በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል በመቀላቀል
https://t.me/aac_pshrdb
ያለዎትን ሀሳብ አስተያት እንዲሁም ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ

ቢሮ የመጀመሪያ ስድስት ወራት እቅድ አፈፃፀም እና የቀሪ ስድስት ወራት የተከለሰ እቅድ ላይ ከአመራርና ሰራተኞች ጋር ገመገመ።።።።።።።።።።።ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 24 ቀን 2017ዓ.ም ...
01/02/2025

ቢሮ የመጀመሪያ ስድስት ወራት እቅድ አፈፃፀም እና
የቀሪ ስድስት ወራት የተከለሰ እቅድ ላይ ከአመራርና ሰራተኞች ጋር ገመገመ
።።።።።።።።።።።
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 24 ቀን 2017ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት በዋና ዋና ስትራቴጂካዊ እቅድ የተግባራት አፈፃፀም ላይ እና የቀሪ ስድስት ወራት የተከለሰ እቅድ ላይ ከአመራርና ሰራተኞች ጋር በጋራ በመገምገም ወይይት አካሂዷል።

የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የሰው ሀብት ስራ አመራር ዘርፍ ኃላፊ አቶ መላኩ ታምሩ እንደተናገሩት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ የማካሄድ ጠቀሜታው የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትን ለማስቀጠል ብሎም የአፈፃፀም ክፍተት ያለባቸውን ተግባራት ለቀጣይ ለማረም እንዲያች በየጊዜው የግምገማ ስረዓት ወሳኝ ሚና አለው ብለዋ።
የቢሮበቀረበው የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ከተቋም ግንባታ አንፃር፣ ምቹ የስራ ከባቢን ከመፍጠር፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አፈታትና ቅሬታን ከመቀነስ፣ ከኢኒሼቲቭ ስራዎች አንፃር፣ ሪፎርም ካደረኩ ተቋማት አንፃር፣ ከአሰራርና አደረጃጀት እና ከተቋሙ ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ እቅድ አንፃር የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በዝርዝር ለውይይት ቀርቧል።

በቀረበው ሪፖርት ላይ ለተነሱ ሀሳብ እና አስተያየቶች የቢሮ አመራሮች ምላሽ ሰተውባቸዋል።

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

ቢሮው በተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓት (ኢስሚስ) ላይ ከተቋማት እና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ለተውጣጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች የአምስተኛ ዙር ስልጠና መስጠ...
31/01/2025

ቢሮው በተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓት (ኢስሚስ) ላይ ከተቋማት እና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ለተውጣጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች የአምስተኛ ዙር ስልጠና መስጠት ጀመረ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 23 ቀን 2017ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ከተቋማት እና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ለተውጣጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች በተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ሥርዓት ላይ በመንግስት ተቋማት በሥራ ላይ ያለውን የሰው ሀብት መረጃ አያያዝ ሥርዓት በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በማድረግ የአሰራር ሥርዓቱን ማዘመን ብሎም የመረጃ አያያዝና የአጠቃቀም ሂደቱን ተደራሽ ለማድረግ የሚያግዝ ስልጠና እሰጠ ይገኛል፡፡

በስልጠናው ላይ የሲስተሙን አተገባበርና ፋይዳ ላይ ማብራሪያ የሰጡት በቢሮው የሰው ሀብት ስራ አመራር ዘርፍ የሰው ሀብት ስምሪትና መረጃ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ለገሰ እንደተናገሩት የሲስተሙ ዓላማ የመንግስት ሰራተኛው መረጃ በከተማ አስታዳደሩ ደረጃ በተማከለ ሁኔታ ለማደራጀት እና የሰው ሀብት መረጃ ልውውጡን በኦን ላይን በማድረግ የወረቀት ስራዎችን ለማስቀረት እንዲቻል ለማድረግ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም የሲስተሙ መተግበር የሚሰጠው ፋይዳ የመንግስት ተቋማት በቴክኖሎጂ ታግዘው አገልግሎት መሰጠት እንዲችሉ በማድረግ ህግና መመሪያን የተከተለ የሰው ሀብት ስምሪት እንዲኖር እንደሚያስችል ገልጸው የሰው ሀብት መረጃ ሪፖርቶችን ከአንድ መረጃ ቋት በማግኘት ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል እንደሚያሰችል ገልፀዋል፡፡

የሲስተሙ ይዘት በመረጃ አያያዝ ስርዓት የተካተቱ አምስት ዋና ዋና ሞጅሎች ያሉት ሲሆን እነዚህም የሰው ሀብት አስተዳደር ሞጅል፣ የመዋቅርና የስራ መደብ ሞጅል፣ የኢንስፔክሽን ሞጅል፣ የሪከርድና ማህደር ሞጅል እና የአስተዳደር ፍርድ ቤት ሞጅሎች ላይ ትኩረት በማድረግ ስልጠናው እየተሰጠ ይገኛል፡፡

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

ቢሮው በቀሪ ስድስት ወር የተከለሰ እቅድ እና በሶስት ዓመት የበጀት እቅድ ላይ ከቢሮ አመራርና ጀነራል ካውንስል አባላት ጋር ተወያየ።።።።።።።።።ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 22 ቀን 2017ዓ...
30/01/2025

ቢሮው በቀሪ ስድስት ወር የተከለሰ እቅድ እና በሶስት ዓመት የበጀት እቅድ ላይ ከቢሮ አመራርና ጀነራል ካውንስል አባላት ጋር ተወያየ
።።።።።።።።።
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 22 ቀን 2017ዓም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ተግባራትን በቀሪ ስድስት ወራት ለማከናወን እንዲቻል የተከለሰ የዘርፍና የቢሮ እቅድ ላይ እና በሶስት ዓመት የበጀት እቅድ ላይ ከቢሮ አመራርና ጀነራል ካውንስል አባላት ጋር ተወያይቷል።

በቢሮ ሀላፊ ደረጃ የሰው ሀብት ስራ አመራር ዘርፍ ኃላፊ አቶ መላኩ ታምሩ እንደተናገሩት እቅድ መከለስ ተግባራትን በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ ለማከናወን እንደሚያስችል ገልፀው በየዘርፎች ማስተካከያ የሚፈልጉ ጉዳዮችን በመነጋገር እንዲስተካከል አሳስበዋል።

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

በክፍለ ከተማው የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማዘመን እና ምቹ የስራ ከባቢን በመፍጠር እረገድ በዘጠና ቀን እቅድ ውጤታማ ተግባራትን ለማሳካት በትኩረት መሰራቱን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፐብሊክ ሰር...
29/01/2025

በክፍለ ከተማው የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማዘመን እና ምቹ የስራ ከባቢን በመፍጠር እረገድ በዘጠና ቀን እቅድ ውጤታማ ተግባራትን ለማሳካት በትኩረት መሰራቱን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት አስታወቀ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 21 ቀን 2017ዓ.ም

በክፍለ ከተማው የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማዘመን እና ምቹ የስራ ከባቢን በመፍጠር እረገድ 2017 በጀት አመት የአገልግሎት አሰጣጡን ከማሻሻል ብሎም የተገልጋይና የሰራተኛ ምች ሁኔታን ለመፍጠር የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ በዘጠና ቀን እቅድ ውጤታማ ተግባራትን ለማሳካት በትኩረት በመስራት ላይ እንደሚገኝ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሚፍታህ ውልጫፎ ተናግረዋል፡፡

ሀላፊው እንደገለፁት ማህበረሰቡ ለአገልግሎት በሚመጣበት ወቅት የሚፈጠሩ እንግልቶችን ለመቀነስ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እና ከብልሹ አሰራር የፀዳ ፈጣን አገልግሎት መሰጠት መቻሉን ጠቅሰው በዋነኝነት የመረጃ መስጫ (display) በማዘጋጀት ተገልጋዩ ተፈላጊውን አገልግሎት ሰጪ አካል በቀላሉ ለማግኘት የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት የአገልግሎት ቅድመ ሁኔታዎችን ለተገልጋዩ ግጽል እንዲሆን መደረጉን ገልጸዋል።

ከዚህም ጋር ተያይዞ የተገልጋዩን ፍላጎት እና የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍና ለመጨመር የወረዳዎችን የመፈፀም አቅም ለማጎልበት በ12 ወረዳዎች የዋና ስራ አስፈፃሚ፣ የፐብሊክ ፅ/ቤት፣ የቤቶች ፅ/ቤቶች እና ተገልጋይ የሚበዛባቸውን ፅ/ቤቶች የማዘመን ስራ 95 በመቶኛ የሚሆነው ስራ እየተገባደደ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል በእሮብ እና አርብ የተገልጋይ ቀን አመራሩና ሰራተኛው በስራ ገበታቸው በመገኘት ተገቢውን አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ሚፍታህ ፅ/ቤቱም ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ማህበረሰብ የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ እንደሚደረግ ገልፀዋል።

በመጨረሻም ምቹ የስራ ከባቢን ከመፍጠር አንፃር ለሰራተኛው የህፃናት ማቆያ ማዕከላትን በመገንባት ስራ ላይ በማዋል በተለይም የእናት ሰራተኞችን ችግር በጥቂቱ ለማቃለል መቻሉን ገልፀው የሰራተኛ ካፍቴሪያ አገልግሎትም እየተሰጠ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

በቢሮው በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርዳይዜሽን ማንዋል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ካውንስል አደረጃጀት ላይ ከተቋማት ከተወጣጡ የቢሮ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡...
28/01/2025

በቢሮው በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርዳይዜሽን ማንዋል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ካውንስል አደረጃጀት ላይ ከተቋማት ከተወጣጡ የቢሮ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 20 ቀን 2017ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥና የውትሶርስ ዘርፍ በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርዳይዜሽን ማንዋል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ካውንስል ( የመማክርት ጉባኤ ) አደረጃጀት በቀረበ ሰነድ ላይ ከተቋማት ከተወጣጡ የቢሮ ኃላፊዎች ጋር ተወያይቷል፡፡

የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርዳይዜሽን ማንዋል ሰነድ ያቀረቡት በቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርዳይዜሽን ምዘና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አድሄና ተበጀ የማኑዋሉ ዝግጅት ዓላማ በከተማ አስተዳደሩ ያሉ የመንግስት ተቋማት እና የልማት ድርጅቶች ውስጥ የሚሰጡ አገልግሎቶች ስታንዳርዳይዝ በማድረግ የአገልግሎት ቅልጥፍናን በመጨመር እና አገልግሎቶችን በስታነዳርዳይዜሽን ማዕቀፍ ልኬት መሰረት ደረጃቸውን በመለካት የህብረተሰቡን አዳጊ ፍላጎት መሙላት እንዲቻል የማኑዋሉ ዋነኛ አላማ መሆኑን በዝርዝር አስገንዝበዋል፡፡

በሌላ በኩል የአገልግሎት አሰጣጥ ካውንስል አደረጃጀት ሰነድ ያቀረብት በቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ክንፈ ፍቅሬ የአገልግሎት አሰጣጥ ካውንስል ( የመማክርት ጉባኤ ) አደረጃጀት በተቋማት የአገልግሎት አቅርቦትና በተገልጋይ ፍላጎት መካከል ያለውን ክፍተት ለመሙላት የሚያስችል መዋቅርና አደረጃጀት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የመድረኩን ማጠቃለያ የሰጡት በቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥና አውትሶርስ ዘርፍ ሀላፊ አቶ በቀለ ተመስገን እንደተናገሩት ዘላቂነት ያለው ለውጥ ለማምጣት የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን በመለካት በተቋማት ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓት ለመዘርካት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው የከተማዋን የአገልግሎት አሰጥጥ ለማሻሻል የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

በቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥ እና አውትሶርስ ዘርፍ በተመረጡ ሁለት ተቋማት ላይ ምርጥ ተሞክሮዎችን ገመገመ።።።።።።።።። ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 19/2017ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳ...
27/01/2025

በቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥ እና አውትሶርስ ዘርፍ በተመረጡ ሁለት ተቋማት ላይ ምርጥ ተሞክሮዎችን ገመገመ
።።።።።።።።።
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 19/2017ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ የሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥና አውትሶርስ ዘርፍ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥንካሬን አስመልከቶ የሁለት ተቋማት ተሞክሮ ግምገማ አካሂዷል።

ተሞክሮውን ያቀረቡት የመሬትን ልማት አስተዳደር ቢሮ እና የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ኤጄንሲ ባለሙያዎች ተሞክሮቻቸውን አቅርበዋል።

በቀረበው ተሞክሮም የቢሮው አገልግሎት አሰጣጥ እና አውትሶርስ ዘርፍ ክትትልና ድጋፍ ቡድን መሪዎች የማጠናከሪያ ሃሳብና ድጋፍ አስተያየት ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የቢሮ አገልግሎት አሰጣጥ እና አውትሶርስ ዘርፍ ሃላፌ አቶ በቀለ ተመስገን በቀረበው ተሞክሮ ያለውን ጥንካሬና ድክመት አንስተው የነዚህ ሁለት ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ ተሞክሮ በከተማው ውስጥ ባሉ ተቋማት ተጠናክሮ የሚሰጥበትን መንገድ አቅጣጫ አስቀምጠው የሁለቱ ተቋማት ተሞክሮ የሚበረታታ መሆኑን አመስግነዋል።

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-።Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

ቢሮው የመንግስት ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ስራ ለማከናወን ከተቋማት ከተውጣጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሮች ጋር ተወያየ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥ...
27/01/2025

ቢሮው የመንግስት ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ስራ ለማከናወን ከተቋማት ከተውጣጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሮች ጋር ተወያየ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 19 2017ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የሰው ሀብት ስራ አመራር ዘርፍ የመንግስት ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ስራ ለማከናወን እና የተቀናጀ የመረጃ አያያዝ ስርዓት ኢስሚስ አተገባበር ላይ ከተቋማት ከተውጣጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሮች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡

በመድረኩ መክፈቻ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት በቢሮ የሰው ሀብት ስራ አመራር ዘርፍ ኃላፊ አቶ መላኩ ታምሩ እንደተናገሩት በከተማ አስተዳደሩ ከ90 ሺ በላይ የሚሆነው የመንግስት ሰራተኛ የመጀመሪያ ዲግሪና ከዛ በላይ የትምህርት ማስረጃ ያለው መሆኑን ገልፀው በየጊዜው የሚታየው የሀሰተኛ ትምህርት ማስረጃ መበራከትን ለማስቀረት ከተቋማት ጋር በመቀናጀት ከአመራር እስከ ሰራተኛ ድረስ በመውረድ የትምህርት ማስረጃ ማጣራት ስራው በአፋጣኝ እንደሚጀመር ተናግረዋል፡፡

በሌላ በኩል የሰው ሀብት ክትትል ድጋፍና ኦዲት ዳሬክቶሬት ዳሬክተር አቶ መላኩ ተመስገን እንደተናገሩት የከተማዋን ተቋማት ሁለንተኛዊ አቅም ለማሳደግ ብሎም የከተማ አስረዳደሩን ተልዕኮ፣ ተግባር እና ሀላፊነት በብቃት ከመፈፀም አንፃር እና በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያሉ እንግልቶችን በመሰረታዊነት ለመቅረፍ በተቋማት የሚገኙ የስራ ሂደቶች በትክክለኛው የተማረ የሰው ሀይል መያዛቸውን ለማረጋገጥ የትምህርት ማስረጃ ትክክለኛነት የማረጋገጥ ስራው በልዩ ትኩረት እንደሚከናወን ገልፀዋል፡፡

ማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100067771711638

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

በቢሮው ዘወትር ሰኞ ማለዳ የሚካሄደው አብሮነት ለለውጥ መርሀግብር የሶስተኛ ምዕራፍ የስድስተኛ ዙር መርሀግብር ተካሄደ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 19 ቀን 20...
27/01/2025

በቢሮው ዘወትር ሰኞ ማለዳ የሚካሄደው አብሮነት ለለውጥ መርሀግብር የሶስተኛ ምዕራፍ የስድስተኛ ዙር መርሀግብር ተካሄደ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 19 ቀን 2017ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ዘወትር ሰኞ ማለዳ የሚያካሄደው አብሮነት ለለውጥ መርሀግብር የሶስተኛ ምዕራፍ የስድስተኛ ዙር ፕሮግራሙን የቢሮው አመራርና ሰራተኞች በተገኙበት አካሂዷል፡፡

በእለቱም የእውቀት ሽግግር እና የህይወት ልምዳቸውን ያካፈሉት በቢሮው የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አየለች ዘለቀ "ስኬታማነት" በሚል ሀሳብላይ የእውቀት ሽግግራቸውን ያካፈሉ ሲሆን ስኬታማነት ሰዎች እንደሚያስቀምጡት ግብ እንደሚለያይ ገልፀው ስኬት የተፈለገውን ግብ ለማሳካት በሚደረግ ጥረት የሚገኝ ውጤት መሆኑን አስገንዝበዋል።

ስኬታማነት የመመዘኛ ቁልፎች እንዳሉት የገለፁት ዳይሬክተሯ አውንታዊ ግለ እውቀት ማዳበር፣ ዝግጁነት በመሆን ግብ ማስቀመጥ እና ጠንዳራ የስራ ባህል ማዳበር ቁልፍ የስኬታማነት መነሻዎች መሆናቸውን አስገንዝበዋል፡፡

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው የ4ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ አጀንዳዎች  ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል ።በዚሁም መሰረት ካቢኔው የሃገራችንን ዲፕሎማሲ ታሳ...
27/01/2025

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው የ4ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል ።

በዚሁም መሰረት ካቢኔው የሃገራችንን ዲፕሎማሲ ታሳቢ ያደረገ የኤምባሲዎች የመሬት ጥያቄን እና የከተማዋን የኢኮኖሚ እንቅቃሴ ለሚያጎለብቱ፣ ሰፊ የስራ እድል እየፈጠሩ ላሉ፣ የዉጪ ምንዛሬ እያስገኙ ላሉ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረቻ ማስፋፊያ ቦታ ጥያቄዎችን መርምሮ ውሳኔ አሳልፏል።

ቢሮው በተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓት (ኢስሚስ) ላይ ከጤናጣቢያዎችና ኮሌጆች ለተውጣጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች የአራተኛ ዙር ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡...
26/01/2025

ቢሮው በተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓት (ኢስሚስ) ላይ ከጤናጣቢያዎችና ኮሌጆች ለተውጣጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች የአራተኛ ዙር ስልጠና መስጠት ጀመረ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 18 ቀን 2017ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ከጤናጣቢያዎችና ኮሌጆች ለተውጣጡ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች በተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ሥርዓት ላይ በመንግስት ተቋማት በሥራ ላይ ያለውን የሰው ሀብት መረጃ አያያዝ ሥርዓት በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በማድረግ የአሰራር ሥርዓቱን ማዘመን ብሎም የመረጃ አያያዝና የአጠቃቀም ሂደቱን ተደራሽ ለማድረግ የሚያግዝ ስልጠና እሰጠ ይገኛል፡፡

በስልጠናው ላይ የሲስተሙን አተገባበርና ፋይዳ ላይ ማብራሪያ የሰጡት በቢሮው የሰው ሀብት ስራ አመራር ዘርፍ የሰው ሀብት ስምሪትና መረጃ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ለገሰ እንደተናገሩት የሲስተሙ ዓላማ የመንግስት ሰራተኛው መረጃ በከተማ አስታዳደሩ ደረጃ በተማከለ ሁኔታ ለማደራጀት እና የሰው ሀብት መረጃ ልውውጡን በኦን ላይን በማድረግ የወረቀት ስራዎችን ለማስቀረት እንዲቻል ለማድረግ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም የሲስተሙ መተግበር የሚሰጠው ፋይዳ የመንግስት ተቋማት በቴክኖሎጂ ታግዘው አገልግሎት መሰጠት እንዲችሉ በማድረግ ህግና መመሪያን የተከተለ የሰው ሀብት ስምሪት እንዲኖር እንደሚያስችል ገልጸው የሰው ሀብት መረጃ ሪፖርቶችን ከአንድ መረጃ ቋት በማግኘት ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል እንደሚያሰችል ገልፀዋል፡፡

የሲስተሙ ይዘት በመረጃ አያያዝ ስርዓት የተካተቱ አምስት ዋና ዋና ሞጅሎች ያሉት ሲሆን እነዚህም የሰው ሀብት አስተዳደር ሞጅል፣ የመዋቅርና የስራ መደብ ሞጅል፣ የኢንስፔክሽን ሞጅል፣ የሪከርድና ማህደር ሞጅል እና የአስተዳደር ፍርድ ቤት ሞጅሎች ላይ ትኩረት በማድረግ ስልጠናው እየተሰጠ ይገኛል፡፡

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

ኤጀንሲው የ2017ዓ.ም የሰራተኛ ደንብ ልብስ ማልበስ እንዲሁም 2ኛውን የሰራተኛ እውቅና እና ሽልማት ስነ-ስርዓት በአድዋ መታሰቢያ ሙዝየም አከናወነ ።።።።።።ጥር 18/2017በዕለቱ በክብር ...
26/01/2025

ኤጀንሲው የ2017ዓ.ም የሰራተኛ ደንብ ልብስ ማልበስ እንዲሁም 2ኛውን የሰራተኛ እውቅና እና ሽልማት ስነ-ስርዓት በአድዋ መታሰቢያ ሙዝየም አከናወነ
።።።።።።
ጥር 18/2017

በዕለቱ በክብር እንግድነት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ-አስኪያጅ ክቡር እንጂነር ወንድሙ ሴታ፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ ክቡር ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የማዘጋጃቤታዊ እና የመሰረተ ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር ዶ/ር ግዛቸው አይካ ተገኝተዋል።

በስነ-ስርዓቱ ላይ ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ ሰራተኞችን የአጄንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ ቃለ-መሃላ ያስፈፀሙ ሲሆን በነዋሪው የተመሰከረላቸው፣ ታታሪ እና ልዩ አስተዋፅዖ ያደረጉ 49 ከዋና መስርያ ቤት እስከ ወረዳ ያሉ ሰራተኞችም እውቅና እና ሽልማት ከዕለቱ የክብር እንግዶች ተቀብለዋል።

ተቋሙ በ2016ዓ.ም ለህዝብ ባስተዋወቀው የተቋም ደንብ ልብስ ላይ ያደረገውን ማሻሻያም ዛሬ ያስተዋወቅ ሲሆን በማጠቃለያ ላይ የዕለቱ የክብር እንግዳ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ-አስኪያጅ ክቡር እንጂነር ወንድሙ ሴታ የስራ-መመርያ ሰጥተዋል።

ጠንካራ ተቋም የሚመዘነው በሚሰጠው የአገልግሎት ጥራት ላይ ተመስርቶ በመሆኑ አመራሩ ተግባራት በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ እንዲሰጡ የማድረግ ሀላፊነቱ የጎላ ነው:- ክቡር ዶ/ር ጀማሉ ጀንበር።።...
25/01/2025

ጠንካራ ተቋም የሚመዘነው በሚሰጠው የአገልግሎት ጥራት ላይ ተመስርቶ በመሆኑ አመራሩ ተግባራት በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ እንዲሰጡ የማድረግ ሀላፊነቱ የጎላ ነው:- ክቡር ዶ/ር ጀማሉ ጀንበር
።።።።።።።።።።።
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 17 ቀን 2017ዓም

የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ከክ/ከተማና ወረዳ ከተውጣጡ አመራሮች እንዲሁም አስተባባሪዎች ጋር የአፈፃፀም ግምገማና ውይይት አካሂዷል።

የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ ክቡር ዶ/ር ጀማሉ ጀንበር እንደተናገሩት ቢሮ በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ ተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ተግባራት እዲሁም ተቋማት በተሰጣቸው ተግባር እና ሀላፊነት መሰረት ተግባራትን ስለማከናወናቸው የሚከታተል እንደመሆኑ መጠን የክትትልና የግምገማ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

የመጀመሪያ ስድስት ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ሶስት ክ/ከተሞች ያቀረቡ ሲሆን የተጠቃለለ የመጀመሪያ ስድስት ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በቢሮ የእቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታደሰ ደፋር የተገልጋይና የሰራተኛ እርካታ ከማሳደግ አንፃር፣ ብቁ የሰው ሀይል መገንባት፣ የስልጠና ጥራትና ተደራሽነት፣ አደረጃጀትና አሰራር ማሻሻል፣ በስታንዳርድ መሰርት የሚሰጡ አገልግሎቶች አንፃር፣ የስታንዳርዳይዜሽን እና ምቹ የስራ ሁኔታን ከመፍጠር አንፃር የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ጠምረው አቅርበዋል።

በቀረበው ሪፖርተር ላይ ከክ/ከተማና ወረዳ የተውጣጡ አመራሮችና አስተባባሪዎች በጋራ ወይይት ተደርጓል።

በመድረኩ ለተነሱ ሀሳብና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ ክቡር ዶ/ር ጀማሉ ጀንበር እንደተናገሩት ጠንካራ ተቋም የሚመዘነው በሚሰጠው የአገልግሎት ጥራት ላይ ተመስርቶ በመሆኑ አመራሩ ተግባራት በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ እንዲሰጡ የማድረግ ሀላፊነቱ የጎላ ነው ያሉ ሲሆን ስራዎችን እየገመገሙ መሄድ ወጥነት ያለው የአሰራር ስርአት ለመዘርጋት እንደሚያስችል ገልፀዋል።

በተጨማሪም በሮብና አርብ የተገልጋይ ቀን ከሌላው ቀናት በትኩረት አመራርና ሰራተኛው ማህበረሰብን ማገልገል እንደሚገባው ገልፀው ሪፎርም የተደረጉ ተቋማት ያሉበትን ደረጃ በየጊዜው መከታተልና መገምገም ይገባል ብለዋል።

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

"ግብረ ሀይሉ ህገወጥነትን ለመከላከል፣ ገበያውን  ለማረጋጋትና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ሊሰራ ይገባል"አቶ ጃንጥራር አባይ የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ  እና የግብረ ...
25/01/2025

"ግብረ ሀይሉ ህገወጥነትን ለመከላከል፣ ገበያውን ለማረጋጋትና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ሊሰራ ይገባል"

አቶ ጃንጥራር አባይ የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ እና የግብረ ሀይሉ ሰብሳቢ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገበያ ማረጋጋት፣ ገቢ መሰብሰብ፣ ህገወጥ ንግድ ቁጥጥር የኢትዮጵያ አዲስ አበባ ታምርት ግብረ ሀይል የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ላይ ውይይት አድርጓል።

ውይይቱን የመሩት የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ እና የግብረ ሀይሉ ሰብሳቢ አቶ ጃንጥራር አባይ እንደተናገሩት በከተማዋ የምርት አቅርቦትን በሚፈለገው ልክና አግባብ ከፍ ከማድረግ፤ ህግና ስርዓትን የተከተለ ጤናማ የግብይት ስርዓትን ከማስፈን አንዲሁም ወቅታዊ የግብይት ስርዓት መሠረት ያደረገ የመረጃ ተደራሽነት ከማስፋት አኳያ ተጨባጭ ዉጤታማ ስራዎች መሠራቱን ጠቅሰዉ ለዉጤቱ መሳካት ከማዕከል አሰከ ወረዳ እንዲሁም ከአጎራባቾቻችን ከተሞች ጋር በየደረጃዉ ያለዉ አመራር ተቀናጅቶ በሙሉ አቅሙ መስራት በመቻሉ ነዉ ብለዋል።

ባለፉት ስድስት ወራት የምርት እጥረትና የዋጋ ንረት እንዳይፈጠር፣ የኩፖን ስርጭት በመጀመር፣ በኮሪደር ልማት የተነሱ የሸማች ሱቆችን ምትክ በመስጠት፣ ህገወጥነትን በመቆጣጠርና በመከላከል፣ የሚዲያ ሽፋን በመስጠት፣ የገቢ አሰባሰብ ስራን በማጠናከር፣ የቅዳሜና እሁድ ገበያ በማስፋት እንዲሁም ግብረ ሀይሉ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡን በቀረበው ሪፖርት ላይ ተመላክቷል።

የግብረ ሀይሉ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የተሰሩ ስራዎች በህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ላይ እሴት የሚጨምሩ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ወራቶች የተሻለ ስራ ለመስራት የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የመሰረተ ልማትና ተያያዥ ጥያቄዎችን በመመለስ፣ በኮሪደር ልማት ለፈረሰባቸው ሸማች ማህበራት ምትክ ቦታ በመስጠት እና ምርት ለመከዘን የሚያስችል ቦታ ማዘጋጀት በአንድ ተቋም የሚፈጸም ባለመሆኑ ትኩረት በመስጠት በቅንጅት ተናበው እንዲሰሩ ጠይቀዋል።

በመጨረሻም የእቅድ ክለሳን በማድረግ፣ የምርት አቅርቦትንና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የሸማች ማህበራት በማጠናከር፣ የቁጥጥርና ህግን የማስከበር ስራ ማጠናከር፣ የገቢ አሰባሰብ ችግርን መፍታት እንዱሁም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ችግር መፍታት በቀጣይ ትኩረት የሚሰጣቸው ተግባራት በመሆናቸው ግብረ ሀይሉ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ የተከበሩ አቶ ጃንጥራር አባይ አሳስበዋል።

በዛሬው እለት በደቡብ ምዕራብ ክልል ዳውሮ ዞን የተገነባውን የኢቲ ማዕድን ልማት አ.ማ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካን መርቀን ስራ አስጀምረናል። ፋብሪካው በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የድን...
24/01/2025

በዛሬው እለት በደቡብ ምዕራብ ክልል ዳውሮ ዞን የተገነባውን የኢቲ ማዕድን ልማት አ.ማ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካን መርቀን ስራ አስጀምረናል። ፋብሪካው በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የድንጋይ ከሰል ምርት ከማሻሻል ባሻገር ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ እድል የፈጠረ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

ዛሬ በመንግስት እና ግል አጋርነት መርሀ ግብር ከአያት አክሲዮን ማህበር ጋር በመተባበር የ13,752 ቤቶች ግንባታን አስጀምረናል::በካዛንቺስ አካባቢ ከኦቪድ ግሩፕ ጋር ካስጀመርነው ጋር ከ1...
23/01/2025

ዛሬ በመንግስት እና ግል አጋርነት መርሀ ግብር ከአያት አክሲዮን ማህበር ጋር በመተባበር የ13,752 ቤቶች ግንባታን አስጀምረናል::

በካዛንቺስ አካባቢ ከኦቪድ ግሩፕ ጋር ካስጀመርነው ጋር ከ15 ሺሕ በላይ ቤቶችን የምናለማ ሲሆን ቅድሚያ የማልማት መብታቸውን በመጠቀም የሚገነቡ የግል አልሚዎችን ጨምሮ በጠቅላላው 20 ሺሕ ቤቶችን የሚገነቡ ይሆናል::

በከተማችን ያረጁ እና ለመኖር ምቹ ያልሆኑ እንደ ካዛንቺስ ያሉ አካባቢዎችን መልሰን ስናለማ በዋነኛነት የህዝቡን ዋንኛ አንገብጋቢ ጥያቄ የሆነውን የመኖሪያ ቤትን ለመመለስ ሲሆን የመኖሪያ ቤቶችን ስንሰራ ቤት ብቻ ሳይሆን ለኑሮ ምቹ የሆነ አካባቢዎችን እንገነባለን::
ካሳንችስ ከመልሶ ማልት በፊት ነባር 8000 መኖሪያና ንግድ ቤቶች በጥቅሉ ወደ 21ሺ ነዋሪዎችን የሚገለገሉበት አካባቢ የነበረ ሲሆን በመልሶ ማልማት ስራችን ሁለት ሺሕ የንግድ ሱቆች እና ሀያ ሺሕ መኖሪያ ቤቶችን በመገንባት ከ100 ሺሕ በላይ ነዋሪዎች የሚገለገሉበት አካባቢ ይሆናል።

ካዛንቺስ ላይ የምንገነባው ይህ የካዛንቺስ አያት መንደር በውስጡ ማህበራዊ ግልጋሎትን የሚሰጡ ተቋማት ጨምሮ የመማሪያ ቦታዎች፣ የጤና ተቋማት፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች፣ አረንጏዴ ቦታዎች፣ ሞሎች፣ ሱቆች እንዲሁም ሰፋፊ የመኪና ማቆሚያዎችን ያካተተ ግዙፍ ፕሮጀክት ሲሆን ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር ነው::

በሚቀጥሉት 18 ወራት ጊዜ ውስጥ የ15 ሺህ ቤቶች ግንባታን ለማጠናቀቅ ያቀድን ሲሆን ሁላችንም ለፕሮጀክቱ ስኬት በጋራ እንድንሰራ አደራ እያልኩ ንጹህ፣ ፅዱ፣ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ተወዳዳሪ የሆነች አለም አቀፍ ከተማ መገንባታችንን አሁንም አጠናክረን ቀጥለናል::

ያስጀመረን ፈጣሪ በድል እንድናጠናቅቅ ይርዳን!

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የቅንጅት ስራዎችን በውጤት መምራት የአገልግሎት አሰጣጡን ከማሻሻል ባሻገር የህዝብ እርካታን በመፍጠር በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለውን መተማመን ለማጠናከር ያስችላል፦ ክቡር ዶ/ር ጀማሉ...
23/01/2025

የቅንጅት ስራዎችን በውጤት መምራት የአገልግሎት አሰጣጡን ከማሻሻል ባሻገር የህዝብ እርካታን በመፍጠር በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለውን መተማመን ለማጠናከር ያስችላል፦ ክቡር ዶ/ር ጀማሉ ጀንበር
።።።።።።።።
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 15 ቀን 2017ዓሞ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት በመጀመሪያ ስድስት ወራት ከአጋር ተቋማት ጋር በትብብር ባከናወናቸው ቅንጅታዊ ስራዎች በዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ዙሪያ ከተቋማቱ ሃለፊዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር ግምገማ በማድረግ የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገብ ተቋማት የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክቷል።

በእለቱ በቀረበው ሪፖርት ቢሮው በ2016 በጀት ዓመት በዕቅድ በያዛቸው ተግባራት ውጤታማነት ላይ በስፋት መሰራቱ የተገለፀ ሲሆን በዝግጅት ምዕራፍ ሊከናወኑ በታቀዱ ስራዎች ላይ እና ዋና ዋና ግቦች ማለትም የረጅም ጊዜ የት/ት ስልጠናዎች ከተቋማት ተልኮ ጋር በማመጣጠን መስጠት፣ክፍተትን መሰረት ያደረገ የአጭር ጊዜ ስልጠና መስጠት፣ ስማርት ወረዳዎች በመፍጠር የአገልግሎት አሰጣጡን ውጤታማ ማድረግ፣ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል የሚያግዙ የተለያዩ የሚዲያ ስራዎች፣ የብቃት ምዘና በማረጋገጥ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፣ የከተማ አስተዳደሩ የፐብሊክ ትራንስፖርት ተደራሽነት ማረጋገጥ፣ የቁጠባና የብድር አገልግሎት ተግባራት እቅድና አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ ክቡር ዶ/ር ጀማሉ ጀንበር እንደተናገሩት የቅንጅት ስራዎችን በውጤት መምራት የአገልግሎት አሰጣጡን ከማሻሻል ባሻገር የህዝብ እርካታ በመፍጠር በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለውን መተማመን ለማጠናከር እንደሚያስችል
ገልፀዋል።

የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት መረጋገጥ ትኩረት የሚሰጠው ዋና ተግባር በመሆኑ ስራዎችን በቅርበት በመከታተልና በመገምገም ማስኬድ እንደሚገባ የገለፁት ሀላፊው በቀጣይ አዳዲስ ሀሳቦችንና ተሞክሮዎችን በመውሰድ ለጋራ ዓላማችን በባለቤትነት መንፈስ መስራት ከሁላችንም ይጠበቃል ብለዋል።

በመጨረሻም በስድስት ወራት የቅንጅት ስራዎች በእቅድ አፈፃፀማቸው የላቀ ተሳትፎ ላስመዘገብ ተቋማት የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር የሚታዩ ችግሮችን በመሰረታዊነት ለመፍታት የተጀመሩ የሪፎርም ትግበራና የዝግጅት ሥራዎች አበረታች ናቸው:-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ።።።።።...
23/01/2025

በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር የሚታዩ ችግሮችን በመሰረታዊነት ለመፍታት የተጀመሩ የሪፎርም ትግበራና የዝግጅት ሥራዎች አበረታች ናቸው:-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
።።።።።።።።።
ጥር 15/2017 ዓ.ም

በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር የሚታዩ ችግሮችን በመሰረታዊነት ለመፍታት የተጀመሩ የሪፎርም ትግበራና የዝግጅት ሥራዎች አበረታች ናቸው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡

አቶ ተመስገን ጥሩነህ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት ዛሬ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም አመራር ዐቢይ ኮሚቴ ሦስተኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂደናል ብለዋል።

በውይይታችን በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንና በመጀመሪያ ዙር የተመረጡ ተቋማት ያከናወኗቸውን የሪፎርም ሥራዎች ገምግመናል ሲሉ ገልጸዋል።

የሪፎርም አስተዳደራዊ ሥራዎች፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሥርዓትን መዘርጋት፣ የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ በመገንባት አገልግሎቶችንና ውሳኔዎችን ማቀላጠፍ ላይ ጥሩ ጅምሮች መኖራቸውንም ተመልክተናል ብለዋል።

በሪፎርሙ የታቀፉ ተቋማትም ያላቸውን ልምዶች የሚቀያየሩበት እና ተቀራርበው የሚሰሩበትን አውድ መፍጠር ተችሏል ሲሉ ጠቅሰዋል፡፡

ተቋማት ያከናወኗቸውን ተግባራት በዝርዝር በመቃኘት ጥንካሬዎችንን ውስንነቶችን የለየን ሲሆን በቀጣይ ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገባቸው ጉዳዮች ላይም አቅጣጫ አስቀምጠናል ሲሉም አመልክተዋል::

ቢሮው በስልሳ ቀናት እቅድ አፈፃፀም በዋና ዋና ተግባራት የተከናወኑ ስራዎችን ያሉበትን ደረጃ ከቢሮው አመራሮችና ጀነራል ካውንስል አባላት ጋር ገመገመ።።።።።።።።።።።።ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ...
22/01/2025

ቢሮው በስልሳ ቀናት እቅድ አፈፃፀም በዋና ዋና ተግባራት የተከናወኑ ስራዎችን ያሉበትን ደረጃ ከቢሮው አመራሮችና ጀነራል ካውንስል አባላት ጋር ገመገመ
።።።።።።።።።።።።
ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ፤ ጥር 14 ቀን 2017ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ በግማሽ በጀት ዓመቱ በስልሳ ቀናት በየዳይሬክቶሬቶች ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ያለበት ደረጃ በቴክኖሎጂ አተገባበር የኢስሚስ ፣ስማርት ኦፊስ፣ የቅሬታና አቤቱታ፣ የንብረት ምዝገባ ሲስተሞች፣ የትምህርት ማስረጃ ማጣራት ተግባራት፣ የሰራተኞች ምጥጥን፣ ምቹ የስራ ሁኔታ ከመፍጠር አንፃር፣ የተቋማት ክትትልና ድጋፍ አንፃር፣ የተቋማት/ወረዳ አቅም ግንባታ ተግባራት አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ በሪፖርት ገምግሟል።

የየስራ ክፍል ዳይሬክተሮችና የዘርፍ ሀላፊዎች ባቀረቡት ሪፖርት ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም አንፃር የኢስሚስ ትግበራ እና የስማርት ኦፊስ ሲስተም ትግበራዎች፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ ዝግጅት፣ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንፃር በተቋማት ክ/ከተማና ወረዳዎች የተከናወኑ ተግባራት እና የተገልጋይና የሰራተኛ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር አንፃር የተከናወኑ ተግባራት እና መሰል ስራዎች አፈፃፀም አቅርበዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ ክቡር ዶ/ር ጀማሉ ጀንበር እንደተናገሩት አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ ከማስደገፍ እና የተጀመሩ ሲስተሞችን ከመተግበረ አንፃር አርአያ መሆን የሚያስችል ስራን ለመስራት መረባረብ ይገባል ያሉ ሲሆን ተግባራትን በተያዘው የጊዜ ገደብ በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ሁሉም የሚጠበቅበትን ሀላፊነት በትኩረት መወጣት ይገባል ብለዋል።

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/aac_pshrdb

👍👍👍 ኢንስታግራም :- https://www.instagram.com/p/DDeo-reok-Y/?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

👍👍👍ቲክቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZMhu7WUet/

??👍👍 ዌብ ሳይት ፦ http://www.pshrdb.gov.et/

Address

Addis Abeba, 5killo
Addis Ababa
12134568

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share