Nahoo Television

Nahoo Television Nahoo TV Nahoo TV is a private Infotainment TV station with a motto of promoting Ethiopian Culture.

Nahoo Tv is a privately held media company established in 2016 in Ethipia with a motto of promoting Ethiopian Culture, History & general well being of the society. Main Office
Rosetta Bldg. 2nd Floor # 14/2010, Addis Ababa, Ethiopia

የአፍሪካ ልማት ባንክ “በኢትዮጵያ ያሉ ሰራተኞቼ ድብደባና እስር ተፈፅሞባቸዋል” ሲል ወቀሳ አቀረበ፡፡የአፍሪካ ልማት ባንክ ባወጣው መግለጫ በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵ...
17/11/2023

የአፍሪካ ልማት ባንክ “በኢትዮጵያ ያሉ ሰራተኞቼ ድብደባና እስር ተፈፅሞባቸዋል” ሲል ወቀሳ አቀረበ፡፡
የአፍሪካ ልማት ባንክ ባወጣው መግለጫ በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ድብደባ፣ እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው አስታውቋል።
ባንኩ እንዳለው ሁለት ሰራተኞቹ የቬና የዲልሎማሲ ጥበቃ ስምምነትን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሮ አስተናጋጅ ሀገራት ስምምነትን የጣሰ ክስተት በኢትዮጵያ መፈጸሙንም አስታውቋል።
የተፈጠረውን ክስተት ለኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ ማመልከቱን የሚገልጸው የአፍሪካ ልማት ባንክ ጉዳዩ መፈጸም እንደሌለበት፣ ህግ መጣሱን እና ጉዳዩ ተመርምሮ እርምጃ እንደሚወሰድ በኢትዮጵያ በኩል ቃል ተገብቶልኛልም ብሏል።
ባንኩ አክሎም ከኢትዮጵያ ጋር መልካም የሚባል ግንኙነት እንዳለው ገልጾ የተፈጠረው ክስተትም ግንኙነቱን እንደማያበላሽ ማስታወቁን አል አይን ኒውስ አስነብቧል።
የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በበኩላቸው "ከአፍሪካ ልማት ባንክ ኢትዮጵያ ቢሮ ጋር የተፈጠረው ክስተት ባንኩ ቢሮውን እንዲዘጋ አላደረገውም፣ የሁለቱ ግንኙነትም አልተቋረጠም" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
ይሁንና የኢትዮጵያ ጸጥታ ሀይሎች በአፍሪካ ልማት ባንክ የአዲስ አበባ ቢሮ ሰራተኞች ላይ ለምን ድብደባ እንደፈጸሙ ከሁለቱም ወገኖች በኩል በይፋ የተገለጸ ነገር የለም። የአፍሪካ ልማት ባንክ በፈረንጆቹ 1963 በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም በተካሄደ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ተቋሙ እንዲመሰረት ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት የተቋቋመ አፍሪካዊ ተቋም ነው።
ባንኩ በአዲስ አበባ ያለውን የኢትዮጵያ ቅርንጫፉን በ1967 የከፈተ ሲሆን ኢትዮጵያ ለምታከናውናቸው የመሰረተ ልማት፣ ግብርና እና ሌሎች የልማት ስራዎች የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል።
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

የዓለም የምግብ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ አሠራር ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም የምግብ ፕሮግራም (ዳብልዩ.ኤፍ.ፒ.) ኢትዮጵያ ውስጥ አቋርጦት የነበረ...
17/11/2023

የዓለም የምግብ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ አሠራር ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም የምግብ ፕሮግራም (ዳብልዩ.ኤፍ.ፒ.) ኢትዮጵያ ውስጥ አቋርጦት የነበረውን የምግብ እደላ በተሻሻለ አሠራር ሊጀምር መሆኑን አስታውቋል።
እርዳታው “እየተሰረቀ ከታለመበት ዓላማ ውጭ ይውላል” በሚል ካለፈው ሰኔ አንስቶ ተቋርጦበት የቆየውን 3 ሚሊየን 2 መቶ ሺህ ተረጂ መድረስ የሚያስችል እርምጃ እንደሆነ ድርጅቱ አመልክቷል።
የኢትዮጵያ መርኃግብሩን ለመጀመር የወሰነው ግልፅ፣ በማስረጃ የተደገፈና በገለልተኛ አሠራር ላይ ያተኮረ የተሟላ ግምገማውን ካጠናቀቀ በኋላ መሆኑን ዳብልዩ.ኤፍ.ፒ. ጨምሮ ገልጧል።
አዲሱ አካሄድ “በስፋት የተሞከረና ጠንካራ የቁጥጥር አሠራር የተከተለ ይሆናል” ሲል ድርጅቱ በትላንትናው እለት ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ አመልክቷል።
እርዳታው በእጅጉ የሚያስፈልጋቸውን ወገኖችና የቤተሰቦቻቸውን አባላት ግልፅ በሆነ መመዘኛ ለመለየት ከያካባቢው ማኅበረሰቦች ጋር በቅርበት መሥራት፤ ምግብ ከሚከማችባቸው መጋዘኖች እደላው ወደሚካሄድባቸው አካባቢዎች በሚጓጓዝበት ወቅት የተጠናከረ ክትትል እንደሚደረግም መግለጫው ይዘረዝራል።
በተጨማሪም የምግብ ዕርዳታ ከታለመለት ዓላማ ውጭ እንዳይውል ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግና ውሎ በሚገኝበትም ወቅት በፍጥነት ሪፖርት ማቅረብ የሚያስችሉ ዘዴዎችን ተግባራዊ እንደሚያደርግ መግለጫው አስረድቷል።
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

የመንግሥት እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ድርድር እንደቀጠለ መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡መንግሥት “ኦነግ ሸኔ” እያለ ከሚጠራው እና (እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሚለው ታጣቂ ...
17/11/2023

የመንግሥት እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ድርድር እንደቀጠለ መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
መንግሥት “ኦነግ ሸኔ” እያለ ከሚጠራው እና (እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሚለው ታጣቂ ቡድን) ጋር ሁለተኛው ዙር የሰላም ድርድር እየተካሄደ መሆኑን ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋዊ ማረጋገጫ ሰጥቷል።
መንግሥት ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ ከሚጠራው ታጣቂ የሚያደርገው ድርድር እንደቀጠለ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በትላንትናው እለት አስታውቋል፡፡
ከመንግሥት ጋር ለአመታት የትጥቅ ግጭት ውስጥ የሚገኘውና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪ ብሎ የፈረጀው ኦነግ ሸኔ የተባለው ታጣቂ ቡድን ከ6 ወራት በፊት ከመንግሥት ጋር በታንዛኒያ አድርጎት የነበረው የድርድር ጥረት ያለ ሁነኛ ስምምነት መጠናቀቁ ተገልጾ ቆይቷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ስለ ጉዳዩ ዝርዝር ነገር ባይገልፁም፤ የመንግሥት እና የቡድኑ ሁለተኛ ዙር ድርድር በታንዛኒያ እየቀጠለ መሆኑን ተናግረዋል። አንባሳደር መለስ አለም "የመጀመርያው ዙር ከሸኔ ጋር የተደረገ ውይይት ነበር። ሁለተኛ ዙር አሁንም ቀጥሏል። እየተካሄደ ነው የሚገኘው" ብለዋል።
የታጣቂ ቡድኑ አዛዥ ማሮ ድሪባ እና ምክትላቸው ገመቹ አቦዬ በታንዛኒያው “የሰላም ውይይት” በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ ኦነግ አረጋግጧል። ታጣቂ ቡድኑ በይፋዊ መግለጫ ድርድሩን በተመለከተ ምንም ሳይባል የቆየው ጃል መሮ ድሪባ እና ጃል ገመቹ አቦዬ ደህንነታቸው ተጠብቆ ወደ ድርድሩ ስፍራ እንዲደርሱ በማሰብ መሆኑን አሳውቋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ ስለ ንግግሩ ዝርዝር ነገር ከመናገር ግን ተቆጥበዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

በኢትዮጵያ የሳንባ ምች በሽታ ትኩረት ያልተሰጠው በመሆኑ ገዳይነቱ በከፈተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑ ተገለፀ።የሳንባ ምች (ኒሞኒያ) በሽታ በተለይ ከ1እስከ 5 የእድሜ ክልል ያሉ ህፃናትን ገዳይ...
16/11/2023

በኢትዮጵያ የሳንባ ምች በሽታ ትኩረት ያልተሰጠው በመሆኑ ገዳይነቱ በከፈተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑ ተገለፀ።
የሳንባ ምች (ኒሞኒያ) በሽታ በተለይ ከ1እስከ 5 የእድሜ ክልል ያሉ ህፃናትን ገዳይ ከሆኑት በሽታዎች መካከል ቀዳሚ መሆኑም ተጠቁሟል።
በዚህም በኢትዮጵያ የአመቱ 36ሺ ህፃናት በሳንባ ምች በሽታ ህይዎታቸው እንደሚያልፍ የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
ይህም ማለት በየቀኑ 1መቶ ህፃናት በዚሁ የሳንባ ምች በሽታ ህይዎታቸውን እንደሚያጡ መረጃው ልብ ይሏል፡።
በተለይ የተሻለ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት እድል በሌላቸው እና ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ባላቸው አካባቢዎች የሚወለዱ ህፃናት ለበሽታው ተጋላጭ መሆናቸውም ተመላክቷል።
በዚህም ከሃገሪቱ አጠቃላይ የሞት ምጣኔ ውስጥ የሳምባ ምች በሽታ 17 በመቶ እንደሚይዝ ነው የተነገረው።
በመሆኑም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ "የሳንባ ምች በሽታን በመከላከል እና በማከም የህፃናትን ህይዎት እንታደግ" በሚል መሪ ቃል የአለም የሳንባ ምች ቀንን በማክበር ላይ ይገኛል።
በዚህም በተለይ ሙሉ በሙሉ መከላከል እና ማከም እንዲሁም ገዳይነቱን መከላከል በሚቻልባቸው ጉዳዪች ዙሪያ ከክልል ጤና ቢሮዎች ጋር ውይይት በማካሄዳ ላይ እንደሚገኝ ናሁ ቴሌቭዥን አረጋግጧል።
የሳንባ በሽታን ለመከላከል አለም አቀፍ አጋዥ አካላት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርብዋል።
ዘገባው የባልደረባችን ሀብታም አያሌው ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

ከኦነግ ሸኔ ታጣቂ ቡድን ጋር እየተካሄደ የሚገኘው ድርድር ግልፅነት የጎደለውና፤ ዘላቂ ሰላምን የማያመጣ መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለፁ፡፡መንግስት ከኦነግ ሸኔ ጋር በታንዛኒያ ዳሬሰላም እያ...
16/11/2023

ከኦነግ ሸኔ ታጣቂ ቡድን ጋር እየተካሄደ የሚገኘው ድርድር ግልፅነት የጎደለውና፤ ዘላቂ ሰላምን የማያመጣ መሆኑን የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለፁ፡፡
መንግስት ከኦነግ ሸኔ ጋር በታንዛኒያ ዳሬሰላም እያካሄደው ያለው ድርድር ግልጸኝነት የጎደለው መሆኑ ናሁ ቴሌቬዥን ያነጋገራቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ገልፀዋል፡፡
ፓርቲዎቹ ‹‹ከህዝብ በስተጀርባ ግልፀኝነት በጎደለው መልኩ የሚደረጉ ድርድሮችና ውይይቶች በዘላቂነት የሀገሪቱን የፖለቲካ ችግር ሊፈታው አይችልም›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) አመራር መጋቢ ብሉይ አብርሃም ሀይማኖት ከናሁ ቴሌቬዥን ጋር በስልክ ባደረጉት ቆይታ መንግስት ከኦነግ ሸኔ ጋር እያደረገው ያለው ድርድር “ግልፅነት የጎደለው ድርጊት ነው” ብለዋል፡፡
የመከላከያ ሰራዊት የሁላችን እና ገለልተኛ ተቋም እንዲሆን ነው የሚፈለገው ያሉት አብርሃም ሆነም ግን ፖለቲካ በሚሻ ድርድር ውስጥ መከላከያ ሰራዊትን አስገብቶ “በጀኔራሎች ደረጃ እተደረገ ያለው ድርድር ተገቢ አይደልም” ሲሉ ገልጸዋል፡፡
የእናት ፓርቲ ብሄራዊ ስራ አስፈጻሚ አባል እና የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ዳዊት ዘሪሁን በበኩላቸው ከኦነግ ጋር እተደረገ ያለው ድርድር፤ በመሰረቱ ከአምስት አመት በፊት ኦነግ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ ግልፅ ያልተደረገ እንደነበር አስታውሰው አሁን ደግሞ በተመሳሳይ ለህዝብ ግልፅ ሳያደርግ ከመጋረጃ ጀርባ እተደረገ ያለው የጎራ ድርድር በቂ ውጤት እንደማያመጣ ገልፀዋል፡፡
በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ሁሉን ያካተተ እና ግልፅነት የሰፈነበት ውይይት እንደሚያስፈልግም የፖለቲካ ፓርቲዎቹ አመራሮች ለናሁ ቴሌቭዥን ተናግረዋ፡፡ አከራካሪ በሚባሉ የወሰን ይገባኛል አለመግባባቶችም ቢሆን በህገ-መንግስት ማዕቀፍ ሊፈቱ እንደማይችሉ ገልፀዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

ሁሉን አቀፍ ሀቀኛ የፖለቲካ ውይይት እና ብሔራዊ እርቅ እንዲደረግ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህብረት ጠየቀ። የፓርቲዎቹ ህብረት አገሪቱ አሁን ለገባችበት ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ መ...
16/11/2023

ሁሉን አቀፍ ሀቀኛ የፖለቲካ ውይይት እና ብሔራዊ እርቅ እንዲደረግ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህብረት ጠየቀ።
የፓርቲዎቹ ህብረት አገሪቱ አሁን ለገባችበት ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ መፍትሄው በትጥቅና በሰላማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱትን ኃይሎች ማግባባት ላይ በማድረስ መሆኑን ገልጧል።
16 የሚሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባል የሆኑበት የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅቶች ህብረት (ኮከስ) ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት “በተወሳሰበ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ውስጥ ትገኛለች” ያለ ሲሆን፤ ዘላቂና እውነተኛ መፍትሄውም የሚመጣው ሁሉንም ባሳተፈ ፖለቲካዊ ውይይት መሆን ይገባዋል ሲል ጠይቋል፡፡
ከኮከሱ አባላት አንዱ የሆነው የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ ፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ሙላቱ ገመቹ ከዚሁ ጋር አያይዘው በሰጡት አስተያየት፤ ፓርቲያቸው በተለይም በኦሮሚያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን አጥብቆ ይሻል ብለዋል፡፡ አሁን አገር የሚስተዳድረው መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር የሚያደርገውን ድርድርም በጉጉት የምንጠብቀው ነው ብለውታል፡፡
ችግሮች ሲከሰቱ በተናጠል ከታጣቂዎች ጋር ከሚደረግ ውይይት በተጨማሪ በሰላማዊ መንገድ ከሚታገሉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ጋር ውይይት መደረግ አለበትም ብሏል፡፡
ሰላማዊ ድርጅቶችን ገፍቶ ከታጣቂዎች ጋር ብቻ ለድርድር በር መክፈት ጥሩ መልእክት አያስተላልፍም፡፡ በመሆኑም ሀቀኛና ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጣ የሚችል ድርድር እና የፖለቲካ ውይይት ማድረግ ይገባል” ነው ያሉት፡፡ የተቃዋሚ ፓለቲካ ድርጅቶቹ ኮከስ ባቀረበው ምክረ ሃሳቡም መንግስትን የሚመራው ገዢው ፓርቲ ለሀቀኛ እና አካታች ውይይት እራሱን እንዲያዘጋጅ፣ አማራ እና ኦሮሚያ ክልልን ጨምሮ በአገሪቱ በተለያዩ አከባቢዎች የተስፋፋው ግጭት ሰላማዊ እልባት እንዲያገኝ ስል ጥሪውን አቅርቧልም፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የታክሲ አገልግሎት ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ መቋረጡን እንዲሁም ህዳር 4 ቀን 2016 ዓ.ም ከሰአት በኃላ በከፊል መጀመሩን የአከባቢው ምንጮችን ጠቅ...
16/11/2023

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የታክሲ አገልግሎት ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ መቋረጡን እንዲሁም ህዳር 4 ቀን 2016 ዓ.ም ከሰአት በኃላ በከፊል መጀመሩን የአከባቢው ምንጮችን ጠቅሶ ናሁ ቴሌቭዥን መዘገቡ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ ከህዳር 5 ቀን ጀምሮ አገልግሎቱ መልሶ በመቋረጡ ለከፍተኛ እንግልት መዳረጋቸውን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
ስለ አገልግሎቱ መቋረጥ ህዳር 05 ቀን 2016 ዓ.ም አምስት የመቐለ የታክሲ ማህበራት በጋራ ለመንግስት ያቀረቡት የፅሁፍ አቤቱታ እንደሚያመለክተው ድርጊቱ አግባብነት የሌለው ነው።
ስራ የማቆም አድማው “ከእወቅናችን ውጭ የተደረገ ኢ-ህጋዊ ተግባር ነው” ያለው ማህበሩ፤ ቢሆንም ግን ያለውን የኑሮና የመለዋወጫ እቃ ውድነትና ግምት ውስጥ ያስገባ የታሪፍ ማስተካከያ ተደርጎ አገልግሎቱ እንዲቀጥል እንጠይቃለን" ብሏል።
የክልሉ መንግስት በትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ በኩል ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ፤ “በተቀመጠው የታሪፍ መመሪያ መሰረት ትርፍ መጫንና ያልተፈቀደ ታሪፍ ማስከፈል ህጋዊ አይደለም ፍፁም የተከለከለ ነው ፤ ስለዚህ ይህንን በመቀበል አገልግሎቱ መቀጠል ይገባል” ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
ቢሮው አያይዞ በአገልግሎት የማቆም አድማው የተሳተፈ የታክሲ ባለቤትና አሽከርካሪ እያንዳንዱ 1 ሺህ 200 ብር እየተቀጣ እንዲመለስ ያሳሰበ ሲሆን የተቀመጠው ቅጣት የማይተገብሩ ታክሲዎች የሰሌዳ ቁጥራቸው እየተፈታ አገልግሎት ከመስጠት እየተከለከሉ እንደሆነ የከተማዋ ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።
የትግራይ የትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ፤ የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች አገልግሎት የማቋረጥና አድማ የመምታት ደርጊቱ ችላ ተብሎ የማይታለፍ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

ለሐድያ ዞን መምህራን ችግር መንግሥት አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥቄ ቀረበ፡፡በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሐዲያ ዞን፣ መምህራን ለገጠማቸው ችግር፣ መንግሥት አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጥ፣ የኢት...
16/11/2023

ለሐድያ ዞን መምህራን ችግር መንግሥት አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥቄ ቀረበ፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሐዲያ ዞን፣ መምህራን ለገጠማቸው ችግር፣ መንግሥት አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጥ፣ የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ጥያቄ አቅርቧል፡፡
የማኅበሩ ፕሬዚዳንት ዶር. ዮሐንስ በንቲ፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ ለወራት ደመወዝ ያልተከፈላቸው የዞኑ መምህራን አቤቱታ ማቅረባቸውንና ማኅበሩም አቤቱታቸውን ተቀብሎ፣ ለትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንዳቀረበ ተናግረዋል፡፡
የደመወዝ መቋረጥ፣ የመምህራኑን ሕይወት ከማናጋት አልፎ፣ የትምህርት ሥርዐቱን ይጎዳዋል፤ ያሉት ዶር. ዮሐንስ፣ ጉዳዩ አስቸኳይ መፍትሔ እንደሚያሻው አሳስበዋል፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን እንዲሁም በከምባታ ዞን “ደሞዝ ተቋርጦብናል” በሚል ምክንያት መምህራን እንዲሁም የጤና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ መምታታቸውን ናሁ ቴሌቭዥን ከዚህ ቀደም መዘገቡ አይዘነጋም፡፡
በሀዲያ ዞን መምህራን በመቱት የስራ ማቆም አድማ ምክንያት በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከትምህርት መራቃቸውን መዘገባችንም ይታወሳል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳን ሪፐብሊክ ሉዓላዊ ም/ቤት ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልቡርሃን ጋር ተወያዩ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ የሱዳን ሪፐብሊክ ሉአላዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳን...
15/11/2023

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳን ሪፐብሊክ ሉዓላዊ ም/ቤት ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልቡርሃን ጋር ተወያዩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ የሱዳን ሪፐብሊክ ሉአላዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃንን እና ልዑካን ቡድናቸውን በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በመገኘት ተቀብለዋል::
በመቀጠል ሁለቱ መሪዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የጋራ በሆኑ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም የጋራ በሆኑ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡
የሱዳን ሪፐብሊክ ሉዓላዊ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን እና ልዑካን ቡድናቸው በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡
ልዑካኑ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምታቀርበውን የምግብ እርዳታ ልትቀጥል መሆኑን አስታወቀች።በስርቆት ምክንያት ቆሞ የነበረው የአሜሪካ የምግብ እርዳታ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ሊቀጥል መሆኑን አሜሪካ አስታውቃ...
15/11/2023

አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምታቀርበውን የምግብ እርዳታ ልትቀጥል መሆኑን አስታወቀች።
በስርቆት ምክንያት ቆሞ የነበረው የአሜሪካ የምግብ እርዳታ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ሊቀጥል መሆኑን አሜሪካ አስታውቃለች። በአመቱ መጀመሪያ ላይ እርዳታው ከቆመ በኃላ አጠቃላይ ማሻሻያዎችን በማድረግ እርዳታው እንዲቀጥል ተደርጓል።
በሃገሪቱ ውስጥ ተከስቶ በነበረው ጦርነት እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ በአስርት አመታት ውስጥ ባስከተለው አስከፊ ድርቅ ምክንያት የምግብ ችግር በቀጠናው ተባብሶ ቀጥሏል።
ይሁን እንጂ ዩኤስኤአይዲ ለኢትዮጵያ የሚሰጠው የምግብ ዕርዳታ እየተሰረቀ እርዳታውን ለሚሹ ዜጎች ሳይሆን ለሌላ አላማ እየዋለ መሆኑን በመግለፅ እርዳታውን ማቋረጡ ይታወሳል።
የምግብ እርዳታው ክፍት በነበረ ጊዜ በርካታ የሃገሪቱ ክፍሎችን የጠቀመ ሰብአዊ ድርጊት ቢሆንም፤ “በትግራይ ክልል የነበሩ ዜጎችን አላካተተም” ሲል በፌዴራል መንግስትና በክልሉ ባለስልጣናት መካከል የነበረውን ግጭት ተጠያቂ አድርጓል።
ዩኤስአይዲ ትላንት ባወጣው መግለጫ ዋሽንግተን ባለፉት ወራት በኢትዮጵያ መልካም የተባለ ዲፕሎማሲያዊ ተሳትፎ እያያደረገች መቆየቷን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ መንግስትና በሰብአዊ አጋሮቻቸው መዋቅሩ ላይ ማሻሻያ በማድረግ እርዳታውን በመላ ሃገሪቱ እንደገና ለማስጀመር ውሳኔ ላይ መደረሱን ማሳወቁን ፍራንስ 24 ዘግቧል።
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

በአማራ ክልል በቀጠለው ግጭት ሳቢያ ነዋሪዎች በማህበራዊና ኢኮኖሚ ቀዉስ ውስጥ መሆናቸውን ገለፁ፡፡ባለፉት ወራት በመከላከያ ሰራዊትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከፍተኛ ውጊያ በነበረባቸው የአማራ...
15/11/2023

በአማራ ክልል በቀጠለው ግጭት ሳቢያ ነዋሪዎች በማህበራዊና ኢኮኖሚ ቀዉስ ውስጥ መሆናቸውን ገለፁ፡፡
ባለፉት ወራት በመከላከያ ሰራዊትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከፍተኛ ውጊያ በነበረባቸው የአማራ ክልል የምዕራብ ጎጃምና የምስራቅ ጎጃም አንዳንድ ከተሞች ነዋሪዎች ለከፍተኛ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እየተዳረጉ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
በተለይ መንገዶች በተሟላ ሁኔታ ባለመከፈታቸው በቂ የምግብ እህል ወደ ከተሞቹ መግባት ባለመቻሉ በርካቶች በእጅጉ እየተቸገሩ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በምዕራብ ጎጃም ዞን የደንበጫ ከተማ ነዋሪዎችም አርሶ አደሩ ባለበት የመንገድ እጥረትና የሰላም ስጋት ምርት ወደ ገበያ እያመጣ አለመሆኑን አስታውቀዋል፡፡
በአካባቢው የሚመረቱ ምርቶችንም ወደ ሌሎች አካባቢዎች ማድረስ ባለመቻሉ ህብረተሰቡ ለድህነት እየተጋለጠ መሆኑን ነዋሪዎችን ጠቅሶ የጀርመን ድምፅ ዘግቧል፡፡
በምዕራብ ጎጃም ዞን በቡሬ ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ የኑሮ ውድነቱ በጣም ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን አመልክተዋል፡፡ “የከተማው ነዋሪ ራሱ ተፈናቃይ ሆኗል” ሲሉ ያለውን ችግር አስረድተዋል፡፡
በደብረማርቆስ ከተማም ቢሆን፤ መንገዶች እንደልብ ባለመከፈታቸው ከፍተኛ ህገወጥ የትራንስፖርት ክፍያ እንደሚጠየቁ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ቀደም ሲል 50 ብር ይጠይቅ የነበረ መንገድ እስከ 300 ብር መድረሱንም አመላክተዋል፡፡ በምዕራብ ጎጃም ዞን የፈረስ ቤት ነዋሪዎችም በበኩላቸው ምርት እንደ ልብ ገበያ ወጥቶ መሸጥ ባለመቻሉ በአካባቢው የርሀብ አደጋ ማንዣበቡን በስጋት ማመላከታቸውን ዘገባው አክሏል፡፡ የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አተ ደሳለኝ ጣሰው ሰሞኑን ለጋዜጠኞች እንደነገሩት አብዛኛው የአማራ ክልል ወደ ሰላም መመለሱንና፣ ስርቆትና ዝርፊያን ደግሞ በጋራ እንስወግደው ሲሉ ጥሪ አቅርበው ነበር፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

በኢትዮጵያ 45 ሚሊየን ህፃናት በድህነት እንደመሚሰቃዩ ጥናት አመላከተ፡፡በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚኖሩ ህፃናት መካከል 75 በመቶ ወይንም 45 ሚሊየን ህፃናት በድህነት ውስጥ እንደሚኖሩ እና መሰረ...
15/11/2023

በኢትዮጵያ 45 ሚሊየን ህፃናት በድህነት እንደመሚሰቃዩ ጥናት አመላከተ፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚኖሩ ህፃናት መካከል 75 በመቶ ወይንም 45 ሚሊየን ህፃናት በድህነት ውስጥ እንደሚኖሩ እና መሰረታዊ ፍላጎታቸው እንዳልተሟላላቸው አፍሪካን ቻይልድ ፖሊሲ ፎረም አስታውቋል።
በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ሁኔታ ህፃናት ለድህነት እና ለረሃብ እንደሚጋለጡ የአፍሪካ ቻይልድ ፖሊሲ ፎረም የፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር አቶ የኋላእሸት መኮንን መናገራቸውን ናሁ ቴሌቭዥን ሰምቷል።
በኢትዮጲያ 45 ሚሊየን ህፃናት በድህነት እንደሚማቅቁ ሲገለፅ ድህነት እና የከፋ ረሀብ የፖለቲካ ፍጆታ እንደሆነ እና ተጠያቂነት የጎደለው መንግስታዊ ማዕቀፍ እና ህፃናቱን ለመታደግ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ዝቅተኛነት የአፍሪካ መንግስታትን ከተወቃሽነት እንደማያድንም ተመላክቷል፡፡
በአፍሪካ የልጆችን ድህነት እና ርሀብ ከማስቀረት አንፃር ብዙ ስራ እንደሚቀር እና የአብዛኞቹ ህፃናት መሰረታዊ ፍላጎታቸው እንደማይሟላላቸው ተመላክቷል። በዚህ ችግር ተጋላጭ የሚሆኑት በገጠር አካባቢ የሚኖሩ እና በሰላም እጦት ምክንያት ከቦታ ቦታ የሚፈናቀሉ ህፃናት እንደሆኑም ፎረሙ ጠቁሟል።
ይህ የህፃናት ረሀብ በአፍሪካ 54 በመቶ ወይንም ከ350 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ህፃናት እንዳሉም እና ከነዚህም መካከል 60 በመቶ የሚሆኑት በከፋ ድህነት ውስጥ እንደሚገኙም ተገልጧል። እንዲሁም በአፍሪካ ውስጥ 110 ሚሊዮን የሚሆኑ ህፃናት በድህነት የመውደቅ አደጋ ላይ መሆናቸውን እና ይህ ጉዳይ አስቸኳይ መፍትሄ የሚሻ መሆኑንም በማሳሰቢያነት ተነስቷል።
ህፃናቱ በሚያጋጥማቸው የከፋ ድህነት ወይንም ረሀብ ምክንያት የአዕምሮ ዕድገት ውስንነት እና የመቀንጨር አደጋ እንደሚያጋጥማቸውም የፎረሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ የኋላእሸት ገልፀዋል።
ዘገባው የባልደረባችን ተስፋሚካኤል ዘውዱ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

የበኒ ሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ለትምሕርት ቤቶች ማሰሪያ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ሊሰበስብ መሆኑን አስታወቀ፡፡በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በግጭትና ሁከት የወደሙና የተጎዱ ትምህርት ቤቶችን ለመጠገን ከ...
15/11/2023

የበኒ ሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ለትምሕርት ቤቶች ማሰሪያ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ሊሰበስብ መሆኑን አስታወቀ፡፡
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በግጭትና ሁከት የወደሙና የተጎዱ ትምህርት ቤቶችን ለመጠገን ከ3 ቢሊየን ብር በላይ ለመሰብሰብ ማቀዱን የክልሉ መንግስት አስታውቋል፡፡ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን የሚመራ የሀብት ማሰባሰብ ኮሚቴ መቋቋሙም ተገልጸዋል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ምትኩ ዘነበ እንደገለፁት ገንዘቡን በክልሉ ከሚገኙ ባለሀብቶች፣ የመንግስትና የግል ተቋማት ለመሰብሰብ ታቅዷል፡፡
በክልሉ 258 የሚሆኑ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና 29 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ ባጠቃላይ ለትምህርት ቤት መልሶ ግንባታና ጥገና 7 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ከዚህ በፊት በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በተደረገው ጥናት መረጋገጡ ተጠቁሟል፡፡
ባለፉት ዓመታት በመተከል እና ካማሺ ዞን ውስጥ ተከስቶ በነበረው ግጭት ምክንያት ወደ 280 በላይ ትምህርት ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ምትኩ ዘነበ ተናግረዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል የተወሰኑት ሙሉ በሙሉ የወደሙ ሲሆን ሌሎች ደግሞ በከፊል ጉዳት እንደረሰባቸው ጠቁመዋል፡፡ በዚህን ዓመት ለትምህርት ቤት ጥገናና መልሶ ግንባታ የሚውሉ ከ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማሰባሰብ ስራ መጀመሩን አመልክተዋል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን ከዚህ ቀደም የትምህርት መሠረተ ልማት ለማሻሻል በተዘጋጀው መርሀ ግብር ላይ በሰጡት ማብራሪያ አብዛኛው በክልሉ ውስጥ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከደረጃ በታች እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡
የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻልና የወደሙትን ለመገንባት የፈዴራል መንግስትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እገዛ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በግጭት ምክንያት የወደሙና የተጎዱ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት 7 ብሊዩን ብር እንደሚያስፈልግም በወቅቱ ገልጸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

2ኛ ዙር የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ዛሬ መሰጠት ይጀምራል፡፡ፈተናው በ46 የፈተና ማዕከላት የሚሰጥ ሲሆን 90 ሺህ 70 አመልካቾች ፈተናውን ለውሰድ ምዝገባ ማድረጋቸውን ትምህርት...
15/11/2023

2ኛ ዙር የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ዛሬ መሰጠት ይጀምራል፡፡

ፈተናው በ46 የፈተና ማዕከላት የሚሰጥ ሲሆን 90 ሺህ 70 አመልካቾች ፈተናውን ለውሰድ ምዝገባ ማድረጋቸውን ትምህርት ሚንስቴር ትላንት ምሽት ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የ2ኛ ዙር የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ከዚህ ቀደም በመጀመሪያ ዙር የተካሄደው የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና (G*T) የአመልካቾች ምዝገባ ከጥቅምት 26 እስከ ህዳር 03 ቀን 2016 ዓ.ም መከናወኑ ይታወቃል።
በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ መሰረት፤ በሁሉም የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች በመንግስትና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው ለመማር የሚፈልጉ አመልካቾች፤ በሙሉ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና (National Graduate Admission Test) ተፈትነው ያለፉ ብቻ መሆን እንዳለባቸው አቅጣጫ መቀመጡ ይታወሳል።
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

ሰላም ለቱሪዝም ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ነገር አስፈላጊ ነው፡፡  አቶ አለማየሁ ጌታቸው  Television
14/11/2023

ሰላም ለቱሪዝም ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ነገር አስፈላጊ ነው፡፡ አቶ አለማየሁ ጌታቸው Television

ሰላም ለቱሪዝም ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ነገር አስፈላጊ ነው፡፡ አቶ አለማየሁ ጌታቸው Television ...

ህዳር 04 ፣ 2016 የምሽት ዜናዎች  Television
14/11/2023

ህዳር 04 ፣ 2016 የምሽት ዜናዎች Television

Powered by Restream https://restream.ioህዳር 04 ፣ 2016 የምሽት ዜናዎች Television For more:ቴ...

ህዳር ሲታጠን ፡የሣምንቱ ተረኛ ባለ ታሪክ  እና የዓለም ሰላም ፍንጭ፡፡ Press@Nahoo Television
14/11/2023

ህዳር ሲታጠን ፡የሣምንቱ ተረኛ ባለ ታሪክ እና የዓለም ሰላም ፍንጭ፡፡ Press@Nahoo Television

ህዳር ሲታጠን ፡የሣምንቱ ተረኛ ባለ ታሪክ እና የዓለም ሰላም ፍንጭ፡፡ Press@Nahoo Television #...

እራስን ማጥፋት ህመም ወይስ ... ቅብጠት @Nahoo Television
14/11/2023

እራስን ማጥፋት ህመም ወይስ ... ቅብጠት @Nahoo Television

እራስን ማጥፋት ህመም ወይስ ..........ቅብጠት @Nahoo Television ...

በመቐለ ከተማ የታክሲ አሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ መምታታቸው ተገለፀ፡፡በመቐሌ ከተማ የታክሲ አሽከርካሪዎች በትላንትናው እለት የሥራ ማቆም አድማ መምታታቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ...
14/11/2023

በመቐለ ከተማ የታክሲ አሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ መምታታቸው ተገለፀ፡፡
በመቐሌ ከተማ የታክሲ አሽከርካሪዎች በትላንትናው እለት የሥራ ማቆም አድማ መምታታቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
የክልሉ የታክሲዎች ማኅበር ግን፣ የታክሲ አሽከርካሪዎች የትራንስፖርት አገልግሎት ማቆማቸው "ተቀባይነት የለውም" ማለቱን ድምጸ ወያነ ዘግቧል። ማኅበሩ፣ ታክሲ አሽከርካሪዎች የትራንስፖርት አገልግሎቱን ያቆሙት ከእውቅናው ውጭ መኾኑን ገልጧል ተብሏል።
የትግራይ የትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ በበኩሉ በመቐለ የተደረገው የታክሲ አገልግሎት ማቋረጥና አድማ “ህጋዊ አይደለም” ብሏል።
ቢሮው ከመቐለ የትራንስፓርት ፅህፈት ቤትና ፓሊስ በጋራ “አካሄድኩት” ባለው ግምገማ የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች ቀድም ሲል አገልግሎት ለማቋረጥና አድማ ለመምታት የሚያበቃ ቅሬታና ጥያቄ አላቀረቡም ሲል ገልጿል።
የትግራይ የትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወ/ሪት ራሄል ሃይለ ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ፤ የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች አገልግሎት የማቋረጥና አድማ የመምታት ደርጊቱ ችላ ተብሎ የማይታለፍ ህጋዊ እርምጃና ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን በመገንዘብ ስራቸው ይቀጥሉ ዘንድ መክረዋል።
የመንግስት ምክርና ማሳሰብያ ችላ ብሎ በአድማ የሚቀጥል ባለንብረትና አሽከርካሪ ግን “ጥብቅ እርምጃ ይወሰድበታል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በመቐለ ከተማ የታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች ባደረጉት አድማ ነዋሪዎች ለእንግልት እና አላግባብ ለሆነ ወጭ መዳረጋቸውን ከአከባቢው የወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ።
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

የቀድሞ ሜቴክ የአሁኑ ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የፓወር ዘርፍ ሀላፊዎች በስርቆት ተጠርጥረው ታሰሩ፡፡በቀድሞ አጠራሩ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ይባል የነበረ...
14/11/2023

የቀድሞ ሜቴክ የአሁኑ ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የፓወር ዘርፍ ሀላፊዎች በስርቆት ተጠርጥረው ታሰሩ፡፡
በቀድሞ አጠራሩ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ይባል የነበረው እና በኢትዮጵያ የፖሊቲካ ለውጥ ከተደረገ በሁዋላ ወታደራዊ ምርቶች በመተው እንደ አዲስ በተዋቀረው ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ስር ያለው የፓወር ኢኪውፕመንት ማምረቻ ፋብሪካ ስምንት አመራሮች ከብረት ስርቆት ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰምቷል።
በቁጥጥር ስር የዋሉት የፋብሪካው አመራሮች አንዱአለም ለገሰ የፓወር ኢኪውፕመንት ማምረቻ ስራ አስኪያጅ፣ ወ/ሮ አልማዝ ብርሀኑ የፋብሪካው የሎጂስቲክስ ሀላፊ፣ መብርሂት ተስፋዬ የፋብሪካው ንብረት አስተዳደር፣ አሚኑ መሀመድ የፋብሪካው ጥበቃ ሀላፊ፣ እንዲሁም ይበልጣል ተረፈ፣ ብርሀኑ ስዩም እና ፍቃዱ ማሞ የተባሉ አመራሮች መሆናቸውን ዋዜማ የበይነ መረብ መገኛኛ አውታር አስነብቧል።
የድርጅቱ ሌሎች ሀላፊዎች ሁሉም አመራሮች ከብረት ስርቆት ጋር በተያያዘ ከመታሰራቸው ውጭ ጉዳዩ በፖሊስ ስለተያዘ በሚል ምክንያት ዝርዝሩን ከመጥቀስ ተቆጥበዋል። በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የፓወር ኢኪውፕመንት ማምረቻ ፋብሪካ አመራሮች የታሰሩት ተቋሙ በጨረታ ከሸጠው ቁርጥራጭ ብረት ስርቆት ጋር በተያያዘ መሆኑም በዘገባው ተመላክቷል።
የፓወር ኢኪውፕመንት ማምረቻ ፋብሪካው ከዚህ ቀደም በርካታ መጠን ያለውን ቁርጥራጭ ብረቶችን ጨረታ በማውጣት ሸጦ ነበር። ለጨረታ ከቀረበው ቁርጥራጭ ብረት ውስጥ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቶ የነበረና በሁዋላ ለግድቡ አይመጥንም ተብሎ፣ እንዲሁም ለግድቡ የብረታ ብረት ስራዎች ተቋራጭ በመቀየሩ ምክንያት ተቆራርጦ እንዲሸጥ የተደረገ የውሀ ማፋሰሻ የተሰራበት ብረትም ይገኝበታል፡፡
የፓወር ኢኪውፕመንትስ ማምረቻ ፋብሪካ ሀላፊዎች ከተጠረጠሩበት የብረት ስርቆት ውስጥ በጨረታ የተሸጠ ብረት ውስጥ የጨረታ አሸናፊው ከቦታው ሳያነሳው ከመጠኑ ማጉደል ይገኝበታል ተብሏል። ብረቱ ተከማችቶ የነበረውም አዲስ አበባ ጎሮ እየተባለ ከሚጠራው ሰፈር አቅራቢ ያለው ቦሌ ካባ የሚባል አካባቢ ነው። ቁርጥራጭ ብረቱ በጨረታ ሲሸጥ በ10 ሚሊየኖች ብሮች አስገኝቷልም መባሉ ዘገባው አክሏል። ተጠርጣሪዎቹ ህዳር 7 2016 አ.ም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

ምክር ቤቱ የቀረበለትን ሞሽን አፀደቀምክር ቤቱ መስከረም 28 ቀን፣ 2016 ዓ.ም በኘሬዘዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የቀረበውን የ2016 የመንግስት የትኩረት አቅጣጫ ሞሽን በመሉ ድምፅ አፅድቋ፡፡...
14/11/2023

ምክር ቤቱ የቀረበለትን ሞሽን አፀደቀ
ምክር ቤቱ መስከረም 28 ቀን፣ 2016 ዓ.ም በኘሬዘዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የቀረበውን የ2016 የመንግስት የትኩረት አቅጣጫ ሞሽን በመሉ ድምፅ አፅድቋ፡፡
6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዛሬ ተካሄዷል፡፡
በጉባኤው በፕሬዘዳንቷ የቀረበውን ሞሽን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤት አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ተሠጥቶባቸዋል፡፡ በመጨረሻም ምክር ቤቱ የቀረበለትን ሞሽን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

አስደናቂው ቦታ በአዲስ አበባ ....የት እንሂድ  Television
14/11/2023

አስደናቂው ቦታ በአዲስ አበባ ....የት እንሂድ Television

አስደናቂው ቦታ በአዲስ አበባ ....የት እንሂድ Television more :ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevisionፌ...

የምክር ቤቱ መረጃዎችየጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ማብራሪያዎች፡-ጠቅላይ ሚኒስትስር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ "ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በክላሽ መንግስትን መጣል ፈጽሞ አይቻልም "...
14/11/2023

የምክር ቤቱ መረጃዎች
የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ማብራሪያዎች፡-
ጠቅላይ ሚኒስትስር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ "ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በክላሽ መንግስትን መጣል ፈጽሞ አይቻልም " ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ እየሰጡ ባሉበት መድረክ ላይ ነው።
• “ብልፅግና ደርግ ነው፣ ሸኔ ነው እንዲሁም ዘውዳዊ ነው” የሚሉ እንዳሉ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ፓርቲው “በአንድ ጊዜ ሶስቱንም መሆን አይችልም” ብለዋል፡፡
• አሁን ባለው ሁኔታ መንግስትን ፈፅሞ በክላሽ መጣል አይቻልም ያሉት ዶ/ር ዐቢይ "ከክላሽ ይልቅ ብእርና ሃሳብ ይዘን ለመወያየት ቅድሚያ መስጠት ይገባል" ብለዋል።
• “በጦር መሳሪያ ከመገዳደል፤ በሀሳብ መገዳደር” የተሻለ ነውም ብለዋል፡፡ “በመገዳደል ልናሳካው የምንችለው ዓላማም ሆነ የሚገኝ ትርፍ የለም” ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ ለኢትዮጵያ የሚበጀውም በውይይት የበለጸገች አገር መገንባት ብቻ ነው” ሲሉ አክለዋል።
• በሌላ በኩል ፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ይዞት የመጣውን ዕድል እንዳያመልጠን “እለምናለሁ እመክራለሁም” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። ይሄ National Dialogue እድል ለኢትዮጵያ መባከን የሌለበት ፤ ካባከነው ሌላ ረጅም ጊዜ የሚጠይቀን ጉዳይ ስለሆነ የምንቃወምም፣ የምንቃረንም የምንፎካከርም ፣ የምንታገልም ሁላችንም በሰከነ አእምሮ ይሄንን እድል ለመጠቀም መሞከር ይኖርብናል ሲሉ አስረድተዋል።
• በሀገሪቱ የቀጠሉ ግጭቶችን በሚመለከት በሱጡት አስተያየታቸው “በመንግስት እቅድ የተጀመረ አንድም ጦርነት የለም” ብለዋል፡፡
• የኣማራ እና የኦሮሞ ህዝብ “ቢፈልግም ባይፈልግም በሰላም መኖር ብቸኛው ምርጫቸው ነው” ሲሉም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅምና የሰላምና ፀጥታን ለማረጋገጥ በመንግስት ስራዎች ላይ ጥያቄ ቀረበ፡፡የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/...
14/11/2023

የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅምና የሰላምና ፀጥታን ለማረጋገጥ በመንግስት ስራዎች ላይ ጥያቄ ቀረበ፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
በመደበኛ ስብሰባው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ያቀረቡትን የፌደራል መንግስቱን ዓመታዊ ዕቅድ የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ የሚሰጡ ይሆናል።
በዚሁ መሰረት የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ጥያቄና ማብራሪያ በማቅረብ ላይ ናቸው። በምክር ቤቱ አባላት የሀገሪቱን የሰላም እና ፀጥታን ለማስጠበቅ መንግስት ምን እየሰራ ነው፣ መንግስት በተደጋጋሚ ለሚያነሳቸው የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅምን በማስመልከት ማብራሪያ ተጠይቋል፡፡
እንዲሁም በተለያዩ አከባቢዎች የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖችን ለመቆጥጠርም ሆነ አባላቱን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል መንግስት ምን እየሰራ እንደሆነም ጥያቄ ቀርቧል፡፡ ከዚህም ባሻገር በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የመልካም አስተዳደር ችግር፣ የመሰረተ ልማት ችግሮችን የተመለከቱ ጥያቄዎች ለጠቅላይ ሚንስትሩ ቀርበዋል፡፡
በሀገሪቱ የቀጠለው የዜጎች መፈናቀል፣ ሞት፣ እንግልት እንዲሁም ዘርን መሰረት ያደረጉ የተደራጁ ጥቃቶች መቼ ሊቆሙ እንደሚችሉም በምክር ቤቱ አባላት ተጠይቋል፡፡
በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የሚሰራጩ ሀሰተኛ እንዲሁም የጥላቻ መረጃዎቸችን ለመቆጥጠር መንግሰስት ምን እየሰራ እንደሆነም ተጠይቋል፡፡ በቅርቡ መነጋገሪያ የሆነውን የ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤትን በሚመለከት የወደቁ ተማሪዎች ቀጣይ እጣ ፈንታ ምን ሊሆን እንደሚችል ጥያቄ ቀርቧል፡፡
አሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሚገኘው የሀገሪቱ የዋጋ ግሽበት እንዲሁም እየተበራከተ የመጣውን የስራ አጥ ቁጥርን በሚመለከት መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎቸቸውን አቅርበዋል፡፡ የዚህን ዜና ዝርዝር እነዲሁም የምክር ቤቱን ውሎና ለተነሱ ጥያቄዎች የተሰጡ ምላሾችን በምሽት የዜና እወጃችን የምናቀርብ ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

ሰውየው ስልጣናቸውን ያስረክቡ   ክፍል 2  talk  Television
13/11/2023

ሰውየው ስልጣናቸውን ያስረክቡ ክፍል 2 talk Television

ሰውየው ስልጣናቸውን ያስረክቡ ክፍል 2 talk Television more :ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTele...

ሦስተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ የቴክኒካል ጥናት መጠናቀቁን እስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ETRSS-2 የተባለችውን ሦስተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ የቴክኒካልና የገንዘብ ጥ...
13/11/2023

ሦስተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ የቴክኒካል ጥናት መጠናቀቁን እስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
ETRSS-2 የተባለችውን ሦስተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ የቴክኒካልና የገንዘብ ጥናት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ እስፔስ ሳይኒስና ጂኦስፓሻል ኢኒስቲትዩት አስታውቋል፡፡
የእስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ እንደገለጹት፣ ዓለም አቀፍ ጨረታ በማውጣት ሦስተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ ዝግጀት እየተደረገ ነው፡፡ ከገንዘብ ጋር የተያዙና ቴክኒካል የሆኑ ጥናቶች ተጠናቀው በመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዢ ስርዓት ውስጥ እንደተካተተ አስረድተዋል፡፡
የጨረታ ሰነድም በመዘጋጀት ላይ የሚገኝ ሲሆን በቀጣዮቹ ወራት ዓለም አቀፍ ግልጽ ጨረታ ይወጣል ብለዋል፡፡
ሦስተኛዋ ሳተላይት ባለከፍተኛ ኃይል በመሆኗ ከመጀመሪያዋ ሳተላይት ለበለጠ ጊዜ ህዋ ላይ ትቆያለችም ብለዋል። ከአገልግሎት አንጻር እንደመጀመሪያዋ ሳተላይት የመሬት ምልከታ ሳተላይት ናት ሲሉ አብራርተዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

ማንኛውም የሚደረጉ ውይይቶች ለህዝብ ይፋ እንዲደረጉ 5 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠየቁ፡፡በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱት ተፎካከሪ ፓርቲዎች መኢአድ ፣ ኢህአፓ ፣ የዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዴ...
13/11/2023

ማንኛውም የሚደረጉ ውይይቶች ለህዝብ ይፋ እንዲደረጉ 5 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠየቁ፡፡
በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱት ተፎካከሪ ፓርቲዎች መኢአድ ፣ ኢህአፓ ፣ የዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲና እናት ፓርቲ በዛሬው እለት የጋራ መግለጫ አውጥተዋል።
ፓርቲዎቹ በጋራ ባወጡት መግለጫቸው ማንኛውም የሚደረጉ ድርድሮችና ዉይይቶችን “የኢትዮጵያ ሕዝብ በይፋ ሊያውቃቸው ይገባል” ብለዋል።
አክለውም ግልጽ ያልሆኑና ከመጋረጃ ጀርባ የሚደረጉ ድርድሮችና ስምምነቶች ከመድረኩ እንደተወጣ ጥያቄ የሚያስነሱ መሆናቸዉ እንዳለ ሆኖ ዉለዉ አድረዉ ወደ ከፋ ጥፋት አገርንና ሕዝብን እንደሚወስዱ ከቅርብ ጊዜ ታሪካችን የምንረዳዉ ጉዳይ ነዉ ሲሉ አስታውሰዋል፡፡
ፕሪቶሪያ ላይ የተደረገዉና እርሱን ተከትሎ ናይሮቢ ላይ በፌደራል መንግሥት እና በሕወሃት መካከል የተደረጉ የተሸፋፈኑ ድርድሮችና፤ ተደረሰባቸዉ የተባሉ ስምምነቶች ዛሬም ድረስ ጥያቄ የሚያስነሱና ወደፊትም ጥያቄ በማስነሳት የሚቀጥሉ መሆናቸውን ፓርቲዎቹ ገልፀዋል።
ከጥቂት ቀናት ወዲህ በመንግሥትና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል ድርድር እየተደረገ ነዉ፤ በተባለዉና የፌዴራል መንግሥት ድርድሩ ስለመታሰቡም ሆነ ስለመጀመሩ እንዲሁም የድርድሩ ተሳታፊዎችን ማንነት ባልገለፀበት ሁኔታ ላይ መረጃዎች መደመጣቸው “የተደበላለቀ ስሜትና ከፍተኛ ስጋት አንዲሰማን አድርጓል” ብለዋል፡፡
ድርድሩ እየተካሄደበት ያለዉ መንገድ የተሸፋፈነ መሆን፣ ለድረድሩ ምክንያት የሆኑ አጀንዳዎች ይፋ አለመደረጋቸው እና ከአገራችን ሕዝብ ጀርባ እየተከናወነ የሚገኝ ድርድር መሆኑ፣ ሠላም የራቀዉ ህዝባችንን ተስፋ መልሶ የሚያጨልም የጎራ ድርድር እንዳይሆን ያለንን ስጋት እንገልጻለንም ብለዋል።
ምንም እንኳን መንግሥትም ይሁን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት በታንዛኒያ ዳሬሰላም ለሰላም ድርድር መቀመጣቸውን እስካሁን በይፋ ባያሳውቁም፤ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ ባይሰጡም፤ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የዲፕሎማቲክ ሰዎች ግን የሰላም ድርድር እየተካሄደ መሆኑን ማሳወቃቸወውን ናሁ ቴሌቭዥን ከዚህ ቀደም መዘገቡ አይዘነጋም። ድርድሩ እየተመራ ያለውም በጦር አዛዦች መሆኑንም የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እማኞችን ጠቅሰው ዘግበዋል።
ለበለጠ መረጃ የናሁ ቴሌቭዥንን የ :

ቴሌግራም :- https://t.me/NahooTelevision
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/Nahooethiopia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCUhnQSskjPYay4TC_hq9uQQ
Web-Site :- http://nahootelevision.com/
ቻናላችን ይቀላቀሉ፡፡
የናሁ ቴሌቭዥንን ስርጭት በቴሌቭዥን መስኮቶቻችሁ ይከታተሉ፡፡
ETHIOSAT
Satellite : NSS12
Frequency :11604/5
Polarisation : Horizontal
Symbol Rate : 45000

Address

Rosetta Bldg. 2nd Floor # 14/2010
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nahoo Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share

Nearby media companies