Central Politics

Central Politics & Broadcasting Production!!!

 #ፍትህ በግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ ለተገደለው ለአቶ አርጋው ሽኩር !! #የሀዲያ ሆሳዕና እግርኳስ ክለብ የልብ ደጋፊ የነበሩት አቶ አርጋው ሽኩር በድንገተኛ አደጋ በተወለዱበት ሀገር ሀዲያ ሆሳ...
17/01/2025

#ፍትህ በግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ ለተገደለው ለአቶ አርጋው ሽኩር !!

#የሀዲያ ሆሳዕና እግርኳስ ክለብ የልብ ደጋፊ የነበሩት አቶ አርጋው ሽኩር በድንገተኛ አደጋ በተወለዱበት ሀገር ሀዲያ ሆሳዕና ከተማ ባልታወቁ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ።

#አቶ አርጋው ሽኩር ሀዲያ ሆሳዕና ወደ ፕሪምየርሊጉ ባደገበት አመት የድሬዳዋ ሀዲያ ተወላጆችን በማስተባበር ለክለባችን የዋሉት ውለታ እና በሀዲያ ጉዳይ ላይ ግንባር ቀደመ ሰው መሆናቸው አይዘነጋም ።

#አቶ አርጋው ሽኩር ቤተሰባቸውን ለመጠየቅ ከድሬዳዋ ሆሳዕና መጥተው ጉዳያቸውን ጨርሰው ወደ መኖሪያ ድሬዳዋ ለማቃናት በሌሊት ሀገር ሰላም ብለው ከሆሳዕና አዲስአበባ ለመሳፈር ስያቀኑ ሆሳዕና ከተማ በኮለኔል በዛብህ ጴጥሮስ አደባባይ አከባቢ በአሰቃቂ ሁኔታ በጩቤ ተወግተው ተገድለዋል !!

#ህግ ባለበት ሀገር በከተማችን ጭካኔ በተሞላ መንገድ የሰው ህይወት የሚያጠፉ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ መጥቷል ።

#ይድረስ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ፤ የሀዲያ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ፤ ሀዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ የወንድማችንን ህይወት የቀጠፉ ሰዎች የማያዳግም ፍርድ እንድሰጥ ፍትህ እንጠይቃለን !!

#ፍትህ በግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ ለተገደለው ለአቶ አርጋው ሽኩር !!

ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለን ነብስ ይማር !!

Hossana Entertainment
Hossana City Administration Communication affairs Office Media
Hadiya.TV
Hadiya= ሀዲያ
Hadiya zone Government Communication Affairs Department
Hadiya Legga
Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau

 ‼️🙏
17/01/2025

‼️🙏

♦ ይሄ ታምር ነው !ምን ማለት ይቻላል ?! የሚሉት ነገር ግራ ገብቷቸዋል !ይህ በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ሎሳንጀለስ በሰዓት 100 ማይል በሚደርስ ሃይለኛ የንፋስ ፍጥነት የነበረውን ወደ አልነበር...
12/01/2025

♦ ይሄ ታምር ነው !

ምን ማለት ይቻላል ?! የሚሉት ነገር ግራ ገብቷቸዋል !

ይህ በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ሎሳንጀለስ በሰዓት 100 ማይል በሚደርስ ሃይለኛ የንፋስ ፍጥነት የነበረውን ወደ አልነበር የቀየረ እጅግ በጣም አደገኛ የሰደደ እሳተ ነው ።

ይህ የሰደድ እሳት በሰው ኃይል ፣ አሜሪካ አለኝ በምትለው ቴክኖሎጂ ሁሉ ማስቆም አልቻለችም ፤ የሰው ሕይወት ጠፍቷል ፣ 130,000 ሰዎች ቤት ለቀው ተሰደዋል ። ቤቶች እና መኪናዎች በሚናድ እሳት አመድ ሆነዋል ።

ሆኖም ግን ፤ በዚህ የሰደድ እሳት ዓለምን ጉድ ያሰኘ ነገር ታይቷል። በምስሉ ላይ የሚታየው ወደ 100 ዓመት የሚጠጋው ሙሉ በሙሉ በእንጨት የተሰራው መኖሪያ ቤት ከሰደድ እሳቱ ተርፏል ። ባለቤቶቹ ለምን እንደሆነ ግራ ተጋብተዋል ፣ የእሳት አደጋ ተከላካይ ባለሙያዎች ይህ ለምን እንደሆነ መልስ አጥተዋል ። የዓለም የብዙኀን መገናኛ በሰፊው በዚህ ታምረኛ ቤት ዙሪያ ዘገባዎችን እየሰሩ ነው። via yednekachew

  ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የላቀ ውጤት አስመዘገቡ በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ የላቀ ውጤት አስመዘገቡ። ከማለዳው 11 ሰዓት ጀምሮ በዱባይ በተካሄደው ውድድር ኢትዮጵ...
12/01/2025

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የላቀ ውጤት አስመዘገቡ

በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ የላቀ ውጤት አስመዘገቡ።

ከማለዳው 11 ሰዓት ጀምሮ በዱባይ በተካሄደው ውድድር ኢትዮጵያውያኑ የተሰጣቸውን ቅድሚያ ግምት አሳክተዋል።

በዚህም በሁለቱም ጾታ ከአንደኛ እስከ አስረኛ ድረስ ያለውን ደረጃ በመያዝ በፍጹም የበላይነት ውድድሩን አጠናቀዋል።

ውድድሩን በሴቶች አትሌት በዳቱ ሂርጳ በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ፥ በወንዶች ደግሞ አትሌት ቡቴ ገመቹ አንደኛ ወጥቷል።FBC

10/01/2025
አስትሮይድ (Asteroid) በህዋ ውስጥ የሚገኙ ድንጋያማ አካላት ናቸው፡፡ በዋነኛነት የስርዓተ ጸሐይ አካል በመሆን በማርስ እና በጁፒተር መካከል ባለው ስፍራ የመቀነት ቅርጽ (Asteroid...
10/01/2025

አስትሮይድ (Asteroid) በህዋ ውስጥ የሚገኙ ድንጋያማ አካላት ናቸው፡፡ በዋነኛነት የስርዓተ ጸሐይ አካል በመሆን በማርስ እና በጁፒተር መካከል ባለው ስፍራ የመቀነት ቅርጽ (Asteroid Belt) ፈጥረው ጸሐይን ይዞራሉ፡፡

እነዚህ የሰማይ አካላት ግዙፍ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ አንዳንዶቹም በመቶ ኪሎሜትሮች የሚቆጠር ዲያሜትር ያላቸው ናቸው፡፡ በአንፃሩ ሜትሮይትስ (Meteorites) ወደ ምድር ከባቢ አየር የገቡ የአስትሮይዶች ወይም ኮሜት ቁርጥራጮች ናቸው። በሌሊት ሰማይ ላይ የምናያቸው የብርሀን ጅራቶች ሜትሮይድ (Meteoroid)፣ ትንሽ የጠፈር አለት ወደ ከባቢ አየር ውስጥ ሲገባና ሲቃጠል የሚፈጠር ነው።
የሜትዮር ሻወር (Meteor Shower) አስደናቂ የብርሃን ትዕይንት በሰማይ ላይ የሚፈጥሩ ሲሆን፤ አብዛኛዎቹ ሜትሮይዶች ጥቃቅን እና መሬት ላይ ከመድረሳቸው በፊት ሙሉ በሙሉ ተቃጥለው የሚጠፉ ናቸው።
በመጠን የገዘፉ እና ጠንካራ የሆኑት አለቶች ከእሳታማው መተላለፊያ እና የመሬት ከባቢ አየር ተርፈው መሬት ላይ ይደርሳሉ።

Meteorites ከተለመዱት የምድር አለቶች የሚጋሩት ነገር ቢኖርም በራሳቸው ደግሞ የተለየ ስሪት እና አወቃቀር ያላቸው በመሆኑ በአይን በማየት ብቻ ለመለየት አዳጋች ይሆናል፡፡ የመስኩ ተመራማሪዎች የሜትሮይትን ስብጥር ለመተንተን የረቀቁ ቴክኒኮችን እና የሳይንስ መመርመሪያ መሳሪያዎችን ይጠቀማሉ። ይህም የማዕድን ይዘቱን ለመመርመር ከምድር ውጭ ያሉ ንጥረ ነገሮች መኖራቸውን መለየት እና የተረጋጋ የአይሶቶፖች ምጥጥንን (isotope ratio) መለካትን ጭምር ያካትታል። እነዚህ ትንታኔዎች የሜትሮይትን አመጣጥ እና ስለ መነሻ ምንጫቸው አስመልክቶ ግንዛቤ ለማግኘት ይረዳሉ።
ሜትሮይት በምድር ላይ የሚያስከትሉት ተጽእኖ እና ጉዳት በአንፃራዊነት እጅግ አነስተኛ ነው፡፡ በየዓመቱ ወደ ምድር ገጽ የሚወርዱትም በቁጥር ጥቂት ናቸው፡፡ አብዛኛው አካላቸው በምድር ከባቢ አየር ውስጥ ሲያልፍ ተቃጥሎ ስለሚያልቅ፤ የሚያደርሱት ጉዳት ያነሰ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ጉልህ የሆነ ውድመት ሊያስከትሉ የሚችሉት በሚሊዮን አንዳንዴም በሺህ ዓመታት የሚከሰቱት ብቻ ናቸው፡፡ ከዚህ አኳያ የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ቴሌስኮፖችን በመጠቀም ካለማቋረጥ እንቅስቃሴያቸውን በንቃት በመከታተል ከፍተኛ ጉዳት ለያመጡ የሚችሉትን አስቀድሞ በመለየት የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃ እንዲወሰድ ያደርጋሉ።
ምንጭ፡ Space science and geo-spatial institute

08/01/2025
 የሀዲያ ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ከብዙ ልመናና ደጅ መጥናት በኋላ ምላሽ በማጣት ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና ለብልፅግና ፓርቲ በአካል አቤቱታ አቅርበው ተመልሰዋል። # እንገፋበ...
02/01/2025


የሀዲያ ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ከብዙ ልመናና ደጅ መጥናት በኋላ ምላሽ በማጣት ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና ለብልፅግና ፓርቲ በአካል አቤቱታ አቅርበው ተመልሰዋል። # እንገፋበታለን። በቀጣይ ወጣቶች ተዘጋጁ! ወጣቱን እንድገድሉት ቆመን አንጠብቅም።
***
ሙሉ አቤቱታው👇

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ከፌዴራል መንግስት አቅጣጫ በተቃራኒው በመሄድ በልጆቻችን ላይ እየፈፀመባቸው ያለውን በደል ስለማሳወቅ፦

ሀገራችን ኢትዮጵያ ከድህነት ለመላቀቅና ወደ ብልጽግና ለመሻገር፣ ሰላምና ደህንነት የተረጋገጠባት ሀገር ሆና ለዜጎቿ ኑሮ ምቹ እንድትሆን ራዕይ ሰንቆ የፌዴራል መንግስትና መሪ ድርጅቱ (ብልፅግና ፓርቲ) በትጋት እየሰራ እንደሆነ እንገነዘባለን። ይህ ታዲያ የሁሉም ክልሎች መንግስታትና በየደረጃው ያሉት የህብረተሰብ ክፍሎች በተመሳሳይ ዓላማ ካልተሳተፉበትና ለትክክለኛ ብልፅግና በጋራ ካልተጉ ግብ የመምታቱ ጉዳይ አጠራጣሪ ይሆናል።

ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እንደ አዲስ የተደራጀ ክልል እንደመሆኑ በክልሉ የሚገኙ ብሄሮችና ብሄረሰቦች መሰረታዊ ጥያቄዎችን ለመመለስ፣ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ እንድሁም የህዝብ ድምፅ በነፃነት የሚሰማበት ክልል መሆን እንዳለበት ይጠበቃል። ነገር ግን ባሁኑ ግዜ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የክልሉን ህዝብ ከማዳመጥና ለክልሉ ብሎም ለሃገር ልማት፣ ሰላምና ብልፅግና በየደረጃው ያለውን የህብረተሰብ ክፍል አቅፎ ከመስራት ይልቅ በውጤት አልባ ተደጋጋሚ ስብሰባዎች፣ የህዝብን ድምፅ በማፈን፣ ግጭት ቀስቃሽ መግለጫዎችንና የመድረክ ንግግሮችን ማድረግ፣ ከሁሉም በላይ ለህዝብ ድምፅ የሚሆኑና የብልጽግና ደጋፊዎች የሆኑ ወጣት ምሁራንን ሰብስቦ ያለፍርድ ለወራትና አመት ማሰር መገለጫው እስከመሆን መድረሱ እጅግ አሳዛኝ ነው።

እንደሚታወቀው ባሁኑ ግዜ የፌዴራል መንግስት ሀገራዊ ምክክርና ዕርቅ ለማድረግ ኮሚሺን አቋቁሞ እየሰራ ይገኛል። በዚህም በሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ሀሳባቸውን በግልጽ በማስመዝገብ ለሀገራዊ ምክክር ቅድመ-ሁኔታዎች እየተጠናቀቁ ይገኛሉ። ከዚህም ጎንለጎን መንግስት ለሃሳብ ልዩነት ያለውን ሆደ-ሰፊነትና ዝግጁነት ግልጽ በማድረግ ታጥቀው ጫካ ለገቡት ቡድኖች ሁሉ የሰላም ጥሪ በማድረግ ለዚህም የሀገር ሽማግሌዎችንና የሀይማኖት አባቶችን አሳታፊ በማድረግ ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ በአይናችን የተመለከትነውና የተደሰትንበት ነው።

ከዚህ ተቃራኒ በሆነ መንገድ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በክልሉ ከ276 በላይ የማህበረሰብ አንቂዎችን ማሰሩን በክልሉ ፕሬዚዳንት ቃል-በቃል የተነገረ እውነታ ነው። በርግጥ አንዳንድ የማህበረሰብ አንቂዎች በተለይም ከሀገር ውጭ በመሆን የሀገራችንን ገጽታ የሚያጠለሹ ተግባራትን በመፈፀም ህዝብ እንዳይረጋጋና ህዝብና መንግስት ተቀራርበው እንዳይሰሩ እንደሚያደርጉ እንገነዘባለን። ነገር ግን በግልጽ ማንነት ቀርበውና በቀና ዕሳቤ ለማህበረሰብ ልማት በሀላፊነት የሚሰሩ የማህበረሰብ አንቂዎች እንዳሉም የታወቀ ነው።

መለሰ አብረሃም ወለቦ የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ መምህር ስሆን ባሁኑ ግዜ በህንድ ሀገር አንድራ ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት (ሶስተኛ ድግሪ) ትምህርቱን ለማጠናቀቅ የምርምር ስራ ውጤት ማቅረብ ብቻ የቀረውና ወደ ሀገርቤት በመምጣት ለጥናቱ የሚሆን መረጃ በማሰባሰብ ላይ ሳለ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ታህሳስ 13/2016 ለእስር ተዳረገ። በዚህም ያለ አንዳችም ክስና ክርክር ለስድስት ወራት በእስር ከቆዬ በኋላ ግንቦት 27/2016 በዋስ በመለቀቁ ከአንድ ወር ቆይታ በኋላ ወደ ትምህርቱ ለመመለ

01/01/2025
 #ከቤራ ትግሉን ወጥር ይህ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው  ጣሰው አደገኛ ፀረ ሃዲያ መሪ ነው። አሁን ለኛ ያለው አማራጭ ትግሉን አጠናክሬን መቀጠል ነው ። እውነ...
30/12/2024

#ከቤራ ትግሉን ወጥር ይህ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው አደገኛ ፀረ ሃዲያ መሪ ነው። አሁን ለኛ ያለው አማራጭ ትግሉን አጠናክሬን መቀጠል ነው ። እውነት ያሸንፋል !

ማን ንስር ማን ቁራ እንደሆነ እንተያያለን🤨🤨****ለሀዲያ ህዝብ የፍትህ፣ የሰላምና የምክክር ጥያቄ ዘመቻ ምላሽ ለመስጠት የሞከረው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተደድር አቶ እንዳሻው ...
28/12/2024

ማን ንስር ማን ቁራ እንደሆነ እንተያያለን🤨🤨
****
ለሀዲያ ህዝብ የፍትህ፣ የሰላምና የምክክር ጥያቄ ዘመቻ ምላሽ ለመስጠት የሞከረው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተደድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በፌስቡክ ገጹ የሀዲያን ህዝብ ከቁራ ጋር ራሱን ደግሞ ከንስር ጋር በማመሳሰል ነቆራውን በጽሁፍ አስነብቦናል።

አቶ እንዳሻው ራሱን ንስር ለማድረግ በሞከረበት ጽሁፉ እሱን የሚደፍር ቁራ እንደሆነ በመግለጽ ለቁራው ምላሽ እንደማይሰጥ፣ ይልቁኑም እንዳይተነፍስ አድርጎ ህይወቱን እስከሚያጠፋው ድረስ ወደ ላይ እንደሚጓዝ ጽፏል። ይህ በቀጥታ የሚያመለክተው አቶ እኝዳሻው መምህር መለሰ አብረሃምን ከዶክተሬት ትምህርቱ ኋላ አስቀርቶ እንድታሰር ካደረገ በኋላ በቁራ መልክ የገለፃቸው የሀዲያ ሽማግሌዎችና መምህር መለሰ አብረሃም እንድሁም የፍትህ ጠያቂው የሀዲያ ማህበረሰብ በተደጋጋሚ በይቅርታ ጥያቄ ወደ ቢሮው መመላለሳቸውን ያመለክታል።

ንስር ምላሽ እንደማይሰጥና ቁራው መተንፈስ እስከማይችል ድረስ እንደሚያቆየው የፃፈው ደግሞ የተከበሩ የሀዲያ ሽማግሌዎች፣ መምህር መለሰና መላው ፍትህና ምክክር ጠያቂ የሀዲያ ማህበረሰብ ለሚጠይቀው ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ መለሰ አብርሃምን ለረጅም ግዜ አስሮ በማቆየት የሀዲያ ህዝብ ድምፅ ታፍኖ እንደሚቀር ያለውን ዕቅድ አመልካች ነው።

ይህ በ Heessoo እና Hiraago ወይም በተረትና ትንቢት ለተካነው የሀዲያ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት ህዝብ በቀላሉ የሚገባው አሽሙር ነው።

በመሆኑም፣

መላው "ቁራ" ተብለህ የተሰደብክ የሀዲያ ማህበረሰብ ከታች በፎቶ እንደሚንመለከተው ሁሉ ቁራው በንስር ጀርባ ተቀምጦ እንጂ ንስር በቁራ ጀርባ እንዳልሆነ ሁሉ፣ አቶ እንደሻው ጠሰው በሀዲያ ጀርባ ተንደላቆ ተቀምጦ የሀዲያን ጭንቅላት ለመብሳትና ለማፍረስ ደጋግሞ እየወጋ ቆይቶ፣ ዛሬ ቦታ ቀይሮ ራሱን ንስር፣ አንተን ቁራ ብሎሃልና ማን ቁራ፣ ማንስ ንስር እንደሆነ የሚታሳይበት ግዜ አሁን ነው።

እስከዚያው "ትዕቢት ውድቀትን ትቀድማለች!" በሉልኝ!

Summoro Baadoro ነኝ።

 #ሆሳዕና ላላችሁ ሆሳዕና ከተማ በርካታ ታዋቂ ጥበበኞችን ከዚህ በፊት አፍርታለች። የኢትዮጵያ አይዶል ደግሞ ቀጣዩን ጥበበኛ ያላችሁበት ሆሳዕና ከተማ መቶ በነፃ አወዳድሮ ዳጎስ ያለ ሽልማት ...
27/12/2024

#ሆሳዕና ላላችሁ

ሆሳዕና ከተማ በርካታ ታዋቂ ጥበበኞችን ከዚህ በፊት አፍርታለች። የኢትዮጵያ አይዶል ደግሞ ቀጣዩን ጥበበኛ ያላችሁበት ሆሳዕና ከተማ መቶ በነፃ አወዳድሮ ዳጎስ ያለ ሽልማት ለመሸለም ምዝገባ እያካሄደ ነው።

የኢትዮጵያ አይዶል በማንኛውም አይነት ተሰጥኦ የምትወዳደሩበትና ችሎታችሁን የምታሳዩበትን ውድድር ምዝገባ ለማጠናቀቅ የቀረው ግዜ ጥቂት ነው!!

ዛሬውኑ መተው ይመዝገቡ።

ካሉበት ሆነው ለመመዝገብ ሊንኩን ይጠቀሙ

https://t.me/EtvEthiopianidolbot

የመብት ተሟጋችና የዩንቨርስቲ መምህር የሆነው "ፕረዚዳንቱን ተችቷል" በሚል በህገወጥ መንገድ ለአንድ ዓመት ያለቅጣት ውሳኔ በእስር እንዲቆይ መደረጉ በአከባቢው ቅሬታ ፈጠረየሰብዓዊ መብት ተሟ...
26/12/2024

የመብት ተሟጋችና የዩንቨርስቲ መምህር የሆነው "ፕረዚዳንቱን ተችቷል" በሚል በህገወጥ መንገድ ለአንድ ዓመት ያለቅጣት ውሳኔ በእስር እንዲቆይ መደረጉ በአከባቢው ቅሬታ ፈጠረ

የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፣ መምህር መለሰ አብረሃም የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ መምህር እንዲሁም የሀዲያ ሚዲያ ኔትወርክ መስራች ሲሆን በሀገረ-ህንድ የዶክትሬት ትምህርቱን እየተከታተለ ካለበት ለምርምር ሥራ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ በኋላ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕሬዚዳንት የሆኑትን አቶ እንደሻው ጣሰውን "በማህበራዊ ሚዲያ ተችተሃል" በሚል ለአንድ ዓመት ሙሉ ያለ ፍርድ ቤት የቅጣት ውሳኔ በእስር ቤት እያሳለፈ እንደሚገኝ ቤተሰቦቹ ለዎላይታ ታይምስ ሚዲያ አረጋግጧል።

ቤተሰቦቹ መለሰ ከታህሳስ 2016 እስከ ግንቦት 2016 ዓ.ም ለ6 ወራት ያለምንም ክስ በሆሰዕና ማረሚያ ታስሮ እንድቆይ ከታደረገ በኃላ በ100 ሺ ብር ዋስ ተለቀው እንደነበር ተናግሯል።

ከእስር ስወጣ ወደ ህንድ ለመሄድና በማረሚያ ቤት በእስር ሆኖ የሰራውን የጥናት ውጤት አስረክቦ ለመመለስ ጉዞ ጀምሮ ኤርፖርት ገብቶ ሙሉ ሂደቱን ካለፈ በኃላ ቀድሞ ከሀገር እንዳይወጣ እግድ ተቀምጦበት ስለነበር ማለፍ አትችልም ተብሎ መመለሱንም አክለዋል።

ከዛ በኃላ በሁለተኛ ቀንም በክልሉ ፕረዚዳንት እንዲታሰር ተደርጎ በመጀመሪያ ወደ ሆሳዕና ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በግዜ ቀጠሮ ስመላለስ ቆይቶ የነበረውን በዋስ ለመልቀቅ ከጫፍ መድረሱን ያወቀው የክልል ፍትህ ቢሮ ዐ/ህግ ጉዳዩን ወደ ሀዲያ ዞን ከፈተኛ ፍ/ቤት ማዞሩን ቤተሰቦቹ አስረድቷል።

ከፈተኛ ፍ/ቤቱም የቀረበበት ክስ የዋስትና መብት የማያስከለክል መሆኑን ጠቅሶ በ200 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈታ በማዘዙ ቤተሰብ የፍርድቤቱን የባንክ አካውንት ቁጥርና የመዝገብ ቁጡር ለመቀበል ሄዶ እዛው እያለ ከህግ ውጪ የከፍተኛ ፍ/ቤት ፕረዚደንት በፍጥነት ወደ መዝገብ ቤት በመዝለቅ የመለሰ አብረሃምን መዝገብ ስጡኝ በማለት መዝገቡን ተቀብሎ በቢሮው አስቀምጦ መውጣቱን ቅሬታ ገልጿል።

ይህ በእንዲህ እንደለ መለሰ ለ4ተኛ ግዜ በመታሰሩ የሀዲያ የሁሉም ጎሳዎች ባህላዊ መሪዎችና የሁሉም የሀይማኖት አባቶች በመሆን ወደ ክልሉ ርዕሰ-መስተዳደር አቶ እንደሸው ጣሰው ቢሮ ሄደው መናገራቸውን ተናግሯል።

በዕለቱ የርዕሰ መስተዳድሩ ዋና አማካሪ የሆኑትን አቶ ንጉሴ አስረስን አግኝተው ተወያይተው አቶ ንጉሴ ለሀዲያ ሽመግሌዎችና የሀይማኖት አባቶችን "የመለስን ጉዳይ ሀላፊነት የምትወስዱት ከሆነ ደብዳቤ ጽፋችሁ መለሰም ደብዳቤ ጽፎ ይዛችሁ ኑ" ብለው እንደነበር ገልጿል።

ሽመግሌዎቹም "ቀጥታ ወደ ሆሳዕና ማረሚያ በመውረድ መለስን አስጠርተው ይህንኑ ነግረውት ከዝህ በኃላ በሚዲያ ሥራ ከክልሉ መንግስት ጋር ግጭት ውስጥ የሚያስገባ ነገር ውስጥ እንደማትገባ ለኛ ቃል ግባልን፣ ይቅሪታ ጠይቀህ ወደ ትምህርትህ ህድ አሉት። መለሰ "እኔ ያጠፋሁትና ያላወኩት ነገር ካለ ይቅርታ ይደረግልኝ" ብሎ ለክልል መንግስት ደብዳቤ ጽፎ ለሽማግሌዎች ሰጣቸው ብለዋል።

ሽማግሌዎቹም ደግሞ ሀላፊነት ወስደው ጉዳዩን እንደሚያዩ ገልጸው ጽፈው አንድ ላይ ለክልሉ ፕሬዚዳንት አማካሪ ሰጡት። እሱም ደብዳቤዎችን ለክልሉ ፕሬዚዳንት ማስረከቡን ነገሯቸው፣ እንጠራችኋለን ብሎ ሸኛቸው። ከዚያ ወድህ በተደጋጋሚ ሽመግሌዎች ቢሄዱም ከበር እንዳያልፉ ጠባቂዎች እየከለከሏቸው ይመለሳሉ" ሲሉ ቤተሰቦቹ በምሬት ይናገራሉ።

በዚሁ መሀል የሀድያ ዞን ከፈተኛ ፍ/ቤት መለሰን በዋስ እንድወጣ መፍቀዱን የተገለፀ ቢሆንም የክልል ፕሬዚዳንት ለዐ/ህጎችና ለደኞች በቀጥታ ስልክ እየደወለ እንዳትፈቱት እንደምላቸውና እምቢ ካሉ ስራቸውን እንደሚ

 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአንዳንድ አከባቢዎች የሚነሱ ግጭቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ በቅንጀት የክልሉ መንግሥትና ሰላምና ፀጥታ እየሰራ ብሆንም የክልሉ ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር   ረጅም እጅ...
17/12/2024


በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአንዳንድ አከባቢዎች የሚነሱ ግጭቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ በቅንጀት የክልሉ መንግሥትና ሰላምና ፀጥታ እየሰራ ብሆንም የክልሉ ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ረጅም እጅ በማስገባት ህዝብ እንዳይረጋጋ እያደረገ ነው።
የግድ ነው አድርጉ🙏
ኮሚሽነር በትላንትናው ዕለት ወደ ቆሴና አካባቢ በድብቅ በመምጣት በቀጣናው ላይ አንፃራዊ ሰላም ብልጭ ስል ሰላም እንዳይሆን ከምፈልገው ሀይል ጋር በመሆን ልዩ ሀይልን እና የዞኑ ፖሊስን በልዩነት መድረክ ይዞው የማይደረግ አስነዋሪ የሆኑ ተግባርን እንድፈፅሙ ትዕዛዝ በግዴታ ሰጥቷል።

ኮሚሽነሩ ትዕዛዝ ስሰጡና ስናገሩ ዞር ብሎ ምንም ልብ ያላሉ እና ከላይ ተሸክሞ የመጣ አጀንዳ እንዳለ የምገልፅ እይታ ተሞልተው ከአንድ ክልል አመራር የማይጠበቅ ንግግር አድርገው ከአድማ በታኞች ጋር ሳይግባባ በጭቅጭቅ ተመልሷል። የሆነ ሁሉ ይሁንና ትዕዛዝ ዛሬ እየተፈፀመ እንደሆነ ንፁሃን ታፍነው እየተወሰደ በተለይም #ሴቶች ታፍነው እየተውሰደና የምወሰድበት እንደማይታወቅ ከቦታው መረጃ ደርሰዋል።

ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ በአንዳንድ አከባቢዎች የሚስተዋሉ የፀጥታ እክልን እንደፈጅ እንደህ አስነዋሪ ተግባር ተፈፅሞ አይታወቅም። የአካባቢውን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ የክልሉ መንግስት ግብረሀይል አቋቁሞና ችግሩን ተለይቶ የሥራ አቅጣጫ ብያዝም ተግባሩ እንድፈጽም የማይፈልጉ ሀይሎች እንዳሉ መንግስት ልብ ልሎ ይገባል።

በተለይም በቆሴ አካባቢ በጉራጌና ሀዲያ አዋሳኝ አከባቢዎች እንዲሁም በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር አከባቢ በተፈጠረ ግጭት በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት እንደረስ ሁለም አካባቢ ሰላም እንዳይሆን የማይፈልገው ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ ከአቶ እርስቱ ይርዳው የወሰደውን ተልዕኮ ስሆን የተልዕኮው ዋና አጀንዳ የጉራጌ ክልልነት እናስፈጽማለን የምል እንደሆነ ልብ እንድትሉ እንገልፃለን።

በክልሉ በእነዚህ አከባቢዎች በተፈጠረው ግጭት ለመፍታት ከማህበረሰቡ ጋር በምደረገው ውይይት እና የተቀናጀ መሠረታዊ የሆነ ተግባቦት ለማድረግ አንፃራዊ ሰላም ለመፍጠር ዋና ካታሪ ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ እና ርስቱ ይርዳው እንደሆነ ህዝብና መንግስት እንድያወቅ እንላለን።

የግል የፖለቲካ ፍላጎታቸውን ለማስረጽ በክልሉ ዘላቂነት ያለውን ሰላም እንዳይሰፍን ከተለያዩ ባለሀብቶች ጋር እየተሞዳሞደ እና ከባለሀብቶችና ከግለሰቦች ጉቦ ብር እየበላ በተለይም ከቶ መላኩ ሹፌርና ከአቶ ፈቀደ እራማቶ ብዙ ግዙ አድስ አበበ በአካል የእየደ ተደጋጋሚ ሙስና እየተቀበለ ስሆን አካባቢው ሰላም ከሆነ የምያገኘው ጥቅም ስለምጎልበት ጦርነት ያውቃል።

ይህንን አስነዋሪ ተግባር የምፈፅም አመራር ለክልላችን የማይመጥን ስለሆነ የማይደግም እንድወድና ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ ወደ ቀጣና የማይመጣና ጦርነት የሚያውጅ ከሆነ ሰላም ይሰፍናል።




አሻጋሪ ነህ ያልነው ከትውልድ ወደ ትውልድ ተሻጋሪ ስራዎችን ስለሚሰራ ነውስራዎቹ ነገን ያማከለ መሆኑን አብዲ ቦሩ ምስክር ነው። አሻግሮ ማየት የሚችልን የሚሻገር ስራን፣ ዛሬም ነገም እንደአዲ...
14/12/2024

አሻጋሪ ነህ ያልነው ከትውልድ ወደ ትውልድ ተሻጋሪ ስራዎችን ስለሚሰራ ነው

ስራዎቹ ነገን ያማከለ መሆኑን አብዲ ቦሩ ምስክር ነው። አሻግሮ ማየት የሚችልን የሚሻገር ስራን፣ ዛሬም ነገም እንደአዲስ የሚጠቅም ስራን ይሰራል። የዛሬ ትውልድ ብቻ አይደለም በስራዎቹ የነገም ትውልድ ይሻገርበታል። አሻጋሪነት በተግባር ማለት ትውልድን ከትውልድ፣ ዛሬን ከነገ የሚያስተሳስር ስራን ሰርቶ ማለፍ መቻል ነው። የምንፈልገው ብልፅግና ሁለንተናዊ እንዲሆን ትውልድን ማስተማር፣ ማብቃት፣ ማዘመን ግድ ነው። እኔደአብዲ ቦሩ አይነት ብዙ ያስፈልገናል። በጠራ አላማ የጠራ ትውልድን ለመፍጠር የሚጀረገው ትግል ይቀጥላል። ዛሬ ተንከባክበን ያሳደግናቸው ልጆች ነገ ሃገርን ይንከባከባሉ፣ ለማህበረሰቡም የሃላፊነታቸውን ይወጣሉ። የነገዎቹን ፍሬዎች በዚህ መልኩ እያሳደግን ሃገራችንንም እናሳድጋለን።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Politics posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Central Politics:

Share

Category