ባለፉት 60 ዓመታት የጉራጌን ማህበራዊ ስሪቶቻችን ከአነጹት የኪነጥበብ ባለሙያዎች ዋነኛው ማህሙድ አህመድ ነው፡፡ ማህሙድ በማህበራዊው ዘርፍ ሀገራዊ ውክልናችን ያጸናንበት፣ መጠርያችን እና ክብራችን ሆኖ በጽናት ቆይቷል፡፡
ከአማርኛ የሙዚቃ ስራዎቹ አንጻር የጉራግኛ ሙዚቃዎቹ እጅግ ጥቂት ይሁኑ እንጂ ስራዎቹ ለዘመናዊ የጉራግኛ ሙዚቃዎች መሰረት የጣሉ ናቸው፡፡
የጉራግኛ ሙዚቃዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ በአለም መድረክ እንዲታወቁ ከነበራቸው የጎላ አስተዋፅኦ ባሻገር መጪውም ጊዜ በዕሱ ከፍታ ልክ የሚመጡ የብሔረሰቡ ድምጻውያን ጥሩ የማዕዘን ድንጋይ ያኖረ ጉምቱ ሰው ነው፡፡
ጋሽ ማህሙድ የመጨረሻ መድረኩ ጥር 3 2017ዓ.ም በሚልንየም አዳራሽ ያቀርባል። የመጨረሻውም አልበም በቅርቡ ይደመጣል። ግለ ታሪኩን ያተተበት መጽሐፍ ሆነ ሌሎች ዝክረ ማህሙድ ዝግጅቶች በተከታታይ ይቀርባሉ።
Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ
"ምር ባኺም አጋ ጥፎነ?ሰናጫት መምር ትትፌነ ..."
"የትምህርት ስርከታችን ባዕ ጥሩ ስብእናም፣ ጥሩ ባለሙያም ከያደርገንም!" ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ
"የትምህርት ስርዓታችን ባለ ጥሩ ስብእናም፣ ጥሩ ባለሙያም አያደርገንም!" ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ
ከሰሞኑ የኢሳቷ ዜና አንባቢ (Anchor) በጉራጌ ዞን እኖር ኤነርና መገር ወረዳ ቆስየ/ቆሴ ከተማ ላይ በጎበዝ አለቆች የተከሰተውን ውድመት አስመልክቶ የተሰረውን ዜና በምታነብበት ጊዜ በቀረፃ ላይ የተፈጠረውን ስህተት እና ያልተገባ ንግግር በራሷ የቲክቶክ አካውንት አጋርታ ብዙሃኑን ማስቆጣቱ ይታወቃል።
ዘቢደር ሚዲያም የልጅቷ ድርጊት ተገቢነት የሌለው መሆኑን ጠቅሳ በግልፅ ለህዝቡ ይቅርታ እንድትጠይቅ አሳስባ ነበር።
ይህን የህዝቡን ቅሬታ መሰረት በማድረግም የዜና አሳላፊዋ ትግስት ተስፋዬ በራሷ የቲክቶክ አካውንት ይቅርታ ጠይቃለች።
Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ
የኢሳቷ ጋዜጠኛ ነገር
በጋዜጠኝነት ሙያ ውስጥ ፀያፍ የሆነ ድርጊት ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት የሙያ ፍቃድ የሚሰጥ ቢሆን ኖሮ በቀጥታ ፍቃድ የሚያስነጥቅ ድርጊት ነበር።
በእርግጥ ነውር የሆኑ የልጅቱ ንግግር እና ድርጊት ላይ ድርጅቱ (ኢሳት) የሚወስነውን ውሳኔ የሚጠበቅ ቢሆንም የዜና ማሰራጫ ስቱዲዮ እጅግ የተከበረ ቦታ አድርገው ለሰሩ እና ለሚሰሩ ጋዜጠኞች አንገት ያስደፋ፣ ሙያውን ለመቀላቀል ለሚያስቡም መጥፎ ትምህርት የሚሆን ነው።
የ"ዜና አንባቢዋ" የሚገርመው ሌላኛው ድርጊት ደግሞ የሆነ የተለየ ነገር እንዳደረገች ጀብደኛ ሰው በራሷ ቲክ ቶክ ገፅ ላይ ነውሯር እዩልኝ ስሙልኝ በማለት የለቀቀችው መሆኑ ነው።
በመሆኑም ልጅቱ የፈፀመችውን ስህተት ተረድታ ይቅርታ እንደምትጠይቅና የጋዜጠኝነት ሙያ ስነ ምግባር አክብራ እንደምትሰራ ተስፋ አለን።
Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ
ቆስየ
ኢሳት ቲቪ በጉራጌ ዞን በእኖር ኤነርና መገር ወረዳ ቆስየ ከተማ የጉራጌ ተወላጆች ላይ የተሰነዘረውን ጥቃት አስመልክቶ የሰራው ዘገባ።
ቅስም ይሰብራል!
አርብ እለት ፒኮክ መናፈሻ አካባቢ አትክልት በማምረት ስራ የሚተዳደሩ ቤተሰቦች እና ልጆቻቸው ቢሮዬ መጡ።'ሰፈሩ ለልማት ሊነሳ ነው እየተባለ ነው።ከወላጆቻችን ዘመን ጀምሮ በአካባቢው ለ73 አመታት ቆይተናል።ድንገት ተነሱ ብንባል ምን ይዋጠን!?' አሉኝ።
'መጀመሪያ የምትሄዱበትን ቦታ ማመቻቸት የመንግስት ግዴታ ነው።ያ ሳይሆን ለማስነሳት እንቅስቃሴ የሚደረግ ቢሆን ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርቤ እግድ እንዲሰጣችሁ አደርጋለሁ!' ብያቸው ተለያየን።ቅዳሜ ጉዳዩ የሚታይበትን አግባብ ሳዘጋጅ ዋልኩ።
እሁድ ጠዋት ደወሉልኝ ።ከቤተክርስትያን ስንመለስ ቤታችን እየፈረሰ አገኘነው አሉ። ከባልደረባዬ ጋር ሄድን ።አይዟችሁ ብለን መትረፍ የሚችለውን ለማስቆም እንሞክራለን አልናቸው ።
እስከ ማታ ለሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጨምሮ ለሚመለከታቸው አካላት የህግ አቤቱታዎችን ስናዘጋጅ አመሸን።ሰኞ ጠዋት ኮሚኒቲው ህጋዊ የህብረት ስራ ማህበር ያላቸው በመሆኑ በማህበራቸው ስም ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ኑርጋ ውክልና እንዲሰጡን ተነጋገርን።
ትላንት ከሰአት ሊቀመንበሩ የጠበቃ ውክልና ለመስጠት የማህበሩን የመመስረቻ ጽሁፍ ስላጡት ለማክሰኞ ጠዋት እንደሚሰጡን ተነጋገርን ።
ዛሬ ጠዋት አቶ ዱላ ከቤታቸው ሲወጡ የማህበሩ አባላት ሰፈር ውስጥ ለማፍረሻ የመጣ ዶዘር ቆሟል።ሌሎች አባላቶች ለኛ ውክልና ለመስጠት ውልና ማስረጃ እየ
የጨዋታ ፕሮግራም ጥቆማ
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ጨዋታ
ወልቂጤ ከተማ vs ከደብረብርሀን ከነማ
ነገ ማክሰኞ
⏰ 09:00 ሰዓት
🏟አበበ ቢቂላ ስታዲየም (አዲስ አበባ)
ማስታወቂያ
ከ1920ዎቹ ጀምሮ የእምድብር 1ኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ትም/ቤት በጉራጌ እና አካባቢው ድንቅ ምሁራንን ያፈራ፤ አንጋፋ የትምህር ማእከል በመሆንም ለብዙዎች ባለውለታ የሆነ አይን ገላጭ የትምህርት እና የእውቀት ማእከል ነው፡፡
ይህ የትምህርት እና የታሪክ ተቋም አሁን ላይ በአገልግሎት ብዛት የተጎዳና የፈራረሰ በመሆኑ መሰረታዊ ጥገና ፈልጋል፡፡
በመሆኑም ይህንን የታሪክ እና እውቀት ማእከል የሆነው የእምድብር 1ኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ትም/ቤት መልሶ ግንባታ ላማካሔድ የምክክር፣ የገቢ እና የትምህርት መርጃዎች ማሰባሰቢያ መድረክ ተዘጋጀ በመሆኑ የቀድሞ ተማዎች፤ በጎ ፍቀደኞች፣ የጉራጌ ተወላጆችና ወዳጆች፤ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ሕዳር 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ በተግባረ ዕድ ቴክኒክ ኮሌድ እንድትገኙ በበጎነት ተጋብዛችኃል፡፡
በትምህርት ልማት ላይ በጎ አሻራ ማኖር ለምትሹ እና የዚህ ት/ቤት ባለደራዎች ሁሉ በመርኃ ግብሩ ላይ በመገኘት ታሪካዊና ሞራላዊ ግዴታችሁን እንደትወጡ በአክብሮት እየጠየቅን በ0911169836 ወይም 0911879963 በመደወል የበለጠ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
የእምድብር 1ኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ትም/ቤት መልሶ ግንባታ አስተባባሪ ኮሚቴ
Zebidar Tube/ ዘቢዳር ቲዩብ
እናትና ልጅ የነጠቀው የወለቴ የእሳት አደጋ