Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Addis Maleda - አዲስ ማለዳ አዲስ ማለዳ በቻምፒየን ኮምንኬሽንስ ተዘጋጅታ በሃገራችን ማኅበራዊ ለውጥ ለማምጣት ከሚዲያ የሚጠበቀውን ሚዛን የጠበቀ እና የተረጋገጠ መረጃ ለዜጎች የማድረስ ሚና ለመወጣት የምትሰራ ሚዲያ ነች።

ኢሕአፓ ለህዳር 27 ለጠራው “ ታላቅ ሕዝባዊ ” ስብሰባ መንግስት አዳራሽ እንደከለከለው ለአዲስ ማለዳ ገለጸቅዳሜ፣ ህዳር 20 ቀን 2018 ዓ.ም ( )የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕ...
29/11/2025

ኢሕአፓ ለህዳር 27 ለጠራው “ ታላቅ ሕዝባዊ ” ስብሰባ መንግስት አዳራሽ እንደከለከለው ለአዲስ ማለዳ ገለጸ

ቅዳሜ፣ ህዳር 20 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ለህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም “ ታላቅ ” ህዝባዊ ስብሰባ የጠራው ባለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ ነበር።

ፓርቲው ይህንን ታላቅ ሲል የጠራው ስብሰባም “ በብሔራዊ ቲያትር አዳራሽ ” እንደሚያካሂድ ከሰኞ በኋላ ባሉት ቀናት ሲያስተዋውቅ ሰንብቷል።

ስብሰባውን ለማድረግም የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የድጋፍ ደብዳቤ እንዲጽፍለት ጠይቋል። አዲስ ማለዳ በተመለከተችውና ቦርዱ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት በጻፈው ደብዳቤ “ ፓርቲው ከቦርዱ ህጋዊ ዕውቅና አግኝቶ የሚንቀሳቀስ መሆኑ ታውቆ በህጉና ሥርዓቱ መሠረት ተገቢው ትብብር እንዲደረግለት ” ጠይቋል።

ይሁንና የከተማው አስተዳደር፣ ፓርቲው ለሚያደርገው “ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ” አዳራሽ እንደከለከለ ኢሕአፓ ለአዲስ ማለዳ ነግሯታል።

ይህ ክልከላ ግን የተነገረው በቃል ደረጃ ብቻ መሆኑን አስታውቋል።

አዲስ ማለዳ ፓርቲው አዳራሹን እንደተከለከለ በገለልተኝነት ለማጣራት ያደረገችው ጥረት ለጊዜው አልተሳካላትም።

ክልከላውን አስመልክቶ ለአዲስ ማለዳ ተጨማሪ ማብራሪያዎችን የሰጡት የኢሕአፓ ፕሬዝደንት አብርሃም ኃይማኖት “ ስብሰባውን ለማካሄድ አስተዳደሩ እንቅፋት እየፈጠረ ቢሆንም አዳራሹን ለማግኘት ከፌደራሉ መንግስት ተቋማት ጋር እየተነጋገሩ ” መሆኑን አመልክተዋል።

ፕሬዝደንቱ “ ሕዝብ የሚጠቀምበትን አዳራሽ አለመስጠት፣ የፖለቲካ ምህዳሩን መዝጋት ነው “ ሲሉም በይነውታል።

በተያዘው ዓመት ምርጫ ይካሄዳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ያስታወሱት አብርሃም “ ‛መንግስት ነጻ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እናደርጋለን’ ሲል ቃል ቢገባም፣ ለሂደቱ ወሳኝ የሆኑትን ጉዳዮች ከወዲሁ መከልከሉ ህገ ወጥነት ነው “ ሲሉም ገልጸውታል።

የአዳራሽ ክልከላው ተገቢም፣ ጠቃሚም አለመሆኑን የጠቀሱት የኢሕአፓው ፕሬዝደንት ድርጊቱ “ የፖለቲካ ምህዳሩን አደጋ ውስጥ መክተት ነው” ብለዋል።

የፌደራሉ መንግስትም ግዴታውን እንዲወጣ አጥብቀው ያሳሰቡት ፕሬዝደንቱ ይህንን ክልከላ የሚያደርጉት የታችኛው የመንግስት መዋቅር አካላትንም ከደርጊታቸው እንዲታቀቡ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

ይህ “ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ” ሰላማዊ፣ ዋነኛ ዓላማውም ከህብረተሰቡ ጋር መወያየት ብቻ መሆኑን አጽዕኖት የሰጡት አብርሃም ታላቅ ያሉትን ስብሰባ መከልከል “ ምርጫ አታድርጉ እንደማለት ነው ” ሲሉ አስገንዝበዋል።

ኢሕአፓ ሰኞ ባወጣው መግለጫ “ በዚህ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ የንጹሃን እልቂት፣ የግፍ እስር፣ ጦርነት፣ ድህነት፣ ረሃብ፣ የሰላም እጦት፣ ስደት፣ መፈናቀል እና ሕዝባችንን ያጎሳቆሉት መከራዎችን ማብቂያ ዙሪያ እንደሚመከርም ” አስታውቆ ነበር።

ልክ የዛሬ ሁለት ዓመት፣ በተመሳሳይ ህዳር ወር፣ ጦርነት ይቁም፤ ተፈናቃዮች ወደቀዬያቸው ይመለሱ፣ መከላከያ ወደ ካምፑ ይግባ! የሚሉ መሪ ሃሳቦችን የያዘ ሰላማዊ ሰልፍ ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ለማካሄድ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ ህዝባዊ ትዕይንቱ ሳይካሄድ፣ የኢሕአፓ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የሰልፉ አስተባባሪዎች ለአራት ወራት ገደማ በአዋሽ አርባ በእስር አሳልፈው፣ መለቀቃቸው አይዘነጋም፡፡

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

ከሦስት ሀገራት “ ፍርደኞችን ለማስተላለፍና አሳልፎ ለመስጠት “ የሚያስችሉ ስምምነቶች ለፓርላማው ተመሩ ቅዳሜ፣ ህዳር 20 ቀን 2018 ዓ.ም ( )የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከቻይና፣ ብራዚልና ...
29/11/2025

ከሦስት ሀገራት “ ፍርደኞችን ለማስተላለፍና አሳልፎ ለመስጠት “ የሚያስችሉ ስምምነቶች ለፓርላማው ተመሩ

ቅዳሜ፣ ህዳር 20 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከቻይና፣ ብራዚልና ደቡብ አፍሪካ ጋር “ ፍርደኞችን ለማስተላለፍና አሳልፎ ለመስጠት ” የሚያስችሉ ስምምነቶችን ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቷል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 50ኛ መደበኛ ስብሰባ በስድስት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህም ከህዝባዊት ቻይና ሪፐብሊክ መንግስት ጋር በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የህግ ትብብር ለማድረግ የተደረገ ስምምነት ላይ ተወያይቷል፡፡

ከህዝባዊት ቻይና ሪፐብሊክ መንግስት እና ከብራዚል ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ መንግስት ጋር ፍርደኞችን ለማስተላለፍ የተደረጉ ስምምነቶችም ላይ መክሯል፡፡

ከደቡብ አፍሪካ ሪፐብሊክ መንግስት ጋር ደግሞ በአሳልፎ መስጠት የደረሰው ስምምነት ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱም ስምምነቶች ቢጸድቁ ኢትዮጵያ ከሀገራቱ ጋር ውጤታማ የወንጀል መከላከል የሁለትዮሽ ትብብር የሕግ ማዕቀፍ ለመፍጠር የሚያስችላት መሆኑን በመገንዘብ ረቂቅ አዋጆቹ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል።

ከእነዚህ በተጨማሪ በአምስት አጀንዳዎች ተወያይቶ ወስኛለሁ ብሏል።

እነርሱም፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ፤ ከዓለም አቀፍ የልማት ማህበር ጋር በተፈረሙ ሁለት የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነቶች፤ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴአትር ለሚሰጧቸው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚከፈሉ የአገልግሎት ክፍዎችን ለመወሰን በቀረቡ ሁለት ረቂቅ ደንቦች፤ የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ረቂቅ ደንብ፤ የኢሚግሬሽን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 114/1997 ለማሻሻል በቀረበ ደንብ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳላፏል።

የተዘረዘሩት ደንቦች ነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትመው ከወጡበት ጊዜ ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት መግለጫ አመልክቷል።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

የህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ዕለታዊ ዜና
28/11/2025

የህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ዕለታዊ ዜና

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

ከቡና ቀጥሎ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ሆኖ የቆየው የቆዳ ምርት ትኩረት በመነፈጉ ኢትዮጵያ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እንዳታገኝ ሆናለች ሲሉ በዘርፉ የተሰማሩ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተ...
28/11/2025

ከቡና ቀጥሎ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ሆኖ የቆየው የቆዳ ምርት ትኩረት በመነፈጉ ኢትዮጵያ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እንዳታገኝ ሆናለች ሲሉ በዘርፉ የተሰማሩ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተናገሩ

አርብ፣ ሕዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

በቆዳ ዘርፍ የተሰማሩ የፋብሪካ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የተናገሩት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በሞጆ ከተማ ተገኝተው የፌዴራል ዋና ኦዲተር ያደረገውን የክዋኔ ኦዲት ግኝት መነሻ በማድረግ የቆዳ ፋብሪካዎች እየወሰዱት ያለውን የማስተካከያ እርምጃ በገመገመበት ወቅት ነው።

የፋብሪካ ኃላፊዎቹና ባለሙያዎች ከቋሚ ኮሚቴው አባላት ጋር በጉዳዩ ላይ በተነጋገሩበት ወቅት የቆዳ ምርት ምንም እንኳን ከቡና ቀጥሎ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ማስገኛ ምንጭ ሆኖ የቆየ ቢሆንም ኢትዮጵያ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እያገኘች አለመሆኗን ተናግረዋል።

ባለሙያዎችና የፋብሪካ ኃላፊዎቹ ለዚህም በምክንያትነት ያቀረቡት ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ በመሆኑ ተገቢው ክትትልና ቁጥጥር ስለማይደረግበት ለቆዳ ፋብሪካዎቹ በግብዓትነት የሚቀርበው ጥሬ ቆዳ ጥራቱን የጠበቀ ባለመሆኑ ነው።

በግብዓትነት የሚቀርበው ጥሬ ቆዳ ጥራት የሌለው ከመሆኑም ባሻገር በአቅርቦት ደረጃም ጥራቱን የጠበቀ በቂ የጥሬ ቆዳ አቅርቦት ባለመኖሩ የቆዳ ፋብሪካዎች ማምረት በሚችሉት ልክ እያመረቱ አለመሆናቸውንም የፋብሪካ ኃላፊዎቹና ባለሙያዎች ለቋሚ ኮሚቴው ገልጸዋል።

በመሆኑም ከቡና ቀጥሎ ሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ስታገኝበት የነበረው የቆዳ ምርት በአሁኑ ሰዓት ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ በመሆኑ ኢትዮጵያ እንደሀገር ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እንዳታገኝ እያደረጋት መሆኗን አመለክተዋል።

የዘርፉ ተዋንያን ይህንን ይበሉ እንጂ መንግሥት በበኩሉ ኢትዮጵያን በ2022 ዓ.ም የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ ነድፌዋለሁ ባለው በአሥር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት ዋና ዋና የኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል የቆዳ ምርት የሚገኝበት የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ አንደኛው የትኩረት አቅጣጫየ ነው ማለቱ ይታወቃል።

ባለፉት አስር ወራት ወደ ውጭ ከተላከው ወርቅ 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር በማስገኘት ወርቅ ከቡና በላይ የውጭ ምንዛሬ ማስመዝገቡን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መግለጻቸው ይታወሳል።

በተመሳሳይ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 468 ሺሕ 967 ሜትሪክ ቶን ቢሊዮን ቡና ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ የተላከ ሲሆን ይህም 653 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማስገኘት በታሪክ ትልቁን ገቢ ማስገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን መግለጹ የሚታወስ ሲሆን ከወርቅና ቡና ቀጥሎ ከፍተኛ ገቢ እየተመዘገበባቸው ከሚገኙ እንደ የቅባት እህሎችና ቅመማ ቅመም እህሎች ከመሳሰሉ ምርቶች ዝርዝር መካከል የቆዳ ምርት ውጤቶች አለመካተታቸውን አዲስ ማለዳ ከተመለከተቻቸው መረጃዎች ለመረዳት ችላለች።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣን የወረዱት የጊኒ ቢሳው ፕሪዚዳንት ወደሴኔጋል መሸሻቸው ተገለጸአርብ፣ ሕዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ( )በሀገሪቱ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ስልጣን ላይ በወጡ...
28/11/2025

በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣን የወረዱት የጊኒ ቢሳው ፕሪዚዳንት ወደሴኔጋል መሸሻቸው ተገለጸ

አርብ፣ ሕዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

በሀገሪቱ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ስልጣን ላይ በወጡት ኃይሎች ታስረው የነበሩት ፕሬዚዳንት ኡማሮ ሲሴኮ ኢምባሎ ወደሴኔጋል መሸሻቸው የተገለጸው ፕሬዚዳንቱ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እነዲለቀቁ የአፍሪካ ሕብረት ጥሪ ካቀረበ ከሰዓታት በኋላ ነው።

እሁድ ዕለት በጊኒ ቢሳው ፕሬዚዳንታዊና ፓርላሜንታዊ ምርጫ ተካሄዶ ነበር። የምርጫው ውጤት ትናትንና ሐሙስ ሊገለጽ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረ ሲሆን ሀገሪቱን ለሁለተኛ ዙር ለመምራት በመወዳደር ላይ የነበሩት ፕሬዚዳንት ኡማሮ ሲሴኮ ኢምባሎ እና ተቀናቃኛቸው ፈርናንዶ ዲያዝ ዳ ኮስታ ግን የምርጫው ውጤት ከመገለጹ በፊት ከማክሰኞ ጀምረው ሁለቱም በየፊናቸው ማሸነፋቸውን መግለጽ ጀመሩ።

በዚህ መካከል ነበር “ብጥብጥ እንዳይከሰትና ሁኔታውን ለማረጋጋት” በሚል በመሃል የገባው የሀገሪቱ ጦር ከአንድ ቀን በኋላ በተደራጁ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች አማካኝነት ረቡዕ ዕለት መፈንቅለ መንግስት ማድረጉንና በኃይል ስልጣን መያዙን በሀገሪቱ ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርቦ የገለጸው።

መፈንቅለ መንግስቱ የተመራው በራሳቸው በፕሬዚዳንት ኡማሮ ሲሴኮ ኢምባሎ የግል ጠባቂና የሃገሪቱ የፕሬዚዳንታዊ ዘብ ዋና አዛዥ በነበሩት ጀኔራል ዴኒስ ንካና ሲሆን ፕሬዚዳንት በመጨረሻም ፕሬዚዳንት ኢምባሎንም ተቀናቃኛቸው ፈርናንዶ ዲያዝንም በጥጥር ስር በማዋል ማሰሩንም አስታወቀ።

በመጨረሻም ከፍተኛ ወታደራዊ ቡድኑ በትናንትናው ዕለት ጀነራል ሆርታ ንታምን የሀገሪቱ መሪ አድርጎ መሾሙን የገለጸ ሲሆን እርሳቸውም በቀጣይ ለአንድ ዓመት የሀገሪቱ መሪ ሆነው ለማስተዳደር ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።

በዚህም በጊኒ ቢሳው በመፈንቅለ መንግስት በኃይል መንበረ ስልጣኑን በተቆጣጠሩት ወታደራዊ መኮንኖች ከረቡዕ ጀምሮ በእስር ላይ የቆዩት ፕሬዚዳንት ኡማሮ ሲሴኮ ኢምባሎ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ የአፍሪካ ሕብረት ጥሪ ካቀረበ በኋላ በአሁኑ ሰዓት ተለቀው ወደሴኔጋል መሸሻቸው ታውቋል።

የሀገሪቱ የቀድሞ ቅኝ ገዥ ፖርቱጋል፣ የምዕራብ አፍሪካ መንግሥታት ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(በእንግሊዝኛ ምህጻሩ ኢኮዋስ)፣ የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግስታት በጊኒ ቢሳው የተካሄደው መፈንቅለ መንግስት የሀገሪቱን ሕገ መንግስት የሚጥስ መሆኑን በመግለጽ በሀገሪቱ ሕግና ስርዓት ወደነበረበት እንዲመለስና የሲቪል መንግስት እንዲቋቋም ሁሉም አካላት ወደንግግርና ውይይት እንዲገቡ በማሳሰብ ላይ ይገኛሉ።

ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሕዝቧ በአስከፊ ድህነት ውስጥ የሚኖርባት ትንሿ ምእራብ አፍሪካዊት ሀገር ጊኒ ቢሳው በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ1974 ከፖርቹጋል ቅኝ ግዛት ነጻ ከወጣች ወዲህ ከዘጠኝ ጊዜ በላይ የተሳኩና ያልተሳኩ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራዎች የተካሄዱባት ሀገር መሆኗንና ይህም ሀገሪቱን በማያቋርጥ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ እንድትሽከረከርና ከዓለማችን እጅግ ድሃ አገሮች መካከል አንዷ እንድትሆን ማድረጉን መረጃዎች ያመለክታሉ።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

ያድምጡት
28/11/2025

ያድምጡት

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

በዘንድሮው የአክሱም ጽዮን የንግሥ ክብረ በዓል 2 ሚሊየን ገደማ ሰዎች ሊገኙ እንደሚችሉ የአክሱም ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ለአዲስ ማለዳ ተናገረዓርብ፣ ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ( )በየዓ...
28/11/2025

በዘንድሮው የአክሱም ጽዮን የንግሥ ክብረ በዓል 2 ሚሊየን ገደማ ሰዎች ሊገኙ እንደሚችሉ የአክሱም ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ለአዲስ ማለዳ ተናገረ

ዓርብ፣ ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

በየዓመቱ በድምቀት የሚከበረውና የበርካታ ቱሪስቶች መስህብ የሆነው የአክሱም ጽዮን የንግስ ክብረ በዓል ዘንድሮም 2 ሚሊየን የሚሆኑ ሰዎች በዓሉን ለመታደም በስፋራው ሊገኙ እንደሚችሉ የአክሱም ከተማ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ ገብረ መድኀን ፍፁምብርሃን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ዕለቱን አስመልክቶ ከሁለት ወራት በፊት ዝግጅት መጀመሩን ያነሱት ኃላፊው ይህንን ክብረ በዓል የሚስተባብሩ የተለያዩ ኮሚቴዎች መዋቀራቸውንና የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በዓሉን ለመታደም ከኢትዮጵያ ውጭ ካሉ ሀገራት ከሚመጡ ዜጎች ባሻገር በርካታ ቁጥር ያላቸዉ ከተለያዩ ክልሎች የሚመጡ ተሳታፊዎች መኖራቸውን የሚገልጹት ኃላፊው “ በዚህም በህዳር 17 እና 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከአማራ ክልል 12 አውቶብሶች እንግዶችን ይዞ እንደመጣና በተመሳሳይ ከሐረርና ድሬደዋ የሚመጡትን ተሳታፊዎችም በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን ” ገልጸዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ለእንግዶቹ ማረፊያ ት/ቤቶችንና እና የማረፊያ ሆቴሎችን ያዘጋጀ መሆኑን፣ በቀን ወደ ከተማዋ ይደረግ የነበረው በረራም ወደ 8 ከፍ መደረጉን በመጥቀስ የኢትዮጵያ አየር መንገድን አመስግነዋል፡፡

ክፍያውንም በሚመለከት “ አምና አስከፍቶን ነበር ነገር ግን ዘንድሮ 20 በመቶ ቅናሽ አድርጓል ” ብለዋል፡፡

ከዚህ ቀደም ባለተለመደ ሁኔታ ከበዓሉ ቀደም ብለዉ ባሉት ቀናት በርካታ ቁጥር ያለዉ ታዳሚ በዘንድሮ ዓመት መመልከታቸዉን ያነሱት ገብረ መድህን የሰላም ሁኔታው ቀድሞም ከተማዋ የተረጋጋች ነበረች አሁን ደግሞ የፀጥታ ሐይሉ በመጠናከሩ ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም ብለዋል፡፡

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

የህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ዕለታዊ ዜና
27/11/2025

የህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ዕለታዊ ዜና

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

የፔሩ የቀድሞ ፕሬዚዳንት በተከሰሱበት የሙስና ወንጀል የአስራ አራት ዓመት እስራት ተፈረደባቸውሐሙስ፣ ሕዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ( )የፔሩ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ማርቲን ቪዝካራ ስልጣን ላይ ...
27/11/2025

የፔሩ የቀድሞ ፕሬዚዳንት በተከሰሱበት የሙስና ወንጀል የአስራ አራት ዓመት እስራት ተፈረደባቸው

ሐሙስ፣ ሕዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

የፔሩ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ማርቲን ቪዝካራ ስልጣን ላይ ከመውጣታቸው በፊት በፈጸሙት ጉቦ የመቀበል የሙስና ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው የአስራ አራት ዓመት እስራት እንደተፈረደባቸው የሃገሪቱ ፍርድ ቤት ገለጸ።

የቀድሞው የፔሩ ፕሬዚዳንት ማርቲን ቪዝካራ በሙስና ወንጀል ተከስሰው የአስራ አራት ዓመት እስር የተፈረደባቸው ወደፕሪዚዳንትነት ስልጣን ከመምጣታቸው አራት ዓመታት ቀደም ብሎ በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2011 እስከ 2014 የደቡባዊቷ ፔሩ ሞኪዩጉዋ ክልል ገዥ በነበሩበት ወቅት ውል ለማስፈጸም ከአንድ የግንባታ ተቋራጭ ድርጅት በተቀበሉት 676 ሺሕ ዶላር የሚጠጋ ጉቦ በፈጸሙት የሙስና ወንጀል መሆኑን የችሎቱ የውሳኔ መዝገብ ያሳያል።

ይሁን እንጂ የቀድሞው ፕሬዚዳንት የፖለቲካ ሴራ ሰለባ መሆናቸውን በመግለጽና ፍርዱ ትክክለኛ አለመሆኑን በመቃወም ካለፈው የጥቅምት ወር ጀምሮ የክሳቸው ሂደት ሲታይ በቆየበት ሁሉ የቀረበባቸውን ክስ በመካድ ሲከራከሩ ቆይተዋል።

“ይህ በቀል እንጂ ፍትሕ አይደለም” ሲሉም በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት የቀድሞው የፔሩ ፕሬዚዳንት የተፈረደባቸውን የእስር ብያኔ ተቃውመዋል።

“ይሁን እንጂ ሊሰብሩኝ አይችሉም” ሲሉም አክለዋል።

የቀድሞው ፕሬዚዳንት የጠበቆች ቡድን የአስራ አራት ዓመት እስር ብቻ ሳይሆን ቪስካራን ለዘጠኝ ዓመታት የመንግሥት ስልጣን ከመያዝ የሚያግደውን የፍርድ ብያኔ በመቃወም ይግባኝ ማለቱንም ገልጿል።

በሌላ በኩል በቀድሞው የፔሩ ፕሬዚዳንት ላይ የተወሰነው የፍርድ ብያኔ በቀድሞ ስያሜው “አዴብሬክት”፥ አሁን ላይ ደግሞ “ኖቮኖር” በመባል የሚታወቀው ግዙፉን የብራዚል የግንባታ ደርጅት ያሳተፈውና በሀገሪቱ መንግስታዊ ስልጣንን ለግል ሃብት መፍጠሪያ መጠቀሚያ በማድረግ ከፍተኛ ቀውስን እየፈጠረ የሚገኘውን የሙስና ወንጀል በመመርመር ላይ ለሚገኘው የፔሩ የፍትሕ አካላት መርማሪ ቡድን ትልቅ ድል መሆኑ ተጠቅሷል።

በፔሩ ከዚሁ ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ ከአውሮፓውያኑ አቆጣጠር 2018 ወዲህ ስድስት ፕሬዚዳንቶች ስልጣን ላይ የወጡና እንዲወርዱ የተደረጉ ሲሆን በዚህም ደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር በማያበራ የፖለቲካ አለመረጋጋት አዙሪት ውስጥ ሆና እንድትቀጥል እያደረጋት መሆኑን አዲስ ማለዳ ከሮይተርስና ከሌሎች ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሐን ዘገባዎች ተመልክታለች።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

የአማራ ክልል በሁለት ዓመታት “ ከ3ሺህ በላይ ጾታዊ ጥቃቶች መፈጸማቸውን ” አረጋገጠያድምጡት!
27/11/2025

የአማራ ክልል በሁለት ዓመታት “ ከ3ሺህ በላይ ጾታዊ ጥቃቶች መፈጸማቸውን ” አረጋገጠ
ያድምጡት!

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

በአማራ ክልል ግጭት ከተቀሰቀሰ ወዲህ ባለፉት ሁለት ዓመታት 3,036 ጾታዊ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ለአዲስ ማለዳ ገለጸ ሐሙስ፣ ሕዳር 18 ቀን 20...
27/11/2025

በአማራ ክልል ግጭት ከተቀሰቀሰ ወዲህ ባለፉት ሁለት ዓመታት 3,036 ጾታዊ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ለአዲስ ማለዳ ገለጸ

ሐሙስ፣ ሕዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

በአማራ ክልል በመንግሥትና በፋኖ ኃይሎች መካከል ግጭት ከተቀሰቀሰ ወዲህ ባለፉት ሁለት ዓመታት 3036 ጾታዊ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የክልሉ ሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ለአዲስ ማለዳ ገለጸ። ጸታዊ ጥቃቱ ወትሮም የነበረ ቢሆንም ግጭትና የሰላም እጦቱ ለጥቃቱ መጨመር ይበልጥ አስተዋጽኦ ማድረጉን መገምገሙንም ክልሉ አስታውቋል።

በክልሉ ከ2015 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ በመንግሥትና በፋኖ ኃይሎች መካከል ግጭት ከተቀሰቀሰ ወዲህ በ2016 ዓ.ም 1,324፤ በ2017 ዓ.ም ደግሞ 1,712፤ በሁለቱ ዓመታት ሕጻናትና ሴቶችን ጨምሮ በድምሩ 3,036 ጸታዊ ጥቃቶች መፈጸማቸውን በአማራ ክልል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሴቶች ንቅናቄ ተሳትፎ ዳይሬክተር ደስታ ፈንታ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ እስከታች እስከ ወረዳ ድረስ የሚወርድ አደረጃጀት ያለው መሆኑን ያመላከቱት ዳይሬክተሯ፤ ቢሮው ጥቃቶችን አስቀድሞ መከላከል ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ መሆኑን አመላክተዋል።

ለዚህም የሴቶችን ጥቃት አስቀድሞ ለመከላከልና ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ጥቃቱ ተፈጽሞ ሲገኝ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ፣ የጤና፣ የፍትሕና ፀጥታ አካላትን ያካተቱ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከሎች መኖራቸውን ተናግረዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታትም ቢሮው በተለመደው መንገድ ጥቃቶች ከመፈጸማቸው በፊት ቀድሞ ለመከለካል ትኩረት አድርጎ ሲሰራ የቆየ ቢሆንም የተፈጸሙት ጥቃቶች ይህንኑ የመከላከል ሥራ አልፈው የተፈጸሙ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።

ይህንንም ለዚሁ ዓላማ ተብለው ማለትም የሴቶችን ጥቃት አስቀድሞ ለመከላከልና ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ጥቃቱ ተፈጽሞ ሲገኝ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ታስበው፤ ከሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ፣ ከጤና፣ ከፍትሕና ፀጥታ አካላት ተውጣትተው ለዚሁ ዓላማ ተብለው በየወረዳው በተቋዓቋሙ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከሎች አማካኝነት በተሰበሰበና በተጎጂዎች ሪፖርት በተደረገ መረጃ ማረጋገጥ መቻሉን አስረድተዋል።

ጥቃቱ ሌላም ጊዜ የነበረ ቢሆንም በክልሉ ያለው ግጭትና የሰላም እጦት ግን ለተፈጸመው ጾታዊ ጥቃት የበለጠ አስተዋጽኦ አድርጓል በሚል ክልሉ መገምገሙንም ዳይሬክተሯ አመላክተዋል።

ጥቃት ፈጻሚውን አካል በተመለከተም ከአዲስ ማለዳ ለቀረበላቸው ጥያቄ ዳይሬክተሯ፤ “የፀጥታና የሰላም እጦት ችግር ሲኖር የመጀመሪያዎቹ ተጋላጮች የሚሆኑት ሕጻናትና ሴቶች ናቸው፤ የሰላም እጦቱም ችግሩን አባብሶት ሊሆን ይችላል የሚል እንጂ ጥቃት ፈጻሚውን በተመለከተ እከሌ ነው፣ እከሌ ነው ይህን ጥቃት የፈጸመው ብሎ ማስቀመጥ የሚቻል ነገር አይደለም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ጾታዊ ጥቃት እኮ በማንም ሊፈጸም ይችላል፤ በግጭት በሚሳተፉ አካላት ብቻ ሳይሆን በቤተሰብ ጭምር ሊፈጸም ይችላል በአባት፣ በወንድም፣ በጎረቤት፣ በአከራይ፣ በተከራይ...እንደገና በግጭት ውስጥ ብቻ ሳይሆን በሰላማዊ ጊዜ እንዲሁም በአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን ከተማም ቢሆን በየትኛውም ቦታ ቢሆን ሊፈጸም ይችላል” ሲሉም አክለዋል።

“ጥቃቱ በማንም ይፈጸም የእኛ ዋነኛው ሥራችን ተጎጂዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ ነው” ያሉት ዳይሬክተሯ፤ አስፈላጊው መረጃና ማስረጃ ተሟዓልቶ ሲገኝ ከሕግና የፍትሕ አካላት ጋር በመተባበር ጥቃት ፈጻሚው አካል ማንም ይሁን በሕግ ተጠያቂ እንዲሆንና ተጎጂዎች ፍትሕ እንዲያገኙ ማድረግን ጨምሮ ተጎጂዎቹ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንዲያገኙ እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።

በሴቶች ላይ የሚደርሰው ጾታዊ ጥቃት ከጾታ ጥቃት በአሻገር ሥነ ልቦናዊ የጤናና፣ ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ጉዳቶችን የሚያስከትል በመሆኑ ትጎጂዎቹ የሥነ ልቦና ምክርና እርዳታ፣ የኢኮኖሚ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸውና መሥራት ለሚችሉ ወደሥራ እንዲገቡ፣ በተላላፊ በሽታዎች እንዳይጠቁ የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ ይገኛል።

በዚህም ጥቃቱ ከደረሰባቸው ሴቶች መካከል አብዛኞቹ አስፈላጊውን ድጋፍ አግኝተው ወደመደበኛ ሕይወታቸው የተመለሱ መሆናቸውንም ዳይሬክተሯዓ ለአዲስ ማለዳ በሰጡት ሰፊ ማብራሪያ አመላክተዋል።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

ኡጋንዳ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ኤርትራን ጨምሮ በአሁኑ ሰዓት በጦርነት ውስጥ ካልሆኑ ሀገራት ከዚህ በኋላ ስደተኞችን እንደማትቀበል አስታወቀችረቡእ፣ ሕዳር 17 ቀን 2018 ዓ.ም ( ) የኡጋንዳ...
26/11/2025

ኡጋንዳ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ኤርትራን ጨምሮ በአሁኑ ሰዓት በጦርነት ውስጥ ካልሆኑ ሀገራት ከዚህ በኋላ ስደተኞችን እንደማትቀበል አስታወቀች

ረቡእ፣ ሕዳር 17 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

የኡጋንዳ መንግሥት እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰውና ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ኤርትራን ጨምሮ በአሁኑ ሰዓት በጦርነት ውስጥ ካልሆኑ ሀገራት ከዚህ በኋላ ስደተኞችን እንደማይቀበል የገለጸው በሀገሪቱ የሚገኙ የስደተኞች ቁጥር ሁለት ሚሊዮን ገደማ መድረሱን ተከትሎ የለጋሶች ድጋፍ መጠን እየቀነሰ በመምጣቱ መሆኑን አስታውቋል።

የኡጋንዳ የእርዳታ፣ የአደጋ መከላከል ዝግጁነትና ስደተኞች ሚኒስትር ሂላሪ ኦኔክ ለዴይሊ ሞኒተር እንደተናገሩት ኡጋንዳ ለስደተኞች እርዳታ የሚውል በያመቱ 240 ሚሊዮን ዶላር ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከፍተኘ የስደተኞች ኮሚሽን ስትቀበል ቆይታለች።

ይሁን እንጂ በአሁኑ ሰዓት ሀገሪቱ ከለጋሾች የምታገኘው የገንዘብ ድጋፍ ወደ አንድ መቶ ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ማለቱንና በዚህ ዓመት የተገኘው ድጋፍ ደግሞ 18 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መሆኑን ሚኒስትሯ ተናግረዋል።

ይህም በኡጋንዳ ሚገኙ የስደተኞች ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መምጣቱና በአንጻሩ ስደተኞችን ለማስተናገድ ሀገሪቱ ከለጋሾች የምታገኘው የድጋፍ መጠን እየቀነሰ መምጣቱ የሃብትና አገልግሎት እጥረት እንዲፈጠርና አፍሪካዊቷን ሀገር ጫና ውስጥ እንድትገባ እንዳደረጋት ተገልጿል።

በመሆኑም አሁንም ቢሆን ኡጋንዳ በሯን ለስደተኞች ክፍት የማድረግ ፖሊሲዋን የምትቀጥልበት ቢሆንም ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ኤርትራን ጨምሮ በአሁኑ ሰዓት ጦርነት ላይ ካልሆኑ ሀገራት የሚመጡ አዳዲስ ስደተኞችን ግን ከዚህ በኋላ የማትቀበል መሆኗን የሀገሪቱ ባለስልጣናት በአጽንኦት ገልጸዋል።

ያም ሆኖ ውሳኔው ከዚህ በፊት ወደኡጋንዳ የገቡትን የማይነካ መሆኑና በሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ነባር ስደተኞች ባሉበት የሚቀጥሉ መሆናቸው ተገልጿል።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

Address

Tsehay Messay Bldg, 4th Floor Near Bambis Supermarket
Addis Ababa
63000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Maleda - አዲስ ማለዳ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Maleda - አዲስ ማለዳ:

Share