ማህደረ አማራ-mahder amhara

ማህደረ አማራ-mahder amhara ማህደረ አማራ የናንተ ድምፅ

31/07/2024



የባህርዳር ዙሪያን ጨምሮ በጎጃም ክፍለ ሀገር በርካታ አካባቢዎች የድሮን ቅኝት ተደርጓል።

አገዛዙ በበርካታ ግንባሮች እየደረሰበት ካለው በትርና ምት አኳያ ማህበረሰባዊ ውድመት ለማድረስ የድሮን ቅኝቶች ያደረገ በመሆኑ ሁሉም ጠረንቃቄ እንዲያደርግ መረጃዎችን እናጋራ።

✍✍✍ከዚህ በፊት ከኢሳት በአማራ ጉዳይ ተባርሬ እና ተከስሼ ነበር ፍርድ ቤት ነፃ ነህ ብሎኝ ከነካሳው አሸነፍኩ! በኬሚሴ ጉዳይም ታፍኜ ተጥያለሁ በኋላም ከጓዶቼ ጋር ለወራት ታስሬ ነፃ ተብያ...
05/11/2023

✍✍✍
ከዚህ በፊት ከኢሳት በአማራ ጉዳይ ተባርሬ እና ተከስሼ ነበር ፍርድ ቤት ነፃ ነህ ብሎኝ ከነካሳው አሸነፍኩ! በኬሚሴ ጉዳይም ታፍኜ ተጥያለሁ በኋላም ከጓዶቼ ጋር ለወራት ታስሬ ነፃ ተብያለሁ!
አሁንም እውነትን እስከያዝን ድረስ ነፃ እንወጣለን በርግጥ እኛ የጮህንለት እና የታሰርንበትን ትግል ከእኛ አልፎ ህዝቡ ተቀብሎታል ትግሉ የህዝብ ስለሆነ እንኳን መታሰር መሞትንም በፀጋ እንቀበለዋለን ትግላችን ተፋፍሞ ከዜሮ ስለጀመረ እናሸንፋለን የአማራ አንድ መሆን እንደታሰርን እንዳይሰማን አድርጎናል።
ጎበዜ ሲሳይ(ከማጎሪያ ቤት)
💚💛❤

የእናትዋ ጎንደር እና የካሲናው ጎጃም ሙዚቃዎች አቀናባሪ እሥራኤል መስፍን ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል😭😭😭ሰው ለካ የሚኖረው በተስፋ ነው❗️   | አንድ ቀን ቢሮ ውስጥ ከስቱዲዮ ወጦ ብቻየን ...
30/10/2023

የእናትዋ ጎንደር እና የካሲናው ጎጃም ሙዚቃዎች አቀናባሪ እሥራኤል መስፍን ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል😭😭😭

ሰው ለካ የሚኖረው በተስፋ ነው❗️

| አንድ ቀን ቢሮ ውስጥ ከስቱዲዮ ወጦ ብቻየን አገኘኝና የተወደደ ሰላምታውን ሰጥቶኝ ተቀመጠ።

ትንሽ ቆይቶ "Man ~ ይቺ የምኖራት ዕድሜ በልጄ ምክንያት የተሰጠችኝ እንደሆነች ታውቃለህ ?" አለኝ።

"እንዴት?!" አልሁት

"ወደ ህንድ ሀገር ለህክምና እንደምሄድ ሳውቅ በህይወት እንደማልመለስ ልቤ ደጋግሞ ይነግረኝ ነበር። ጓደኛዬ ነፍሰ ጡር እንደሆነች ስትነግረኝ ውስጤ ተለወጠ። ታክሜ በሕይወት ተመልሼ ልጄን እንደማይ እርግጠኛ ሆንሁ። ይሄው አሁን በየቀኑ ሳያት ዕድሜ ትጨምርልኛለች" አለኝ።

እኔም በእምነቱ በተስፋው በጣም ተደነቅሁ።

ዛሬ ግን እሥራኤል ደከመ ከዚህ በላይ በተስፋ አልቀጠለም፤ በሕክምና ሳለ ሆስፒታል ውስጥ አረፈ።

ዕረፍተ ነፍስ ያድልህ❗️😭😭😭
የታደለ ሮባ ኢትዮጵያ
የአስቻለው ፈጠነ እናትዋ ጎንደር እና ካሲናው ጎጃም
የአንድ ሴት ልጅ አባት ነው።

የሙዚቃዎች አቀናባሪ እሥራኤል መስፍን ሥርዓተ ቀብሩ ዛሬ ጥቅምት 17 ቀን 2016ዓ.ም በ9:00 ሰዓት የካ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ጀርባ ሚሌኒየም ፓርክ ውስጥ ይፈፀማል ።

ነፍስህ በሰላም ትረፍ 💔
ወንድምህ አበበ ጥላሁን

23/10/2023

ከቡሬ ወደ ቁጭ ዛሬ ጠዋት በ 30 መኪና ተጭኖ የሄደው ወንበዴ ቡድን 9 መኪና ሙትና ቁስለኛ ይዞ ወደ ቡሬ ተመልሷል!
ፋኖ 💪

"…ለማንኛውም ይሄ የምታዩት የስንዴ ልመና አቁማ ስንዴ መሸጥ ኤክስፖርት ማድረግ በጀመረችዋ የዘመነ ብልጽግናዋ ኢትዮጵያ ኦሮሚያ ወለጋ እና ሰሜን ጎንደር ውስጥ ነው። "…7 ሚልዮን ህጻናት ወ...
23/10/2023

"…ለማንኛውም ይሄ የምታዩት የስንዴ ልመና አቁማ ስንዴ መሸጥ ኤክስፖርት ማድረግ በጀመረችዋ የዘመነ ብልጽግናዋ ኢትዮጵያ ኦሮሚያ ወለጋ እና ሰሜን ጎንደር ውስጥ ነው።

"…7 ሚልዮን ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት አልሄዱም። ለድጋሚ ጦርነት ማሟቁን ሁሉም ተያይዞታል። ትግሬም እርሙን ካወጣ በኋላ በሰለስቱ ቀይ ባሕር ወደብ ወደብ ብሎ ሊሞት ነው። ኦሮሞም ያለ ገላነ ዲማ ሌላ ወሬ ትቷል። እነ ደሳለኝ መሃል ሜዳ የከሰረው ፓስተር እንኳ ኤርትራን ይሞልጫት፣ ትግሬን ጮቤ ያስረግጥ ጀምሯል።

"…የተለቪዥኗ ኢትዮጵያ ማርና ወተት የምታፈስ ከንዓን ናት፣ ገሃዷ የእውን ዓለሟ ኢትዮጵያ ግን ራብ፣ ጠኔ፣ ጦርነት፣ ወረርሽ፣ ወባና ኮሌራ ሕዝቧን እንዲህ እንደምታዩት እየረፈረፈ የደቀቀች ሆናለች። ጨቅላ መሪዋ ደግሞ ሁሉን ትቶ በካምቦሎጆ ከጎረምሶች ጋር ቅሪላ ሲገፋ ይውላል።

ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም (ልጅ ያሬድ) ማረሚያ ቤት እንዲወርድ ታዘዘ ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም ባልቻ በቅጽል ሥሙ (ልጅ ያሬድ) በቀረበበት ተደራራቢ ክስ ማረሚያ ቤት እንዲወርድ በፌደራል ከፍተኛ...
18/10/2023

ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም (ልጅ ያሬድ) ማረሚያ ቤት እንዲወርድ ታዘዘ
ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም ባልቻ በቅጽል ሥሙ (ልጅ ያሬድ) በቀረበበት ተደራራቢ ክስ ማረሚያ ቤት እንዲወርድ በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 1ኛ የፀረ-ሽብርና የሕገ-መንግስት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ትዕዛዝ ተላልፏል።የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም ባልቻ በቅጽል ሥሙ( ልጅ ያሬድ) በተባለ ግለሰብ ላይ ተደራራቢ ክሶችን አቅርቧል።
በተለይም በኮምፒዩተር የሚፈጸም ወንጀል ድንጋጌን መተላለፍ፣ የቤተክርስቲያንና የሰዎችን ክብርና መልካም ስም በማጉደፍ፣ ጥላቻ ንግግር ማሰራጨት የሚሉ ነጥቦች ይገኙበታል።ክሱ ከደረሰው በኋላ ተከሳሹ ያቀረበውን የዋስትና ጥያቄው ፍርድ ቤቱ ውድቅ በማድረግ በማረሚያ ቤት ሆኖ ጉዳዩን እንዲከታተል አዟል።
ይሁንና ተከሳሹ ችሎት በቀረበበት ጊዜ ዐቃቤ ሕግ ለቤተክርስቲያን ክብር፣ ለማህበረሰቡ ስነልቦና፣ እሴትና ባህል ሲባል በክሱ ላይ የቀረቡ ዝርዝር ነጥቦች እንዳይታተም በሚዲያ እንዳይቀርብ እንዲሁም ችሎቱ በዝግ እንዲሆን አቤቱታ አቅርቧል።አቤቱታውን የመረመረው ፍርድ ቤቱም የማህበረሰቡን ክብርና ስነልቦናን ከግምት ውስጥ በማስገባት የክሱ ዝርዝር ጉዳይ በሚዲያ እንዳይሰራጭ ችሎቱ በዝግ እንዲሆን ብይን መስጠቱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።ልጅ ያሬድ በቅርቡ ለማህበራዊ ትስስር ገፅ ተከታዮቹ ባጋራው የቲክቶክ ቪዲዮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክብር የሚነካ እና የእምነቱ ተከታዮችን ያስቆጣ ተግባር መፈጸሙን ተከትሎ፤ በርካቶች "በሕግ መጠየቅ አለበት" የሚል ሃሳባቸውን ሲያንፀባርቁ እንደነበር ይታወሳል።ይህንንም ተከትሎ በቲክቶክ ቪዲዮ ባጋራው ሕገ ወጥ ይዘት ያለው መልዕክት ሳቢያ፤ ነሃሴ 27/2015 በቁጥጥር ሥር መዋሉ ይታወቃል።

የትምህርትና የጤና ተቋማትን ለጦር መጋዘን እና ካምፕነት የሚጠቀም ብቸኛው ደንቆሮ ስርአት  #ብልፅግና ይባላል።ደስ የሚለው ነገር እንደ ቅጠል እየረ'ገፋችሁ መሆኑ ነው
18/10/2023

የትምህርትና የጤና ተቋማትን ለጦር መጋዘን እና ካምፕነት የሚጠቀም ብቸኛው ደንቆሮ ስርአት #ብልፅግና ይባላል።

ደስ የሚለው ነገር እንደ ቅጠል እየረ'ገፋችሁ መሆኑ ነው

18/10/2023

የመጀመሪያው መታመን በእግዚአብሔር ሲሆን
ቀጣዩ ግን እግዚአብሔር የደገፈው የፋኖ ክንድ ነው በእውነቱ እየሆነ ያለው ተዓምር ነው የበላይ ትንፋሾች የኦነጉን መንግሥት ትንፋሽ እያሳጠሩት ነው አማራ💚💛❤💪

17/10/2023

ንፁሃንን በመጨፍጨፍ ህዝብን ማንበርከክ አይቻልም!

ሰሜን ሸዋ ዞን በረኸት ወረዳ ከማለዳዉ 2:30 ላይ በከተማዋ በሚገኘዉ አባይ ባንክ እና ፖሊስ ጣቢያዉ መሀከል በተፈፀመ የድሮን ጥቃት አንድ ሹፌርን ጨምሮ ሻይ ቤት በመስራት የሚተዳደሩ ንፁሀን ዜጎች ተገድለዋል።
እንዲሁም ቀትር 6 ሰዐት ላይ በድጋሚ በከተማዋ 04 ቀበሌ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ከከተማዉ ሸሽተዉ ወደ ገጠር በመኪና ተሳፍረዉ በማቅናት ላይ የነበሩ በርካታ ንፁሀን ዜጎችን ተገድለዋል💔

የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ እና ጨፍጫፊ ሠራዊት ደብረ ማርቆስ፤ አብማ ማርያም ቤተ-ክርስቲያን ላይ የፈጸመው የከባድ መሣሪያ ድብደባ!
17/10/2023

የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ እና ጨፍጫፊ ሠራዊት ደብረ ማርቆስ፤ አብማ ማርያም ቤተ-ክርስቲያን ላይ የፈጸመው የከባድ መሣሪያ ድብደባ!

በፋሽዝም መሪነት ወደ
17/10/2023

በፋሽዝም መሪነት ወደ

እባካችሁ እናት ቅድስት ቤተክርስቲያንን አታሳዝኗት።
16/10/2023

እባካችሁ እናት ቅድስት ቤተክርስቲያንን አታሳዝኗት።

የትግራይ ኢሊቶችና ፖለቲከኞች አሁንም ድረስ የገደላቸው አማራ እንደሆነ ነው የሚያስቡት። ይገርማል ትላንት ደብረሲና ድረስ መጥተው እህቶቻችንን ደፍረው፣ ማይካድራ ላይ ህዝባችንን በገፍ አርደው...
16/10/2023

የትግራይ ኢሊቶችና ፖለቲከኞች አሁንም ድረስ የገደላቸው አማራ እንደሆነ ነው የሚያስቡት። ይገርማል ትላንት ደብረሲና ድረስ መጥተው እህቶቻችንን ደፍረው፣ ማይካድራ ላይ ህዝባችንን በገፍ አርደው፣ እንዳንማር መማሪያ ትምህርት ቤቶችን አውድመው፣ ታመን እንዳንታከም ሆስፓታሎቻችንን አውድመውብን፣ "ሞኝ አማራ " አህያ አማራ " እያሉ በሙዚቃ ጭምር ህዝባችንን ከሰብአዊነት ደረጃ ዝቅ አድርገው ሲገልፁ እንዳልነበር ዛሬም ፀፀት ሳያድርባቸው እየዛቱ ይገኛሉ። እየታዘብን!

ውሸታቸውን ነው!ቀይ ባሕርን ለኢትዮጵያ አያስቡትም። ውሸታቸውን ነው። አንድ አገር ቀዳሚ ህልውናው  የሚረጋገጠው ጠንካራ ተቋም ሲኖር እንጅ ውሃ ዳር ስላለው ብቻ አይደለም። ተቋም እያፈረሱ በ...
15/10/2023

ውሸታቸውን ነው!

ቀይ ባሕርን ለኢትዮጵያ አያስቡትም። ውሸታቸውን ነው። አንድ አገር ቀዳሚ ህልውናው የሚረጋገጠው ጠንካራ ተቋም ሲኖር እንጅ ውሃ ዳር ስላለው ብቻ አይደለም። ተቋም እያፈረሱ በባሕር አገር አይፀናም። ውሸታቸውን ነው።

ለምሳሌ!

ቴሌ በአማራ ተያዘ ብለው ዘመቱ። የሀሰት መረጃ የሚሰጡ እነ አብይ። ዘማች ኦ ኤም ኤንና የኦነግ ፌስቡከኛ።

የአፋር ጨው በአማራ ባለሀብት ተያዘ ብለው ዘመቱ። የሀሰት መረጃ የሚሰጡት ከብሔር ወጥተን በቀጠና እናስብ የሚሉት እነ አብይ ዘጋቢያቸው ኦ ኤም ኤን።

አሁን ስለ ቀይ ባሕር እያወሩ በልማት ባንክ ዘመቱ። የአማራ ባለሐብት ነው ገንዘቡን የሚወስደው ብለው በሀሰት አስዘመቱ። ኃላፊ ቀየሩ።

አሁን የተቀየረው ሰው የኦሮሚያ የኢኮኖሚ አብዮት የሚል ቡድን አባል ነው። ከዛ ኬኛ አክሲዮን ኃላፊ፣ ቀጥለው ወደ ስንቄ ባንክ አመጡት። ብሔራዊ ባንክ "መስፈርት አያሟላም" አለ። አብይ አህመድ በቀጥታ ደውል "ፍቀዱ" አለ። በግድ ኃላፊ ሆነ። ከዛም ወደ ልማት ባንክ አመጡት። ከበርካታ የሀሰት ዘመቻ በኋላ።

ብርሃነ መስቀል አበበ ሰኚ የሚባለው በራሱ የሚዘባስቅ የሚመስለው ካለ ተሳስቷል። እነ አብይ አጀንዳ አስይዝ እያሉት ነው። በአንድ በኩል በጎሳው ተቋም እየወረረ፣ እያፈረሰ በሌላ በኩል ወደ ወረዳ አንመልከት ይላል። ይህ ቀበሌያም ሁላ።

ንግድ ባንክን በአቤ ሳኖ፣ ገቢዎችን በአዳነች አቤቤ ቀያየሩት። ስለእነዚህ ተቋማት አያወሩም። ዘመድ አዝማድ አጠራቅመውታል። አፍርሰዋቸዋል።

ለአገር መሰረቱ ተቋም ነው። ተቋም እያፈረሰ ባሕር አፋልጉኝ ይላል። ለኢትዮጵያ ባሕር እንደማትፈልጉ የታወቀ ነው። እኛ ኢሬቻ አናከብርም። ለኢሬቻ ቤርሙዳ ትሪያንግልም ካሳሳችሁ ሄዶ ማክበር መብታችሁ ነው።

የባሕር በር የምንፈልገው ለኢትዮጵያ አስበን ነው ግን አትበሉን። ቅጥፈት ነው። ምፅዋን ተጠቀሙ ስትባሉ "አማራ ይጠቀምበታል" ብላችሁ አልተዋችሁትም?

እንጅባራ አሁን…! "…የአናብስቶች ምድር  የእነ ቀኝአዝማች ስሜነህ፣ የእነ አድማስ አላምነህ ሀገር ሳትማ ዳንጊያ፣ የእነ ፊታውራሪ ባይህ፣ የእነ በላይ ዘለቀ ምድር የግዮን መፍለቂያ ሰከላ ከ...
13/10/2023

እንጅባራ አሁን…!

"…የአናብስቶች ምድር የእነ ቀኝአዝማች ስሜነህ፣ የእነ አድማስ አላምነህ ሀገር ሳትማ ዳንጊያ፣ የእነ ፊታውራሪ ባይህ፣ የእነ በላይ ዘለቀ ምድር የግዮን መፍለቂያ ሰከላ ከአገው ምድር ፋኖዎች ጋር በመናበብ ፀረ ዐማራውን ሸንጎን እና ፀረ ሃገር አረመኔውን የኦሮሙማ ሥርዓት በአፍጢሙ ለመድፋት እየተፋለሙ ይገኛል።

"…አሁን ቅንድብ ለይተው በሚመቱት ፋኖዎች የቆሰሉ የአገዛዙ ሁለት ፓትሮል ቁስለኛ እንጅባራ ሆስፒታል የገባ ሲሆን ሌላ ሁለት መኪና ሙሉ ዋይዋይ እያለ የሚጮህ የሸንጎ ቁስለኛ ወደ ቻግኒ እንዲሄድ ተደርጓል። የሚገርመው ከአዘና የሄዱት የእሁዲት ፋኖዎች በአዘና በኩል አድርገው ወደ እንጅባራ ሲመጡ በትንሽ የተኩስ ልውውጥ ነው አዘናን የተቆጣጠሩት ተብሏል። በአዘና በተደረገው ውጊያ ከአገው ሸንጎ 6 ተዋጊዎች በዐማራ ፋኖ ተኩስ ወዲያው የተሸኙ ሲሆን በአዘና እስረኛ በሙሉ በፋኖ ነፃ ወጥቷል።

• አሁን ጉዙ ወደ ግምጃቤት።

• ድል ለዐማራ ፋኖ…!
• ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…!

fecbook- https://www.facebook.com/profile.php?id=100084016098194
Telegram- https://t.me/mahedereamhara

ፀረ  አማራው የአብይ አህመድ ሰራዊት ከባህር ዳር ጥበበ ግዮን ሆስፒታል 6 ታካሚዎችን አውጥቶ በመረሸን የሆስፒታሉ ሰራትኞች እና አስተዳደር ሰራቶችን አባሯል፡፡ በዚህም ሆስፒታሉ ሙሉ በሙሉ ...
13/10/2023

ፀረ አማራው የአብይ አህመድ ሰራዊት ከባህር ዳር ጥበበ ግዮን ሆስፒታል 6 ታካሚዎችን አውጥቶ በመረሸን የሆስፒታሉ ሰራትኞች እና አስተዳደር ሰራቶችን አባሯል፡፡ በዚህም ሆስፒታሉ ሙሉ በሙሉ ስራ አቁሟል። ሆስፒታሉ ውስጥ ተኝተው የሚታከሙና ተመላላሽ ታካሚዎች ህይወት አደጋ ላይ ወድቋል። ይህ ሆስፒታል ከአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለሚመጡ ታማሚዎች የተሻለ ህክምና የሚሰጥበት ተቋም ነበር።

እስካሁን፦
ከፍኖ ተሰላም ሆስፒታል
ከወልዲያ ሆስፒታል
ከጎንደር ሪፈራል ሆስፒታል
ከጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

ታካሚዎችን በማውጣት የመረሸን ተግባር ተፈፅሟል።

ዐማራነት ቃል ኪዳን ነው ፤ ትውልድ ሁሉ ይጠብቀዋል ! ወንድም አስረስ ሳይዛ አውቀዋለሁ። ደፋር ነው። እውቀት የአካዳሚክ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ዕውቀትና ብስለት አለው። ለዐማራ ህዝብ ቃል በ...
13/10/2023

ዐማራነት ቃል ኪዳን ነው ፤ ትውልድ ሁሉ ይጠብቀዋል ! ወንድም አስረስ ሳይዛ አውቀዋለሁ። ደፋር ነው። እውቀት የአካዳሚክ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ዕውቀትና ብስለት አለው።

ለዐማራ ህዝብ ቃል በገባው መሰረት ፤ ቃል ኪዳኑን ሊጠብቅ ጠላትን እየተጋደለ ያለ በዐማራ ፖለቲካ ውስጥ ወሳኝ ሚኖ የሚኖረው ሰው ነው !

ዐማራነት ዘመናትን ይሻገር ዘንድ ድልድይ ከሚሆኑ ሰዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን ፥ በዐማራ ፖለቲካ መስተካከል እና እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ በተለይም ለአለፉት አራት አመታት መስእዋትነት የከፈለ፣ መስመሮችን የገራና ሀሳቦችን ያፈለቀ ጀግና ነው !

የእሱና የኔ ወዳጅነት የተጀመረው የዐማራ ብሄርተኝነት ታንቆ ሊሞት ጫፍ በደረሰበት ወቅት "የዐማራ ባለአደራ መንግስት ይቋቋም" የሚላትን ሀሳብ የወለደ ጊዜ ነው ! ወደፊት በዐማራ ፖለቲካ መስመር ጥራት ላይ ተስፋ ከምጥልባቸው እና በዐማራ ፖለቲካ ማግኘት ከምፈልጋቸው ሰዎች ውስጥ የመጀመሪያው ነው !

እግዚአብሔር የጀግኖችን ክንድ ያበርታ !

@ይድነቃቸው ሸዋንግዛው

13/10/2023

ወራሪው የብልፅግና ሰራዊት በእንጅባራ ውጊያ ከፈተ።

የብልፅግና ሰራዊት ከተማዋን በከባድ መሳሪያ ድምፅ ሰላማን እያደፈረሰ ንፁሀንን እየረሸነ ቢቆይም ከየአቅጣጫው በጥቅሻ ተጠራርተው የመጡት ፋኖዎች በአሁኑ ሰዓት ከተማዋን በመክበብ ባንዳውን በጥይት አረር እያነደዱት ይገኛሉ። የአዊ ዞኗ ዋና ከተማ እንጅባራ በክንደ ነበልባል ልጆቿ ዙሪያዋን ተከባለች። ወራሪው ቡድን በትላልቅ ህንፃወች ላይ ድሽቃና መትረየስ ጠምዶ እየተጠባበቀ ነው። ከሰዓታት በኋላ የድል ብስራት እንጠብቃለን።
ድል ለነበልባሉ ፋኖ

Address

Baher Dar
Bahir Dar
BAHERDAR

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ማህደረ አማራ-mahder amhara posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ማህደረ አማራ-mahder amhara:

Videos

Share