ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ግብረሰዶማዊነትን ይዟል ስለተባለው የ'ሳሞአ' ስምምነት ምን አሉ?
ሐሙስ መጋቢት 12 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በሕዳር ወር 2016 በሳሞአ ደሴት ላይ በአውሮፓ ሕብረት እና በአፍሪካ እንዲሁም የካሪቢያን አገራት መካከል የተፈረመው ስምምነት ተቃውሞ እየገጠመው ይገኛል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ እና ‘ስለ ኢትዮጵያ ዝም አንልም ትውልድን ከግብረሰዶም እንታደግ’ ማህበርን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዳያጸድቀው ማሳሰባቸውን አዲስ ማለዳ መዘገቧ አይዘነጋም። በመንግስት በኩልም ምላሽ የተሰጠበት ሁኔታ አልነበረም።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች እና ከተለያዩ ክልሎች ከተውጣጡ አባቶች ጋር ባደረጉት ቆይታ የ'ሳሞአ' ስምምነትን በተመለከተ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትሩም ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመጡ አባት በተነሳው ጥያቄ ላይ ብዙ ሲወራ እሰማለሁ ብለው ለኢትዮጵያ የማይጠቅም አንቀጽ ካለው ኢትዮጵያ ላይ አይፈጸምም ማለት ነው ሲሉ ተናግረዋል።
"ብዙ መሰቃየት አያስፈልግም። አንደኛ ኢትዮጵያ ሌላ አገር የምትፈራረማቸው ማንኛውም ስምምነቶች ሕግ የሚሆኑ ወደ ፓርላማ ሄደው ratify [ሲጽደቁ] ሲደረጉ ብቻ ነው" በማለትም ተናግረዋል።
ዐቢይ አህመድ አክለውም የኢትዮጵያን እሴት እና ባህል የሚሸ
#amhara #oromia #politics #ethiopia #addisababa #AbiyAhmedAli
ለእስረኞች ምሕረት ሊደረግ እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ፍንጭ ሰጡ
ሐሙስ መጋቢት 5 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ትላንት ምሽት በተካሄደ መርሃ ግብር ላይ መንግስት እስረኞችን በምህረት ሊለቅ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትላንት ምሽት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም የካቢኔ አባላት በተገኙበት በተካሄደ 'የኢትዮጵያ ተቋማት የስኬት ሽልማት' ዝግጅት ላይ የጾም ወቅቶቹ የምሕረትና የዕርቅ ጊዜ ሊሆኑ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
ዐቢይ አህመድ በመድረኩ "በዚህ በረመዳን እና በአብይ ጾም ለብዙ ደኀዎች ምግብ ለማብላት፣ ካለን ለማካፈል፣ ከተጣላናቸው ለመታረቅ፣ ካሰርናቸው ለመፍታት ልባችንን በብዙ አስፍተን ኢትዮጵያን አንድ የማትሸበረክ፤ የማትሸነፍ፣ እንደጠላቶቿ ፍላጎት ያልሆነች፣ በባዳ የተገዙ ወንድሞቻችን በዕርቅ የምንመልስበት ወርና 2 ወር እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ" ሲሉ መናገራቸውን አዲስ ማለዳ ከብሔራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያው ተመልክታለች።
———
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት እንዲሁም ሃሳብ፣ አስተያየት እና የሚዲያ ሽፋን ጥቆማ ለማድረስ
የአዲስ ማለዳ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ፤ ለሌሎችም ያጋሩ!
Telegram (https://t.ly/SOXU) | Facebook (https://t.ly/flx8) | YouTube (https://t.ly/vSgS) | X (https://t.ly/mxA)| www.addismaleda.com | 0961414141
#ቃለ_መጠይቅ!
በደቡብ ኢትዮጵያ ከሚነሱ የአደረጃጀት ጥያቄዎች ጋር በተገናኘ ከፓርላማ አባላት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ!
ነገ ነሐሴ 26/2015 ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ላይ በአዲስ ማለዳ የዩ ቲዩብ ቻናል👉 youtube.com/@addismaledanews ላይ ይጠብቁን ይጠብቁን!
#አዲስ_መንገደኛ
አዲስ ማለዳ ለእናንተ ለውድ ቤተሰቦቿ መረጃዎችን ከማድረስ በተጨማሪ፤ መረጃ ሰጭ፣ አዝናኝና አስቂኝ የመንገድ ላይ ጥያቄና መልሶችን ይዛ ቀርባለች።
ሙሉ ዝግጅቱን ለመከታተል ተከታዩን ሊንክ ይጠቀሙ👇 https://youtu.be/uXfNHbcQyRs
#ልዩ_ቃለ_መጠይቅ
የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ምን እየሰሩ ይሆን?
አዲስ ማለዳ ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትርና ከአሁኑ የአግራ (AGRA) ሊቀመንበር ኃይለ ማሪያም ደሳለኝ ጋር ልዩ ቃለ መጠይቅ አድርጋለች፡፡ በቃለ መጠይቁ የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ አሁን ላይ ስለ ኢትዮጵያ ምን ይታያቸው ይሆን? በሊቀመንበርነት የሚመሩት አግራ ለኢትዮጵያ ምን እየሰራ ነው? የሚሉና ሌሎች ጥያቄዎችን አንስተን ጥሩ ቆይታ አድርገናል፡፡
ከአግራ እስከ ግለሰባዊ ጉዳዮች የተነሱበትን ቃለ መጠይቅ በቅርብ ቀን ይጠብቁን!
እስከዚያው ከሥር ባለው ሊንክ ቤተሰብ ይሁኑ!
https://www.youtube.com/@addismaledanews
የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ተማሪ መጸዳጃ ቤት ውስጥ ሕይወቱ አልፎ ተገኘ
=======#=======
ማክሰኞ ግንቦት 1 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ የአንደኛ ዓመት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የነበረው አበባው ስንሻው መጸዳጃ ቤት ውስጥ ገብቶ የመግቢያውን በር በመቆለፍ በቀበቶ ራሱን አጥፍቶ መገኘቱን ዩኒቨርሲቲዉ አስታወቀ።
ዩኒቨርሲቲዉ፤ ተማሪዉ እዚህ አሳዛኝ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ ያበቁትን ጉዳዩች ተጨማሪ ማጣራት የሚያስፈልግ ቢሆንም፤ ‹‹ፈተና ከበደኝ›› በሚል ሲጨናነቅ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል።
ነገር ግን አዲስ ማለዳ ከዩንቨርስቲው ተማሪዎች ባገኘችው መረጃ መሰረት፤ በዩኒቨርስቲው በተደጋጋሚ ተማሪዎች ህይወታቸው አልፎ ከቀናት በኋላ የሚገኙ ሲሆን፤ ከቀናት በፊትም አንድ ተማሪ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በቅጥር ግቢው ውስጥ ተገድሎ መገኘቱ ተገልጿል። ይህ ሁኔታ በዓመቱ ሲከሰት ለአራተኛ ጊዜ ነዉም ተብሏል።
ተማሪዎች በሌሊት ወደ ቤተክርስቲያን ሲወጡና ከመሸ በግቢዉ ሲንቀሳቀሱ በስለት እየተወጉ የተገደሉ ተማሪዎች መኖራቸዉንም የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች ገልጸዋል።
ዛሬ ከረፋዱ 3 ሰዓት አካባቢ የተማሪ አበባው ስንሻውን ሕልፈት ተከትሎ የተማሪዉ አስክሬን ከግቢዉ በሚወጣበት ወቅትም፤ የተቃውሞ ሰልፍ በወጡ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች እና በፀጥታ ኃይሎች መካከል አለመግባባት መፈጠሩ ታውቋል።
በዚህ
በቤተክርስትያኒቷ ሕገ ወጥ ሲመት አከናውኗል ተብሎ የተፈረጀው ቡድን በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ታጅቦ ወደ ወሊሶ ከተማ መግባቱ ተነገረ
=======#=======
ሐሙስ የካቲት 2 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ሕገ ወጥ ሲመት አከናውኗል ተብሎ የተፈረጀው ቡድን በመከላከያ፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በኦሮሚያ ልዩ ኃይል፣ በኦሮሚያ ፖሊስ ታጅቦ ወደ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ወሊሶ ከተማ መግባቱን የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ዘግቧል።
በዚህም ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ የለያቸው አካላት ወደ ከተማዋ ይመጣሉ መባሉን ተከትሎ፤ ምእመናን፣ ወጣቶች በፀጥታ ኃሎች መታፈሳቸው ተገልጿል።
በሌላ በኩል፤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጋር በተገናኘ የተከሰተው ክስተት ዛሬም በተለያዩ አካባቢዎች ውጥረት እንዲፈጠር አድርጎ መቀጠሉ ተገልጿል።
በዚህም፤ ዛሬ ጠዋት የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት መቀመጫ በሆነችው አምቦ ከተማ የሀገረ ስብከቱ የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አባ ጴጥሮስ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት አካባቢ በሀገረ ስብከቱ ውስጥ ከሚገኘው ማረፊያቸው በጸጥታ ኃይሎች መወሰዳቸው ታውቋል።
እንዲሁም፤ የደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ቀሲስ ጥዑመ ልሳን ምሥጋናው በኦሮሚያ የጸጥታ ኃይሎች የዱላ ድብደባ ደርሶባቸው በአሁኑ ሰዓት በሻሸመኔ 010 ፖሊስ ጣቢያ በእስር ላይ እ
የጸጥታ ኃይሉ የሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ በሙሉ ሰብሮ በመግባት ምእመናን ላይ እየተኮሰ በመግደል ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ
=======#=======
ቅዳሜ ጥር 27 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በአሁኑ ሰዓት የሻሸመኔ ከተማ የጸጥታ ኃይል የሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ በሙሉ ሰብሮ በመግባት ውስጥ በሚገኙት ምእመናን ላይ እየተኮሰ በመግደል ላይ እንደሚገኝ ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ዘግቧል።
የጸጥታ ኃይሉ ፎቅ ላይ በመሆን በቀጥታ ቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ውስጥ ወዳሉት ምእመናን በስናይፐር እየተኮሰ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ በዚህም አንዲት ሴት መገደሏንና ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ምእመናንና መቁሰላቸውን ዘገባው አመላክቷል።
ከውጪ በኩልም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ሕገ ወጥ የተባለው ቡድን ያደራጃቸው ቡድኖች ድንጋይ በመወርወር ላይ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፤ በዚህም የቤተ ክርስቲያኑን በር መስበራቸውም ተገልጿል።
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ፣ ጌዲዮ፣ አማሮ፣ ቡርጂና ምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን እንደተናገሩት፤ በተለያየ አቅጣጫ እየተተኮሰ እነደሆነና የጸጥታ አካላት የመከላከል ሥራ እንዳልሠሩ ገልጸዋል።
በተጨማሪም የከተማዋ ነዋሪ ያልሆኑ ግለሰቦችን በመኪና ጭኖ እያስገባ ነው ሲሉ ብፁዕነታቸው ጠቁመዋል። ምእመናን አሁንም በጽናት እንዲጠብቁ መልዕክ
የህክምና ቁሳቁሶችን የጫኑ አራት የጭነት መኪናዎች መቀሌ ደረሱ
=======#=======
ሰኞ ጥር 15 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በኢፌዴሪ የጤና ሚኒስቴር ድጋፍ የተገኙና የተለያዩ የህክምና መስጫ ቁሳቁሶችን የጫኑ ተጨማሪ አራት የጭነት መኪናዎች ትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ መድረሳቸውን አለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታወቀ።
የህክምና መስጫ ቁሳቁሶቹ በክልሉ ለሚገኙ ጤና ጣቢያዎች እንደሚከፋፈሉ የተገለጸ ሲሆን፤ ቁሳቁሶቹ የህክምና መሳሪያዎችን፣ እንደ ኢንሱሊን እና አንቲባዮቲክ ያሉ መድሃኒቶችን እንዲሁም የእናቶች እና የህጻናት ጤና መጠበቂያ ግብዓቶችን ያካተቱ መሆናቸውም ተገልጿል።
https://t.me/addismaleda
የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዕርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ትግራይ ክልል መግባታቸውን አስታወቀ
=======#=======
ረቡዕ ኀዳር 7 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የዓለም ምግብ ፕሮግራም የሰብአዊ ዕርዳታ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ትግራይ ክልል መግባታቸውን አስታውቋል።
ተሽከርካሪዎቹ በጎንደር አድርገው ወደ ትግራይ ክልል መግባታቸውንም ነው የገለጸው።
አልሚ ምግቦቹ በቀጣዮቹ ቀናት ውስጥ ለህብረተሰቡ የሚከፋፈሉ የገለጸ ሲሆን፤ በቀጣይም አልሚ ምግቦችን ጨምሮ ተጨማሪ የምግብና የህክምና ቁሳቁስ ወደ ትግራይ ክልል እንደሚልክም ገልጿል።
በትናንትናው ዕለት ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ማህበር የአስቸኳይ ጊዜ እና የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ ለመስጠት የሚያስችሉ የህክምና ቁሳቁሶችን የያዙ ኹለት ተሽከርካሪዎች መቀሌ መድረሳቸውን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡
መቀሌ የደረሱት መድሃኒቶች አስቸኳይ የህክምና ድጋፍ ለሚሹ ሰዎች እንደሚሆኑ የገለጸው ማህበሩ፤ በሚቀጥሉት ቀናቶችም ሌሎች ተጨማሪ ድጋፎች ወደ ክልሉ እንደሚገቡም ገልጿል።
https://t.me/addismaleda
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን በድሮን የታገዘ የመብራት ትርኢት ያሳያል
=======#=======
አርብ መስከረም 27 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ ነው የተባለለትን በድሮን የታገዘ የመብራት ትርኢት (drone light show) ዛሬ መስከረም 27/2015 በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንደሚያሳይ አስታውቋል።
ትርኢቱ ከምሽቱ 1 ሰዓት ከ30 ጀምሮ እንደሚከናወን ያስታወቀው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፤ በትናንትናው ዕለት ትርኢቱ ምን እንደሚመስል ለማየት ያደረገውን ሙከራ ቪዲዮ በይፋዊ የትስስር ገጹ አጋርቷል።
https://t.me/addismaleda
የአብን አባላት የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤትን ስብሰባ ረግጠው ወጡ
=======#=======
ማክሰኞ ሰኔ 14 ቀን 2014 (አዲስ ማለዳ) የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች 6ኛው ምክር ቤት፤ በ1ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ፣ 15ኛ መደበኛ ጉባዔውን በዛሬው ዕለት እያካሄደ የሚገኝ ሲሆን፤ ከም/ቤቱ አባላት ውስጥ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባላት ስብሰባውን አቋርጠው ወጥተዋል።
ምክር ቤቱ እያከናወነው በሚገኘው በዚህ ስብሰባው ላይ፤ የምክር ቤቱን 1ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ-ጉባዔ መርምሮ ማጽደቅ እንዲሁም የፌዴራል መንግስት መሥሪያ ቤቶችን የ2013 በጀት ዓመት ሒሳብ፤ የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ለማዳመጥ አጀንዳ ተይዞ ነበር።
የአብን ተወካይ የምክር ቤት አባላቱ ስብሰባውን ረግጠው የወጡበት ምክንያትም፤ በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ አማካኝነት የምክር ቤቱ ቀዳሚ አጀንዳ ወለጋ ጊምቢ ስለተጨፈጨፉት ወገኖቻችን ብሄራዊ የሃዘን ቀን መታወጅ፣ ስብሰባውም በህሊና ጸሎት እንዲጀመር እንዲሁም ጠቅላይ ሚኒስትሩም በም/ቤቱ ቀርበው በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ ለአፈ-ጉባኤው ጥያቄ ቀርቦ በአፈ-ጉባኤው አጀንዳው እንዲያዝ ባለመፈቀዱ ምክንያት ነው።
በዚህም ምክንያት የምክር ቤቱ አባላት የሆኑት የፓርቲው ተወካዮች ስብሰባውን አቋርጠው ለመውጣት መገደዳቸውን የአብን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) አስረድተዋል።
የፓ
"በፓሊስ ሠራዊት ውስጥ ሻለቃ ነኝ። ስለዚህ መሳሪያ ባነሳ አትገረም"፡- ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ
=======#======
አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ "አገር ለመታደግ እዘምታለሁ" ማለቱን ተከትሎ ከስካይ ኒውስ ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ከጋዜጠኛው ለቀረበለት "መሳሪያ በማንሳት ወደ ጦር ግንባር ዘምተህ ትዋጋለህ ወይ?" የሚል ጥያቄ "በፓሊስ ሠራዊት ውስጥ ሻለቃ ነኝ ስለዚህ መሳሪያ ባነሳ አትገረም" ሲል ምላሽን ሰጥቷል።
አትሌት ሀይሌ በቃለ መጠይቁ መግቢያ ላይም "ወንድማማች እና እህትማማች ሕዝቦች ነን። እኔ ከማንም ጋር ችግር የለብኝም፤ እኔ ችግር ያለብኝ አገሬ ኢትዮጵያን ላፍርስ ከሚሉ ጋር ነው!" ሲልም ተናግሯል።
የኢትዮጵያ ህዝብም ወደ ግንባር ለመዝመት እያሳየ ያለው ተነሳሽነት እጅግ የሚደነቅ መሆኑንም ሀይሌ በቃለ ምልልሱ ላይ ገልጿል።
https://t.me/addismaleda
"የምንፈልገው ኢትዮጵያዊ መሆን አሊያም ኢትዮጵያ መሆን ነው" ጠቅላይ ሚኒስትር (ዶ/ር) ዐቢይ አህመድ
=======#=======
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በግንባር ሆነው ባስተላለፉት መልዕክት "ከእኔ ጀርባ የምታዩት ጠላት እስከትናንትና ድረስ ሙሉ በሙሉ የያዘው ተራራ ነው። ዛሬ አስለቅቀነዋል! ካሳጊታን ይዘናል ዛሬ ደግሞ ጭፍራንና ቡርቃን እንይዛለን" ብለዋል።
"የሰራዊቱ ሞራል እጅግ ደስ ይላል፤ ጦርነቱ በከፍተኛ ድል ነው እየተከናወነ ያለው፤የኢትዮጵያ ነጻነት እስኪረጋገጥ ወደኋለ አንልም!" ሲሉም ተናግረዋል።
"የምንፈልገው እኛ ሞተን የምትቆም ኢትዮጵያን ማየት ነው።" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የምንፈልገው ኢትዮጵያዊ መሆን አሊያም ኢትዮጵያ መሆን ነው። ሲሉም ገልፀዋል።
አክለውም "ሁሉንም በድል እንደምናሳካ በጣም እርግጠኛ ነኝ። ህዝባችን ከጎናችን ነው። በውጭ ያሉ ወገኖቻችን ባላቸው አቅም እየጮሁ ነው፤ የእኔ ሥራ ደግሞ በግንባር ሆኖ ጦርነቱን መምራት ነው። በጣም ትላልቅ ድሎች አሉ! ይቀጥላል።"
ጠላት ከእኛ ጋር ሊስተካከል የሚችል ቁመና የለውም እናሸንፋለን! ነጻ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለልጆቻችን እናሸጋግራለን። ውጤቱ በጣም ጥሩ ነው በርቱ!" ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
https://t.me/addismaleda