Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Addis Maleda - አዲስ ማለዳ አዲስ ማለዳ በቻምፒየን ኮሚኒኬሽንስ አሳታሚነት ለአንባቢያን የምትደርስ ሳምንታዊ የቅዳሜ ጋዜጣ ነች።
(14)

የአዲስ ማለዳ የሳምንቱ አንኳር ዜናዎችእሁድ ሚያዝያ 13 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ)1. በኢትዮጵያ በ8 ክልሎች የሚገኙ ከ41 በሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች በኮሌራ ወረርሽኝ መጠቃታቸውን የዓለም...
21/04/2024

የአዲስ ማለዳ የሳምንቱ አንኳር ዜናዎች

እሁድ ሚያዝያ 13 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ)

1. በኢትዮጵያ በ8 ክልሎች የሚገኙ ከ41 በሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች በኮሌራ ወረርሽኝ መጠቃታቸውን የዓለም ጤና ድርጅት ገልጿል። በአንጻሩ በወባ ወረርሽኝ 1 ነጥብ 1 ሚሊየን ዜጎች መያዛቸው የተገለጸ ሲሆን ባለፈው ዓመት ከተመዘገበው ጋር ሲነጻጸር መቀነሱን ነው የዓለም ጤና ድርጅት የገለጸው።

2. የአማራ እና ትግራይ ክልሎች ከሚወዛገቡባቸው የራያ አካባቢዎች አንዱ በሆነው ራያ አላማጣ ወረዳ “የህወሓት ኃይሎች ጀመሩት በተባለው ጥቃት በተፈጠረው ግጭት ላይ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በደቡብ ትግራይ እና በሌሎች የተያዙ የትግራይ ግዛቶች የተፈጠረው ግጭት ላይ ህወሓት የለበትም በማለት ያስተባበሉ ሲሆን፤ በአንጻሩ የፕሬዝዳንቱን ማስተባበያ ተከትሎ የአማራ ክልል መንግስት ባወጣው መግለጫ “በርካሽ ፖለቲካዊ ብያኔና ፍረጃ በጊዜያዊ አሥተዳደሩ ካቢኔ አማካኝነት የአማራ ክልል ተማሪዎችን መማሪያ መጽሐፍ እንደ ሰበብ ተጠቅሞ በይፋ ጦርነት” አውጇል፤ “በሙሉ አቅሙ ወደ ጦርነት ገብቷል” ብሏል። ኢዜማ በሌሎች ክልሎች ያሉ ልዩ ኃይሎች እና ታጣቂዎች ሁሉ ፈርሰው “ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ልዩ መብት" መጎናፀፍ አሁን በአማራ ክልል ያለው ቀውስ እንዲቀጣጠል መነሻ ነው ሲል ወቅሷል። ዝርዝሩን
https://addismaleda.com/archives/36472

3. የኦሮሞ ነጻነት ግንባር በቀናት ልዩነት ባወጣቸው መግለጫዎች በፖለቲከኛው በቴ ኢርጌሳ ግድያ ዙሪያ ድርጊቱን የተመለከቱ አንድ የጥበቃ ሰራተኛ እንዲሁም አስክሬኑን ከአውሬ ሲጠብቁ የነበሩ ሰዎች የገቡበት አልታወቀም አልያም ተገድለዋል ብሏል። እንዲሁም አመራሩ በቴ ኡርጌሳ በፖለቲካዊ ግድያ ነው የሞቱት የሚል እምነት እንዳለውም ገልጿል።ዝርዝሩን https://addismaleda.com/archives/36458

4. በየዓመቱ ሚያዚያ 23 ቀን ሠራተኞች ጥያቄዎቻቸውን እና ብሶታቸውን በአደባባይ የሚያሰሙበትና የሚያከብሩት ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ) ለሁለተኛ ጊዜ በአደባባይ የማይከበር መሆኑን የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) አስታውቋል።

5. ሔዋን የተሰኘ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የጽንስና ማህጸን ልዩ የህክምና ባለሞያዎች ታማሚዎች በየዕለቱ በሚገጥማቸውን የተለያዩ ጫናዎች ምክንያት ህክምናን ማቋረጥ እና ለሞት መዳረግን መቀነስ ዓላማው ያደረገ የሴቶች ጤና ድጋፍ በጎ አድራጎት ድርጅት በይፋ ተመስርቷል።

6.የሹዋሊድ በዓል በዓለም ቅርስነት ከተመዘገበ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ማክሰኞ ሚያዝያ 8 ቀን 2016 ተከብሮ ውሏል።

7. ከዚህ ቀደም ለአገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ተከልለው የቆዩ የወጪ፣ የገቢ፣ የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ዘርፎች ለውጭ ባለሃብቶች ከፍት እንዲሆኑ የተወሰነ ሲሆን፤ በዚህም ከማዳበሪያ እና ነዳጅ በስተቀር የውጭ ባለሀብቶች በጥሬ ቡና፣ በቅባት እህሎች፣ ጫት፣ ጥራጥሬ፣ ቆዳ እና ሌጦ፣ የደን ውጤቶች እና የቁም እንስሳት የመላከ የወጪ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ መፈቀዱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን እና የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገልጸዋል፡፡

8. የጋምቤላ ክልላዊ መንግስት "ከአመራር የማስፈፀም አቅም ጋር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችን" ለመቅረፍ በሚል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊነትን ጨምሮ ስምንት አዲስ ሹመቶችን ይፋ አድርጓል።

9. ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀው በድንበርተኞቹ የአፋር እና ሶማሊ ክልል አጎራባች የሚኖሩ ጎሳዎች መካከል የሚነሱ ግጭቶችን ለመቋጨት በዘላቂነት ለመቅረፍ የተኩስ አቁም ስምምነት ተደርጓል። ሙሉ ፅሁፉ https://t.me/addismaleda/19034

10. ገዢው ብልፅግና ፓርቲ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ የሚል መጠሪያ ያላቸው የፓርቲው አባላት የመንግስትን ገጽታን በሰው ሰራሽ መንገድ መገንባት እና መንግሥትን በሚተቹ እና በሚቃወሙ ግለሰቦች ላይ ደግሞ የሐሰተኛ መረጃ እንዲሁም ‘የጥላቻ ንግግር’ የሚሆኑ ጽሑፎችና ምስሎች ማሰራጨቱን ቢቢሲ በምርመራ አረጋግጫለሁ ብሏል። በዚሁ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ፓርቲ ባወጣው መግለጫ ሥልጣን ከያዘ መንግሥት የማይጠበቅ ድርጊት ነው ያለ ሲሆን መንግሥት ከመሰል ድርጊቱ እንዲቆጠብና ለእስካኹኑ ድርጊቱ ሕዝቡን ይቅርታ እንዲጠይቅ አሳስቧል።

11. የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የፈጸሙት ወንጀል ይቅርታ የማይከለክል፣ ከተወሰነባቸው የጊዜ ቆይታ ውስጥ አንድ ሶስተኛ እና ከዚያ በላይ የሚሆን ያሳለፉ እንዲሁም ከከሳሾቻቸው ጋር እርቅ ለፈጸሙ አንድ ሺህ 460 ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታውቋል።

12. የቡድን 7 አባል አገራት በኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መካከል የባህር በር ለማግኘት የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል የተፈጠረው ውጥረት እንዳይባባስ ለመከላከል አገራቱ ሁሉንም የውይይት መንገዶች ክፍት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። በአንጻሩ የሶማሊያ መንግስት ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የደረሰችበትን የመግባቢያ ሰነድ እስካልሰረዘች ድረስ ንግግር ማድረግ ፈጽሞ የማይሆን ነገር ነው ሲል ገልጿል።

13. ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተገኙበት በተደረገ የድጋፍ ሰልፍ ላይ “በጫካ፣ በአንዳንድ ስፍራ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን፤ ከላካችሁ ኃይል ይልቅ ኢትዮጵያ ትበልጣለች፤ ከሚከፍሏችሁ ይልቅ ኢትዮጵያ ትበልጣለች” ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram | Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141

ሕክምና በማቋረጥ ለከፋ ችግርና ሞት የሚዳረጉ ሴቶችን ለመታደግ 'ሔዋን' የበጎ አድራጎት ድርጅት ተመስርቷል። ልዩ ዝግጅቱን በዩ ትዩብ ገጻችን
20/04/2024

ሕክምና በማቋረጥ ለከፋ ችግርና ሞት የሚዳረጉ ሴቶችን ለመታደግ 'ሔዋን' የበጎ አድራጎት ድርጅት ተመስርቷል። ልዩ ዝግጅቱን በዩ ትዩብ ገጻችን

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

በ“ጫካ” የምትገኙ ኢትዮጵያውያን፤ ከላኳችሁ እና ከሚከፍሏችሁ ይልቅ ኢትዮጵያ ትበልጣለች- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይቅዳሜ ሚያዝያ 12 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) “በጫካ፣ በአንዳንድ ስፍራ የም...
20/04/2024

በ“ጫካ” የምትገኙ ኢትዮጵያውያን፤ ከላኳችሁ እና ከሚከፍሏችሁ ይልቅ ኢትዮጵያ ትበልጣለች- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

ቅዳሜ ሚያዝያ 12 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) “በጫካ፣ በአንዳንድ ስፍራ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን፤ ከላካችሁ ኃይል ይልቅ ኢትዮጵያ ትበልጣለች፤ ከሚከፍሏችሁ ይልቅ ኢትዮጵያ ትበልጣለች” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ተገኝተው ለመግስታቸው በተደረገ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ነው ይህን የተናገሩት። በንግግራቸውም “ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ሰላምና ብልጽግና በጋራ እንድንቆም ከከፋፋይ፣ ከሰፈርተኝነት፣ ከመንደር እሳቤ ወጥታችሁ አብራችሁን ቁሙ” ብለዋል።

የባህል፣ የቋንቋ እና የማንነት መገለጫዎች በተፈጥሮ የተለያዩ በመሆናቸው ይህንን መደፍጠጥ አይቻልም ያሉት ተቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ነገር ግን የኛ የቋንቋ፣ የባህል እና የአቀማመጥ ልዩነት ኢትዮጵያን የሚበትን መሆን የለበትም” ሲሉ ተደምጠዋል።

በመድረኩ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በማለት እንደገለጹት “አንድነት ኃይል ነው” የሚለውን አባባል በተግባር ያሳየው የጉራጌ ሕዝብ፤ “ሊከፋፍሉን፣ ሊለዩን፣ ሊያባሉን ለሚፈልጉ፤ በየዕለቱ ገንዘባቸውንና እውቀታቸውን ለሚያጠፉ ሁሉ” ትምህርት መሆን አለበት።

የማትለምንና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ በጋራ እንድናሻግር፤ “የሳታችሁ ወንድሞቻችን ልቦና እንዲሰጣችሁ እኔና የወልቂጤ ሕዝብ በጋራ መልዕክት እናስተላልፋለን”ም ብለዋል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ሁለት አመለካከት አለ ያሉት ዐቢይ አህመድ፤ አንደኛው ኢትዮጵያ ትፈርሳለች፣ ትበታታናለች የሚል ሲሆን “እኛ ደግሞ ኢትዮጵያ ትበለጽጋለች፤ የአፍሪካ የነጻነት፣ የኢኮኖሚ፣ የሰላምና የአንድነት ምሳሌ ትሆናለች እንላለን” ሲሉ ገልጸዋል።

ሃሳቦቹ በቀላሉ አይታረቁም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የጉራጌ ሕዝቦች መርካቶን ነጻ እንዳወጣችሁ፤ ዛሬ አዲስ አበባን ከሽንት፣ ከቆሻሻ፣ ከአልባብሌ እሳቤ፣ እጅግ ኋላ ቀር ከሆነ የኑሮ ዘዬ አላቀን ወደእውነተኛ የብልጽግና ምልክት ለማሻገር የምናደርገውን ሂደት” እንድትደግፉ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የብልጽግና ፓርቲ “እስካሁን ለፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር” የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንዲጠይቅ ኢዜማ አሳሰበቅዳሜ ሚያዝያ 12 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ...
20/04/2024

የብልጽግና ፓርቲ “እስካሁን ለፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር” የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንዲጠይቅ ኢዜማ አሳሰበ

ቅዳሜ ሚያዝያ 12 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የብልጽግና ፓርቲ አስተዳደር ህቡዕ “የሚዲያ ሠራዊት” አቋቁሟል መባሉን ተከትሎ የኢትዮጵያ ሕዝብን ይቅርታ ጠይቆ ፍትህ አንዲያሰፍን ጠይቋል።

ገዢው ብልፅግና ፓርቲ “የሚዲያ ሠራዊት” የሚል መጠሪያ ያላቸው የፓርቲው አባላት የመንግስትን ገጽታን በሰው ሰራሽ መንገድ መገንባት እና መንግሥትን በሚተቹ እና በሚቃወሙ ግለሰቦች ላይ ደግሞ የሐሰተኛ መረጃ እንዲሁም ‘የጥላቻ ንግግር’ የሚሆኑ ጽሑፎችና ምስሎች ማሰራጨቱን ትላንት ቢቢሲ በምርመራ አረጋግጫለሁ ማለቱ ይታወሳል።

የፌስቡክ እናት ኩባንያ 'ሜታ' ጉዳዩን እንዳረጋገጠ ያስታወሰው ኢዜማ እንደገለጸው፤ ድርጊቱ የገዢውን ፓርቲ ሃሳብን የመግለጽ መብትን በመጨፍለቅ “አምባገነንነቱን” ከማሳየት ባለፈ “በውዳሴ ከንቱ ራስን አሸዋ ላይ የማቆም” አካሄድ ነው ሲል አሳስቧል።

የገዢው ፓርቲ ኃላፊዎች “የኃላፊነት ቦታቸውን ሊያስጠብቅላቸው የሚችል የትኛውንም ነገር ከማድረግ እንደማይመለሱ” በአገር አቀፉ ምርጫ ወቅት ያደረጓቸውን ነገሮች ማስታወስ በቂ ነው ሲል ኢዜማ ገልጿል።

ድርጊቱ ከአንድ መንግስት የሚጠበቅ አይደለም ያለው ፓርቲው የሕግ አካላት በተቀመጡ የወንጀል ድንጋጌዎች መሰረት ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጠይቋል።

ከአንድ ወር ገደማ በፊት ሮይተርስ የዜና ወኪል ከ30 በላይ የፌደራል እና የአካባቢ ባለስልጣናትን፣ ዳኞችን፣ ጠበቆችን፣ ባለሥልጣናት እና በደል የሚደርስባቸውን ሰለባዎች በማነጋግር አደረግኩት ባለው ምርመራ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ስልጣን ከመጡ ከወራት በኃላ “ኮሬ ነጌኛ” የተባለ ስውር የደህንነት ኮሚቴ መቋቋሙን ዘግቦ ነበር።

ይኽ የደህንነት ኮሚቴ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ዕውቅና መመስረቱ የተገለጸ ሲሆን ቋሚ አባላት ያሉት እና በአዲስ አበባ የብልጽግና ህንጻ ውስጥ የራሱ የሆነ ቋሚ ቢሮ እና አዳራሽ እንዳለው በመግለጽ፤ የአገር ሽማግሌዎችን ግድያ እና የታዋቂውን የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ እንዲሁም በሱ ግድያ ዙሪያ የተካሄዱ የአፍኖ ማሰር እና የ200 ንጹሐንን ግድያ ላይ ኃላፊነቱን እንደሚወስድ ተገለጾ ነበር።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

የአዲስ ማለዳ የዓርብ ሚያዝያ 11 ቀን 2016 ዕለታዊ ዜናዎች በዩ ትዩብ ቻናላችን ይመልከቱ https://youtu.be/uTe2dUYor8o———ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣...
19/04/2024

የአዲስ ማለዳ የዓርብ ሚያዝያ 11 ቀን 2016 ዕለታዊ ዜናዎች በዩ ትዩብ ቻናላችን ይመልከቱ https://youtu.be/uTe2dUYor8o
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram | Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ለአንድ ሺህ 460 ታራሚዎችን በምሕረት ለቀቀ ዓርብ ሚያዝያ 11 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ለአንድ ሺህ 460 ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን ...
19/04/2024

የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ለአንድ ሺህ 460 ታራሚዎችን በምሕረት ለቀቀ

ዓርብ ሚያዝያ 11 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ለአንድ ሺህ 460 ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን ቢሮው በሰጠው መግለጫ አስታወቀ።

መግለጫውን የሰጡት የቢሮው ኃላፊ ብርሃኑ ጎሽም የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ሚያዚያ 7 ቀን 2016 ባካሄደው 6ኛ ዙር 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ስብሰባ ለሁለተኛ ዙር የሚሰጠውን ይቅርታ ምክንያት በማድረግ በክልሉ የይቅርታ አሰጣጥ ስርዓት መወሰኛ አዋጅ ቁጥር 136/1998 መሰረት ለአንድ ሺህ 431 ወንድ እና ለ29 ሴት በድምሩ ለአንድ ሺህ 460 ታራሚዎች ምሕረት ተደርጓል ብለዋል።

ይቅርታ የተደረገላቸው ተራሚዎች የፈጸሙት ወንጅል ይቅርታ የማይከለክል፣ ከተወሰነባቸው የጊዜ ቆይታ ውስጥ አንድ ሶስተኛ እና ከዚያ በላይ የሚሆን ካሳለፉ፣ ከከሳሾቻቸው ጋር እርቅ የፈጸሙ እንዲሁም እድሜያቸውን መሰረት በማድረግ ይቅርታ መደረጉ ተገልጿል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀው የአፋር እና ኢሳ ጎሳዎች ግጭትን ለመቋጨት የተኩስ አቁም ስምምነት ተደረገዓርብ ሚያዝያ 11 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በድንበርተኞቹ የአፋር ሕዝቦች እና...
19/04/2024

ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀው የአፋር እና ኢሳ ጎሳዎች ግጭትን ለመቋጨት የተኩስ አቁም ስምምነት ተደረገ

ዓርብ ሚያዝያ 11 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በድንበርተኞቹ የአፋር ሕዝቦች እና ኢሳ በሚል መጠሪያ በሚታወቁት በሶማሌ ክልል የሚኖሩ ጎሳዎች መካከል የሚነሱ ግጭቶች በውስን አርብቶአደሮች መካከል ከሚፈጠር ግብግብነ እስከ ተካረረ እና በትጥቅ ግጭት ድረስ በየጊዜው ይከሰታል።

በዛሬው ዕለት ሚያዝያ 10 ቀን 2016 በተካሄደ ውይይት የሁለቱ ወንድማማች ህዝቦች ግጭት በዘላቂነት እንዲያበቃ የተኩስ አቁም https://t.me/addismaleda/19034
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

ጋምቤላ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊን ጨምሮ ስምንት አመራሮች በአፈጻጸም አቅም ከኃላፊነት ተነሱ  ዓርብ ሚያዚያ 11 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የጋምቤላ ክልላዊ መንግስት የሰላምና ጸጥ...
19/04/2024

ጋምቤላ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊን ጨምሮ ስምንት አመራሮች በአፈጻጸም አቅም ከኃላፊነት ተነሱ

ዓርብ ሚያዚያ 11 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የጋምቤላ ክልላዊ መንግስት የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊነትን ጨምሮ ስምንት አዲስ ሹመቶችን ይፋ አድርጓል።

አዲስ ማለዳ ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ባገኘችው መረጃ ሹመቶቹ የተሰጡት "ከአመራር የማስፈፀም አቅም ጋር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችን" ለመቅረፍ መሆኑ ተመልክቷል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዑሞድ ኡጁሉ እንደገለጹት መንግስት በዛሬው እለት የተሰጡት አዳዲስ ሹመቶች የሕዝቡን የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በአፋጣኝ ለመመለስ ነው።

በመሆኑም
👉 ባጓል ጆክ - የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ
👉 ቻም ኡቦንግ - የፍትህ ቢሮ ኃላፊ
👉 ቱት ጆክ - የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ
👉 ቾል ኬድ - የገጠር መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር
👉 ቾል ማቢየል - የብዙሃን መገናኛ አገልግሎት ኃላፊ
👉 ጉባይ ጆክ - የጤናና ጤና ነክ ክትትልና ቁጥጥር አገልግሎት ኃላፊ
👉 ላም ታንግ - የስራና ክህሎት ቢሮ የስራ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
👉 ጋትዊች ቢየል - የውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ምክትል ስራ አስኪያጅ ተደርገው ተሹመዋል።

በአንጻሩ የጋምቤላ ክልል መንግስት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ አልተወጡም ያላቸውን 4 ከፍተኛ አመራር ከሥልጣን ማንሳቱ እና በነሐሴ ወር መጨረሻ 2015፤ 13 አመራሮች ከኃላፊነታቸው መነሳቱ አይዘነጋም።

በወቅቱ በክልሉ የተወሰኑ አካባቢዎች ተከስቶ ከነበረው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ በተደረገው ግምገማም አመራሮች ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን የክልሉ መንግስት አመላክቶ ነበር።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

18/04/2024

የአዲስ ማለዳ የሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዕለታዊ ዜናዎች በዩ ትዩብ ቻናላችን ይመልከቱ

በሌሎች ክልሎች ልዩ ኃይልና ታጣቂዎች ሲበተኑ ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተሰጠው መብት ለአሁኑ ቀውስ መነሻ ነው- ኢዜማሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ባለፉት ጥቂት ቀናት ...
18/04/2024

በሌሎች ክልሎች ልዩ ኃይልና ታጣቂዎች ሲበተኑ ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተሰጠው መብት ለአሁኑ ቀውስ መነሻ ነው- ኢዜማ

ሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ባለፉት ጥቂት ቀናት በአላማጣ እና አከባቢው የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ታጣቂዎች "የኃይል እርምጃ እየወሰዱ" መሆኑን ተከትሎ መንግሥት “ጦርነት የሚጎስመውን የሕወሓት ስብስብ በፕሪቶሪያው ሥምምነት መሠረት ትጥቅ እንዲፈታ” በማድረግ ሕግ እና ሥርዓት እንዲያስከብር ሲል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ አሳሰበ።

አዲስ ማለዳ ከፓርቲው መግለጫ እንደተመለከተችው፤ ቡድኑን [ህወሓት] ትጥቅ የማስፈታት ጉዳይ ዛሬም ቢሆን ከአጎራባች ክልሎች አልፎ ለአገር ሉዓላዊነት ጠንቅ ሊሆን እንደሚችል መታሰብ ይኖርበታል ብሏል።

መንግስት ቡድኑ በፈረመው ሥምምነት መሠረት በሰላሳ ቀናት ውስጥ መሣሪያ አስረክቦ ወደ ሰላም አስተሳሰብ እንዲመጣ ሊደረግ ሲገባ ይበልጥ እራሱን አደራጅቶ ዛሬም ንፁሀን ዜጎችን ለመከራ ለእንግልት እና ከቀያቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ እንዲወድቁ እያደረገ ይገኛል ሲል ኢዜማ ህወሓትን ተችቷል።

ኢ-ሕገ መንግስታዊ አደረጃጀት የነበረው የክልል ልዩ ኃየል ትጥቅ በማስፈታት መዋቅሩ እንዲፈርስ ሲደረግ፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅና የሌለው "ፓርቲ" ከመሆኑ ባሻገር “መሣሪያ የታጠቁ የራሱ ኃይሎች ያሉት ብቸኛ ስብስብ” ነው ሲል ኢዜማ መግለጹን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተመልክታለች።

በተለይ በሌሎች ክልሎች ያሉ ልዩ ኃይሎች እና ታጣቂዎች ሁሉ ፈርሰው ወጥ በሆነ የጸጥታ አመራር ሥር ሆነው እንዲንቀሳቀሱ ቢደረግም “ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ልዩ መብት በማጎናፀፍ በሌሎች ክልሎች በሌለ እና ፈጽሞ በማይታሰብ መልኩ ታጣቂ ኃይል የማሠማራት መብት በመሰጠቱ” አሁን በአማራ ክልል ያለው ቀውስ እንዲቀጣጠል መነሻ መሆኑን ጠቁሟል።

ሕወሓት አንዴ "ትጥቅ ፈትተናል” ሌላ ጊዜ ደግሞ "የምንፈልገውን ለማድረግ በቂ ኃይል አለን” በማለት ከፕሪቶሪያው ሥምምነት ባፈነገጠ መልኩ "ሲያምታቱ"፤ የፈደራል መንግሥቱ እያሳየ ያለው ኃላፊነቱን በአግባቡ ያለመወጣት፣ ደካማ መረጃ አሰጣጥ፣ ቸልተኝነት እና መሰል ግዴለሽነት የተሞላ ተግባር በእጅጉ የሚያሳዝነን፣ በፅኑ የምናወግዘውም ነው” ብሏል።

አሁን የተከሰተውን አለመረጋጋት እና ችግር ለመፍታት የፌደራል መንግስት “የአንበሳውን ድርሻ” እንደሚወስድ የገለጸው ኢዜማ፤ መንግሥት የፕሪቶሪያውም ሥምምነት ተከብሮ በአስቸኳይ ትጥቅ እንዲፈታ እና “ጦርነት የሚጎስመውን ስብስብም ሥርዓት እንዲያሲዝ” በማለት ፓርቲው አሳስቧል።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ እንድገለጸው ይኽ መሆን ካልቻለ “ህወሓት ሰሞኑን የጀመረው ዳግም ወረራ በዜጎች ሕይወት፣ አካል እና ንብረት ላይ ለሚደርሰው ውድመት እና ምስቅልቅል መንግሥት ሙሉ ኃላፊነቱን የሚወስድ ይሆናል”።

የአማራ እና ትግራይ ክልሎች ከሚወዛገቡባቸው የራያ አካባቢዎች አንዱ በሆነው ራያ አላማጣ ወረዳ በትጥቅ የተደገፈ ግጭት መጀመሩን አዲስ ማለዳ ከተለያዩ ወገኖች የሚሰጡ መረጃዎችን እያቀረበች መዘገቧ አይዘነጋም።

"የህወሓት ኃይሎች ጀምረውታል" ከተባለው ጥቃት ተከትሎ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በዚህ ጉዳይ ላይ “ህወሓት እጁ የለበትም” ያለ ሲሆን በአንጻሩ የአማራ ክልል መንግስት “ህወሓት አራተኛ ዙር ወረራ ፈጽሞብናል” በማለት የሚቃረን መግለጫ ማውጣታቸው አይዘነጋም።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን እድሳት በገንዘብ እጥረት ሳቢያ እየተጓተተ ሲሆን ለማጠናቀቅ 85 ሚልየን ብር ያስፈልጋልሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በኢትዮጵያ የፓ...
18/04/2024

የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን እድሳት በገንዘብ እጥረት ሳቢያ እየተጓተተ ሲሆን ለማጠናቀቅ 85 ሚልየን ብር ያስፈልጋል

ሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በኢትዮጵያ የፓትሪያርክ ሹመት የሚፈጸምበቱ በቸኛ ስፍራ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን የህንፃ እድሳት እንዲጠናቀቅ 85 ሚሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።

የቤተ ክርስቲያኗ አስተዳደር ሰበካ ጉባዔ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የህንፃ እድሳቱ እስካሁን 75 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን 90 ሚሊዮን ብር ገደማ እንደፈጀ ተጠቁሟል።

የቤተ ክርስቲያኗ የእድሳት ሂደት ለ16 ወራት ያህል ጥናት ሲደረግበት ቆይቶ "በቅርስ እድሳት ልምድ ካለው" ቫርኔሮ ከተባለ ድርጅት ጋር በ172 ሚሊዮን ብር የሥራ ውል መጀመሩን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተረድታለች።

በዚህ የእድሳት ሂደት ከውጪ ለሚገቡ እቃዎች የውጭ ምንዛሪ እጥረት እንዲሁም ቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ ገቢ ታገኛለች በሚል ግምት ህብረተሰቡ ለመርዳት ፍቃደኝነት አለማሳየታቸው እንደ ተግዳሮት ተጠቅሰዋል። ድጋፍ የሚሰበሰብባቸው መንገዶችም እንደቀጠሉ ነው።

እድሳቱ ከተጀመረ አንድ ዓመት ከግማሽ ገደማ ያስቆጠረ ሲሆን መጋቢት 30 ቀን 2016 እንደሚጠናቀቅ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በገንዘብ እጥረት ሳቢያ ለሦስት ወራት እንዲራዘም መደረጉን አዲስ ማለዳ ከታደመችበት መግለጫ ሰምታለች።

የቤተ ክስርስቲያኗ አስተዳዳሪ ሊቀ ስልጣን ቆሞስ አባ ሲራክ አድማሱ እንደገለጹት እድሳቱ ከኢትዮጵያ ቅርስና ጥበቃ ህጋዊ ፈቃድ አግኝቶ የሚታደስ መሆኑን ጠቁመው በግንባታ ሂደት ያጋጠመ ችግር የለም ብለዋል።

የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን በ1924 ከተመሰረተ ጀምሮ ከ90 ዓመታት በላይ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

የሠራተኞች ጥያቄ የሚቀርብበት ዓመታዊው የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ) ዘንድሮም በአደባባይ አይከበርም ተባለ ሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በየዓመቱ ሚያዚያ 23 ቀን ሠራተኞች ጥ...
18/04/2024

የሠራተኞች ጥያቄ የሚቀርብበት ዓመታዊው የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ) ዘንድሮም በአደባባይ አይከበርም ተባለ

ሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በየዓመቱ ሚያዚያ 23 ቀን ሠራተኞች ጥያቄዎቻቸውን እና ብሶታቸውን በአደባባይ የሚያሰሙበትና የሚያከብሩት ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን (ሜይዴይ) ለሁለተኛ ጊዜ በአደባባይ እንደማይከበር የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) አስታወቀ።

የዘንድሮ አከባበርን በተመለከተ ኢሠማኮ ከኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውምን አዲስ ማለዳ ከኮንፌደሬሽኑ ያገኘችው መረጃ ያመላክታል።

በዚህም በኢትዮጵያ ለ49ኛ ጊዜ በዓለም ደረጃ ደግሞ ለ135ኛ ጊዜ የፊታችን ሚያዝያ 23 ቀን 2016 የሚከበረው በዓል "የአገሪቱን አጠቃላይ ሁኔታ በማገናዘብ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር ያሉ ከባቢዎችንም ከግምት በመክተት እንደ ባሕር ዳር፣ ኮምቦልቻና ፊንፊኔ ዙሪያ ካሉት ውጪ" በአዳራሽ ውስጥ ለማክበር ተወስኗል ተብሏል።

ባለፈው ዓመትይ 48ኛው የሠራተኞች ቀን በዓልን ኢሠማኮ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንዲሁም በክልሎች በሰላማዊ ሰልፍ ለማክበር ቢያቅድም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ቢሮ መከልከሉ አይዘነጋም።

ዘንድሮ በአዳራሽ ይከበራል በተባለው ዝግጅት በሠራተኛው በኩል ምላሽ ለሚነሱ ጥያቄዎች የመንግሥት ተወካዮች ምላሽ እንደሚሰጡ ኮንፌዴሬሽኑ ገልጿል።

እንዲሁም የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ የኢሰማኮ ጠቅላይ ምክር ቤት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ለመገናኘት የሚጠይቅ ደብዳቤ መጻፉንና ምላሽ እየተጠበቀ መሆኑ ተጠቁመዋል።

በአንጻሩ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አመራሮች ነሐሴ 24 ቀን 2015 ለመጀመሪያ ጊዜ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ ጋር ባደረጉት ውይይት ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል፣ የደመወዝ ግብር ቅነሳ እንዲሁም ለዓመታት የተቋረጠው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አማካሪ ቦርድ ሥራ እንዲጀምር ተጠይቀው ነበር።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

የአዲስ ማለዳ የረቡዕ ሚያዝያ 09 ቀን 2016 ዕለታዊ ዜናዎች በዩ ትዩብ ቻናላችን ይመልከቱ
17/04/2024

የአዲስ ማለዳ የረቡዕ ሚያዝያ 09 ቀን 2016 ዕለታዊ ዜናዎች በዩ ትዩብ ቻናላችን ይመልከቱ

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

በ15 ሰዓታት ውስጥ ከ1 ነጥብ 6 ሚልየን ብር በላይ አስመልሻለሁ ሲል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀረቡዕ ሚያዝያ 9 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ15 ሰዓታት ውስ...
17/04/2024

በ15 ሰዓታት ውስጥ ከ1 ነጥብ 6 ሚልየን ብር በላይ አስመልሻለሁ ሲል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ

ረቡዕ ሚያዝያ 9 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ15 ሰዓታት ውስጥ 1 ሚሊየን 600 ሺህ 479 ብር ያላግባብ ከተወሰደበት ገንዘብ ላይ ማስመለሱን ገለጸ።

ባንኩ ካወጣው መረጃ አዲስ ማለዳ እንደተመለከተችው እስከ ትላንት ድረስ 95 በመቶ ማለትም ብር 762 ሚልየን 941 ሺህ 341 አስመልሶ ነበር። ዛሬ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ላይ እንዳስታወቀው ደግሞ 95 ነጥብ 4 በመቶ ወይም ብር 764 ሚልየን 567 ሺህ 820 የሚሆነውን አስመልሷል።

ባንኩ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ መጋቢት 7 ቀን 2016 በተፈጠረ ችግር ምክንያት ብር 801 ሚሊየን 417 ሺህ 747 ከ81 ሳንቲም ያለአግባብ ተወስዶብኛል ማለቱ ይታወሳል።

በዚህም በተደጋጋሚ ካደረጋቸው ጥሪዎች እና ማስጠንቀቂያዎች በኋላ በአሁን ሰዓት 95 ነጥብ 4 በመቶውን እንዳስመለሰ አስታውቋል።

ቀሪውን 36 ሚሊየን 848 ሺህ 584 ብር ለማስመለስ እየተሰራ ነውም ተብሏል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

     #ተጨማሪ ህወሓት በአማራ ክልል ላይ “በሙሉ አቅሙ” ወረራ መፈጸም ጀምሯል- የአማራ ክልላዊ መንግስትረቡዕ ሚያዝያ 09 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከ...
17/04/2024

#ተጨማሪ
ህወሓት በአማራ ክልል ላይ “በሙሉ አቅሙ” ወረራ መፈጸም ጀምሯል- የአማራ ክልላዊ መንግስት

ረቡዕ ሚያዝያ 09 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከስህተቱ መማር “የተሳነው” ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) “የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል” በማለት አስታወቀ።

አዲስ ማለዳ የተመለከተችው የክልሉ መንግስት መግለጫ መጋቢት 16 ቀን 2016 “በርካሽ ፖለቲካዊ ብያኔና ፍረጃ በጊዜያዊ አሥተዳደሩ ካቢኔ አማካኝነት የአማራ ክልል ተማሪዎችን መማሪያ መጽሐፍ እንደ ሰበብ ተጠቅሞ በይፋ ጦርነት” አውጇል፤ “በሙሉ አቅሙ ወደ ጦርነት ገብቷል”... https://t.me/addismaleda/19014
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

ወቅታዊ አላማጣ እና አካባቢው ጋር የተያያዙ መረጃዎች በአዲስ ማለዳ የቴሌራም አድራሻ https://t.me/addismaledaድረ ገጽ https://addismaleda.com/archives/364...
16/04/2024

ወቅታዊ አላማጣ እና አካባቢው ጋር የተያያዙ መረጃዎች በአዲስ ማለዳ
የቴሌራም አድራሻ https://t.me/addismaleda
ድረ ገጽ https://addismaleda.com/archives/36466 ያግኙ።
እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

    #ተጨማሪ  "የአማራ ታጣቂዎች" ያቋቋሟቸውን አስተዳደሮች ለማፍረስ ከፌደራል መንግስት ጋር ተስማምተናል ሲል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀማክሰኞ ሚያዝያ 08 ቀን 2016 (አዲስ...
16/04/2024

#ተጨማሪ
"የአማራ ታጣቂዎች" ያቋቋሟቸውን አስተዳደሮች ለማፍረስ ከፌደራል መንግስት ጋር ተስማምተናል ሲል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ

ማክሰኞ ሚያዝያ 08 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በምዕራብ ትግራይ በፀለምቲ አካባቢ እና በደቡብ ትግራይ አንዳንድ አካባቢዎች በአማራ ታጣቂዎች... ዝርዝሩን https://t.me/addismaleda/19013 ቴሌግራም ገጻችን ላይ ያንብቡ።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

የህወሓት ታጣቂዎች ወረራ ፈጽመዋል ቢባልም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ህወሓት የለበትም ብሏል👉🏿 አብን አጋጣሚውን  "ይህ በራያ ብቻ የማይቆም ይልቁንም የሁሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ" ነው ...
16/04/2024

የህወሓት ታጣቂዎች ወረራ ፈጽመዋል ቢባልም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ህወሓት የለበትም ብሏል

👉🏿 አብን አጋጣሚውን "ይህ በራያ ብቻ የማይቆም ይልቁንም የሁሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ" ነው ብሎታል

ማክሰኞ ሚያዝያ 8 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በራያ አላማጣ አካባቢዎች "የህወሓት ታጣቂዎች" በፈጸሙት ጥቃት የተኩስ ልውውጥ መጀመሩ ቢዘገብም ችግሩ “በአማራና ትግራይ ክልል አስተዳደር መካከል አይደለም” ብሏል።

የፕሪቶሪያው ስምምነት እንዲተገበር ለመጠየቅ በራያ አካባቢዎች ቅዳሜና እሁድ የተካሄደውን ሰልፍ ተከትሎ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ኃይሎች ከፈቱት በተባለው ጥቃት የተኩስ ልውውጥ መጀምሩን ነዋሪዎች እና የአካባቢውን ባለስልጣናት ዋቢ ያደረጉ ዘገባዎችን አዲስ ማለዳ ተመልክታለች።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በበኩሉ ህወሓት “አራተኛ ዙር በሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል” ሲል ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ከሷል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው "በደቡብ ትግራይ እና በሌሎች የትግራይ ግዛቶች የተፈጠረው ግጭት በፌደራል መንግስትና በጊዜያዊ አስተዳደሩ ወይም በህወሓት፤ አሊያም በአማራ እና በትግራይ ክልል አስተዳደሮች መካከል የተፈጠረ አይደለም" በማለት ማጋራታቸውን አዲስ ማለዳ ተመልክታለች።

የአማራ ህዝብ “የቡድኑ ወረራ ቀጥተኛ ሰለባ እና ገፈት ቀማሽ ነው” ያለው አብን፤ የፌዴራልና የአማራ ክልል መንግስታትም በሕዝብ ላይ “የተቃጣውን የጥፋት ወረራ” በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ ጥሪውን አቅርቧል።

ጌታቸው ረዳ አክለውም የፕሪቶሪያውን ስምምነት የሚገጥሙትን ተግዳሮቶች ለመፍታት በአዲስ አበባ ስብሰባ ላይ መሆናቸውን ጠቁመው፤ "ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚሰሩ ስራዎችን ለማደናቀፍ የሚፈልጉ አካላት የፈጸሙት ነው" ብለዋል።

እንዲሁም ይኽ ክስተት ስምምነቱ ላይ ተጽዕኖ እንደሚኖረው አያጠያይቅም ያሉት ጌታቸው፤ ሰላምና ንግግር ብቸኛው መንገድ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

የአማራ ሕዝባዊ ንቅናቄ እንደገለጸው መንግስት እየተፈጸመ የሚገኘውን ጥቃት በዝምታ የሚመለከት ከሆነና "ሕህዝባችን ስርአቱን አምኖ ችግሮች ሁሉ በሕግ አግባብ ይፈታሉ የሚል ቀናኢነቱ ማታለያ ሆኖ ከዋለ፤ "ይህ በራያ ብቻ የማይቆም ይልቁንም የሁሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ እንዲሆን መንግስት የፈቀደ መሆኑን ታሪክ የሚመዘግበው ሀቅ ነው”።

የአማራና ትግራይ ክልሎች ጥያቄ በሚነሳባቸው አካባቢዎች ውጥረት ሲነግስ ይኽ የመጀመሪያው አይደለም። በራያ አካባቢ የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው አካባቢዎች ወፍላ ወረዳ፣ ዛታ ወረዳ፣ ኮረም ከተማ፣ አላማጣ ከተማ፣ አላማጣ ወረዳ እና ራያ ባላ ወረዳ ናቸው።

የፌደራል መንግስቱ ጉዳዩ በሕዝበ ውሳኔ እንደሚፈታ መግለጹን ተከትሎ የሕዝብ አሰፋፈር እና የተፈናቃዮች "ትክክለኛነት" ጉዳይ እያወዘገበ የሚገኝ ሲሆን ለሕዝበ ውሳኔ የማይመች ሁኔታ ለመፍጠር በሚደረግ ጥረት ከአማራ እና ትግራይ ክልሎች ውንጀላዎች ይደመጣሉ።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

የበቴ ኡርጌሳ ሞት ፖለቲካዊ ግድያ ነው ሲል ኦነግ አስታወቀማክሰኞ ሚያዚያ 07 ቀን 2016(አዲስ ማለዳ)የኦሮሚያ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመራሩ በቴ ኡርጌሳ በፖለቲካዊ...
16/04/2024

የበቴ ኡርጌሳ ሞት ፖለቲካዊ ግድያ ነው ሲል ኦነግ አስታወቀ

ማክሰኞ ሚያዚያ 07 ቀን 2016(አዲስ ማለዳ)የኦሮሚያ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመራሩ በቴ ኡርጌሳ በፖለቲካዊ ግድያ ነው የሞቱት ብለን እናምናለን ብሏል።

በቴ ኡርጌሳ በኦሮሞ ነፃነት ትግል በህዝቦቹ ዘንድ የተወደደ እና የተከበረ መሆኑን የሚገልጸው የኦነግ መግለጫ ‘ነገር ግን በቴ በጠላቶች እና በኢትዮጵያ መንግስት ዘንድ ፈሪ ነው ልክ እንደ ሌሎቹ ታጋዮች የተገረፈው ለዚህ ነው" ሲል አመላክቷል፡፡

በተጨማሪም መንግስት የኦነግ አመራሮች ኦሮሞን ለመበጣበጥ የድርጅቱን ትግል ለማደናቀፍ ወደ ኦሮሚያ እየመጡ አቅመ ደካሞችን ለማዳከም ከአመራሮች እስከ አባል በማሰር፣ በመግደል፤ ሁሉንም የኦሮሚያ ታጋዮችን በመግደል ሀገሪቷን እየመራ ያለውን መንግስት የፖለቲካ ግድያ እያመላከቱ ነው ብሏል።

አክሎም የበቴ ኡርጌሳ ፍትህ እንደባለፈው ግድያ በኦሮሚያ እንዳይቀር እንደ አርቲስት ዳዲ ገላን፣ ሃጫሉ ሁንዴሳ፣ አባ ገዳ ካራዩ ተድበስብቦ እንዳይቀር ነፃ ምርመራ በውጭ አካላት እንዲደረግ ጠይቋል።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት በቴ ኡርጌሳ በመቂ ከተማ ካረፉበት ሆቴል እኩለ ሌሊት ላይ “በጸጥታ አካላት” ከተወሰዱ በኋላ ተገድለው መገኘታቸውን አዲስ ማለዳ መዘገቧ ይታወሳል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram | Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141

የአዲስ ማለዳ የሚያዝያ 07 ቀን 2016 ዕለታዊ ዜናዎች በዩ ትዩብ ቻናላችን ይመልከቱ
15/04/2024

የአዲስ ማለዳ የሚያዝያ 07 ቀን 2016 ዕለታዊ ዜናዎች በዩ ትዩብ ቻናላችን ይመልከቱ

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

የሹዋሊድ በዓል በዓለም ቅርስነት ከተመዘገበ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከነገ ጀምሮ ይከበራል ሰኞ ሚያዝያ 07 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ነስሪ ዘከሪያ በክልሉ ከ...
15/04/2024

የሹዋሊድ በዓል በዓለም ቅርስነት ከተመዘገበ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከነገ ጀምሮ ይከበራል

ሰኞ ሚያዝያ 07 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ነስሪ ዘከሪያ በክልሉ ከነገ ጀምሮ የሚከበረው የሹዋሊድ በዓል ያለ አንዳች የጸጥታ ቸግር እንዲከበር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል አሉ።

በዓሉን ተከትሎ የጸጥታ ችግር እንዲከበር ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በጋራ በመቀናጀት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውም ተገልጿል።

እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ በዓሉ በሚከበርባቸው አካባቢዎች በቂ የጸጥታ ኃይሎችን በማሰማራት የቅድመ ዝግጅት ስራ ተሰርቷል። በዓሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊው የጸጥታ ስራ ይቀጥላል ተብሏል።

በተጨማሪም በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ የሚፈጠረውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ እንዲቻል የተወሰኑ መንገዶች ለትራፊክ ዝግ እንደሚሆኑ ኮሚሽነር ነስሪ ገልፆል፡፡

ኢትዮጵያ በ2016 ዓመት የሹዋልኢድ ክብረ በዓል፣ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እና የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓምድርን በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የዓለም ቅርስነት ማስመዝገቧ ይታወሳል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

በፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ ግድያ ዙሪያ የዓይን እማኞች የደረሱበት አልታወቀም፤ “አሳፋሪ” ምርመራ እየተደረገ ነው- ኦነግ ሰኞ ሚያዝያ 07 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) አጠቃላይ የሚታየው ሁኔታ...
15/04/2024

በፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ ግድያ ዙሪያ የዓይን እማኞች የደረሱበት አልታወቀም፤ “አሳፋሪ” ምርመራ እየተደረገ ነው- ኦነግ

ሰኞ ሚያዝያ 07 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) አጠቃላይ የሚታየው ሁኔታና የመንግስት የጸጥታ አካላት ባህሪ “በደርግ ጊዜ እና ቀይ ሽብር” ወቅትን ይመስላሉ ሲል ኦነግ ገልጿል።

ድርጊቱን የተመለከቱ አንድ የጥበቃ ሰራተኛ እንዲሁም አስክሬኑን ከአውሬ ሲጠብቁ የነበሩ ሰዎች የገቡበት አልታወቀም አልያም ተገድለዋል ተብሏል።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር የአባሉን ግድያ በተመለከተ በማስረጃ አረጋግጫለሁ ያላቸውን ጉዳዮች ይፋ ያደረገ ሲሆን የግድያውን ሂደት እንዲሁም በዓይን እማኖች ላይ የደረሱ ክስተቶችን https://addismaleda.com/archives/36458
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

የአዲስ ማለዳ የሳምንቱ አንኳር ዜናዎች እሁድ ሚያዝያ 06 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) 1. የአዲስ አበባ ፖሊስ በከተማዋ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ “የጽንፈኛው የፋኖ አመራር”...
14/04/2024

የአዲስ ማለዳ የሳምንቱ አንኳር ዜናዎች

እሁድ ሚያዝያ 06 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ)

1. የአዲስ አበባ ፖሊስ በከተማዋ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ “የጽንፈኛው የፋኖ አመራር” ካላቸው አካላት ጋር በዚህ ሳምንት በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሁለት "የፋኖ" አባላት ሲገደሉ፤ ሁለት የፖሊስ አባላት ቆስለዋል።

2. የመላው ኢትዮጵያ እንድነት ድርጅት (መ.ኢ.አ.ድ)፣ አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፣ እናት ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢ.ሕ.አ.ፓ) በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ፖለቲከኞች "ተጠያቂነት በሌለው አኳኋን ወደማይታወቅ ቦታ" በመንግስት እየተወሰዱ ነው ብለዋል። ሙሉ ዘገባው https://t.me/addismaleda/18972 ይመልከቱ

3. በሳዑዲ ዓረቢያ ሽሜሲ ማቆያ ማዕከል በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ዜጎችን መመለስ ተጀምሯል። 70 ሺህ ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደአገራቸው በሚቀጥሉት አራት ወራት ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

4. በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ውስጥ 221 ለእሳት አደጋ፣ 218 ለጎርፍ አደጋ፣ 27 ለትራፊክ አደጋ እንዲሁም 17 ለመሬት መንሸራተት አደጋ ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎች መለየታቸውን እና የቅድመ መከላከል ሥራ እየተሠራ እንደሆነ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል፡፡

5. አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ የጅምላ ግድያ መበራከት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል አለ። “የኢትዮጵያ መንግስት ተአማኒነት ያለው ጥረት እያደረገ አይደለም" ተብሏል፤ ዝርዝሩን https://t.me/addismaleda/18999

6. በጋምቤላ ክልል በጆርና በኢታንግ ልዩ ወረዳ ተከስቶ በነበረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት እጃቸው አለባቸው የተባሉ 14 አመራሮችና አንድ ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

7. በተለያዩ አካባቢዎች እምነትን መሰረት አድርገው የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በተመለከተ መንግስት ንጹሃን ዜጎችን ከጥቃት የመጠበቅ ሕጋዊና መንግስታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ጠባቂ አባቶች ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትም በአማራ ክልል ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች እየተባባሱ በመሆኑ የክልሉ መንግስት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቋል።

8. መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀውና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) ብሎ የሚጠራው ቡድን የኦነግ አመራሩ በቴ ኡርጌሳ በመቂ ከተማ ካረፉበት ሆቴል እኩለ ሌሊት ላይ “በጸጥታ አካላት” ከተወሰዱ በኋላ ተገድለዋል ሲል ገልጿል። የክልሉ መንግስት ከተሟላ ምርመራ በፊት ምንም ማለት አይቻልም ብሎ ለጊዜው ባልታወቁ ሰዎች ሲል ገልጾታል። የዚህ ዝርዝር https://addismaleda.com/archives/36451

9. ለሁለት ዓመታት በትግራይ ክልል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት ለ17 ወራት ሳይከፈል የቆየው የጡረታ አበል እየተከፈለ እንደሆነ አዲስ ማለዳ ከአረጋውያን ማህበሩ አረጋግጣለች። ዝርዝሩን https://t.me/addismaleda/18961 ያንብቡ

10. በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን አመያ ወረዳ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ንጹሀን እየተገደልን ነው ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል። ልዩ ስሙ ቆታ በተባለ ከተማ ታጣቂዎች "ከ40 በላይ ሰዎችን በመግደል ባንኮችን መዝረፋቸው" ለአዲስ ማለዳ ጥቆማ ደርሷል; ሙሉ ዘገባው https://t.me/addismaleda/18964

11. በ15 ቀናት ውስጥ ከ700 በላይ እግረኞች በመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 395/2009 መሰረት መቀጣታቸውን አዲስ ማለዳ ከባለስልጣኑ ሰምታለች።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram | Facebook | YouTube | X | www.addismaleda.com | 0961414141

"የፋኖ አባላት" የተባሉ ሁለት ሰዎች አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ መገደላቸውን ፖሊስ አስታወቀ ዓርብ ሚያዚያ 04 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የአዲስ አበባ ፖሊስ በአዲ...
12/04/2024

"የፋኖ አባላት" የተባሉ ሁለት ሰዎች አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ መገደላቸውን ፖሊስ አስታወቀ

ዓርብ ሚያዚያ 04 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የአዲስ አበባ ፖሊስ በአዲስ አበባ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ “የጽንፈኛው የፋኖ አመራር” ካላቸው አካላት ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አባላቱን መግደሉን አስታወቀ።

ፖሊስ በመዲናዋ “የሽበር ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ” ይዘው እየተንቃሰቀሱ መሆኑን በፀጥታ አካላት በተደረገ ክትትል ማወቅ ተችሏል ሲል ገልጿል።

አባላቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል “እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፈቃደኛ ባለመሆን ከፖሊስ አባላት ጋር ተኩስ በመክፈታቸው የቡድኑ መሪ ናሁሰናይ አንዳርጌ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት፤ አቤኔዘር ጋሻው ተሰማ በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድለዋል" ብሏል።

እንዲሁም በተኩስ ልውውጡ ሁለት የፖሊስ ሰራዊት አባላት መቁሰላቸው የተገለጸ ሲሆን ሀብታሙ አንዳርጌ የተባለ ግለሰብ “በጽንፈኛው አካላት” ተገድሏል ሲል ገልጿል።

ተጨማሪም አንድ የቡድኑ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊሰ አስታውቋል።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

በኢትዮጵያ የጅምላ ግድያ በአስደንጋጭ ሁኔታ እየተለመደ ነው- አምነስቲ ኢንተርናሽናልሚያዝያ 04 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ዓለም አቀፉ የመብቶች ተሟጋች ተቋም አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኢት...
12/04/2024

በኢትዮጵያ የጅምላ ግድያ በአስደንጋጭ ሁኔታ እየተለመደ ነው- አምነስቲ ኢንተርናሽናል

ሚያዝያ 04 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ዓለም አቀፉ የመብቶች ተሟጋች ተቋም አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ የጅምላ ግድያ መበራከት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል አለ።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል በጥር ወር በአማራ ክልል መራዊ ከተማ የተፈጸመ “የጅምላ ግድያን” አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ የመንግስት ቸልተኛነት ለከፋ ጉዳት አጋላጭ ሆኗል በማለት ወቅሷል።

በአማራ ክልል ጥር 21 ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል በነበረበት ዕለት ከ50 የሚበልጡ ሰዎች መገደላቸውን መረጃ አግኝቻለሁ ያለው የመብት ድርጅቱ፤ ከ20 የሚበልጡ አስክሬኖች በመንገድ ላይ ተጥለው የሚያሳይ የሳተላይት ምስል ዛሬ አጋርቷል።

“የኢትዮጵያ መንግስት ተአማኒነት ያለው ጥረት አለማድረጉ የተገደሉት ቤተሰቦች ፍትህ እንዳያገኙ፣ መሰል ወንጀሎች ለመከላከል እንዳይቻልና ለከፋ ጉዳት የሚያጋልጥ ሆኗል” ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል መንግስትን ወቅሷል።

ከሦስት ሳምንታት በፊት የመራዊ ጥቃትን በተመለከተ የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶችን ለኢትዮጵያ መንግስት መላኩን ያስታወቀው ድርጅቱ፤ እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘ እና እየተጠባበቀ መሆኑን ገልጿል።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል በግድያው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ለፋኖ የሚዋጉ ሰዎችን ቤት ለቤት በመፈለግ እንደወሰዱ እና አንዳንዶችን ደግሞ ያሉበትን እንዲጠቁሙ በማስገደድ ከቤት እየወሰዱ እንደገደሉ አመልክቷል።

ከአንድ ዓመት በፊት የመንግስታቱ ድርጅት መርማሪዎች ይፋ እንዳደረጉት ከሆነ ለሁለት ዓመታት በጦርነት ውስጥ በቆየው ትግራይ ክልል ብቻ ከፈረንጆቹ 2020 ጀምሮ ከ48 በላይ “ትላልቅ” ግድያዎች ተፈጽመዋል።

ይኹን እንጂ ጥር 24 ቀን 2016 ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዙ ወንጀሎች በተመለከተ የፌደራል መንስግቱ “ተገቢውን እርምጃ በእርሱ በኩል” መውሰዱን እንዳስታወቀ አዲስ ማለዳ ዘግባ ነበር።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

እምነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች አለመተማመን ለመፍጠር የሚደረጉ ናቸው - የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ሐሙስ ሚያዝያ 03 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በተለያዩ አካባቢዎች እምነትን መሰረት አድር...
11/04/2024

እምነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች አለመተማመን ለመፍጠር የሚደረጉ ናቸው - የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ

ሐሙስ ሚያዝያ 03 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በተለያዩ አካባቢዎች እምነትን መሰረት አድርገው የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በተመለከተ መንግስት ንጹሃን ዜጎችን ከጥቃት የመጠበቅ ሕጋዊና መንግስታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ጠባቂ አባቶች ጠየቁ።

ከበላይ ጠባቂ አባቶች ዛሬ ከተሰጠው መግለጫ አዲስ ማለዳ እንደተመለከተችው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለያዩ የሃይማኖት ተከታይና አባቶች ላይ ጥቃት፣ የግፍ ግድያ፣ እገታና ዝርፊያ እየተፈጸመ መሆኑ ተመላክቷል።

የጉባዔው የበላይ ጠባቂዎች በመግለጫቸው እምነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች አለመተማመን ለመፍጠር የሚደረጉ መሆናቸውን ጠቁሟል።

በዚህም መንግስት መሰል ድርጊት የሚፈጽሙትን ለህግ እንዲያቀርብና ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይከሰቱ ተገቢውን ጥበቃና ሕግ የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

ፖለቲከኞች የእምነት ተቋማትን ለፖለቲካ ዓላማ ከማዋል እንዲቆጠቡ እንዲሁም የሃይማኖት መሪዎች ፖለቲካዊ አቋምን በእምነት ተቋማት እንዳያንጸባርቁ የበላይ ጠባቂ አባቶች አሳስበዋል።

ከሰሞኑን በባህር ዳር ከተገደሉት ሙስሊሞች በተጨማሪ በሌሎች አካባቢዎችም በሌሎች እምነቶች ላይ መድረሳቸውን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተመልክታለች።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

የፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ የቀብር ስርዓት ተፈጸመ ሚያዝያ 03 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት በቴ ኡርጌሳ የቀብር ስርዓት በትውል...
11/04/2024

የፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ የቀብር ስርዓት ተፈጸመ

ሚያዝያ 03 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት በቴ ኡርጌሳ የቀብር ስርዓት በትውልድ መንደራቸው መቂ ከተማ መሰረት ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን መፈጸሙን ፓርቲው አስታዉቋል።

ከበቴ ኡርጌሳ ግድያ ጋር በተያያዘ እስካሁን የወጡ መረጃዎች የተጠናቀሩበትን የአዲስ ማለዳ ዘገባ https://addismaleda.com/archives/36451 ያንብቡ
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

 #ማስታወቂያ
11/04/2024

#ማስታወቂያ

11/04/2024

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በቴ ኡርጌሳ መገደላቸው ተሰምቷል። ፖለቲከኛው በምርጫ እና በተያያዥ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ከጥቂት ወራት በፊት አዲስ ማለዳ ስቱዲዮ ተገኝተው ቆይታ አድርገው ነበር። ሙሉ ዝግጅቱን https://www.youtube.com/watch?v=otwEbsB57IU ይመልከቱ።

ፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ “በጸጥታ አካላት” ከተያዘ በኋላ ነው የተገደለው- የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ግድያው “ባልታወቁ ሰዎች” የተፈጸመ ነው- የኦሮሚያ ክልል መንግስትሚያዝያ 03 ቀን 2016 ...
11/04/2024

ፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ “በጸጥታ አካላት” ከተያዘ በኋላ ነው የተገደለው- የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት

ግድያው “ባልታወቁ ሰዎች” የተፈጸመ ነው- የኦሮሚያ ክልል መንግስት

ሚያዝያ 03 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) ብሎ የሚጠራው ቡድን ቃል አቀባይ ኦዳ ተርቢ በኩል ባወጣው መግለጫ በቴ ኡርጌሳ በመቂ ከተማ ካረፉበት ሆቴል እኩለ ሌሊት ላይ “በጸጥታ አካላት” ከተወሰዱ በኋላ ተገድለዋል ሲል ገልጿል።

ኢሰመኮን ጨምሮ ሌሎችም የኦነግ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ግድያ ነጻ ምርመራ እንዲድረግበት እየጠየቁ ሲሆን... ዝርዝሩን ከድረ ገጻችን https://addismaleda.com/archives/36451 ይመልከቱ
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!

Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141

Address

Tsehay Messay Bldg, 4th Floor Near Bambis Supermarket
Addis Ababa
63000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Maleda - አዲስ ማለዳ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Maleda - አዲስ ማለዳ:

Videos

Share



You may also like