17/08/2024
Justice | ፍትሕ 💔
የሴቶች ና የማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
ክብርት ዶክተር ኢርጎጌ ተሰፋዬ :-
| በሀገራችን የህፃናትን መብትና ደህንነት እንዲጠበቅ ለማድረግ በተለያዩ አካባቢዎች እየተከሰቱ ባሉ ማህበራዊ ችግሮች ምክንያት ተጋላጭና ተጎጂ የሆኑ ህፃናትን ለመታደግ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚ/ር የተለያዩ ተግባራት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ሲሆን በተለይ የአሰራር ስርኣት በመዘርጋት በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች የሚመዘገቡበትና ተገቢውን ሁሉን አቀፍ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል የህፃናት የጉዳይ የመረጃ አያያዝ ዲጂታል ስርአት ( Child Case Managment Degital System ; CPIMS ) ከ UNICEF ጋር በመተባበር እስከ ቀበሌ በመዘርጋት የቅንጅት ስራዎች እንዲጠናከሩ እየተደረገ ይገኛል።
በቅርቡ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደለችውን ህፃን ሄቨን በተመለከተ ለደረሰው ዘግናኝ ኢሰብአዊ ወንጀል በሚኒሰትር መስሪያ ቤታችንና በራሴ ስም የተሰማንን ሀዘን እየገለፅሁ ጉዳዩ ዉሳኔ የተሰጠበት ቢሆንም ይግባኝ ለመጠየቅ የሚኬድበት አግባብ ትክክል ባለመሆኑ ከሚመለከታቸው የፍትህ አካላት ጋር በመሆን ጉዳዩን የምንሰራበትና የምንከታተለው እንደሆነ እንገልፃለን ።
የሴቶች ና የማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
ክብርት ዶክተር ኢርጎጌ ተሰፋዬ
🙏🙏🙏