አንተነህ አብርሃም

አንተነህ አብርሃም free speech, free spirit.
(1)

19/11/2023

ትክክል ነው።

14/11/2023
14/11/2023

ሸኔ እየቀመሰች ነው

President Alsisi called his slave to Cairo. The slave for free so-called Isayas is feeling happy to get an order about t...
13/11/2023

President Alsisi called his slave to Cairo. The slave for free so-called Isayas is feeling happy to get an order about the Ethiopian quest for access to the sea from Sisi. Shame for Eritrea. Victory for Ethiopia. በባርነት ያደገ መቸም ክብር አይወድለትም።

እኔ የምለው እዚህ ጎግል ካርታ ላይ እየገባ የክልሎችን ድንበር እያነሳ እንዳሻው ያለከልካይ የሚያዘዋውረው ሰውዬ ምነው የቀይ ባህሩን አካባቢ ብታሳዩት? እዚሁ መንደር ለመንደር ለምን ይርመጠመ...
12/11/2023

እኔ የምለው እዚህ ጎግል ካርታ ላይ እየገባ የክልሎችን ድንበር እያነሳ እንዳሻው ያለከልካይ የሚያዘዋውረው ሰውዬ ምነው የቀይ ባህሩን አካባቢ ብታሳዩት? እዚሁ መንደር ለመንደር ለምን ይርመጠመጣል? እስቲ ዝም ብለህ አሰብን ቆርጠህ ቀላቅል በሉት። በዛው በነካ እጁ ከሶማሌ ላንድም ቦትረፍ አድርግና አገናኝልን በሉት።

11/11/2023

ሩሲያ ስትዋጋ የጦርነት ጉዳቷ ጠፍቷት አይደለም። ናታንያሁ የተከፈተባቸውን ጦርነት እንደ መልካም አጋጣሚ እየተጠቀሙበት ያሉት አስከፊነቱን አጥተውት አይደለም። ቀሚስ ምሽጉ መሆን የለብንም።

11/11/2023

የሶማሊያ ፓርላማ አባላት ክንቻ።🤣😂🤣😂🤣😂🤣

ሼሕ መሐመድ ሰላም ላንተ ይሁን። ከእጅህ በልተናል። ውለታህ አለብን። ፈጣሪ ለምትወዳት ሀገርህ ያብቃህ።
10/11/2023

ሼሕ መሐመድ ሰላም ላንተ ይሁን። ከእጅህ በልተናል። ውለታህ አለብን። ፈጣሪ ለምትወዳት ሀገርህ ያብቃህ።

10/11/2023

እውነት ነው።

06/11/2023

የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነትን አንደኛ ዓመት በተመለከተ ከኢፌዴሪ መንግሥት የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ለሰላም ባላቸው የጸና አቋም የተነሣ የውጭም ሆኑ የውስጥ ጠላቶች በተነሡ ጊዜ ሁሉ እየተጠቁም ቢሆን አስቀድመው የሰላምን አማራጭ ይፈልጋሉ፡፡

የፈሩ፣ ዐቅመ ቢሶችና ደካሞች መስለው እስከሚታዩ ድረስ ችግሮችን በሰላም ለመፍታት እስከጥግ ድረስ ይሄዳሉ፡፡ መንግሥት የሰላም አማራጭን አብዝቶ የሚፈልገው ጦርነትየኢትዮጵያን ሕዝብ ወደ ሰላም፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነት እና ብልጽግና ስለማያመጣ ነው።

እነዚህ የሰላም አማራጮች ተሟጥተው ማለቃቸውን ሲመለከቱ ግን የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት እንደ አራስ ነብር ተነሥተው ጠላቶቻቸውን አደብ ያስገዛሉ፡፡ የጥንትም የቅርብም ታሪካችን ይሄንን ይመሰክራል፡፡

በትግራይ ከሁለት ዓመታት በፊት የተፈጠረው ሁኔታ ወደ ጦርነት ከማምራቱ በፊት መንግሥት የሰላም አማራጮችን ሁሉ ሞክሯል፡፡ የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ሞክረዋል፡፡ እናቶች እያለቀሱ ለምነዋል፡፡ የጦርነት ነጋሪት ከልክ በላይ እየተጎሰመ እንኳን ከትግራይ ክልል ጋር የነበረው ግንኙነት እንዳይቋረጥ ትዕግሥት አስጨራሽ መንገድ መንግሥት ተጉዟል፡፡

የተለያዩ ወገኖች መንግሥት በብቸኝነት ኃይል የመጠቀም ሕገ መንግሥታዊ መብቱን እንዲጠቀም እየወተወቱት እንኳን ለውይይትና ለፖለቲካዊ ንግግር ቅድሚያ በመስጠት ከልክ በላይ ትችቶችን አስተናግዷል፡፡

በተለያዩ ጊዜያት መንግሥት የኃይል የበላይነት እንዳለው እያረጋገጠ እንኳን ለትግራይ ሕዝብ ሲል ጦርነትን ለማቆምና ከጦርነት ቦታዎች ለመውጣት ቆራጥ ውሳኔ ወስኖ ተግባራዊ አድርጓል፡፡

በጦርነት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ እርዳታ ለትግራይ ሕዝብ እንዲደርስ መንገዶችን ከፍቶ አሳልፏል፡፡ እርዳታ የጫኑ መኪኖች በሄዱበት እየቀሩ እንኳን ከሕዝብ የሚበልጥ የለም በሚል ችግሩን ተቋቁሞ እርዳታ እንዳይቋረጥ አድርጓል፡፡

ይህ ሁሉ ተደርጎ የሚፈለገው ሰላም ባለመምጣቱ ወደ ግጭት ተገባ፡፡ በዚህም የተነሣ ሕግ የማስከበር ሥራውን እንዲፈጽም መንግሥት ተገድዷል፡፡ መንግሥት ተገድዶ በገባበት በዚያ ጦርነት የደረሰውን ኪሣራ ከትግራይ ሕዝብና ከክልሉ መንግሥት በላይ የሚያውቀውየለም፡፡

ጦርነትን ብቸኛ አማራጫቸው ያደረጉ ኃይሎች የትግራይን ወጣቶች ለእሳት ማግደዋቸዋል፡፡ የኢትዮጵያን እናቶች በሃዘን እሳት ጠብሰዋቸዋል፡፡ የክልሉን ብሎም የሀገርን ኢኮኖሚ አውድመዋል፡፡ የትግራይ ሕዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የነበረውን ዘመናት የተሻገረ ወገናዊነት አበላሽተዋል፡፡

በጦርነቱ መጨረሻ የፌዴራል መንግሥት ሁሉን ነገር በኃይል ለመፈጸም የሚያስችል ወታደራዊ ቁመና ነበረው፡፡ ነገር ግን ጦርነቱ በሰላም ስምምነት ቢቋጭ ሀገርን አትራፊ የሚያደርግ መሆኑ ስለታመነበት የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዲፈረም አድርጓል፡፡

ይሄንን ያደረገበት ከመርሑ የመነጨ ምክንያት ነበረው፤ በምንም መልኩ ለትውልድ ቂምና በቀልን ማውረስ የለብንም፤ ጦርነት አሸናፊና ተሸናፊን ይፈጥራል፤ ሰላም ግን ሁሉንም አሸናፊ ያደርጋል፤ መጪው ትውልድ በአሸናፊና ተሸናፊ ትርክት ውስጥ ከሚያድግ ሁሉንም አሸናፊ በሚያደርገው የሰላም ትርክት ውስጥ ቢያድግ ይሻላል በሚል የተደረገ ነው፡፡

ለተጎዱ የተለያዩ ማኅበረሰቦች የሚያገግሙበት ፋታ ለመስጠት የተሰጠ ዕድልም ነው፡፡ ይህ ውሳኔ ሀገርን ለመገንባትና ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት ሲባል የተከፈለ መሥዋዕትነት ነው፡፡

ከሰላም ስምምነቱ በኋላ መንግሥት በሆደ ሰፊነትና ቁስሉ እንዲሽር ካለው ፍላጎት ረጅም ርቀት ተጉዟል፡፡ ከስምምነቱ መፈረም በኋላ የጥላቻውን ጉም በመግፈፍ ወደ ትግራይ በግንባር ቀደምነት የተጓዘው በአፈ ጉባኤው የተመራው የፌዴራል መንግሥቱ ልዑክ ነበር፡፡ ይህ ልዑክ ከተጓዘ በኋላ የቴሌኮሙኒኬሽን፣ የባንክና የአውሮፕላን አልግሎቶች በፍጥነት እንዲጀምሩ ተደርገዋል፡፡

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በተመሠረተ ጊዜ መሳሳብና መጓተትን ለማስቀረት ሲባል የአመራሩን ድርሻ ክልሉ እንዲወስድ በማድረግ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፋታ አግኝቶ ፊቱን ወደ ሰላምና ልማት እንዲያዞር ተደርጓል፡፡

የግብርና ሥራውን ለማገዝ የሚመለከተው የሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በክልል ደረጃ ከሚጠበቅበት በላይ ሠርቷል፡፡ ዩኒቨርሲቲዎችንና ትምህርት ቤቶችን ወደ አገልግሎት ለመመለስ የትምህርት ሚኒስቴር ከተልዕኮ በላይ ተጉዟል፡፡

የመከላከያ ሠራዊት የሕዝቡን ችግር ለመፍታት ከራሱ በጀት ቀንሶ አያሌ ተግባራት አከናውኗል፡፡ የሰላም ስምምነቱን እንደ ዕድል በጠቀም ሕዝብን ከችግር በማዳን፣ መንግሥታዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን በማስመጀር ኃላፊነቱን ተወጥቷል፡፡ አንዳንድ ነገሮችን እያገዘ፤ አንዳንድ ነገሮችን ችሎ እያለፈ፤ አንዳንድ ነገሮችን እየመከረ፤ አንዳንድ ነገሮችንም ራሱ እየሠራ የሰላም ስምምነቱ በተሟላ ልኩ በሂደት እንዲፈጸም ለማድረግ ሞክሯል፡፡

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በአንዳንድ ነገሮች ወደኋላ እየቀረና ስምምነቱን በተሟላ ሁኔታ ሳይፈጽም እያነከሰ እንኳን ለክልሉ የሚደረገውን ሁለንተናዊ ድጋፍ የፌዴራል መንግሥቱ አላቋረጠም፡፡

ከፌዴራል መንግሥቱም አልፎ ክልሎች ከአነስተኛ በጀታቸውና ገቢያቸው በመቀነስ የትግራይ ክልልን ደግፈዋል፡፡ አከራካሪ የሚባሉ አካባቢዎችን በተመለከተ የፌዴራል መንግሥቱ አቋም ወስዶ ሠርቷል፡፡ የፌዴራል መንግሥት በዚህ ረገድ ያለው አቋም ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋግጥ፣ ሁሉንም ወገን በሚጠቅም መንገድ ፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትና ብልጽግናን በሚያረጋግጥ መንገድ መፍትሔ መሰጠት አለበት፡፡

ክረምት ደርሶ የእርሻ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ተፈናቃዮች ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱ፤ የአካባቢ ነዋሪዎች በመረጧቸው አካላት እንዲተዳደሩ፤ በመጨረሻም ደረጃ በደረጃ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ሕዝበ ውሳኔ እንዲደረግ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡ እነዚህን ሁሉ አቋሞችና ተግባራት የኢትዮጵያ ሕዝብና ዓለም አቀፉም ማኅበረሰብ በሚገባ ያውቃል፡፡

ይህ ሁሉ ቢደረግም እንኳን በዚያኛው ወገን እግር የመጎተት አዝማሚያ ይታያል፡፡ ይህ ግን ዘላቂ ሰላምን፣ ብልጽግናንና የሕዝቦችን ኅብረ ብሔራዊ አንድነት አያረጋግጥም፡፡

የፌዴራል መንግሥት የፕሪቶሪያውን ስምምነት በተመለከተ ከሚጠበቅበት በላይ ተጉዟል፡፡ በዚህም ለሰላም ያለውን ጽኑ አቋም ደጋግሞ አሳይቷል፡፡

የፕሪቶሪያው ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲከበር መንግስት አሁንም ቁርጠኛ አቋም አለው፡፡ ሁሉም አካላት ተመሳሳይ ቁርጠኝት በማሳየት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ሊወጡ ይገባል፡፡

ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

አዲስ አበባ

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

04/11/2023

የህግደፍ ሰዎች እንዋጋ እንዋጋ በለው እያሉን ነው። ፈጽሞ ሊተዉን አልቻሉም። እና በፈረንጅ የተገዛን ፈረንጅ ከተማ የሰራልን ህዝቦች ነን። እናንተ ቆጮ ፍቃችሁ የምትበሉ ናችሁ እያሉን ነው። በውስጥ ጉዳያችንን ገብተው መፈትፈቱን ላፍታም ማቆም አልቻሉም።

04/11/2023

ይደመጥ ወደብ ወሳኝ ነው

04/11/2023
03/11/2023

የኤርትራ ኤሊቶች የኢትዮጵያ ጥላቻ ከልክ ያለፈ ነው ስንል በማስረጃ ነው። የምትመለከቱት ግለሰብ አስመራ ከተማ ከአዲስ አበባ እንዲበልጥ ያስረዳበትን ሂደት ስትሰሙ የጥላቻ ደረጃው ይገባችኋል። ሂሊና ያለው ይፍረድ።

30/10/2023

በዘረተኝነት ፈተና ያልወደቅነው የኢትዮጵያ ልጆች የመጨረሻዋን ሳቅ የምንስቀው እኛው ነኝ። ዘረኞች ይዋረዳሉ።

29/10/2023

ለምን ተዋናይ አልሆነችም ይህች ልጅ ስሟስ ማን እስቲ ንገሩኝ።

የኬኒያ ዋና ከተማ ከአዲስ አበባ ጋር በከባድ ፉክክር ላይ ናት። የኢትዮጵያውያን የግል ንብረት ብቻ በሆኑት ውብ ህንጻዎች የተሞላችው አዲስ አበባ ከአውሮፓዊያን ቅኝ ገዥ ሃብታሞች ከተማ ከሆነ...
29/10/2023

የኬኒያ ዋና ከተማ ከአዲስ አበባ ጋር በከባድ ፉክክር ላይ ናት። የኢትዮጵያውያን የግል ንብረት ብቻ በሆኑት ውብ ህንጻዎች የተሞላችው አዲስ አበባ ከአውሮፓዊያን ቅኝ ገዥ ሃብታሞች ከተማ ከሆነችው ናይሮቢ ጋር እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ በሚሉ ትንቅንቆች ውስጥ ገብታለች። መጨረሻውን ያሳምርልን።

29/10/2023

2875 likes, 631 comments. “ with ”

28/10/2023

ኤርትራ ልጆች ወደ እውነት እየመጡ ነው። አብሮ መኖርና ማደግ ይሻላል እያሉ ነው። እኛም የምንለው ይሄንኑ ነው።

27/10/2023

858 likes, 147 comments. “Part 36 |”

የቀድሞ ባልደረባችን በቀለ ሙለታ (አንቀጸ) በድንገተኛ ህመም በሞት መለየቱ እጅግ አስደንግጦኛል። ነፍስህ በሰላም ትረፍ።
27/10/2023

የቀድሞ ባልደረባችን በቀለ ሙለታ (አንቀጸ) በድንገተኛ ህመም በሞት መለየቱ እጅግ አስደንግጦኛል። ነፍስህ በሰላም ትረፍ።

ይሄንን ጀግና ኢትዮጵያዊ እንዴት እንዳላወቅኩት ገርሞኛል። ብቸኛ ኢትዮጵያዊ ይመስለኛል። እውቀት ጥግ ድረስ የሄደ ባለምጡቅ አእምሮ ጋቢሳ እጀታ ይባላል። ዓለም በጭንቅላቱ ይደመማል።
26/10/2023

ይሄንን ጀግና ኢትዮጵያዊ እንዴት እንዳላወቅኩት ገርሞኛል። ብቸኛ ኢትዮጵያዊ ይመስለኛል። እውቀት ጥግ ድረስ የሄደ ባለምጡቅ አእምሮ ጋቢሳ እጀታ ይባላል። ዓለም በጭንቅላቱ ይደመማል።

መንሱር ጀማል ያቅሙን አያደረገ ነው። ሁላችንም የእሱን አርአያነት እንከተላለን።
24/10/2023

መንሱር ጀማል ያቅሙን አያደረገ ነው። ሁላችንም የእሱን አርአያነት እንከተላለን።

1150 likes, 145 comments. “ ”

Very Good Newsየአማራና ኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተፈናቃዮችን መልሶ በማቋቋም ዙሪያ መከሩየኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን ባሕር ዳር በመገኘት ከአማራ ክልል ...
24/10/2023

Very Good News

የአማራና ኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተፈናቃዮችን መልሶ በማቋቋም ዙሪያ መከሩ

የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን ባሕር ዳር በመገኘት ከአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር መክረዋል።

ባለፉት ዓመታት ከኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለው በመጠለያ ጣቢያዎችና በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት በቁርጠኝነት እየሠራ መሆኑን በምክክሩ ወቅት ተገልጿል።

በጥፋት ኃይሎች ጥቃት ከመኖሪያ አካባቢያቸው የተፈናቀሉና ሐብት ንብረታቸው የወደመባቸውን ወገኖች በመለየት በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር አብረው ከኖሩት የኦሮሞ ሕዝብ ጋር አብሮነታቸውን ለማስቀጠል ቅንጅታዊ ጥረት እንደሚያስፈልግም ተወያይተዋል።

የሁለቱን ክልል ሕዝቦች አንድነትና አብሮነት የሚጻረሩ ኃይሎችን በመታገል የዜጎችን ደኅንነትና ሐብት ንብረት የማፍራት ነጻነትን ማረጋገጥ እንደሚገባም መግባባት ላይ መድረሳቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡

ተፈናቃዮች እያሳለፉት ያለውን ችግር ያገናዘበ ፈጣን ስምሪት በመውሰድ ወደ መደበኛ ሕይወታቸው እንዲመለሱ የማድረግ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲደረግም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ምንጭ፡ፋና

23/10/2023

ስለወደብ ባለቤትነት ያለውን ውዝግብ ስዩም ተሾመ በአጭሩ አስቀምጦታል። ሌሎች የኤርትራዊያንን አቋም በማጤን ያለ ጦርነት የወደብ አክሰስ ማግኘት አይሆንም ይላሉ። ያሉት ሁሉ አማራጮች አልቀው ጦርነት ውስጥ የሚገባ ከሆነ የኢትዮጵያን ታሪክ ወደቀደመው ታላቅነት የሚመልስ አጋጣሚ ተፈጠረ ማለት ነው። በሚገባ እንጠቀምበታለን። ይሄው ነው።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251911403407

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አንተነህ አብርሃም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share


Other Social Media Agencies in Addis Ababa

Show All