Zagu Media

Zagu Media እንኳን ወደ Zagu Media በሰላም መጣችሁ!
ወቅታዊ፣ አገራዊ፣መዝናኛ እና የተለያዩ መረጃዎችን በብርሃን ፍጥነት ወደ እናንተ እናደርሳችሁላን!

የኢትዮጵያ ቅጥረኛ ወታደር ከዩክሬን ጎን ሆኖ ሩሲያን እየተዋጋ እንደሆነ ተገለጸሩሲያ ከዩክሬን ጎን የቆሙ ቅጥረኛ ወታደሮችን ማንነት ይፋ አድርጋለችኢትዮጵያን ጨምሮ ከ89 ሀገራት የተውጣጡ ከ...
15/03/2024

የኢትዮጵያ ቅጥረኛ ወታደር ከዩክሬን ጎን ሆኖ ሩሲያን እየተዋጋ እንደሆነ ተገለጸ

ሩሲያ ከዩክሬን ጎን የቆሙ ቅጥረኛ ወታደሮችን ማንነት ይፋ አድርጋለች
ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ89 ሀገራት የተውጣጡ ከ13 ሺህ በላይ ቅጥረኛ ወታደሮች ለዩክሬን እየተዋጉ ነው ተብሏል

ኢትዮጵያዊው ቅጥረኛ ወታደር ከዩክሬን ጎን ሆኖ ሩሲያን እየተዋጋ እንደሆነ ተገለጸ።

ለአንድ ሳምንት በሚል የተጀመረው የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ሁለት ዓመት ያለፈው ሲሆን ጦርነቱ አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጎን ቆመው እየተዋጉ ያሉ ቅጥረኛ ወታደሮችን ማንነት ይፋ አድርጋለች።

እንደ ሩሲያ መከላከያ ሚንስቴር መረጃ ከሆነ አንድ ኢትዮጵያዊ ከዩክሬን ጎን ሆኖ ሩሲያን እየወጋ ይገኛል ተብሏል።

ይህ ኢትዮጵያዊ እስካሁን በህይወት እንዳለ የተገለጸ ሲሆን ወታደሩ ኢትዮጵያዊ ከመሆኑ ውጪ ማንነቱ ይፋ አልተደረገም።

በአጠቃላይ ይህ ጦርነት ከተጀመረበት የካቲት 2014 ዓ.ም ጀምሮ ከ89 ሀገራት የተውጣጡ 13 ሺህ 387 ቅጥረኛ ወታደሮች ከዩክሬን ጎን ተሰልፈዋል።

ከጠቅላላው ቅጥረኛ ወታደሮች ውስጥም 5 ሺህ 962 ያህሉ በሩሲያ ጦር መገደላቸው ተገልጿል።

ፖላንድ ቅጥረኛ ወታደሮችን በማዋጣት ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን 2 ሺህ 960 ዎቹ ተገድለዋል ተብሏል።

ከፖላንድ በመቀጠል አሜሪካ፣ ካናዳ፣ ጆርጂያ እና ብሪታንያ ብዙ ዜጎቻቸው ከዩክሬን ጎን የቆሙ በቅጥረኛ ወታደርነት የተመዘገቡ ሀገራት ናቸው።

ከአፍሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ 13 ሀገራት የተውጣጡ 249 ወታደሮች ከዩክሬን ጎን ሆነዋል የተባለ ሲሆን 103 ያህሉ መገደላቸው ተገልጿል።

ናይጀሪያ፣ አልጀሪያ እና ደቡብ አፍሪካ በአንጻራዊነት ብዙ ዜጎቻቸው ለዩክሬን በቅጥረኛ ወታደርነት የተመዘገቡባቸው ሀገራት ናቸው።

Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ

አስፋዉ መሸሻ አረፈጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ በአሜሪካ ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ትላንት ማታ ማረፉ ተስምቷል::ለዘመድ ወዳጅና ለአድናቂወቹ መፅናናትን እንመኛለን።
14/01/2024

አስፋዉ መሸሻ አረፈ

ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ በአሜሪካ ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ትላንት ማታ ማረፉ ተስምቷል::

ለዘመድ ወዳጅና ለአድናቂወቹ መፅናናትን እንመኛለን።

በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል...
29/12/2023

በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ-ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ ለመጀመር አልቻሉም ነበር ብሏል ሚኒስቴሩ።

በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ሲያካሂድ መቆየቱ ተገልጿል።

" የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የአስሩ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ጸጥታ አካላት ትናንት ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም በጉዳዩ ዙሪያ የመከሩ ሲሆን አሁን በክልሉ አንጻራዊ ሰላም የተፈጠረ በመሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን መጥራትና ማስተማር እንደሚችሉ ውሳኔ ላይ ተደርሷል። " ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

በዚህም መሰረት ከጥር 1/2016 ጀምሮ ባሉ ሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን ጠርተው የመማር ማስተማር ስራቸውን ይጀምራሉ ተብሏል።

በመሆኑም በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የተመደቡ ተማሪዎች ዩኒቨርስቲዎቹ የሚያደርጉትን ጥሪ እንዲከታተሉ ጥሪ ቀርቧል።

የቱሪዝም ሚኒስቴር በተጋነነ ዋጋ የሚያከናውነው ግዢ መታረም እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳስቧል፡፡ቋሚ ኮሚቴው የቱሪዝም ሚ...
28/12/2023

የቱሪዝም ሚኒስቴር በተጋነነ ዋጋ የሚያከናውነው ግዢ መታረም እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳስቧል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው የቱሪዝም ሚኒስቴርን የ2014 በጀት ዓመት ሂሳብ ኦዲት ሪፖርት መነሻ በማድረግ ይፋዊ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ወ/ሮ አራሬ ሞሲሳ ተቋሙ ለደንብ ልብስ ግዢ በሚል ያከናወነው ክፍያ የተጋነነ ስለመሆኑ ጠቁመው፤ በቀጣይ የቱሪዝም ሚኒስቴርም ሆነ ሌሎች ተቋማት የሚመሩበት ወጥ የሆነ መመሪያ በገንዘብ ሚንስቴር ሊዘጋጅ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ያሉት ክፍተቶች ተፈትሸው ተጠያቂነት እንዲሰፍን፣ ከተቋሙ የለቀቁ ሰራተኞች የተቋሙን ንብረት ተመላሽ እንዲያደርጉ እንዲሁም ያለአግባብ ለቤት እድሳት የወጣው ገንዘብ ተመላሽ እንዲደረግ ቋሚ ኮሚቴው ለሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎች ናቸው፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሰረት ዳምጤ በበኩላቸው በተቋሙ በየቀኑ ነዳጅ የሚሞላላቸው ተሸከርካሪዎች እንዲሁም ያለአግባብ የተከፈሉ ወጪዎች መኖራቸው በኦዲት ግኝት እንደተረጋገጠ ገልጸው፤ ተቋሙ የእርምት እርምጃ አለመውሰዱን አስረድተዋል፡፡

የቱሪዝም ሚንስቴር ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ በበኩላቸው ተቋሙ የውስጥ ኦዲት፣ የስነምግባር፣ የፋይናንስ፣ የንብረትና የተለያዩ ክፍሎችን በአዲስ መልክ በማደራጀትና ለባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት ቀደም ሲል የነበሩት የኦዲት ግኝቶች እንዳይደገሙ ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ ስለመሆናቸው ለቋሚ ኮሚቴው አብራርተዋል፡፡

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የአየር ትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎትን ጀመሩ።ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከክፍያ በፊት  እስከ ስድስት መቶ ሺህ ብር ቅድሚያ ...
28/12/2023

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የአየር ትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎትን ጀመሩ።

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከክፍያ በፊት እስከ ስድስት መቶ ሺህ ብር ቅድሚያ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችል አዲስ የአየር ትራንስፖርት ክፍያ አሰራርን ይፋ አድርገዋል።

ይህ አገልግሎት ተጠቃሚዎች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎትን ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን አዲስ የክፍያ አማራጭ ነው።

''ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል'' የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ አገልግሎት በ6 ወር ወይም በ12 ወር በሚደርስ የብድር ክፍያ የሚሰጥ መሆኑን የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን አቶ ዩሃንስ ሚሊዮን የአገልግሎቱ ይፉ መደረግን አስመልክተው ተናግረዋል።

ደንበኞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን በዳሸን ባንክ የሂሳብ ቁጥር መክፈት እንደሚገባቸው እና በተጨማሪም በባንኩ ቢያንስ ለሶስት ወራት አገልግሎት ያገኙ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

ስምምነቱን አስመልክቶ የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና የንግድ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ለማ ያዴቻ ከዳሽን ባንክ ጋር በመተባበር የቀረበው አዲስ የክፍያ አማራጭ ከአየር መንገዱ የሞባይል መተግበሪያ ጋር የተቀናጀ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል ።

ደንበኞች የተፈቀደላቸው የብድር መጠን ሲያልቅ ማደስ የሚችሉ ሲሆን በአንዴ የወሰዱትን ብድርም ለተለያዩ በረራዎች ከፍለው መጠቀም ይችላሉ ተብሏል።

በሁለቱ ተቋማት ስምምነት በቀረበው በዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈቀደው የብድር ገንዘብ መጠን እስከ ስድስት መቶ ሺህ (600,000) ብር የሚደርስ ነው።

የሚፈቀደው ብድር ወለድ የሚታሰብበት ሲሆን ይህም ደንበኛው በመረጠውና ብድሩን በወሰደበት የጊዜ ገደብ ከብድሩ ጋር አብሮ የሚከፈል ይሆናል ተብሏል።

ሰበር‼️ጦርነት ይቁም፣ ሰላም ይስፈን የሚል ሰላማዊ ሰልፍ በትግራይ መቀሌ ሊካሄድ ነውበታህሳስ 21/2016 መቀሌ ላይ በመላ ኢትዮጵያ ጦርነት ይቁም ሰላም ይስፈን የሚል የተቃዉሞ ሰልፍ ተጠር...
28/12/2023

ሰበር‼️

ጦርነት ይቁም፣ ሰላም ይስፈን የሚል ሰላማዊ ሰልፍ በትግራይ መቀሌ ሊካሄድ ነው

በታህሳስ 21/2016 መቀሌ ላይ በመላ ኢትዮጵያ ጦርነት ይቁም ሰላም ይስፈን የሚል የተቃዉሞ ሰልፍ ተጠርቷል። የትግራይ አስተዳደር ሰልፉን መፍቀዱ ተሰምቷል።

EMS ከሰልፉ አስተባባሪዎች አንዱ የሆኑትን የህግባለሞያና ጠበቃ አበራ ንጉስ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ይሁኑ እውነታ አስረድተዋል።

በሰልፉ በየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢ ያሉ ጦርነቶች እንዲቆሙ፣
ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ፣
በማንነታቸው የታሰሩ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣

መንግስት የፖለቲካ ጥያቄዎችን በሆደ ሰፊነት በመነጋገርና በድርድር እንዲፈታ፣

ሀገሪቱ ከገባችበት የሰላም እጦት ፋታ እንድታገኝ ጦርነት ቆሞ ሰላም እንዲሰፍን የሚጠይቅ ሰልፍ ለተሃሳስ 21 ተዘጋጅቶ የመቐለ ከንቲባ መፍቀዳቸውን አቶ አበራ ንጉስ ለ EMS ዛሬ ማምሻውን ገልፀዋል።

ተመሳሳይ የሰልፍ ጥሪ በአዲስ አበባ ተጠይቆ መከልከሉ ይታወሳል።

28/12/2023

የገንዘብ ሚንስቴር ዴኤታው ኢዮብ ተካልኝ፣ ኢትዮጵያ በመጪው ጥር ወር ከቦንድ አበዳሪዎቿ ጋር ውይይት እንደምትጀምር እና ውይይቱ እንዳለቀ ሳይከፈል የቀረውን የዕዳ ወለድ ወዲያው ለመክፈል የሚያስችል ብቃት አለን ማለታቸውን የአሜሪካ የአማርኛው ድምፅ ዘግቧል። ሚንስትር ዴኤታው፣ ገንዘቡ በውይይቱ ወቅት ለዩሮ ቦንድ አበዳሪዎቹ ለመተማመኛ የሚያስፈልግ ከሆነም በተለየ አካውንት አስቀምጠን ውይይቱን መቀጠል እንችላለን ማለታቸውም በዘገባው ተጠቅሷል። ኢዮብ፣ ወለዱን መክፈል የማንችለው በአቅም ማነስ ሳይሆን የመርኽ ጉዳይ በመሆኑ ነው ሲሉ መናገራቸውም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ ለተበደረችው የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮ ቦንድ፣ መክፈል ለነበረባት 33 ሚሊዮን ዶላር ወለድ የተሰጣት ተጨማሪ 14 ቀናት ባለፈው ሰኞ በመጠናቀቁ፣ ከጋና እና ዛምቢያ ቀጥሎ ብድር መክፈል ያልቻለች ሦስተኛዋ የአፍሪካ አገር መሆኗ ይታወሳል።

28/12/2023

ኢሰመጉ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ የተለያዩ ቀበሌዎች የታጠቁ ኃይሎች በተለያዩ ቀናት በንጹሃን ዜጎች ላይ በፈጸሙት ጥቃት 56 ሰዎች ዘግናኝ በሆነ ሁኔታ እንደተገደሉ አስታውቋል። ኢሰመጉ፣ በበርካታ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት እንዲኹም እገታ መፈጸሙንም ገልጧል። ከተገደሉት መካከል ስድስት የአንድ ቤተሰብ አባላት እንደሚገኙበት ኢሰመጉ ጠቅሷል።በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ ልዩ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን አካባቢ በተመሳሳይ ኅዳር 14 የታጠቁ ቡድኖች በፈጸሙት ጥቃት በዘጠኝ የቤተክርስቲያኒቱ አባላት ላይ "የጅምላ ግድያ" መፈጸሙን መረዳቱንም ኢሰመጉ አመልክቷል። መንግሥት ወንጀሉን የፈጸሙ አካላትን ባስቸኳይ ለፍርድ እንዲያቀርብና የሕግ የበላይነትን እንዲያረጋግጥም ኢሰመጉ ጠይቋል።

አማራ ባንክ በበጀት ዓመቱ የ481 ሚሊየን ብር ኪሳራ እንዳጋጠመው አስታወቀ።ባንኩ በተለያዩ ወጪዎች ምክንያት በአመቱ መጨረሻ ላይ ኪሳራ ማስመዝገቡን ገልጿል፡፡ባንኩ ጠቅላላ የሀብት መጠኔ ከ2...
28/12/2023

አማራ ባንክ በበጀት ዓመቱ የ481 ሚሊየን ብር ኪሳራ እንዳጋጠመው አስታወቀ።

ባንኩ በተለያዩ ወጪዎች ምክንያት በአመቱ መጨረሻ ላይ ኪሳራ ማስመዝገቡን ገልጿል፡፡

ባንኩ ጠቅላላ የሀብት መጠኔ ከ28 ቢሊየን ብር በላይ ደርሷልም ብሏል።

የባንኩ የተከፈለ ካፒታልም 5.8 ቢሊየን ብር ደርሷል።
ባንኩ በ2015 የሂሳብ አመት ጠቅላላ የሀብት መጠኑ 28.4 ቢሊየን ብር መድረሱን አስታውቋል።

በተጠናቀቀው የ2015 ዓ.ም የሂሳብ ዓመት ከ1መቶ ሺህ በላይ የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚዎችን መድረስ የቻለ ሲሆን ፤ አጠቃላይ ገቢውም ከ1.8 ቢሊየን ብር በላይ ሆኗል ነው የተባለው።

ባንኩ ከ1 ሚሊየን በላይ ደንበኞችን ማፍራት መቻሉ የተገለፀ ሲሆን፤ ከ14.9 ቢሊየን ብር በላይም ብድር አቅርቧል።

በ2015 የሂሳብ ዓመት የቅርንጫፍ ቁጥሬን ከ290 በላይ አድርሻለሁ ያለው ባንኩ፤ ከ19.8 ቢሊየን ብር በላይ የተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰብ መቻሉን አስታውቋል።

አማራ ባንክ ከ140 ሺህ በላይ በሆኑ ባለአክሲዮኖች በብር 4.8 ቢሊየን የተከፈለ ካፒታል እና በብር 6.5 ቢሊየን የተፈረመ ካፒታል ከአንድ አመት በፊት ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው።

ባንኩ በዛሬው ዕለት ሁለተኛውን የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ በጎልፍ ክለብ በማካሄድ ላይ ይገኛል።

በእሳት አደጋ የአንድ ሰው ህይወት ቀጠፈ፡፡ሌሊት 8:03 ሰዓት ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ገርጂ ሰላም ሰፈር እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በተነሳ የእሳት አደጋ የአንድ ሰዉ ህይወት አልፏል።ሟ...
28/12/2023

በእሳት አደጋ የአንድ ሰው ህይወት ቀጠፈ፡፡

ሌሊት 8:03 ሰዓት ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ገርጂ ሰላም ሰፈር እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በተነሳ የእሳት አደጋ የአንድ ሰዉ ህይወት አልፏል።

ሟቹ ብቻዉን ተከራይቶ የሚኖር ሲሆን ለጊዜዉ ምክንያቱ ባልታወቀ የእሳት አደጋ ዕድሜዉ 35 ዓመት የተገመተ ሰዉ ህይወቱ አልፏአል።

የእሳት አደጋዉ ጥሪ ዘግይቶ በመድረሱና የግለሰቡ ህይወቱ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ከመድረሳቸዉ በፊት ያለፈ መሆኑ ተነግሯል።

በእሳት አደጋዉ በንብረት ላይ መጠነኛ ጉዳት ደርሷል ተብሏል።

አዴን ከአማራ ክልል መንግስት ጋር የሰላም ስምምነት መፈራረሙ ተሰምቷል።የሕወሓት አጋር የሆነውና በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(አዴን) ከክልሉ መንግስት ጋር የሰላም...
27/12/2023

አዴን ከአማራ ክልል መንግስት ጋር የሰላም ስምምነት መፈራረሙ ተሰምቷል።

የሕወሓት አጋር የሆነውና በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(አዴን) ከክልሉ መንግስት ጋር የሰላም ስምምነት መፈራረሙን ታውቋል።ከተመሰረተ ሶስት አመታትን እንዳስቆጠረ የሚነገርለት ፓርቲው የአመራሮቹን መቀመጫ መቀሌ አድርጎ በአማራ ክልል ይንቀሳቀስ ነበር።ለጊዜው በምስጢር የተያዘው ስምምነት በዚህ ሳምንት መጨረሻ ለህዝብ ይፋ ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከዋዜማ ሬዲዬ ዘገባ ላይ መረዳት ይቻላል።

26/12/2023

በገበሬ ስም ያወጡትን የአፈር ማዳበሪያ ለግል ጥቅማቸው በማዋል መምህራን ደሞዘ እንዳይከፈላቸዉ ያደረጉ 10 አመራሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉ ተነግሯል

በከምባታ ዞን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ በገበሬ ስም ያወጡትን የአፈር ማዳበሪያ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል የተባሉ የቀድሞ 10 አመራሮች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የወረዳው አስተዳደር ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል፡፡

አመራሮቹ በቀድሞ የደቡብ ክልል አስተዳደር ስር በታቀፈው የከምባታ ጠምባሮ ዞን ፤ከቀበሌ አንስቶ እስከ ወረዳ ድረስ የነበሩ ናቸው ተብሏል፡፡

በአመራር ሃላፊነታቸው ወቅት ከ10 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የአፈር ማዳበሪያ ለገዛ ጥቅማቸው ማዋላቸውን ነው የልዩ ወረዳው አስተዳደር አቶ አበራ አፍሪጦ ለጣቢያችን የተናገሩት፡፡

ማዳበሪያው በብድር የመጣ በመሆኑ እንዲከፍሉ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ፍቀደኛ ባለመሆናቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስተዳዳሪው ገልጸዋል፡፡

ነገር ግን የማዳበሪያው እዳ በጊዜው መከፈል ስላለበት ከመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ ተቆራጭ መሆኑን አቶ አበራ ለጣቢያችን ተናግረዋል፡፡

ከዚህም የተነሳ ባለፉት ሁለት ወራት ለመምህራን የወር ደሞዛቸው በአግባቡ ሊከፈላቸው አልቻለም ብለዋል፡፡

ይህም አሁን ላለነው አመራሮች ከፍተኛ ፈተና ሆኖብናል ያሉት የልዩ ወረዳ አስተዳዳሪ አመራሮቹ ጉዳያቸው በህግ እየታየ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ባሳለፍነው ሳምንት የከምባታ ዞን የጠምባሮ ልዩ ወረዳ መምህራን ደሞዝ በአግባቡ እየተከፈለን ባለመሆኑ በከባድ የኑሮ ጫና ውስጥ እንገኛለን ሲሉ መናገራቸው አይዘነጋም፡፡

© ኢትዮ ኤፍ ኤም

ኢትዮጵያ እዳዋን የመክፈያ ተጨማሪ ቀናቶቿን ሳትከፍል አጠናቀቀችኢትዮጵያ የ33 ሚሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ብድር ወለድ ትናንት በቀነ ገደቡ ሳትከፍል መቅረቷን ብሉምበርግ ዘግቧል። የወለዱ መክ...
26/12/2023

ኢትዮጵያ እዳዋን የመክፈያ ተጨማሪ ቀናቶቿን ሳትከፍል አጠናቀቀች

ኢትዮጵያ የ33 ሚሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ብድር ወለድ ትናንት በቀነ ገደቡ ሳትከፍል መቅረቷን ብሉምበርግ ዘግቧል።

የወለዱ መክፈያ ዋናው ቀነ ገደብ ያለፈው ከሁለት ሳምንት በፊት ሲሆን፣ ቀነ ገደቡ የ14 ተጨማሪ የእፎይታ ቀናት ነበረው።

መንግሥት የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ብድር ወለዱን ከሁለት ሳምንት በፊት ያልከፈለው፣ ሁሉንም አበዳሪዎች በእኩል ለማስተናገድ እንደሆነ መግለጡ ይታወሳል።

የወለድ መክፈያው የእፎይታ ጊዜ ትናንት ማብቃቱን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ የውጭ ዕዳዋን መክፈል ያልቻለች አገር ሆናለች።

 #ሰበር‼️ጦርነት ይቁም፣ ሰላም ይስፈን የሚል ሰላማዊ ሰልፍ በትግራይ መቀሌ ሊካሄድ ነውበታህሳስ 21/2016 መቀሌ ላይ በመላ ኢትዮጵያ ጦርነት ይቁም ሰላም ይስፈን የሚል የተቃዉሞ ሰልፍ ተ...
25/12/2023

#ሰበር‼️

ጦርነት ይቁም፣ ሰላም ይስፈን የሚል ሰላማዊ ሰልፍ በትግራይ መቀሌ ሊካሄድ ነው

በታህሳስ 21/2016 መቀሌ ላይ በመላ ኢትዮጵያ ጦርነት ይቁም ሰላም ይስፈን የሚል የተቃዉሞ ሰልፍ ተጠርቷል። የትግራይ አስተዳደር ሰልፉን መፍቀዱ ተሰምቷል።

EMS ከሰልፉ አስተባባሪዎች አንዱ የሆኑትን የህግባለሞያና ጠበቃ አበራ ንጉስ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ይሁኑ እውነታ አስረድተዋል።

በሰልፉ በየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢ ያሉ ጦርነቶች እንዲቆሙ፣
ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ፣
በማንነታቸው የታሰሩ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣

መንግስት የፖለቲካ ጥያቄዎችን በሆደ ሰፊነት በመነጋገርና በድርድር እንዲፈታ፣

ሀገሪቱ ከገባችበት የሰላም እጦት ፋታ እንድታገኝ ጦርነት ቆሞ ሰላም እንዲሰፍን የሚጠይቅ ሰልፍ ለተሃሳስ 21 ተዘጋጅቶ የመቐለ ከንቲባ መፍቀዳቸውን አቶ አበራ ንጉስ ለ EMS ዛሬ ማምሻውን ገልፀዋል።

ተመሳሳይ የሰልፍ ጥሪ በአዲስ አበባ ተጠይቆ መከልከሉ ይታወሳል።

25/12/2023

ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ ዛቻ መሰንዘሯን ቀጥላለች።

በያዝነው ዓመት ብቻ በአራት ዙሮች የተካሄደው የህዳሴው ግድብ ድርድር ያለውጤት መበተኑን ተከትሎ የግብፅ ባለስልጣናት ዛቻ የቀላቀሉ ንግገሮችን ማሰማታቸውን ቀጥለዋል። በቅርቡ አስተያየታቸውን የሰጡት የአገሪቱ የመስኖ እና የውሃ ኃብት ሚኒስትር የአገራቸው የውሃ ደህንነት አደጋ የሚጋረጥበት ከሆነ “ተመጣጣኝ የሆነ እርምጃ” እንወስዳለን ሲሉ ተሰምተዋል። ይህ እርምጃ ምን እንደሆነ ግን ዘርዝረው አልገለፁም።

አራተኛው ዙር ድርድር ያለውጤት ባለፈው ሳምንት እንደተቋጨ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢትዮጵያን በአቋሟ ግንችር ብላ ስምምነት ላይ እንዳይደረስ አስቸግርላች የሚል ክስ ሰንዝሮባት ነበር። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም በበኩሉ ይህ የግብፅ መግለጫ ዓለም አቀፍ መርኆዎችን የጣሰ ነው ሲል አጣጥሎታል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አክሎም ግብፅ የቅን ግዛት ዘመን አስተሳሰብ ላይ ቆማ ቀርታለች ሲል ወርፏታል።

የካይሮው የመስኖ እና ውሃ ኃብት ሚኒስትር ሃኒ ሰዋሊም በሳምንቱ የእረፍት ቀናት ወቅት አል-አራቢያ በተባለ የቴሌቭዥን ጣብያ ቀርበው ስለታላቁ የህዳሴ ግድብ በተጠየቁበት ወቅት ኢትዮጵያ በግድቡ ያላት ፍላጎት የኤልክትሪክ ኃይል ከማመንጨትም አልፎ ፖለቲካዊ የበላይነት የመያዝ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያዊያኑ በግድቡ የገነቡት የውሃ ቋት እናመነጨዋለን ለሚሉት የኤሌክትሪክ ኃይል ከሚያስፈልገው እጅግ የበለጠ ነው ሲሉ የተሰሙት ሚኒስትሩ እንደዚህ የተጋነነ ሐይቅ ለመገንባት የፈለገችው ኢትዮጵያ ሌላ ድብቅ ፍላጎት ስላላት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በግድቡ ሐይቅ ግንባታ ላይ ብቻም ሳይሆን ለድርድሩ ይዛው በምትቀርበው አቋም እንዲሁም የግድቡ ባላት አስተያየት ከኤሌክትሪክ ኃይል የሚሻገር ዓላማ እንዳላት ግልፅ ነው ሲሉም አክለዋል።

“የህዳሴው ግድብ የፖለቲካ ጥቅም ይኖረዋል፤ ኢትዮጵያ የናይል ውሃን እንድትቆጣጠር እና የበላይነት እንዲኖራት ግብፅ አትፈቅድም” ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ግብፅ በግድቡ ዙርያ ዛቻ የተቀላቀለበት ንግግር ስታደርግ ይህ የመጀመሪያው ጊዜ አይደለም። ተደጋጋሚ ድርድሮችም ባለፉት ዓመታት ተከናውነዋል። ይሁንና ውጤት ሲያስገኙ አላስተዋለም። ኢትዮጵያም የግብፅን ማስፈራሪዎች ችላ ብላ ከታሰበበት ጊዜ እጅጉን ዘግይቶም ቢሆን ግድቡን ለማጠናቀቅ ተቃርባለች።

በግጭቶች ክፉኛ በደደቀችው ኢትዮጵያና ከዓለም ትልልቅ የጦር ኃይሎች የአንዱ ባለቤት በሆነችው መካከል ቀጥተኛ ጦርነት ይጫራል ተብሎ ባይታሰብም ዲፕሎማሲያዊ ቁርሿቸው ሌሎች የፀጥታ እና የምጣኔ ኃብት መዘዞችን ሊያስከትሉ ግን ይችላሉ።

የመንግሥት ሰራተኞች ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ ይሰጣል!ባለፈው ሳይሰጥ የቀረው የመንግሥት ሰራተኞች ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ...
25/12/2023

የመንግሥት ሰራተኞች ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ ይሰጣል!

ባለፈው ሳይሰጥ የቀረው የመንግሥት ሰራተኞች ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ ይሰጣል ተባለ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ባለፈው ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ መላው ሰራተኞችን በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።

የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና፦
- ለአመራሮች ፣
- ለባለሙያዎች
- ለሰራተኞች አርብ 12/04/2016 ሊሰጥ የነበረ ሲሆን ፈተናው የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ባጋጠመው " ቴክኒካል ችግር " ምከንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ መገለፁ ይታወሳል።

ሰራተኞች በእለቱ ከረፋዱ 5:00-11:30 ፈተናው ሲጠብቁ የነበረ ሲሆን ከፍተኛ መጉላላት እና እንግልት ሲደርስባቸው ነው የዋለው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል። ቢሮው በቀጣይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን አስታውቋል።

ተፈታኞች ከዚህ ቀደም በኦረንቴሽን ወቅት የተቀመጡ መስፈርቶችን በሙሉ አሟልተው ለፈተና እንዲገኙ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ከደቡብ አሜሪካ የተውጣጡ ስደተኞች አንድ ላይ ወደ አሜሪካ ድንበር አቀኑ!በሺዎች የሚቆጠሩ ከማዕከላዊ እና ደቡብ አሜሪካ አገራት የተውጣጡ ስደተኞች በእግራቸው ወደ ዩናይትድ ...
25/12/2023

በሺዎች የሚቆጠሩ ከደቡብ አሜሪካ የተውጣጡ ስደተኞች አንድ ላይ ወደ አሜሪካ ድንበር አቀኑ!

በሺዎች የሚቆጠሩ ከማዕከላዊ እና ደቡብ አሜሪካ አገራት የተውጣጡ ስደተኞች በእግራቸው ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ድንበር እያቀኑ ነው።

ሕፃናትና አዋቂዎች ሳይቀሩ 8 ሺህ ገደማ የሚሆኑ በአብዛኛው ከቬንዝዌላ፣ ኩባ እና ሜክሲኮ የመጡ ስደተኞች ናቸው ወደ አሜሪካ ድንበር እያቀኑ ያሉት።

ግለሰቦቹ “የደኅነት ስደት” የሚባል በግዙፍ ቀይ ቀለም የተፃፈ ፅሑፍ ይዘው ነው ወደ ድንበር እያቀኑ ያሉት።የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን ለጉብኝት ወደ ሜክሲኮ መዲና ለመምጣት ማቀዳቸው በተሰማ ማግስት ነው ይህን የሆነው።

ብሊንከን ስደተን ለመቆጣጠር ከሜክሲኮ መንግሥት ጋር ስምምነት ይገባሉ ተብሎ ተገምቷል።

በአውሮፓውያኑ 2022 እና 2023 ወደ አሜሪካ ለመግባት አቅደው ሜክሲኮ ድንበር ላይ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከሁለት ሚሊዮን በላይ ነው።

በመስከረም 2023 ብቻ የአሜሪካ ድንበር ጥበቃ 200 ሺህ ያህል ግለሰቦች የሜክሲኮ ድንበርን አቋርጠው ሊገቡ ሲሉ እንደያዛቸው የዩኤስ ሃገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት መረጃ ያሳያል።

Via BBC

የሰዳን ጦር መሪ ቁልፍ ከተማ የለቀቁ ወታደራዊ አዛዦችን ተጠያቂ እንደሚያደርጉ ገለጹ።የሱዳን ጦር አዛዦ ጀነራል አልቡርሃን በጀነራል ሀምዳን ደጋሎ ወይም ሄሜቲ የሚመሩት ጦር ቁልፍ የተባለችው...
25/12/2023

የሰዳን ጦር መሪ ቁልፍ ከተማ የለቀቁ ወታደራዊ አዛዦችን ተጠያቂ እንደሚያደርጉ ገለጹ።

የሱዳን ጦር አዛዦ ጀነራል አልቡርሃን በጀነራል ሀምዳን ደጋሎ ወይም ሄሜቲ የሚመሩት ጦር ቁልፍ የተባለችውን የዋድ መዳኒ ከተማ መያዙን ተከትሎ "ግዴለሽ" ያሏቸውን የጦር አዛዦች ተቆጥተዋል።ጦሩ ሳይዋጋ የአልገዚራን ዋና ከተማ በመልቀቁ ትችት አጋጥሞታል።

በሀገሪቱ ለስምንት ወራት ከዘለቀው ውጊያ መሸሻ ቦታ ተደርጋ ከምታተየው የአልገዚራ ግዛት 300ሺ ሰዎች ለመፈናቀል ተገደዋል።የዋድ መዳኒ ከተማ ከተያዘች ከአራት ቀናት በኋላ ጀነራል አል ቡርሃን ስለጉዳዩ በአደባባይ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።ጀነራል አል ቡርሃን "እያንዳንዱን ግዴለሽ የሆነ አዛዥ ተጠያቂ እናደርጋለን። ከተማዋ እንድትለቀቅ ያደረጉ ሁሉ ያለምህረት ተጠያቂ ይደረጋሉ" ብለዋል።

የሱዳን ጦር ተቀናቃኝ የሆነው ፈጥኖ ደራሽ ኃይል እንዴት ሊገባ እንደቻለ እንደሚመረምረው ገልጿል።
ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች አጠቃላይ የአልገዚራ ግዛትን መቆጣጠራቸውን አስታውቀዋል። ግጭቱ ወደ ጎረቤት ግዛቶች ይሰፋፋል በማል ስጋት የእርዳታ ሰራተኞች ከአጎራባች ግዛቶች ለቀው በመውጣት ላይ ይገኛሉ።በዋና ከተማዋ ካርቱም ግጭት በተነሳ ጊዜ ተሰደው ወደ አልገዚራ የመጡ ስደተኞች በድጋሚ ለመፈናቀል ተዳርገዋል።

ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ከአልገዚራ በስተምስራቅ በኩል ያለችውን የገዳርፍ ግዛት ለመያዝ ሊንቀሳቀሱ ይችላሉ የሚል ስጋት ተፈጥሯል።ሱዳንን ለሶስት አስርት አመታት ለሚጠጋ ጊዜ የመሩት ኦመር ሀሰን አልበሽር በህዝባዊ አመጽ ከስልጣን ከወረዱ በኋላ ከተመሰረተው የሲቪል መንግስት ጋር ሲያስተዳድሩ በነበሩ ጀነራሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ሀገሪቱን ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ከቷታል።

Address

Bahir Dar
6000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zagu Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Zagu Media:

Videos

Share