ሸዋ Times

ሸዋ Times ሽዋ በኢትዮጵያ ገጸ ምድር መሃል ላይ የሚገኝ ታሪካዊ ሥፍራ ነው!

ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ ትናንት ምሽት ባሕር ዳር ከተማ በግፈኞች በግፍ ተገድሏል። ዶ/ር አንዱዓለም በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የ...
02/02/2025

ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ ትናንት ምሽት ባሕር ዳር ከተማ በግፈኞች በግፍ ተገድሏል። ዶ/ር አንዱዓለም በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽትና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊት ሃኪም፣ ተመራማሪና መምህር፣ እንዲሁም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ነበር።

ከእግዚአብሔር በታች የስንት ሰው ህይወት የሚታደገው ዶ/ር አንዱዓለም በግፈኞች ጥይት ተደብድቦ ነው የተገደለው።

ነፍስ ይማር!

ለበጎ ሥራ ተባበሩ መልካም ማድረግ ለራስ ነው። ሸዋ ደብረብረሃን የሀበሻ አረጋውያንና ምስኪኖች መርጃ ልማት ማህበርን እናግዝ!🔔  ከበረከቱን ተካፈሉ  የድርጅቱ ሒሳብ ቁጥሮች 1)የኢትዮጵያ ን...
01/02/2025

ለበጎ ሥራ ተባበሩ መልካም ማድረግ ለራስ ነው። ሸዋ ደብረብረሃን የሀበሻ አረጋውያንና ምስኪኖች መርጃ ልማት ማህበርን እናግዝ!

🔔 ከበረከቱን ተካፈሉ

የድርጅቱ ሒሳብ ቁጥሮች

1)የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000188800193
2)አኩፋዳ ማይክሮ ባንክ 0566
3)አማራ ባንክ 9900025227507
4)አባይ ባንክ 2042119990867016
5)አዋሽ ባንክ 013081190227500
6)ወጋገን ባንክ 0078377530201
7)ዳሽን ባንክ 0048110766011
8)አቢሲኒያ ባንክ 147421982

25/01/2025

ንፁሃን አርሶ አደሮችን በግዴታ ዝመት ማለት ኪሳራ እንጂ ትርፍ የለውም! የሚመለከታችሁ ሁሉ ቆማችሁ አስቡበት!

22/01/2025

እሳቱ ሸዋ! 🔥

19/01/2025

እንኳን አደረሳችሁ!

"አፄ ቴዎድሮስ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የምንጊዜም ክስተት ናቸው። እስከ ዘመነ ምፅአት ቢሆን እንኳ በትውልድ ልብ ውስጥ በቅብብሎሽ የሚሻገሩ መሪ ቢኖሩ አፄ ቴዎድሮስ ናቸው።"//ጥር 6 - የ...
14/01/2025

"አፄ ቴዎድሮስ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የምንጊዜም ክስተት ናቸው። እስከ ዘመነ ምፅአት ቢሆን እንኳ በትውልድ ልብ ውስጥ በቅብብሎሽ የሚሻገሩ መሪ ቢኖሩ አፄ ቴዎድሮስ ናቸው።"

//ጥር 6 - የዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ 206'ኛ የልደት ቀን//

ስልጣን ላይ ያሉት የአብን አመራሮች ባህርዳር እንደሚገኙ የለጠፉት የፌስቡክ ኦስት ስርአስተያየቶች መቶ % በሚባል ደረጃ ተቃውሞ ናቸው። በዚህ ደረጃ ህዝብ ከተቃወመህ ማንን ወክለህ ነው ስልጣ...
13/01/2025

ስልጣን ላይ ያሉት የአብን አመራሮች ባህርዳር እንደሚገኙ የለጠፉት የፌስቡክ ኦስት ስርአስተያየቶች መቶ % በሚባል ደረጃ ተቃውሞ ናቸው። በዚህ ደረጃ ህዝብ ከተቃወመህ ማንን ወክለህ ነው ስልጣን ላይ ያለኸው ? እኝህ ባለስልጣናት አስበውት ያውቁ ይሆን?

ሻንጣ ተሸካሚው ዘመድኩን!በነገራችን ላይ ዘመድኩን በቀለ የአማራን ፍርፋሪት ሲለቅም ያደገ እና የኖረ ስለሆነ አሁንም የአማራ ጉዳይ ይመለከተኛል ብሎ የሚቅበዘበዘው እንደፍርፋሪቱ ቀላል መስሎት...
08/01/2025

ሻንጣ ተሸካሚው ዘመድኩን!

በነገራችን ላይ ዘመድኩን በቀለ የአማራን ፍርፋሪት ሲለቅም ያደገ እና የኖረ ስለሆነ አሁንም የአማራ ጉዳይ ይመለከተኛል ብሎ የሚቅበዘበዘው እንደፍርፋሪቱ ቀላል መስሎት ነው። ለረጅም ጊዜ ሸዋ እየተዘዋወረ ሲቀላውጥ የኖረ የባህታዊ ተብየው ገብረመስቀል ሻንጣ ተሸካሚ ነበር። ወዳጄ የአማራ ህዝብ የሚገባህን እንጅ የማህገባህን አይሰጥህም።

ዜና እረፍት!ፖለቲከኛው አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸው ተሰማ፡፡አቶ ቡልቻ ማረፋቸው የተሰማው ዛሬ ማለዳ ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ ስም የነበራቸው አቶ ቡልቻ የምጣኔ ሀ...
06/01/2025

ዜና እረፍት!

ፖለቲከኛው አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸው ተሰማ፡፡

አቶ ቡልቻ ማረፋቸው የተሰማው ዛሬ ማለዳ ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ ስም የነበራቸው አቶ ቡልቻ የምጣኔ ሀብት ባለሙያውም ነበሩ፡፡

ነፍስ ይማር!

ከሰም ስኳር ፋብሪካ አፋር የመሬት መንቀጥቀጡ ያደረሰው ጉዳት ይህንን ይመስላል።
05/01/2025

ከሰም ስኳር ፋብሪካ አፋር የመሬት መንቀጥቀጡ ያደረሰው ጉዳት ይህንን ይመስላል።

ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ዐረፉበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በ5ኛው ኢትዮጵያዊው ፓትርያርክ በብፁዕ አቡነ ጳውሎስ  ነሐሴ 22 ቀን 1997 ዓ.ም ከተሾሙ 17 ጳጳሳት አንዱ የሆኑት ...
04/01/2025

ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ዐረፉ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በ5ኛው ኢትዮጵያዊው ፓትርያርክ በብፁዕ አቡነ ጳውሎስ ነሐሴ 22 ቀን 1997 ዓ.ም ከተሾሙ 17 ጳጳሳት አንዱ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ዐረፉ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የድሬዳዋ እና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳሳት የነበሩት ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ትናንት ከምሽቱ አምስት ሰዓት አካባቢ በመንበረ ፓትርያርክ በሚገኘው ማረፊያ ክፍላቸው እንዳረፉ ለማወቅ ተችሏል።
ብፁዕነታቸው በሰሜን አሜሪካ ለረጅም ዓመታት አገልግሎት በመስጠት እንደሚታወቁ የገለጠው ዐደባባይ ሚዲያ የልብ ሕመም እንዳለባቸው ሐኪም ሲነግራቸው በዚህ ዕድሜዬ ቀዶ ጥገና አይደረግልኝም ወደ አገሬ ሔጄ ለአገሬ አፈር ልብቃ ማለታቸውን ዘግቧል።
የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን።
ነፍሳቸውን በቅዱሳን እቅፍ ያሳርፍልን።

01/01/2025

የማንናገረው የምንናገረው አጥተን ሳይሆን ለአንድነታችን ሲባል ዝምታን መርጠን ነው።

🔴 በአዲስ አበባ አቆጣጠር  ከሌሊቱ 7:13 (01:13 am)፣ በአፋር ክልል አዋሽ አካባቢ ከሰሞኑ ከደረሱት የመሬት መንቀጥቀጥ ክሰተቶች በመጠኑ ከፍተኛ የሆነ መንቀጥቀት ተከሰተ። በአካባቢው...
31/12/2024

🔴 በአዲስ አበባ አቆጣጠር ከሌሊቱ 7:13 (01:13 am)፣ በአፋር ክልል አዋሽ አካባቢ ከሰሞኑ ከደረሱት የመሬት መንቀጥቀጥ ክሰተቶች በመጠኑ ከፍተኛ የሆነ መንቀጥቀት ተከሰተ።

በአካባቢው ሌሊት 7:ሰዓት ከ13 ላይ የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ በሬክተር ስኬል 5.2 የደረሰ እንደሆነ የጀርመን የጂኦሳይንስ የምርምር ማዕከል (The German Research Centre for Geosciences | GFZ) አስታውቋል።

በንጉሡ ዘመን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተደርጐ ያልተሳካው በተለምዶ "የታህሳሱ ግርግር" በመባል የሚታወቀው የመንግስት ግልበጣ ግዴታውን ከመሩት ሠዎች መካከል አንዱ የነበሩት ግርማሜ ንዋይ ...
24/12/2024

በንጉሡ ዘመን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተደርጐ ያልተሳካው በተለምዶ "የታህሳሱ ግርግር" በመባል የሚታወቀው የመንግስት ግልበጣ ግዴታውን ከመሩት ሠዎች መካከል አንዱ የነበሩት ግርማሜ ንዋይ ሲሆኑ ፤ በወቅቱ ሙከራው ከከሸፈ በኃላ ግርማሜ ንዋይ ከተሸሸጉበት ደብረ ዘይት ድሬ ጨለባ በሚባል ሥፍራ ላይ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር ባደረጉት የቶክስ ልውውጥ ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል።

ከላይ በምስሉ ላይ የግርማሜ ንዋይ አስክሬን በአዲስ አበባ ከተማ የጦር ሆስፒታል ውስጥ ተቀምጦ ይታያል።

ታህሳስ 15 ቀን 1953 ዓ.ም
አዲስ አበባ

23/12/2024

እረ መሬት መንቀጥቀጥ!

21/12/2024

ሀገር ሰሪው ሸዋ!

ከ - ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ለ - አቶ መርሻ ናሁሰናይ ዳግማዊ አጼ ምኒሊክ ታመው ለጠበል ደብረ ሊባኖስ ገዳም በነበሩበት ወቅት የድሬዳዋ ከተማ መስራችና አስተዳዳሪም ለነበሩት ለአቶ መርሻ ናሁ...
20/12/2024

ከ - ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ
ለ - አቶ መርሻ ናሁሰናይ

ዳግማዊ አጼ ምኒሊክ ታመው ለጠበል ደብረ ሊባኖስ ገዳም በነበሩበት ወቅት የድሬዳዋ ከተማ መስራችና አስተዳዳሪም ለነበሩት ለአቶ መርሻ ናሁሰናይ የፃፉት ደብዳቤ ፤ እንዲህ ይላል...

" ሞአ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ ዳግማዊ ምኒሊክ ስዩመ እግዚአብሄር ንጉሠነገስት ዘኢትዮጵያ ፤ ይድረስ ለአቶ መርሻ እንዴት ሰንብተሃል? እኔ እግዚአብሄር ይመስገን ደህና ነኝ። የፈረንሳይ የምድር ባቡር ኩባንያዎች የባቡሩን ስራ መጀመራችን ነው ብለዋልና እንግዲህ የስራውን ነገር ከነጋድራስ ይገዙ ጋር እየተመካከራችሁ እንዲሰራ ይሁን።

ታህሳስ 12 ቀን 1901 ዓመተ ምህረት
ከደብረሊባኖስ ተጻፈ

Address

Adama

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሸዋ Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share

Category