![ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ ትናንት ምሽት ባሕር ዳር ከተማ በግፈኞች በግፍ ተገድሏል። ዶ/ር አንዱዓለም በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የ...](https://img3.medioq.com/279/896/599788642798966.jpg)
02/02/2025
ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ ትናንት ምሽት ባሕር ዳር ከተማ በግፈኞች በግፍ ተገድሏል። ዶ/ር አንዱዓለም በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽትና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊት ሃኪም፣ ተመራማሪና መምህር፣ እንዲሁም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ነበር።
ከእግዚአብሔር በታች የስንት ሰው ህይወት የሚታደገው ዶ/ር አንዱዓለም በግፈኞች ጥይት ተደብድቦ ነው የተገደለው።
ነፍስ ይማር!