የአሳንሰር ጨዋታ - Discover Ethiopia

የአሳንሰር ጨዋታ - Discover Ethiopia የታሪክ እና የባህል እንዲሁም ልዩ ልዩ አዝናኝ እና ትኩስ መረጃዎች የምንጋራበት ገፅ ነው፡፡

አሳንሰር የአማርኛ ቃል ሲሆን በእንግሊዘኛው ሊፍት /ኢሊቤተር/ ማለት ነው፡፡ ኢትዮጵያ በየዘርፉ እምቅ ሀብት አላት፡፡ ስለዚህ በዚህ ገፅም በተለይ ስለ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን መረጃዎችን እንለዋወጣለን…. (Talk about Ethiopia & Ethiopians) Ethiopia is A Land of Great Civilization, A Land of Hospitality............

የአየር መንገዳችን ስም ሲነሳ አብረው የሚነሱት ካ ፕ ቴ ን    መ ሐ መ ድ   አ ህ መ ድ¤ ¤ ¤የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለአሁኑ ስምና ዝናው ካበቁት ኢትዮጵያዊያን መካከል አንዱ ካፕቴን...
18/11/2024

የአየር መንገዳችን ስም ሲነሳ አብረው የሚነሱት ካ ፕ ቴ ን መ ሐ መ ድ አ ህ መ ድ
¤ ¤ ¤

የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለአሁኑ ስምና ዝናው ካበቁት ኢትዮጵያዊያን መካከል አንዱ ካፕቴን መሐመድ አህመድ ናቸው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተቋቋመው በ1946 ዓም ነበር። አየር መንገዱ በተቋቋመት ዘመን የበረራ መስመሮቹ ውስን የነበሩ ሲሆን ይኸውም ከአአ - ካይሮ እና ደርሶ መልስ ነበር።

በ1963 ዓም ካፒቴን መሐመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነው ተሾሙ። ከዚህ ጊዜ በኋላ ካፕቴኑ በሁለቱም ስርዓት ማለትም በንጉሳዊውና በደርግ ስርዓት አየር መንገዱን በዋና ስራ አስኪያጅነት አስተዳድረዋል። በዚህም ወቅት አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ውስጥ ተፎካካሪ እንዲሆንና ዘመናዊነቱ እንደተጠቀ እንዲቀጥል በማድረግ ጉልህ ሚና ተጫውተዋል።...
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን / የኢትዮጵያን አየር መንገድ ወደ ዘመናዊና ተወዳዳሪ አየር መንገድ እንዲሸጋገር መሰረት ከጣሉት የመጀመሪያዎቹ CEO ዎች ውስጥ ካፕቴን መሐመድ አህመድ አንዱና በቀዳሚነት የሚጠቀሱ ናቸው። ከ1963 ዓም ወዲህ አየር መንገዱ ዘመናዊና ግዙፍ የመጓጓዣ አይሮፕላኖችን ከቦይንግ ኩባንያ በመግዛት የበረራ አድማሱን ወደ የተለያዩ አፍሪካ አገራት፣ መካለኛው ምስራቅ እንዲሁም እስከ ቻይናና አውሮፖ ድረስ እንዲያስፋፋ አድርጓል።....
ከአብዮቱ ፍንዳታ በኋላ የአየር መንገዱ ህልውና አደጋ ላይ ወድቆ እንደነበር የሚታወስ ነው። ያ ዘመን ለአየር መንገዳችን ወሳኝ ጊዜ ነበር። ደርግ ስልጣን ላይ በወጣ ማግስት የሚከተለው መርህ የሶሻሊዝም ርዕዮተ ዓለምን እንደሆነ አወጀ። ይህ አየር መንገዱ የአውሮፕላን አቅራቢው ከሆነው የቦይንግ ኩባንያ ጋር ያለውን ግንኙነት ፈተና ውስጥ የሚጥል ሆነ። በዚህ ጊዜ ስራ አስኪያጁ በደርጉ ሊቀመንበር መንግስቱ ኃ/ ማሪያም መመሪያ መሰረት አየር መንገዱ የሚገለገልበት የአሜሪካን ሰራሽ ቦይንግ አይሮፕላን በሶቭየቶቹ አንቶኖቭ እንዲተካ የሚያስገድድ ትእዛዝ ደረሳቸው። ሆኖም ግን ካፕቴን መሐመድ እምቢ አሻፈረኝ አሉ።

በድርጅቱ አስራር ውስጥ ጣልቃ መግባት ድርጅቱን ለኪሳራ እንደሚዳርግና ከገበያ ውጪ እንደሚያደርግ ለሊቀመንበሩ አሳሰቡ። በመጨረሺያም ምክረ ሀሳቡ አሳማኝ ሆኖ በመገኘቱ ስራቸውን ያለምንም ተጽዕኖ እንዲሰሩ ተፈቀደላቸው። በዚህም ምክንያት አየር መንገዱ ጥራት ያለውና ዘመናዊ አገልግሎት መስጠቱን ቀጠለ።

ካፕቴን መሐመድ አህመድ አትራፊ ሆኖ በቀጠለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በስራ አስኪያጅነት እስከ 1990 ድረስ በመስራት ከዚያም በስራ ዕድገት ወደ አፍሪካ አቪዬሽን ወደ ናይሮቢ ተዛውረው በመስራትም አገልግለው በአሁኑ ወቅት በጡረታ ላይ የሚገኙ ሰው ናቸው ::
_____
የእኚህን ሰው ታሪክ በደንብ ለማወቅ የፍሰሀ ደስታን መፅሀፍ ማንበብ ጠቃሚ ነው። አየር መንገዱን በዚያ ዘመን እንዴት ከኪሳራ ወደ ትርፍማና ዘመናዊ ድርጅት እደቀየሩት መረዳት ይቻላል።

አንጋፋው ጋዜጠኛ ዜናነህ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።አንጋፋው ጋዜጠኛ ዜናነህ ፥ በኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቭዥን እንዲሁም በዴቼ ቬለ ሬድዮ ለረዥም ዓመታት አገልግሏል።ጋዜጠኛ ዜናነህ ለረዥ...
10/11/2024

አንጋፋው ጋዜጠኛ ዜናነህ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

አንጋፋው ጋዜጠኛ ዜናነህ ፥ በኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቭዥን እንዲሁም በዴቼ ቬለ ሬድዮ ለረዥም ዓመታት አገልግሏል።

ጋዜጠኛ ዜናነህ ለረዥም ጊዜያት ባደረበት ህመም ህክምናውን ሲከታተል ከነበረበት እስራኤል ቴል አቪቭ ዛሬ ጠዋት አርፏል።

በስልሳ ስምንት ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አንጋፋው ጋዜጠኛ ዜናነህ አዘዞ ጎንደር ነው የተወለደው።

ከ1970ዎቹ እስከ ሰማኒያዎቹ አጋማሽ ድረስ በኢትዮጵያ ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት በተለይ በዜና አንባቢነት አገልግሏል።

በ1980ዎቹ አጋማሽ ወደ እስራኤል ያቀናው ዜናነህ በህመም ተዳክሞ ከሥራው እስኪርቅ ድረስ በኢየሩሳሌም የዶቼ ቬለ ራዲዮ ዘጋቢ በመሆን ሲያገለግል ቆይቷል።

" ይህ ዶቼ ቨለ ነው !! " ከሚለው የዲቼቬለ ሬድዮ ጣቢያ መለያ አንስቶ የተለያዩ ዝግጅቶች መክፈቻም የአንጋፋው ጋዜጠኛ ድምፅ ነው።

የዶቼ ቬለ አድማጮች ዜናነህን ከመካከለኛው ምስራቅ በእስራኤል አረብ ግጭት እና ጦርነቶች ብሎም በቀጣናው በሚነሱ ፖለቲካዊ ዘገባዎች ያውቁታል።

የዜናነህ መኮንን የቀብር ሰነ ስረዓት ቴል አቪቭ ውስጥ በሚገኝ ፓርክ ያኮም መካነ መቃብር እንደሚፈጸም ልጁ ቢታንያ ዜናነህ ገልጻለች።

ዜናነህ ባለትዳር እና የሶስት ሴቶች ልጆች አባት ነበር።

#ዶቼቨለ

07/10/2024
🛑 አዲስ አበባ :  የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተዛሬ መስከረም 26 ቀን 2017 ዓም ምሽት 2:10 ሰዓት አካባቢ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ደረሷል።በአዲስ አ...
06/10/2024

🛑 አዲስ አበባ : የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

ዛሬ መስከረም 26 ቀን 2017 ዓም ምሽት 2:10 ሰዓት አካባቢ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ደረሷል።

በአዲስ አበባ ከተማ በተለይ በየካ አባዶ፣ አያትና አራብሳ፣ጀሞ፣ ጉለሌ ኮንዶሚኒየምና አፖርትመንት ነዋሪዎች፣ በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋው ተረብሸው ከቤታቸው ውጭ መሆናቸውን የሚያሳዩ የፎቶ እና ቪዲዮ ማስረጀዎች እየወጡ ይገኛል።

በሬክተር ስኬል 4.9 እንደተመዘገበ የተነገረው የመሬት መንቀጥቀጥ የተሠማባቸው አዲስ አበባ ፣ አማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ፣ ደቡብ ወሎ ፣ ደሴና ኮሞቦልቻ ፣ አፋር ክልል ፣ ፈንታሌ ፣ ኦሮሚያ ምስራቅ ሸዋ ናቸው ተብሏል።

ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ**********************ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በአደረባቸው ህመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡...
17/09/2024

ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
**********************

ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በአደረባቸው ህመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

የፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ህልፈተ ህይወትን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሰማቸውን ሃዘን ገልፀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሃዘን መግለጫ፤ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ረዘም ላለ ጊዜ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ስሰማ ከልብ አዝኛለሁ ብለዋል።

በኢትዮዽያ ገንቢ የፖለቲካ ባህል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ምልክት ነበሩ ሲሉም ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ያቆዩት ውርስ እና ቅርስ ፀንቶ እንዲቀጥል ነፍሳቸውም በሰላም እንድታርፍ ተመኝተዋል።

ምንጭ :- ኢቢሲ

ታሪክ እና ትዝታ !!!  ተደሰቱ 🤞                                                       መጋቢት 23 ቀን 1952 ዓ.ም
16/09/2024

ታሪክ እና ትዝታ !!!

ተደሰቱ 🤞 መጋቢት 23 ቀን 1952 ዓ.ም

14/09/2024
ሰላም ንዋይ ደበበ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷልሰላም የድምፃዊ ንዋይ ደበበ እና የአይዳ ሐሰን ወንድ ልጅ ነበር በጋብቻ ተሳስረው አሜሪካን አገር ለረጅም አመት የኖሩት ንዋይና_አይዳ ከቅርብ ዓ...
14/09/2024

ሰላም ንዋይ ደበበ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል

ሰላም የድምፃዊ ንዋይ ደበበ እና የአይዳ ሐሰን ወንድ ልጅ ነበር

በጋብቻ ተሳስረው አሜሪካን አገር ለረጅም አመት የኖሩት ንዋይና_አይዳ ከቅርብ ዓመታት በፊት በይፋ መለያየታቸውን ቢገልፁም እንደ_ቤተሰብ ብዙም አልተራራቁም።

በትዳር ሕይወታቸው የተባለች ሴት ልጅና የተባለ ወንድ ልጅ በጋራ ያፈሩት ንዋይና አይዳ ልጆቻቸውን ያሳደጉት ቨርጂንያ ውስጥ ሲሆን፣ ሰላም ከጊዜ በኋላ በገጠመው የጤና_እክል የተነሳ ሕክምና ሲከታተል ቆይቷል።

በተለይ የኩላሊት ኢንፌክሽን ተጠቂ በነበረበት ሰዓት አንድ ኩላሊት እናቱ አይዳ ሰጥታው ንቅለ ተከላ ማድረጉ ይታወሳል።

አይዳ እና ንዋይ ደበበ እንዲሁም ለመላዉ ቤተሰብ እግዚያብሔር መፅናናትን እንዲሰጣቸው እንመኛለን።

ነፍስ ይማር!

ምንጭ :- ጌጡ ተመስገን

የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት እና የውጤት መግለጫ አድራሻ ይፋ ሆነየ2016 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ውጤት እና የውጤት መግለጫ አድራሻ...
09/09/2024

የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት እና የውጤት መግለጫ አድራሻ ይፋ ሆነ

የ2016 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ውጤት እና የውጤት መግለጫ አድራሻ ይፋ ሆነ፡፡

የ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን በሚከተሉት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የውጤት መግለጫ አማራጮች ከጳጉሜ 4 ቀን ከሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ማወቅ ይችላሉ።

በዚህ መሰረት

1. ፖርታል፡- https://result.eaes.et

2. በቴሌግራም ቦት (Telegram Bot):- https://t.me/EAESbot

3. በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡- 6284 ላይ ‘R’ን በማስቀደም
የመለያ ቁጥር በማስገባት (ምሳሌ R1234567) መልዕክት በመላክ ውጤትዎን ማወቅ ይችላሉ፡፡ ይህ አማራጭ ኢትዮ ቴሌኮም የሚያስከፍለው መደበኛ የSMS ክፍያ ይኖረዋል።

ከውጤት መግለጫ ፖርታልና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማታም ይችላሉ፡፡

የፕሮፌሰር አንድሪያስ እሸቴ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ**************የፕሮፌሰር አንድሪያስ እሸቴ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስተ ካቴደራል ተፈፅሟል።ፕሮፌሰር አንድሪያስ...
08/09/2024

የፕሮፌሰር አንድሪያስ እሸቴ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ
**************

የፕሮፌሰር አንድሪያስ እሸቴ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስተ ካቴደራል ተፈፅሟል።

ፕሮፌሰር አንድሪያስ እሸቴ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በ79 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወቃል፡፡

በመምህርነት እና በፕሬዚዳንትነት ባገለገሉበት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ወዳጆች ዘመዶቻቸውና የሙያ አጋሮቻቸው በተገኙበት የሽኝት ሥነ-ሥርዓት መካሄዱን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ከኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት ዘመን ጀምሮ ሕገ-መንግሥት በማርቀቅና በማማከር ከፍተኛ ተሳትፎ ማድረጋቸውን እና በተለያዩ የመንግሥት ኃላፊነቶች ማገልገላቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡

ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ ከ1995-2003 ዓ.ም በመምህርነትና ፕሬዝዳንትነት አንጋፋውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያገለገሉ ሲሆን በፕሬዝዳንትነት ቆይታቸው ለዩኒቨርሲቲው ዘላቂ ልማት ዘርፍ ብዙ ሥራዎችን ሠርተዋል።

ፕሮፌሰር አንድሪያስ በፈላስፋነታቸው፣ በሰው ወዳድነታቸው፣ በአንደበተ ርትዑነታቸው፣ በጠንካራ መምህርነታቸውን እና በጨዋታ አዋቂነታቸው ይታወቃሉ።

ምንጭ :- ኢቢሲ

ደራሲ እና ኢንጂነር ታደለ ብጡል ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ******************ኢንጂነር ታደለ ብጡል የባንክ ባለሙያ፣ ሲቪል መሀንዲስ እና ደራሲ ናቸው። ማራዥት እና ሦስትዮሽ የተሰኙ ...
04/09/2024

ደራሲ እና ኢንጂነር ታደለ ብጡል ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
******************

ኢንጂነር ታደለ ብጡል የባንክ ባለሙያ፣ ሲቪል መሀንዲስ እና ደራሲ ናቸው። ማራዥት እና ሦስትዮሽ የተሰኙ የግጥም መድብሎች እንዲሁም የክቡር ዶ/ር ከበደ ሚካኤል፣ የሀኪም ወርቅነህ እሸቴ፣ የአፄ ቴዎድሮስ እና የልዑል አለማሁ ቴዎድሮስን ግለ ታሪኮች ፅፈዋል። የአማርኛ የምልክት ቋንቋ መዝገበ ቃላትንም አዘጋጅተዋል።

ደራሲ እና ኢንጂነር ታደለ ብጡል በተለያዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ላይ በመሳተፍም ይታወቃሉ። በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት የማታ ትምህርት ያስጀመሩ ናቸው። በታዋቂው አርበኛ የተሰየመውን ወንድራድ ት/ቤትን ከሌሎች ጋር በመሆን አቋቁመዋል። የአክሱም ሀውልት ብሄራዊ አስመላሽ ኮሚቴ አባልም ነበሩ።

የተለያዩ ባህላዊ እና ትውፊታዊ ቅርሶችን ከተለያዩ ክፍላተ ዓለማት በራሳቸው ወጪ ገዝተው በመሰብሰብ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የተለያዩ ሙዚየሞች በመለገስ ታሪካዊ አስተዋጽኦ አድርገዋል።
የ2008ዓ.ም የበጎ ሰው ተሸላሚው የሀገር ባለውለታ ኢንጅነር ታደለ ብጡል በህክምና ሲረዱ ቆይተው እሑድ ነሐሴ 26 /2016ዓ.ም በ97 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ቀብራቸው ሐሙስ ነሐሴ 30 ቀን 2016ዓ.ም በመንበረ ጽባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ከቀኑ 6፡00ሰዓት ይከናወናል።

ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።የቀድሞ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር  አንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 201...
29/08/2024

ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

የቀድሞ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም አርፈዋል።

ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለን…

ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ የዓመቱ የሰብል ልማት ተመራማሪ ተብለው ተመረጡየአሜሪካው ስመጥር ፑርዱ ዩኒቨርሲቲ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታን በአከናወኑት የግብርና ምርምር ሥራ የዓመቱ...
28/08/2024

ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ የዓመቱ የሰብል ልማት ተመራማሪ ተብለው ተመረጡ

የአሜሪካው ስመጥር ፑርዱ ዩኒቨርሲቲ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታን በአከናወኑት የግብርና ምርምር ሥራ የዓመቱ የሰብል ልማት ተመራማሪ አድርጎ መርጧል፡፡

በተለያየ ጊዜ በአካሄዱት ምርምር “ሃይብሪድ” የሆኑ የማሽላ ዘሮችን መፍጠር የቻሉ አንጋፋ ምሁር ሲሆኑ፣ በዚህ ለወገን ጠቃሚ ተግባራቸውም በዘርፉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና የተቸራቸው ኢትዮጵያዊ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ናቸው፡፡

አትሌት መዲና ኢሳ በገንዘቤ ዲባባ ተይዞ የነበረውን የ5000 ሜትር የሴቶች የሩጫ ውድድር ሪከርድ በመስበር አሸነፈች።ኢትዮጵያ በፔሩ ሊማ እየተካሄደ በሚገኘው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ከ20...
28/08/2024

አትሌት መዲና ኢሳ በገንዘቤ ዲባባ ተይዞ የነበረውን የ5000 ሜትር የሴቶች የሩጫ ውድድር ሪከርድ በመስበር አሸነፈች።

ኢትዮጵያ በፔሩ ሊማ እየተካሄደ በሚገኘው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና በ5000 ሜትር ሴቶች በአትሌት መዲና ኢሳ አማካኝነት የወርቅ ሜዳሊያ አግኘች።

በዚሁ እርቀት የብር ሜዳሊያው ደግሞ በአትሌት መቅደስ አለምእሸት አማካኝነት ተገኝቷል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአሳንሰር ጨዋታ - Discover Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የአሳንሰር ጨዋታ - Discover Ethiopia:

Share