Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency The Ethiopian News Agency (ENA) is the sole national wire service of Ethiopia.
(305)

The 82 years old ENA, engaged in the gathering and dissemination text news, audio and video stories about local and international events to media enterprises and the public. The Ethiopian News Agency (ENA) is the sole national wire service of Ethiopia.

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከ1934 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 82 ዓመታት በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ውስጥ የዜና አገልግሎት ተግባር በማከናወን ላይ የሚገኝ ብቸኛው ተቋም ነው፡፡

ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመስኖ ልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ- ምክትል ርዕሰ መስተዳድር  ጌታሁን አብዲሳአዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረ...
15/01/2025

ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመስኖ ልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ- ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመስኖ ልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ ገለጹ።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳና የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶይስሃቅ አብዱልቃድር በመተከል ዞን ፓዊ ወረዳ የመስኖ ልማት ስራዎችን ጎብኝቷል።

አቶ ጌታሁን በመተከል ዞን ፓዊ ወረዳ በመስኖ እየለሙ የሚገኙ የልማት ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸው የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሰብሎችን በክላስተር የማልማት ስራም ይበልጥ ሊጠናከር እንደሚገባም ገልጸዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይስሃቅ አብዱልቃድር፤ እንደ ሀገር የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ የተጀመረውን የኢኮኖሚ አቅም ለመገንባት የመስኖ ልማት ስራዎችን ላይ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

የፓዊ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ይርጋ አሰፋ በወረዳው የተገኘውን ሰላም በመጠቀም የተለያዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ አበረታች የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

15/01/2025

ኢዜአ - በዲጂታል አማራጭ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም!

ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት መፍጠር የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ - ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ለአየር ...
15/01/2025

ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት መፍጠር የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ - ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት መፍጠር የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።

በኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብና ሥርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ላይ ትኩረቱን ያደረገ አውደ ጥናት በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።

በመርህ ግብሩ ላይ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ የተለያዩ ተቋማት አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ የኢትዮጵያን የምግብ ሥርዓት ትራንስፎርሜሽን ለአየር ንብረት የማይበገር ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

የምግብና ስርዓተ-ምግብ ሽግግር ለማረጋገጥ ብሎም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥራዓት ለመፍጠር የሚከናወኑ ቅንጅታዊ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል፡፡

በማምረት፣ በማከማቸት፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር እና ደህንነቱ የተጠበቀ ምግብ ለተጠቃሚው ለማድረስ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በዚህም የኢትዮጵያ ሥርዓት ምግብ አካታች በሆነ መልኩ ምርትና ምርታማነት ለመጨመር፣ የክምችት አቅም ማሳደግ፣ የምግብና ሥርዓት ምግብን በማጣመር በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት ለማሳደግ፣ በቤተሰብ ደረጃ የስርዓተ-ምግብ ሁኔታን ለማሻሻል፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የተመጣጠነ የአመጋገብ ስርዓት ለማጠናከር የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል፡፡

የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው የሕብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ እና የተመጣጠነ ምግብን ተደራሽ ለማድረግ በማሰብ የሰቆጣ ዲክላሬሽንን በመተግበር የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በህጻናት ላይ ሊከሰት የሚችለውን መቀንጨር ለመከላከል የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የፓሪስ ስምምነት ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

የአውደ ጥናት መድረኩ እስከ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ ታውቋል።


የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዘወትር ተግባር ሊሆን ይገባል- ከንቲባ ከድር ጁሃርድሬዳዋ፣ ጥር 07/2017(ኢዜአ)፦ የአቅመ ደካማ ህብረተሰብ ክፍሎችን ማህበራዊ ችግሮች ለማቃለል የሚከናወኑ የበጎ...
15/01/2025

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዘወትር ተግባር ሊሆን ይገባል- ከንቲባ ከድር ጁሃር

ድሬዳዋ፣ ጥር 07/2017(ኢዜአ)፦ የአቅመ ደካማ ህብረተሰብ ክፍሎችን ማህበራዊ ችግሮች ለማቃለል የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የዘወትር ተግባራት ሊሆኑ እንደሚገባ የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።

በአስተዳደሩ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ሲሳተፉ ለቆዩ በጎ ፍቃደኞች የዕውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንዳሉት፤ በዘንድሮ ዓመት የአስተዳደሩን ነዋሪዎች ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት በተከናወኑ የበጎ ፈቃድ ስራዎች አበረታች ውጤቶች ተገኝተዋል።

በ14 ዘርፎች አይነተ ብዙ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መከናወናቸውን ከንቲባው ጠቁመዋል።

ለአብነትም 238 አዳዲስ ቤቶች ሲገነቡ፣ ከ70 በላይ ቤቶች ደግሞ ታድሰው የአቅመ ደካማ ህብረተሰብ ክፍሎችን ማህበራዊ ችግሮች እንደፈቱ ተናግረዋል።

በመሆኑም የበርካቶችን ማህበራዊ ችግሮች ለማቃለል የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የዘወትር ተግባራት ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል።

አስተዳደሩም ለችግር የተጋለጡትን ነዋሪዎችን ሕይወት የማሻሻል የጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።

የድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ካሊድ መሐመድ በበኩላቸው፣ የበጎ ፈቃድ ስራ ስራዎች የድሬዳዋን የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ እያጠናከረ መሆኑን ገልጸዋል።

ባለፈው የክረምት ወቅት 120 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመትና ከ296 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደረገ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት መከናወኑን ጠቅሰዋል።

በዕለቱ ዕውቅና ያገኙ ተቋማትና ግለሰቦችን አመስግነው፤ በቀጣይም የጀመሩትን የበጎ ፈቃድ ተግባራት እንደሚቀጥሉ ጠይቀዋል።



በጎንደር ከተማ እየተካሄዱ ያሉት የፋሲለደስ እድሳት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች እድገት እጅግ አበረታች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡-...
15/01/2025

በጎንደር ከተማ እየተካሄዱ ያሉት የፋሲለደስ እድሳት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች እድገት እጅግ አበረታች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ እየተካሄዱ ያሉት የፋሲለደስ እድሳት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች እድገት እጅግ አበረታች ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በጎንደር ከተማ እየተካሄዱ ያሉት የፋሲለደስ እድሳት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች እድገት እጅግ አበረታች ነው። በሥራው ለተሳተፉ ሁሉ በተለይም በክብር ለተሞሉት እንግዳ ተቀባይ የጎንደር ነዋሪዎች በሙሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል።


15/01/2025

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የነዳጅ አቅርቦትና ስትራቴጂክ ሸቀጦች ላይ የመንግስትን ድጎማ በማስመልከት የሰጡት ማብራሪያ

የአማራ ክልል የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በጎንደር ከተማ መካሄድ ጀመረ አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- 16ኛው የአማራ ክልል የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በጎንደር ከተማ መካሄድ...
15/01/2025

የአማራ ክልል የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በጎንደር ከተማ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- 16ኛው የአማራ ክልል የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በጎንደር ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

"ድንቅ ምድር፥ ድንቅ ባህል" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው የባህል ፌስቲቫሉ ከዛሬ ጥር 7 እስከ 9/2017 ዓ.ም ይቆያል።

በፌስቲቫሉ ላይ በክልሉ የተለያዩ የዞንና የወረዳ የባህልና የኪነ-ጥበብ ቡድን አባላት ባህላዊ እና ኪነ-ጥበባዊ ትዕይንታቸውን በጎንደር ከተማ መስቀል አደባባይ እያቀረቡ ይገኛል።

በባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል ማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ዘርፍ አስተባባሪ እና የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው፣ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ጸጋዬ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።


የተፋሰስ ልማት ውጤታማነት ማሳያ - ሐረማያ ሃይቅ ላለፉት 17 ዓመታት ደርቆ የነበረው የሐረማያ ሃይቅ በተሰራ የተፋሰስ ልማትና በተደረገለት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች ወደነበረበት እንዲመ...
15/01/2025

የተፋሰስ ልማት ውጤታማነት ማሳያ - ሐረማያ ሃይቅ

ላለፉት 17 ዓመታት ደርቆ የነበረው የሐረማያ ሃይቅ በተሰራ የተፋሰስ ልማትና በተደረገለት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች ወደነበረበት እንዲመለስና የውሃው መጠንም ከዓመት ዓመት እንዲጨምር አስችሏል።

በሐረማያና አካባቢው ባሉ ተፋሰሶች ላይ የሚከናወኑ የተፈጥሮ ኃብት ጥበቃ ስራዎች የአርሶ አደሩንና ወጣቱን ተጠቃሚነት ከማጎልበት አንጻር ተጨባጭ ውጤት እያስገኙ መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናግረዋል።

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የሐረማያ ሃይቅ ተፋሰስ ልማት ፕሮጀክት አስተባባሪና የተፈጥሮ ሃብት አጠቃቀም መምህር ዲኔ ረሺድ እንደገለፁት፤ የአየር ንብረት ለውጥ ችግርን ለመቋቋም የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው።

ባለፉት ዓመታት በአካባቢው የተከናወኑት የአፈርና ውሃ እንዲሁም ሌሎች የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በተለይም ላለፉት 17 ዓመታት ደርቆ የነበረው የሐረማያ ሃይቅ በተደረገለት የተፋሰስ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች ወደነበረበት እንዲመለስና የውሃው መጠንም ከዓመት ዓመት እንዲጨምር ማስቻሉን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ በተከናወኑ ስራዎች የአርሶ አደሩንና የወጣቶችን የልማት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እየተቻለ መሆኑንም ገልጸዋል።

በሐረማያ ሐይቅ ወጣቶች ተደራጅተው በዓሳ ማስገር እና በመዝናኛ ስራዎች ላይ ተሰማርተው ገቢ ማግኘት መቻላቸውን ጠቁመው፤ ዩኒቨርሲቲውም ለዚህ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።

የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የከርሰ ምድር ውሃን ከማጎልበት አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የተናገሩት ደግሞ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ተቋም መምህርና የውሃ ሃብት መሃንዲስ በቀለ ግርማ ናቸው።

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ የሚገኘውና በቅርቡ የተመለሰው የሐረማያ ሐይቅ ለዚህ የበቃው የዩኒቨርሲቲውና የአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም አርሶ አደሩ በዙሪያው ላይ በሚገኙ ተፋሰሶች ላይ ባከናወነው የተለያዩ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች መሆኑን አንስተዋል።

በተለይም በአሁኑ ወቅት መስኖን በመጠቀም ለሚከናወኑ ምርትና ምርታማነት የማሳደግ ስራዎች በአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ የሚከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ለአርሶ አደሩ ጠቀሜታን እየሰጡ መሆኑንም አስረድተዋል።

የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎችን በማጠናከር ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ላይ የተጀመሩ ስራዎች መጠናከር እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል።

የ2017 ዓ.ም ሀገራዊ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ንቅናቄ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ትናንት በይፋ ማስጀመራቸው ይታወቃል።


በመዲናዋ የጥምቀት ክብረ በዓል አምስት ሺህ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ ተግባራት ይሰማራሉ- ማኅበሩአዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፦ የጥምቀት ክብረ በዓል በድምቀት እንዲከበር አምስት ሺህ በጎ...
15/01/2025

በመዲናዋ የጥምቀት ክብረ በዓል አምስት ሺህ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ ተግባራት ይሰማራሉ- ማኅበሩ

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፦ የጥምቀት ክብረ በዓል በድምቀት እንዲከበር አምስት ሺህ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን ለማሰማራት ዝግጅት ማጠናቀቁን የአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር አስታወቀ፡፡

በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በአደባባይ ደምቆ የሚከወነው ጥምቀት በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ)) የሰው ልጅ ወካይ የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ ተመዝግቧል።

ከአያሌ አድባራት የሚወጡ ታቦታት በተለያዩ ስፍራዎች በአንድ ስፋራ በሚያድሩበት እና ዕልፍ አዕላፍ ምዕመናን በሚታደሙበት በዚህ በዓል ታዲያ የበጎ ፈቃድ ወጣቶች ሚና አይተኬ ነው።

ታቦታት ባሕረ ጥምቀት አድረው እስኪመለሱ ድረስ በዓሉ ኀይማኖታዊና ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ በድምቀትና በሰላም እንዲከበር ወጣቶች በተለያዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ይሰማራሉ።

በአዲስ አበባ ለሚከበረው የጥምቀት በዓል የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከሚሰጡ የወጣት አደረጃጀቶች መካከል አንዱ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማኅበር ነው።

የማኅበሩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ የተመኝ አስማማው ለኢዜአ እንዳለችው፤ ማህበሩ ጥምቀት ኃይማኖታዊና ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ በድምቀት እንዲከበር በየዓመቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያከናውናል።

በዘንድሮ ክብረ በዓልም በማስተባበር፣ በጽዳትና በሌሎች የበጎ ፈቃድ ተግባራት ለሚሰማሩ ወጣቶቹ ከወዲሁ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል ብላለች።

በዚህም የጥምቀት የአደባባይ በዓል በድምቀትና በሰላም እንዲከበር ከጸጥታና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የበኩሉን ሚና ለመወጣት በቂ ዝግጅት ማጠናቀቁን ነው ያብራራችው።

በመሆኑም ከከተራ ጀምሮ ባሉ ሥነ ስርዓቶች ሁሉ አምስት ሺህ በጎ ፈቃድ ወጣቶችን በየታቦት ማደሪያዎች ይሰማራሉ ነው ያሉት።



በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ266 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏልአዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵ...
15/01/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ266 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በ2017 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከ266 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የክልሉ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ።

83 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውም ተጠቁሟል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አክሊሉ አዳኝ (ኢ/ር) እንዳሉት ቢሮው የህብረተሰቡን የንፁህ መጠጥ ውሃ ጥያቄ ምላሽ መስጠት የሚያችሉ ተግባራትን በማከናወን ላይ ነው።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 4 የከተማ እና 79 የገጠር በድምሩ 83 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ግንባታ በማጠናቀቅ ከ266 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አመልክተዋል።

በሌላ በኩል በግማሽ ዓመቱ ለ13ሺህ 935 ዜጎች በማዕድን ዘርፍ የስራ እድል እንደተፈጠረም ጠቁመዋል።

ከ490 ሺህ በላይ ዜጎች የተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችንና የሶላር ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆናቸውንም ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።


በምንከፍለው ግብር ለህዝብ አገልግሎት የሚውሉ መሠረተ ልማቶች የሚገነቡነበት መሆኑን በመገንዘባችን ግብራችንን በወቅቱ ከፍለናል - ግብር ከፋዮችሠመራ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- በምንከፍለው ...
15/01/2025

በምንከፍለው ግብር ለህዝብ አገልግሎት የሚውሉ መሠረተ ልማቶች የሚገነቡነበት መሆኑን በመገንዘባችን ግብራችንን በወቅቱ ከፍለናል - ግብር ከፋዮች

ሠመራ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- በምንከፍለው ግብር ለህዝብ አገልግሎት የሚውሉ መሠረተ ልማቶች የሚገነቡ መሆናቸውን በመገንዘባችን ግብራችንን በወቅቱ ከፍለናል ሲሉ የአፋር ክልል ግብር ከፋዮች ገለጹ።

በክልሉ የሠመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ግብር ከፋይ አቶ አንዋር መኮንን እንዳሉት እኛ የምንከፍለው ግብር መልሶ ለህዝብ ጥቅም የሚውሉ ልማቶች በጊዜያቸው እንዲጠናቀቁ ያደርጋል።

በዚሁ ግንዛቤ ግብራቸውን በጊዜው በመክፈላቸው የተለያዩ መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉ ከማድረግ ባለፈ ለሀገር እድገት የራሳቸውን ሃላፊነት በወቅቱ እንዲወጡ እንዳስቻላቸውም ተናግረዋል።

ግብር በመክፈላቸው መንገዶች፣ ጤና ተቋማት እና ትምህርት ቤቶች እንዲገነቡ ዕድል የሚሰጥ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ሌላው ግብር ከፋይ አቶ አወል ኢድሪስ ናቸው።

በመሆኑም ሁሉም ሰው የሚጠበቅበትን ግብር በወቅቱ እንዲከፍል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በበኩሉ ባለፉት ስድስት ወራት ከ2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሠብሰቡን ገልጿል።

የቢሮው ሃላፊ አቶ አወል አብዱ ለኢዜአ እንደገለፁት በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት በግማሽ መጀት ዓመቱ 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።

ከዚህም 2 ቢሊዮን 671 ሚሊዮን 393ሺህ አራት ብር መሠብሰቡን ገልጸው፤ በዚህም የዕቅዱን 97 በመቶ ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል።

ይኸም ባለፈው ዓመት ተመሣሣይ ወቅት ከተሰበሰበው ጋር ሲነፃፀር ከ794 ሚሊየን ብር በላይ ብልጫ ያለውና በመቶኛም የ42 በመቶ ብልጫ የታየበት መሆኑን አስረድተዋል።

እንደ ሃላፊው ገለጻ፤ የተሻለ አፈጻጸም ሊኖር የቻለው በወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች ላይ የግንዛቤ ማሣደጊያ ስራዎች በመከናወናቸውና ባለሙያዎችም በቁርጠኝነት በመሥራታቸው ነው።

ይህም ሆኖ ከደረሠኝ አሰጣጥና አቆራረጥ ጋር አሁንም የሚስተዋሉ ችግሮች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ ሃላፊነታቸውን በማይወጡ ግብር ከፋዮች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል።


በአሪ ዞን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷልጂንካ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን ለታላቁ ...
15/01/2025

በአሪ ዞን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል

ጂንካ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከቦንድ ሽያጭ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገቢ ማሰባሰብ ንቅናቄ መርሀ ግብር ዛሬ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ ተጀምሯል።

የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ በንቅናቄ መርሀ ግብሩ ላይ እንደገለፁት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ለማጠናቀቅ በዞኑ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሀብት አሰባሰብ ንቅናቄ ተጀምሯል።

ከጥር 7 ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 2017 ዓ.ም ለአራት ወራት በሚቆየው የቦንድ ሽያጭ ንቅናቄ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

የዞኑ ህዝብም እንደ ወትሮው ቦንድ በመግዛትና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ የሀብት አሰባሰብ ስራው ውጤታማ እንዲሆን እገዛ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

በንቅናቄ መርሀ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የጂንካ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ደሳለኝ ደጀኔ እንደገለፁት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የወደፊት ተስፋ በመሆኑ ለግድቡ የሚታጠፍ እጅ የለንም ብለዋል።

የህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ከተቀመጠበት ጊዜ ጀምሮ ቦንድ በመግዛትና ሌሎች ድጋፎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸው፤ አሁንም ቦንድ በመግዛት ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።

የግድቡ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት እስኪበቃ ድጋፋችን አይቋረጥም ያለው ደግሞ ወጣት ባንታየሁ አለሙ ነው።

ለግድቡ ግንባታ ማጠቃለያ የተጀመረውን የሀብት ማሰባሰብ ስራ በስኬት ለማጠናቀቅ ቦንድ በመግዛት እና ህብረተሰቡን በማስተባበር የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋንጫ በሚያዚያ ወር ወደ አሪ ዞን እንደሚደርስ የተገለፀ ሲሆን ዋንጫውን በመቀበል የሀብት አሰባሰቡ ላይ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት መደረጉም ተመልክቷል።



የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ የዘወትር ተግባር ሆኖ ሊቀጥል ይገባል - አቶ አገኘሁ ተሻገር ጋምቤላ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ በማህበረሰቡ ዘንድ መለመድ ያለበትና...
15/01/2025

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ የዘወትር ተግባር ሆኖ ሊቀጥል ይገባል - አቶ አገኘሁ ተሻገር

ጋምቤላ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ በማህበረሰቡ ዘንድ መለመድ ያለበትና የዘወትር ተግባር ሆኖ ሊቀጥል እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለፁ።

በፍትህ ሚኒስቴርና በተጠሪ ተቋማት አማካኝነት በጋምቤላ ከተማ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተሰሩ አምስት የአቅመ ደካሞች ቤቶች ተጠናቀው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር በተገኙበት ዛሬ ለተጠቃሚዎች ተላልፈዋል።

አፈ ጉባዔው በዚሁ ወቅት እንዳሉት መንግስት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባለፉት የለውጥ አመታት ሰው ተኮር በሆኑ የልማት ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል።

በተለይም በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጧሪና ደጋፊ የሌላቸውን አቅመ ደካማ ወገኖች ኑሮ ለማሻሻል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ውጤት እየታየባቸው ይገኛል ብለዋል።

በመሆኑም በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካማች ቤት ግንባታና እድሳትን ጨምሮ በአረንጓዴ አሻራ፣ በአካባቢ ፅዳት እና በሌሎችም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተጀመሩ ስራዎች የዘወትር ተግባር ሊሆኑ ይገባል ነው ያሉት።

ሰው ተኮር የሆኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎችን በማጠናከር አቅመ ደካማ የሆኑ ዜጎችን የመደገፉ ስራ ባህል ሆኖ ሊቀጥል እንደሚገባም ተናግረዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት ከሚደረጉ ተግባራት አንዱ ነው ብለዋል።

በተለይም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የተሰሩ ተግባራት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረጉ ይገኛሉ ነው ያሉት።

ሁሉም ዜጋ ተባብሮና ተቀናጅቶ ከሰራ የማንሻገረው ችግር አይኖርም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሯ፤ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህላችንን ይበልጥ ልናጠናክር ይገባል ብለዋል።

የፍትህ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ወደ ክልሉ በመምጣት ላደረጉት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ወይዘሮ ዓለሚቱ ምስጋና አቅርበዋል።

የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን(ዶ/ር) እንዳሉት ሚኒስቴሩና ተጠሪ ተቋማቱ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳት፣ የትምህርት ቁሳቁስ እና ሌሎች ድጋፎችን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

በጋምቤላ ከተማ በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከሶስት ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ አምስት የአቅመ ደካማ ቤቶችን ሰርተው ዛሬ ማስረከባቸውንም ተናግረዋል።


ወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ  የአዋጭነት ጥናት ሰነድ ተረከበአዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፦ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የአዋጭነት ጥናት ሠነድን አጠናቆ...
15/01/2025

ወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የአዋጭነት ጥናት ሰነድ ተረከበ

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፦ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የአዋጭነት ጥናት ሠነድን አጠናቆ አስረክቧል።

ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተጠሪ ተቋም የሆነው የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አገልግሎት በጥናትና ማማከር ዘርፍ፤ በአዋጭነት ጥናት፤ በንብረት ትመና እና በተለያዩ የአገልገሎት ዘርፎች ከተለያዩ መንግስት ተቋማት ጋር ላለፉት ዓመታት ሲሰራ የቆየ አንጋፋ ተቋም ነው።

በዚህንም አገልግሎቱ በወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ላይ ያደረገውን የአዋጭነት ጥናት አጠናቆ ዛሬ አስረክቧል።

የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሽፈራው ሰለሞን እና የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አማን የጥናት ሰነዱን ተረካክበዋል።

አቶ ሽፈራው በዚሁ ወቅት እንደገለፁት የአዋጭነት ጥናት ሰነድ ፋብሪካውን በፍጥነት ወደ ተግባር ገብቶ የሃገር ውስጥ የስኳር ተደራሽነት ሽፋን ከማሳደጉ በተጨማሪ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነት ያግዛል።

የወንጅ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አማን በበኩላቸው ወንጅ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ እንደ ሃገር በርካታ ስራዎችን የሚሰራ ፋብሪካ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አሁን የተረከበው የአዋጭነት ጥናት ሰነድን በአጭር ጊዜ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ማረጋገጣቸውን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያገነኘው መረጃ ያመለክታል።

የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋም ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል - ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁንአዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- በተለያዩ አካባቢዎች የመንግሥት...
15/01/2025

የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋም ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል - ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፡- በተለያዩ አካባቢዎች የመንግሥትና የህዝብን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች መደበኛ ህይወታቸውን እንዲመሩ መልሶ የማቋቋም ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን ገለጹ።

ኮሚሽነሩ ይህን ያሉት በአማራ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች የተሀድሶ ስልጠናና መልሶ ማቋቋም ሂደት በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ የሳራባ ማዕከል በተጀመረበት ወቅት ነው።

የሰላም አማራጭ ችግሮችን በሰከነ መንፈስ ለመፍታት ወሳኝ መንገድ መሆኑን ገልጸው፥ ታጣቂዎች የመንግሥትንና የህዝብን የሰላም ጥሪ እየተቀበሉ መሆናቸው ለሀገር ትልቅ ተስፋ ነው ብለዋል።

ወደ ተሃድሶ ማዕከል የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎችም ህዝቡን ለመካስ ዝግጁ መሆናቸውን አሳይተዋል ያሉት ኮሚሽነሩ፥ ይህም በጫካ ለሚገኙ የታጠቁ ቡድኖች ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን አንስተዋል።

ኮሚሽኑ የቀድሞ ታጣቂዎች መደበኛ ህይወታቸውን እንዲመሩ ለማስቻል በትግራይ፣ በአፋር፣ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

የመልሶ ማቋቋምና የድጋፍ ሥራዎችም ተጠናክረው መቀጠላቸውን ነው የጠቆሙት።

የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዴር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያው፤ የቀድሞ ታጣቂዎች አለመግባባትን በንግግር ለመፍታት መወሰናቸው የሰላምን ዋጋ መገንዘባቸውን ያረጋገጠ መሆኑን ገልጸዋል።

ሀገር የመገንባት አካል መሆን ዕድለኝነትና ታሪካዊ ኃላፊነት ነው ያሉት ምክትል ኮሚሽነሩ፥ የቀድሞ ታጣቂዎችም ያገኙትን መልካም እድል በመጠቀም የሰላምና የልማት ሃይል እንዲሆኑ አስንዝበዋል።

የሀገር ሽማግሌዎች ተወካይ አቶ እያዩ ጀምበር፥ አለመግባባት ቢኖር እንኳ በመነጋገር መፍትሔ ማምጣት እንደሚቻል ነው ያነሱት።

በጠብመንጃ ወይም በኃይል የሚፈታ ችግር እንደሌለ በማንሳት፥ በጫካ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች ለሰላም ቅድሚያ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።

ሰላም ካለ ልማት ይኖራል ያሉት አቶ እያዩ፥ ሁሉም አካል ለክልሉ ህዝብ ሰላም ቅድሚያ መስጠት እንዳለበት ተናግረዋል።

ወደ ተሃድሶ የገቡ የቀድሞ ታጣቂዎች ተወካይ ሰለሞን አስማረ፥ ግጭትና የኃይል አካሄድ ማንንም እንደማይጠቅም በመገንዘብ የሰላም ጥሪውን መቀበላቸውን ገልጿል።

የተሃድሶ ስልጠናውን አጠናቀው ሲወጡም ከዚህ ቀደም የበደሉትን ማህበረሰብ ለመካስ መዘጋጀታቸውን አንስቷል።


ነዳጅን ጨምሮ ስትራቴጂክ የሚባሉ ሸቀጦች አስተማማኝ አቅርቦት እንዲቀጥል መንግስት ከፍተኛ ድጎማ አድርጓል - ሚኒስትር አህመድ ሽዴአዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፦ ነዳጅን ጨምሮ ስትራቴ...
15/01/2025

ነዳጅን ጨምሮ ስትራቴጂክ የሚባሉ ሸቀጦች አስተማማኝ አቅርቦት እንዲቀጥል መንግስት ከፍተኛ ድጎማ አድርጓል - ሚኒስትር አህመድ ሽዴ

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ)፦ ነዳጅን ጨምሮ ስትራቴጂክ የሚባሉ ሸቀጦች አስተማማኝ አቅርቦት እንዲኖራቸው መንግስት ከፍተኛ ድጎማ ማድረጉን የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ገለጹ፡፡

መንግስት ባለፉት ዓመታት ከ267 ቢሊዮን ብር ለነዳጅ ድጎማ ማድረጉንም ያስታወሱት ሚኒስትሩ፤ በዘንድሮው በጀት ዓመት ብቻ ለነዳጅ ድጎማ ተጨማሪ 100 ቢሊዮን ብር በጀት መጽደቁን አውስተዋል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የነዳጅ አቅርቦት እና ድጎማን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ከተደረገ ወዲህ የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ተጠናክሮ ለኢኮኖሚው ዕድገት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ሰፊ ስራዎች በመሰራት ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

ማሻሻያው የውጪ ምንዛሪ ግኝቱ በከፍተኛ ደረጃ እንዲሻሻ፣ ከልማት አጋሮች ጋር ያለው የልማት ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል፣ የኤክስፖርት አፈጻጸም እንዲሻሻል ጨምሮ የባንኮች የቁጠባ መጠን እንዲያድግ ብሎም በሁሉም መስኮች ውጤታማ አፈጻጸም እንዲመዘገብ ማስቻሉን ገልጸዋል፡፡

የምንዛሬ ተመኑ በገበያ እንዲወሰን ከመደረጉም ሊመጡ የሚችሉ የዋጋ ጭማሪዎች ህብረተሰቡ ላይ ጫና እንዳያሳድሩም ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን አብራርተዋል።

በዚህም ነዳጅን ጨምሮ ስትራቴጂክ የሚባሉ ሸቀጦች አስተማማኝ አቅርቦት እንዲኖራቸው መንግስት ከፍተኛ ድጎማን በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

ለአብነትም ለአፈር ማዳበሪያ፣ ለነዳጅ፣ ለደመወዝ ጭማሪ፣ ለመድኃኒት፣ ለመሠረታዊ ሸቀጦች፣ ለከተማና እና ገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ጨምሮ ለሌሎችም በዓመት ከ400 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በሕብረተሰቡ ላይ ጫና እንዳያስከትልም ሪፎርሙ በከፍተኛ ጥንቃቄ እና ኃላፊነት እየተሰራ ስለመሆኑ ነው ያነሱት።

መንግስት በሀገሪቷ አስተማማኝ የነዳጅ አቅርቦት እንዲኖር በዓመት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር በመመደብ ነዳጅን በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

በውጪ ምንዛሪ የሚገዛውን የነዳጅ ምርትም በሀገር ውስጥ በብር እንዲሸጥ ከማድረግ በተጨማሪ በከፍተኛ የመንግስት ድጎማ ወደ ህብረተሰቡ እንዲተላላፍ በመደረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት መንግስት በአጠቃላይ 267 ቢሊዮን ብር ለነዳጅ ድጎማ ማድረጉን ጠቅሰው በዓለም ዋጋ የሚገዛውን የነዳጅ ምርት ከዓለም ዋጋ በታች እንዲሁም ከጎሮቤት ሀገራትም ዋጋ በታች በከፍተኛ ድጎማ እያቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።

እያንዳንዱ ተጠቃሚ በሚገዛው ነዳጅ ላይ የመንግስት ድጎማ መኖሩን ያነሱት ሚኒስትሩ በዘንድሮው በጀት ዓመት ብቻ ለነዳጅ ድጎማ ተጨማሪ 100 ቢሊዮን ብር በጀት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ መደረጉንም አስታውሰዋል።

መንግስት በሀገሪቱ አስተማማኝ የነዳጅ አቅርቦት እንዲኖር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ያረጋገጡት።

በከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ ከውጪ የሚገባውን እንዲሁም በከፍተኛ ድጎማ ለህዝብ የሚቀርበውን የነዳጅ ምርት በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

በመንግስት ከፍተኛ ድጎማ የሚቀርበውን የነዳጅ ምርት በኮትሮባንድ ወደ ጎሮቤት አገራት እንዳይወጣ ግብረ ሃይል ተቋቆሞ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ለዚህም ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

የነዳጅ የግብይት ስርዓቱን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።



Address

Belay Zeleke
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian News Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian News Agency:

Videos

Share

Category

Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency is the sole national wire service of Ethiopia which gathers information through its 36 branch offices across the country and disseminates news and related stories as well other productions to public and commercial media across Ethiopia.

Ethiopian News Agency was established in 1942, which makes it the oldest national news agency in Africa.