት ቤቶች ሀረሪ ቋንቋ መምህራን እንዲሟሉ ያደረገው ጥረት የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑን ገልፀዋል።

ከመፅሀፍት አቅርቦት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ማጣቀሻ ና አጋዥ መፅሀፍቶች፣ የመምህራን መመሪያዎች ሊዘጋጁ ይገባል ብለዋል።

ከባለድርሻ አካላት ጋርም በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

የሀረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ቋሚ ኮምቴ ሰብሳቢዎችና አባላት የተለያዩ አስተያየት እና ሀሳብ ያነሱ ሲሆን በተለይ በመምህራን ኮሌጅ መምህራንን አስተምሮ ማስመረቅ ብቻ ሳይሆን በሞያው ብቁ ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል ብለዋል።

በመጨረሻም የሀረሪ ብሔራዊ ጉባዔ ትምህርትና ቋንቋ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀምዲ ሰልሀዲን አቅጣጫዎችን ያስቀመጡ ሲሆን ወጣቶች ወደ መምህርነት ሙያ እንዲመጡና ሞያውን እንዲወዱ የተለያዩ ንቅናቄዎች መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።

በስራ ላይ ያሉት መምህራንም ትውልድ የመገንባት ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ በትኩረት መሰራት እንዳለበት ና በቀጣይ ትምህርት ዘመን የተሻለ ስራ ለመስራት ከባለድርሻ አካላት ጋር ቁርኝትን በማጠናከር የጋራ እቅድ አቅዶ መሰራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

ሀምዛ ዩሱፍ
07/10/17

የሐረሪ ክልል አራተኛውን የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ለማዘጋጀት ዋንጫውን ተረከበ። **********የሐረሪ ክልል አራተኛውን የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ለማዘጋጀት ዋንጫውን ተረክቧል። በ...
14/06/2025

የሐረሪ ክልል አራተኛውን የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ለማዘጋጀት ዋንጫውን ተረከበ።
**********
የሐረሪ ክልል አራተኛውን የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ለማዘጋጀት ዋንጫውን ተረክቧል።

በዛሬው እለት ዋንጫው ሀረር ሲደርስ ከሀማሬሳ ጀምሮ ደማቅ አቀባበል እየተደረገ ይገኛል።

ሦስተኛው የሃይማኖት ጉባኤ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ "ሃይማኖቶች ለሰላም፣ ለመከባበር እና ለአብሮነት" በሚል መሪ መልዕክት በባሕርዳር ከተማ መካሄዱ ይታወቃል።

ዘጋቢ ፦ይድነቃየው ጌታቸው
7/10/2017

ምህራፍ ሁለት ‘ስለኢትዮጵ' መድረክ በድሬዳዋ እየተካሄደ ይገኛል።******ምህራፍ ሁለት 20 ኛው ‘ስለኢትዮጵያ’ የውይይት መድረክ "መሰረተ ልማት ስለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ አ...
14/06/2025

ምህራፍ ሁለት ‘ስለኢትዮጵ' መድረክ በድሬዳዋ እየተካሄደ ይገኛል።
******
ምህራፍ ሁለት 20 ኛው ‘ስለኢትዮጵያ’ የውይይት መድረክ "መሰረተ ልማት ስለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ ይገኛል።

በውይይት መድረኩ ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፣ የኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ድኤታ ዶክተር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀርን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

ዘጋቢ፦ሄኖክ ግርማ
07/10/17

13/06/2025

ኢራን በእስራኤል ከተሞች ላይ የሚሳኤል ጥቃት ፈፀመች
*********
ኢራን በእስራኤል ለተፈፀመባት የአየር ጥቃት የአጸፋ ምላሽ ነው ያለችውን የሚሳኤል ጥቃት በእስራኤል ከተሞች ላይ ፈፅማለች፡፡

የኢራን መንግስት ዜና አገልግሎትን ጠቅሶ አልጀዚራ እንደዘገበው ኢራን አድቃቂ የሚል ስያሜ የሰጠችውን የበቀል እርምጃ ማምሻውን መጀመሯ ታውቋል።

የኢራንን ሚሳኤሎች ለማክሸፍ እስራኤል አይረን ዶም ፀረ ሚሳኤሎችን መተኮሷም ነው የተገለፀው፡፡

ኢራን በፈፀመችው ጥቃት ቴል አቪቭ በሚገኘው የእስራኤል መከላከያ መስሪያ ቤት አቅራቢያ የእሳት አደጋ መከሰቱ ተነግሯል፡፡

በተጨማሪም ሰባት በሚሆኑ በማእከላዊ እስራኤል በሚገኙ ቦታዎች ሚሳኤሎች መውደቃቸው ተገልጿል።

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ምሽት ላይ ባደረጉት ንግግር ባለፉት 24 ሰአታት ውስጥ የእስራኤል ሃይሎች ከፍተኛ የጦር አዛዦችን ፣ ከፍተኛ የኑክሌር ሳይንቲስቶችን እና ከፍተኛውን የባላስቲክ ሚሳኤል ጦር መሳሪያ እንዳስወገዱ ተናግረዋል።

ኔታንያሁ አክለውም ተጨማሪ ጥቃት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው በኢራን ላይ የሚደረገው መጪው ጥቃት ከፍተኛ እንደሚሆን አስታውቀዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክርቤት በእስራኤልና ኢራን ጉዳይ ለመምከር አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቶ በአሁኑ ሰዓት ኒውዮርክ በሚገኘው ዋና መስርያቤቱ ውይይት መጀመራቸውን የዘገበው ደግሞ ቢቢሲ ነው ።

6/10/2017

የመምህራን ጥያቄዎች በግልፅ መነጋገር ከተቻለባቸው መፈታት ይችላሉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) *********ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተወጣ...
13/06/2025

የመምህራን ጥያቄዎች በግልፅ መነጋገር ከተቻለባቸው መፈታት ይችላሉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*********

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተወጣጡ መምህራን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በውይይታቸው የመምህራን ጥያቄዎች በግልፅ መነጋገር ከተቻለባቸው መፈታት እንደሚችሉ አንስተዋል፡፡

ከመምህራን ብቃት፣ ከስልጠና እና ከትምህርት ፍኖተ ካርታ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች ፍተሻ እንደሚያስፈልጋቸውም ተናግረዋል፡፡

አሰራሮችን፣ ህጎችን እና ስትራቴጂዎችን በመፈተሸ ትላንት በነበረው እውቀት የተሰሩ ስራዎች የጎደሉትን ነገሮች በመለየት ለመፍትሄ ይሰራል ብለዋል፡፡

በድህረ እውነት ዘመን መምህራን እውነትና እውቀትን የማጣራት መሰረት ሊሆኑ ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ካለፈ ታሪክ ተገቢውን ትምህርት መውሰድ ይገባል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ኢቢሲ እንደዘገበው መምህራን ያለውን ችግር እና እድል በቅጡ ሊረዱ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

የመምህራን ጥያቄዎች በሌላ ዘርፍ ከተሰማሩ ሠራተኞች ጋር በማሰናሰል በፖሊሲ ማዕቀፍ በሒደት ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራም ገልጸዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

6/10/2017

13/06/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተወጣጡ መምህራን ጋር ያካሄዱት ውይይት።

Address

Red Cross Street
Harar
1331

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Mass Media Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harari Mass Media Agency:

Share