Efita Mereja እፍታ መረጃ

  • Home
  • Efita Mereja እፍታ መረጃ

Efita Mereja እፍታ መረጃ ታማኝና ወቅታዊ መረጃዎችን እናደርሳለን..!

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መኖሪያ ቤት እና ስቱዲዮ ጥገና ሊደረግለት ነው። እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መኖሪያ ቤት እና ...
24/04/2024

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መኖሪያ ቤት እና ስቱዲዮ ጥገና ሊደረግለት ነው።

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መኖሪያ ቤት እና ስቱዲዮ የጥገና ስራ ለማከናወን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ከ ቢዋይ ኤምቲ ኮንትራክተር እና ዳሎል አማካሪ ድርጅት መካከል የተቋሙ የበላይ ኃላፊዎች በተገኙበት በ15/08/2016 ዓ.ም የስራ ርክክብ ተደርጓል።

በፕሮግራሙ ላይ መልእክታቸውን ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ቅርሱ የነበረውን አሻራና ይዘት በጠበቀ መልኩ የቅርስ ጥገና መርሆዎችን በተከተለ መንገድ በጥንቃቄ መከናወን እንዳለበት ገልፀው፡፡የጥገና ስራው በተያዘለት የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ጥራቱን ጠብቆ መጠገንና ለሃገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ መሆን እንደሚኖርበት አሳስበዋል፡፡

በመጨረሻም ስራ ተቋራጩ ይህን ታሪካዊ ቅርስ ጥገና ማድረግ በመቻላቸው እድለኛ እንደሆኑ ገልጸው ስራውን በተፈለገው ጊዜና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ አከናውነው እንደሚያስረክቡ ቃል ገብተዋል፡፡


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

ባይደን ፊርማቸውን ሲያኖሩ ቲክቶክ ፍርድ ቤት እንተያይ ብሏል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በባይት ዳንስ ባለቤትነት ያለው "  #ቲክቶክ " ድርሻው ለአሜሪካ ኩባንያ ተሽጦ ከቻይና ካልተ...
24/04/2024

ባይደን ፊርማቸውን ሲያኖሩ ቲክቶክ ፍርድ ቤት እንተያይ ብሏል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በባይት ዳንስ ባለቤትነት ያለው " #ቲክቶክ " ድርሻው ለአሜሪካ ኩባንያ ተሽጦ ከቻይና ካልተፋታ በመላው አሜሪካ እንዲታገድ የቀረበላቸው ረቂቅ ሕግ ላይ ፊርማቸውን በማኖር ሕግ ሆኖ እንዲወጣ አድርገዋል።

"ቲክቶክ ድርሻው ለአሜሪካ ኩባንያ እንዲሸጥ የተሰጠው ጊዜ ከ9 ወር እስከ 1 ዓመት ብቻ ሲሆን በዚህ ጊዜ ይህንን ካላደረገም እስከወዲያኛው ከአሜሪካ እንደሚታገድ ተገልጿል።

አሁን በአሜሪካ ብቻ 170 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ያሉት ቲክቶክ ሙሉ በሙሉ የመታገዱ ነገር እውን ወደ መሆኑ ተቃርቧል።

የቲክቶክ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ሹ ዚ ቼው የትም አንሄድም። ለመብታችን በፍርድ ቤት እንታገላለን። ሀቁ እና ህገ መንግስቱ ከጎናችን ናቸው፣ እናሸንፋለን ብለን እንጠብቃለን ሲሉ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለዩክሬን ፣ እስራኤል እና ታይዋን የቀረበው የ95 ቢሊዮን ዶላር የድጋፍ ጥቅል ረቂቅ ሕግ ላይ ፊርማቸውን አኑረዋል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤቱ ያስቀመጣቸው መፍትሔዎች “በሙሉ” በገዢው ፓርቲ የተያዙ ናቸው  ብሏል። በኢትዮጵያ ውስጥ የትጥቅ ትግል እያደረገ የሚገኘው እና በአገሪቱ ...
24/04/2024

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤቱ ያስቀመጣቸው መፍትሔዎች “በሙሉ” በገዢው ፓርቲ የተያዙ ናቸው ብሏል።

በኢትዮጵያ ውስጥ የትጥቅ ትግል እያደረገ የሚገኘው እና በአገሪቱ ፓርላማ “አሸባሪ” ተብሎ የተፈረጀው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነሠ) ዛሬ ረፋድ የብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት ለአገሪቱ ስብራት ያስቀመጣቸው መፍትሔዎች በሙሉ በገዢው ፓርቲ የተያዙ ናቸው ስለማለቱ ተመልክተናል።

እፍታ መረጃ ከድርጅቱ ይፋዊ የኤክስ ገጽ እንደተመለከተችው “የብልጽግና ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት” የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ እና ለትውልድ የተሸጋገሩ ቀውሶች ለመፍታት ፍኖተ ካርታውን “አሳትሟል” በማለት ገልጿል።

የብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤቱ በመግለጫው “የታሪክ ስብራቶቹን” ለመጠገን ፖለቲካዊ ችግሮችን በአገራዊ ምክክር፤ እንዲሁም በሽግግር ፍትሕ እና በተሐድሶ ለመጠገን መስራት እንደሚገባ መግለጹን እፍታ መረጃ ዘግባ እንደነበር ይታወሳል።

ታጣቂ ቡድኑ “ሦስቱም ሂደቶች ሙሉ በሙሉ በገዢው አካል ባለቤትነት የተያዙ እና በጥቃቅን የሚተዳደሩ ናቸው” ማለቱንም እፍታ መረጃ ከመግለጫው ተመልታለች። “እንደ የሽግግር ፍትህ እና ብሔራዊ ውይይት ያሉ የቃላት ጫወታውችም ሕዝቡን ለማደናገር እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እጅ መንሻ ነው” ሲል የኦርሞ ነጻነት ግንባር አስታውቋል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

ጉድ በል ጎንደር ያስባለውን መረጃ ስናጋራችሁ  👇ታዋቂው የቱርክ ተዋናይ ትምህርት ቤቱን ወደፍርስራሽነት መለወጡ አነጋጋሪ ሆኗልደ። ቻላር አርቱግሩል የተባለው ተዋናይ በልጅነቱ ይማርበት የነበ...
24/04/2024

ጉድ በል ጎንደር ያስባለውን መረጃ ስናጋራችሁ
👇
ታዋቂው የቱርክ ተዋናይ ትምህርት ቤቱን ወደፍርስራሽነት መለወጡ አነጋጋሪ ሆኗልደ።

ቻላር አርቱግሩል የተባለው ተዋናይ በልጅነቱ ይማርበት የነበረውን የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቱን ገዝቶ ያወደመው ያኔ ተማሪ ሳለሁ ይገርፉኝ የነበሩ መምህራንን ለመበቀል ነው ማለቱም ብዙሀኑን ማነጋገሩን ተመልክተናል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

አዲስ የተገነባውን የመቄዶንያ ህንፃ ለማጠናቀቅ 1.7 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ተነግሯል። ዛሬ ሚያዝያ 16/2016 ዓም የኢትዮ ቴሌኮም "ሚያዚያን ለመቄዶንያ" በተሰኘው መርሃ ግብር አስመ...
24/04/2024

አዲስ የተገነባውን የመቄዶንያ ህንፃ ለማጠናቀቅ 1.7 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ተነግሯል።

ዛሬ ሚያዝያ 16/2016 ዓም የኢትዮ ቴሌኮም "ሚያዚያን ለመቄዶንያ" በተሰኘው መርሃ ግብር አስመልክቶ የመቄዶንያ መስራች አቶ ቢኒያም በለጠ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል።

"ሚያዚያን ለመቄዶንያ" በተሰኘ መርሃ ግብር በዚህ ወር የኢትዮ ቴሌኮም ማህበራዊ ትስስር ገፆችን በሚቀላቀሉ አዲስ ተከታዮች (Followers) ብዛት ልክ 30 ብር እንዲሁም በሚጋሩ ልጥፎች (Share) ልክ 10 ብር ለመቄዶንያ አረጋዊያን እና ህሙማን መርጃ ማዕከል ኢትዮ ቴሌኮም ገቢ አንደሚያደርግ አቶ ቢኒያም በለጠ ተናግሯል።

የተገልጋዮችን ቁጥር 17,500 ወደ 20,000 ለማድረስ እና ሆስፒታል እንዲሆን በማሰብ በ3.5 ቢሊዮን ብር በመገንባት ላይ ያለው ባለ 15 ወለል ያለው ሕንፃ በተጀመረ በ3 ዓመት ውስጥ 2 ቤዝመንት፤ ግራውንድ እና 12 ፎቅ ወደ ላይ በመገንባት በሶስት ዓመት ተኩል የሕንፃው ግንባታውን ወደ ማጠናቀቁ ተቃርበናል ተብሏል። በአሁን ወቅት ህንፃውን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ አቶ ቢነያም ተናግሯል።

መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማህበር ምንም ጧሪና ደጋፊ የሌላቸውን በተለይም ደግሞ እራሳቸውን ችለው መንቀሳቀስ፣ መመገብ እና መፀዳዳት የማይችሉ የአልጋ ቁራኛ የሆኑና የሰው ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው አረጋውያንንና አዕምሮ ሕሙማንን ከወደቁበት ጎዳና ላይ በማንሳት 7,500 በላይ የሚሆኑ ተረጂዎችን በአዲስ አበባ፣ ደሴ፣ ድሬዳዋ፤ ሻሽመኔ፣ አደዋ፤ ባህርዳር፣ ሐረር፤ ጋምቤላ እና ጎሬ፣ መቱ፣ ጂማ፤ ሰንዳፋ በኬ፣ ሐዋሳ፣ አሶሳ፣ ጎንደር፣ ደብረማርቆስ፣ አምቦ፣ ኮረም፣ ሰመራ፣ ሰቆጣ፣ አምደወርቅ፣ ላሊበላ፣ አዲስ ዘመን፤ አምቦ እና አርባምንጭን ጨምሮ በአጠቃላይ በ25 ከተሞች ውስጥ እየስራ ይገኛል።

በቀጣይ ወሊሶ፣ በሱልልታ፣ ሰበታ፣ ደብረ ብርሃን፤ ሆሳዕና፣ ዲላ፣ ጂግጂጋ፣ እና በሌሎች የሀገሪቱ ከተሞችን ለመስራት ከወዲሁ እንቅስቃሴ ተጀምሯል።

በኢትዮ ቴሌኮም የትስስር ገፆች ላይ በሚቀላቀሉ አዳዲስ ተከታዮች ወይም (Follower) ብዛት 30 ብር እና በሚጋሩ ልጥፎች (Share) ልክ 10 ብር ለመቄዶንያ እርዳታ ስለሚደረግልን ቴሌግራም፣ ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም፣ ሊንክዲን፣ ዩትዩብ፣ ቲክቶክ ይፋዊ የትስስር ገፆች ፎሎው እና ሼር በማድረግ መቄዶንያን ያግዙ! መባሉንም ሰምተናል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም በዙራያው በሰፈሩ ሰዎች የታዘ መሬቱን ለማስመለስ የካሳ ክፍያ መጠየቁን አስታውቋል። በአማራ ክልል የሚገኘው ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም...
24/04/2024

አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም በዙራያው በሰፈሩ ሰዎች የታዘ መሬቱን ለማስመለስ የካሳ ክፍያ መጠየቁን አስታውቋል።

በአማራ ክልል የሚገኘው ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም ከ30,000 እስከ 50,000 የሚሆኑ ፀበልተኞች እንደሚጸበሉበት ይሁን እንጂ የገዳሙ መሬት ሰዎች ስለሰፈሩበት እንኳን ለጸበልተኞች ለመነኮሳቱም እጅግ በመጣበቡ ገዳሙ በከፍተኛ ችግር ላይ ይገኛል ተብሏል።

የገዳሙ ይዞታ የጠበበው ከበርካታ ዓመታት ጀምሮ ለመፈወስ ወደ ስፍራው የሚሄዱ ፈውስ ያገኙ ጸበልተኞችና አርሶአደሮች ከሕመማቸው ከተፈወሱ በኋላ በገዳሙ መሬት ቤት እየሰሩ እዚያው በመኖራቸው መሆኑን የገዳሙ መነኮሳት አስረድተዋል።

ሰዎቹ በአንድ ሳይሆን ቀስ በቀስ እዛው መኖር እንደጀመሩ ተጠቁሟል።

በገዳሙ ይዞታ የሰፈሩ ከ250 በላይ አባውራዎች ይነሱ ዘንድ ለጠየቁት ካሳና ለሌሎች አገልግሎቶች ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ አሳውቋል።

ለዚህም ሚያዚያ 19/2016 ዓ/ም በካፒታል ሆቴል የገቢ ማሰባሰብ መርሀ ግብር እንደተዘጋጀ በማስታወስ በውስጥም በውጪ ያሉ ኢትዮጵያዊያን እርብርብ እንዲያደርጉ ገዳሙ ጥሪ አቅርቧል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

እስራኤል የሀማስ የመጨረሻ ምሽግ ይገኝባታል የምትላትን ራፋን ለማጥቃት በቀጣይ ሳምንት ንጹሀንን ልታስወጣ ነው ተባለ።እስራኤል የሀማስ የመጨረሻ ምሽግ ይገኝባታል የምትላትን የራፋ ከተማ ለማጥ...
24/04/2024

እስራኤል የሀማስ የመጨረሻ ምሽግ ይገኝባታል የምትላትን ራፋን ለማጥቃት በቀጣይ ሳምንት ንጹሀንን ልታስወጣ ነው ተባለ።
እስራኤል የሀማስ የመጨረሻ ምሽግ ይገኝባታል የምትላትን የራፋ ከተማ ለማጥቃት በሚቀጥለው ሳምንት ንጹሃንን ማስወጣት እንደምትጀሞር ተገልጿል።
እስራኤል ከራፋ ለሚወጡ ሰዎች መጠለያ የሚሆን በ10ሺዎች የሚቆጠር ድምኳን መግዛቷን ሮይተርስ የእስራኤል ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
በግብጽ ድንበር የምትገኘው የጋዛ ከተማ ግማሽ አመት በሆነው የእስራኤል እና ሀማስ ጦርነት ሸሽተው በመጡ ተፈናቃዮች ተጨናንቃለች። ይህ የእስራኤል ራፋን የማጥቃት እቅድ የስደተኛ ማዕበል ሊከሰት ይችላል የምትለውን ግብጽን እና ምዕራባውያን ስጋት ውስጥ ከቷል።
በንጹሀን ጥበቃ ጉዳይ ከአሜሪካ መንግስት ጋር ለሳምንታት ውይይት ከተካሄደ በኋላ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር እያንዳንዳቸው ከ10-12 ሰዎች ማስጠለል የሚችሉ 40,000 ድንኳኖችን መግዛቱን ዘገባው ጠቅሷል።
በኢንተርኔት የተሰራጨ ቪዲዮ ከራፋ በአምስት ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ካን ዮኒስ ነጭ ድንኳኖች ተደርድረው ያሳያል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ የጦር ካቢኔት የንጹሀን ማስወጣትን ስራ ለማስጀመር በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ይሰበሰባል ተብሏል።
እስራኤል በራፋ ከተማ ጥቃት እንዳታደርስ የእስራኤል እና ሀማስ አደራዳሪዎች ግብጽ፣ ኳታር እና አሜሪካ ጫና ቢያደርጉም፣ እስራኤል የማጥቃት እቅዷን አልቀለበሰችም።
እስራኤል የሀማስ የመጨረሻ ምሽግች የሚገኙት በራፋ ስለሆነ ራፋን ማጥቃት ሀማስን ሙሉ በሙሉ ለመደምስስ አስፈላጊ ነው ብላ ታምናለች።
ባለፈው ጥቅምት ወር ሀማስ ያደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እስራኤል በጋዛ እየወሰደችው ባለው መጠነሰፊ የአየር እና የምድር ጥቃት የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር ከ34ሺ በላይ አልፏል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

በአዲስ አበባ እየተገነባ ያለ መኖሪያ ቤት የግንባታ ግብዓት ተንዶ በሌላ ቤት ውስጥ ተኝተው የነበሩ 7 ሰዎችን ለሕልፈት ዳረጉ። ዛሬ ሚያዝያ 16 ሌሊት 11 ሰዓት ላይ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ...
24/04/2024

በአዲስ አበባ እየተገነባ ያለ መኖሪያ ቤት የግንባታ ግብዓት ተንዶ በሌላ ቤት ውስጥ ተኝተው የነበሩ 7 ሰዎችን ለሕልፈት ዳረጉ።

ዛሬ ሚያዝያ 16 ሌሊት 11 ሰዓት ላይ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 12፣ ጠሮ መስጂድ አካባቢ እየተገነባ ያለ የግለሰብ መኖሪያ ቤት የግንባታ ግብዓት በአቅራቢያው ባለ ሌላ መኖሪያ ቤት ላይ ተንዶ በቤቱ ውስጥ ተኝተው የነበሩ 7 ሰዎችን ለሕልፈት ዳርጓል።

የሟቾቹን አስከሬን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች አውጥተው ለፖሊስ ማስረከባቸው ተገልጿል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

ባለፈው ሳምንት ብቻ 7 ሰዎች ናቸው መገደላቸውን የኮሬ ዞን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በኮሬ ዞን በታጣቂዎች አማካኝነት ንጹሃን ላይ የሚደርስ ጥቃት በእርቀ ሰላም ተፈቶ ቆሞ የነበረ ቢሆንም ከ4 ...
23/04/2024

ባለፈው ሳምንት ብቻ 7 ሰዎች ናቸው መገደላቸውን የኮሬ ዞን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

በኮሬ ዞን በታጣቂዎች አማካኝነት ንጹሃን ላይ የሚደርስ ጥቃት በእርቀ ሰላም ተፈቶ ቆሞ የነበረ ቢሆንም ከ4 ወራት ወዲህ በማገርሸቱ የንጹሐን ግድያ፣ የንብረት ዘረፋ እየተፈጸመ መሆኑን የዞኑ ባለስልጣትና ነዋሪዎች የገለፁ ሲሆን መንግሥት መፍትሄ እንዲሰጥም ተጠይቋል።

ባለስልጣናቱና ነዋሪዎቹ ለድርጊቱ የ ኦነግ ሸኔ ታጣቂዎችን ተጠያቂ ሲያደርጉ ከምዕራብ ጉጂ ዞን ጋላና ወረዳ የታጠቁ ኃይሎች በቀጠናው ላይ ገብተው 4 ሰዎችን በአንድ ቀን መግደላቸውንም ነው የተናገሩት።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

አርቲስት አማኑኤል ሐብታሙ በፖሊስ ተይዞ መወሰዱ ተነግሯል። በበርካ የፊልም ስራዎቹ ተወዳጅነትን ያተረፈው አርቲስት አማኑኤል የአንድ ሰው ትአትር የሆነውን “ ዕብደት በህብረትን ቲአትርን ለማ...
23/04/2024

አርቲስት አማኑኤል ሐብታሙ በፖሊስ ተይዞ መወሰዱ ተነግሯል።

በበርካ የፊልም ስራዎቹ ተወዳጅነትን ያተረፈው አርቲስት አማኑኤል የአንድ ሰው ትአትር የሆነውን “ ዕብደት በህብረትን ቲአትርን ለማሳያት ከአዲስ አበባ ወደ እስራኤል ሀገር ሊሄድ ሲል ከአዲስ አበባ ኤርፖርት ለጥያቄ ትፈለጋለህ ብለው ፖሊሶች ይዘውት ወደ ፖሊስ ጣቢያ መሄዳቸው ነው የተነገረው::

አርቲስቱ በፖሊስ የተወሰደበት ምክንያት ከቲአትሩ ጋር የተያያዘ ይሁን አይሁን የተገለፀ ነገር የለም።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

የ5 ሕፃናት እና ሴቶችን ሕይወት ጨምሮ 16 ዜጎቻችን ሕይወታቸውን ማጣታቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ እስታውቋል። በጀልባ መገልበጥ አደጋ የ16 ኢትዮጵያውያን ሕይወት ሲጠፋ አብረው የተሳፈ...
23/04/2024

የ5 ሕፃናት እና ሴቶችን ሕይወት ጨምሮ 16 ዜጎቻችን ሕይወታቸውን ማጣታቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ እስታውቋል።

በጀልባ መገልበጥ አደጋ የ16 ኢትዮጵያውያን ሕይወት ሲጠፋ አብረው የተሳፈሩ 28 ዜጎችን እስካሁን ማግኘት አልተቻለም።

ትላንት ምሽቱን ከየመን የባህር ዳርቻ ልዩ ስሙ " አራ " ከሚባል ስፍራ 77 ኢትዮጵያውያን ሕገ ወጥ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ ጅቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ " ጎዶሪያ " በሚባል አካባቢ በደረሰባት የመገልበጥ አደጋ እስካሁን ድረስ የ5 ሕፃናት እና ሴቶችን ሕይወት ጨምሮ 16 ዜጎቻችን ሕይወታቸውን አጥተዋል።

እስካሁን አብረው ተሳፍረው የነበሩት ውስጥ 28 ፍልሰተኞችን ማግኘት እንዳልተቻለ እና 1 ሴትን ጨምሮ 33 ፍልሰተኞች በሕይወት ተርፈው ድጋፍ እየተደረገላቸው ነው።

ከ2 ሳምንት በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ በደረሰ አደጋ የ38 ፍልሰተኛ ዜጎች ሕይወት አልፎ ነበር።

ከጅቡቲ ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት የሚደረገው ህገ ወጥ ጉዞ እጅግ አደገኛ ከመሆኑም በላይ በየጊዜው የዜጎችን ሕይወት እያሳጣ እንደሆነ በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ገልጿል።

በዚህም ዜጎች ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ለከፋ አደጋ እየዳረጉ ይገኛሉ ብሏል።

ዜጎች የሀሰት ስብከት በመታለል ውድ ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው በዚህ አደገኛ የጉዞ መስመር ከመንቀሳቀስ እንዲቆጠቡ እና የፍትህ አካላትም ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን ከገጠራማ የአገራችን አካባቢዎች ዜጎቻችን በመመልመል ለስደት በሚዳርጓቸው ግለሰቦች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ አሳስቧል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

የእስላማዊ ትብብር ድርጅት (ኦአይሲ) እስራኤል በጋዛ "አሰቃቂ ጭፍጨፋ" እየፈፀመች ነው አለ። በካን ዩኒስ ናስር ሆስፒታል ውስጥ የ283 ሰዎች አስከሬን በጅምላ ተቀብሮ መገኘቱ ተገልጿል።እስ...
23/04/2024

የእስላማዊ ትብብር ድርጅት (ኦአይሲ) እስራኤል በጋዛ "አሰቃቂ ጭፍጨፋ" እየፈፀመች ነው አለ።

በካን ዩኒስ ናስር ሆስፒታል ውስጥ የ283 ሰዎች አስከሬን በጅምላ ተቀብሮ መገኘቱ ተገልጿል።
እስራኤል ለአራት ወራት ውጊያ ካደረገችበት ካን ዩኒስ ከሁለት ሳምንት በፊት መውጣቷን ተከትሎ ነው የጅምላ መቃብሩ በናስር የህክምና መስጫ ማዕከል የተገኘው።

መቀመጫውን ሳኡዲ አረቢያ ያደረገው የእስላማዊ ትብብር ድርጅት ባወጣው መግለጫ የጅምላ መቃብሩ “እስራኤል በሆስፒታሉ የተጠለሉና በመቶዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮችና ታማሚዎችን አሰቃይታ መግደሏን ያመላክታል” ብሏል።
በህክምና ተቋሙ ውስጥ የተገኘው የጅምላ መቃብር “የጦር ወንጀል፣ በሰብአዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀልና የተደራጀ የመንግስት ሽብርተኝነት” መፈጸሙን እንደሚያሳይም ጠቁሟል።

ይህ ድርጊት ምርምራና ተጠያቂነት ይፈልጋል ያለው የእስላማዊ ትብብር ድርጅት፥ እስራኤል በአለማቀፉ የወንጀል ህግ ማዕቀብ ሊጣልባት እንደሚገባም አሳስቧል።

አለማቀፉ ማህብረሰብ በተለይም የጸጥታው ምክርቤት “እስራኤል በጋዛ ሰርጥ የምትፈጽመውን ወረራና የጦር ወንጀል” እንዲያስቆሙም በድጋሚ ጥሪውን አቅርቧል ሲል አናዶሉ ዘግቧል።

እስራኤል በአለማቀፉ የፍትህ ፍርድቤት በዘር ማጥፋት ወንጀል ክስ እንደተመሰረተባት ይታወሳል።

ቴል አቪቭ ንጹሃንን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶቿን እንድታቆምና የሰብአዊ ድጋፎች ያለገደብ እንዲገቡ እንድትፈቅድ ውሳኔ መተላለፉም አይዘነጋም።

የጸጥታው ምክርቤትም በጋዛ በአስቸኳይ ተኩስ እንዲቆም ውሳኔ ቢያሳልፍም ሰባተኛ ወሩን የያዘውና ከ34 ሺህ በላይ ፍልስጤማውያንን ህይወት የቀጠፈው ጦርነት እስካሁን አልቆመም።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ሊባኖስ  ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ። አደጋው ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም እየተጓዘ የነበረ የቤት አውቶሞቢል  ከኮሶበር ወደ አ...
23/04/2024

በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ሊባኖስ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ።

አደጋው ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም እየተጓዘ የነበረ የቤት አውቶሞቢል ከኮሶበር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ከነበር የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ጋር ቀሲም በተባለ ልዩ ቦታ በመጋጨቱ የደረሰ ነው።

በአደጋው የአራት ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፈ በ14 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት፤ በስምንት ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

የደብረ ሊባኖስ ወረዳ ትራፊክ ደህንነት አስተባባሪ ረዳት ኢንስፔክተር ኃይለማርያም ደባሌ÷ የአደጋው መንስኤ በፍጥነት ማሽከርከር እና ቅድሚያ አለመሰጠት መሆኑን መናገራቸዉን ከወረደዉ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

ብፁዕ አቡነ ዲሜጥሮስ የሊባኖስ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገረ ስብከት አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምህላ፣ የዕርቅ እና የጸሎት አዋጅ አውጀዋል። ብፁዕነታቸው ያስተ...
23/04/2024

ብፁዕ አቡነ ዲሜጥሮስ የሊባኖስ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገረ ስብከት አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምህላ፣ የዕርቅ እና የጸሎት አዋጅ አውጀዋል።

ብፁዕነታቸው ያስተላለፉት ሙሉ መልእክት እንዲህ የሚል ነው።

በመላው ዓለም ለምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ

"ቅረቡ ኀቤሁ ወያበርኅ ለክሙ" ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ያበራላችሁማል:: መዝ 33፥5

የምሕላ፣ የዕርቅ እና የጸሎት አዋጅ።

በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም በየጊዜው ረኀብ፣ መከራ፣ የሰው ልጅ ዕልቂት ማስተናገድ የተለመደ እየሆነ መጥቷል። በሀገርም ሆነ በመላው ዓለም የሚደርሰው መከራ በሰው አለመታዘዝ ምክንያት ከእግዚአብሔር የተላከ የመቅሠፍት በትር መሆኑን አስተዋይ አእምሮ ያለው ሁሉ የሚገነዘበው ሀቅ ነው።

በመሆኑም እግዚአብሔር በምሕረቱ እንዲጎበኘን በቸርነቱ ይቅር እንዲለን ሁላችንም ወደ እግዚአብሔር በምህላ፣በዕርቅ፣ በጾም እና በጸሎት መቅረብ ይገባናል።

"ወደ እኔ ተመለሱ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር" ዘካ 1፥3 "ኅሡ ሰላማ ለሀገር ወጸልዩ በእንቲአሃ ኀበ እግዚአብሔር እስመ በሰላመ ዚአሃ ይከውን ሰላምክሙ" ኤር 29፥7 ስለ ሀገር ሰላም ወደ እግዚአብሔር ጸልዩ በእርሷ ሰላም ሰላማችሁ ይሆናልና በማለት የሀገር ሰላም የሰው ሁሉ ሀሳብ መሆን እንዳለበትና ሁሉም ስለ ሰላም ወደ ፈጣሪው መቅረብ እንዲገባው ቅዱስ መጽሐፍ ያስረዳል።

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በወንጌል "በስሜ ብትሰባሰቡ በመካከላችሁ እሆናለሁ" ማቴ 18፥20 በሚለው አምላካዊ ቃል መሠረት በፍቅር ልንሰባሰብ ያስፈልጋል። ሰላም በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት እና በዕርቅ እንጂ በጦርነትና በእንቢተኝነት አይመጣምና ፍጹም ሰላም ለዓለም እንዲሆን በመላው ዓለም ያላችሁ ሰላምን የምትሹ ሁሉ ስለሀገር፣ ሰለዓለም መጸለይ ይገባናል።

ስለሆነም በመላው ዓለም እና በኢትዮጵያ በየጊዜው በሚከሰተው ረኀብ፣ ጦርነት፣ የሰው ልጅ ዕልቂት ምክንያት ሀገረ ስብከታችን በተደጋጋሚ የምህላ፣ የዕርቅ አዋጅ ሲያወጣ የቆየ ቢሆንም ነገርግን ሁላችንም የእግዚአብሔርን ድምፅ ሰምተን ባለመመለሳችን እስካሁን ድረስ መከራችን እንደቀጠለ ነው።

በሀገረ ስብከታችን እና በመላው ዓለም የምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ከእግዚአብሔር ቁጣ ለማምለጥ ከመከራውም ለመዳን ዛሬን እንጂ ነገን በሕይወት ለመኖራችን እርግጠኛ ባልሆንበት የሕይወት ዘመናችን ልዩነትን ትተን አንድነትን፣ ኃጢአትን ትተን ጽድቅን፣ ጦርነትን ትተን ሰላምን በመከተል አምላካችን እንዲታረቀን በቤተክርስቲያን ስም እናሳስባለን።

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

ውድ የእፍታ መረጃ ቤተሰቦች ከውድ ጊዜያቹ ላይ ቀንሳቹ በቻናላችን የምናጋራቸውን ዜናዎች በማንበብ እና አስተያየት በመስጠት  ለምትሰጡንን ገንቢ ሀሳብ ከልብ እናመሰግናለን!! አስተያየቶቻቹ አ...
23/04/2024

ውድ የእፍታ መረጃ ቤተሰቦች ከውድ ጊዜያቹ ላይ ቀንሳቹ በቻናላችን የምናጋራቸውን ዜናዎች በማንበብ እና አስተያየት በመስጠት ለምትሰጡንን ገንቢ ሀሳብ ከልብ እናመሰግናለን!!

አስተያየቶቻቹ አይለዩን። እኛን የበለጠ ስለሚያድሱንና ስለሚገነቡን!!!


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

የተለያዩ የጦር መሣሪያ በቆመ ባጃጅ ዉስጥ መገኘቱን ፖሊስ ገለፀ። በምዕራብ ኦሞ ዞን ቤሮ ወረዳ  ሕገ-ወጥ መሣሪያው የተያዘው ሲያሊ በተሰኘ ቀበሌ ወስጥ  ህፃናት በሚጫወቱበት ቦታ ቁሞ በነበ...
23/04/2024

የተለያዩ የጦር መሣሪያ በቆመ ባጃጅ ዉስጥ መገኘቱን ፖሊስ ገለፀ።

በምዕራብ ኦሞ ዞን ቤሮ ወረዳ ሕገ-ወጥ መሣሪያው የተያዘው ሲያሊ በተሰኘ ቀበሌ ወስጥ ህፃናት በሚጫወቱበት ቦታ ቁሞ በነበረ ባለ ሶስት እግር( ባጃጅ) ወስጥ ያለን ፌስታል ጎትተው በሚያወጡበት ሰአት መገኘቱ ተጠቁሟል።

በፌስታሉ ውስጥ 1 ኤፍ ዋን የተሰኘ የእጅ ቦንብን ጨምሮ የጦር ሜዳ አጉሊ መነፀር፣ 18 ጥይት እንዲሁም 1 የወገብ ትጥቅ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።

ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪው (ባጃጅ) ባለንብረት ለጊዜው እንዳልታወቀና የወረዳው ፖሊስ በምርመራ ሒደት ላይ እንደሚገኝም እፍታ መረጄ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፃ ለመመልከት ችሏል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

👇👇👇👇👇👇👇👇
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/-Subscrib?si=yxWZnPB9dVumDLX1
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/efitamedia
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የፌስቡክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61558303567204

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቀሲስ በላይ ጉዳይ ከቤተክርስቲያኗ ጋር የሚያገናኘው ነገር እንደሌለ አስታወቀች። ከሰሞኑ ቀሲስ በላይ መኮንን በሀተኛ ሰነድ 6 ሚሊዮን 50 ሺህ ...
22/04/2024

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቀሲስ በላይ ጉዳይ ከቤተክርስቲያኗ ጋር የሚያገናኘው ነገር እንደሌለ አስታወቀች።

ከሰሞኑ ቀሲስ በላይ መኮንን በሀተኛ ሰነድ 6 ሚሊዮን 50 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ገንዘብ ለማዘዋወር ሞክረዋል በሚል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉበት ጉዳይ ከቤተክርትያኗ ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር እንደሌለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ማስታወቋን ዶቸቬለ ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ግለሰቡ በቤተክርስቲያኗ በከፍተኛ ኃላፊነት የሚያገለግሉ ቢሆንም፤ ተጭበርብሯል ከተባለው ሰነድ ጋር ግን ቤተክርስቲያኗን የሚያገናኛት ምንም ነገር እንደሌለ አስታውቃለች፡፡

መምህር ዶ/ር አካለወልድ ተሰማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትሪያርክ ህዝብ ግንኙነት የሚዲያ ክፍል ዋና ኃላፊ “ሊቀ አዕላፍ በላይ መኮንን በህግ ጥላ ስር በዋሉበት ጉዳይ ላይ ቤተክርስቲያን ጉዳዩን የመከታተል ጥረት ላይ ትገኛለች ማለታቸውን ሸገር ታይምስ ሚዲያ ከዜና ምንጩ ዘገባ ለመመልከት ችሏል።

ኃላፊው “እስካሁን በተደረገው ክትትል “ሊቀ አዕላፍ በላይ መኮንን በህግ ጥላ ስር የዋሉበት ጉዳይ ከቤተክርስቲያናችን ጋር የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ እንደሌለና በግል ህይወታቸው ውስጥ የገጠማቸው ነገር እንደሆነ ነው የተረዳነው” ብለዋል።

መምህር ዶ/ር አካለወልድ አክለውም በቀጣይ ጉዳዩ ቤተክርስቲያንን የሚጎዳ ነገር አለው ወይ? የሚለው በህግ ክፍል በኩል ማጣራት እንዲደረግ ትዕዛዝ መተላለፉንም አመልክተዋል፡፡


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ከዩኒቨርስቲው ፊት ለፊት በተለምዶ "ፍየል ገበያ" አካባቢ አንድ ወጣት ሞቶ ተገኝቷል። የሟችን ማንነት ማወቅ ያልቻሉት በአካባቢው ላይ የነበሩ ሰዎች ተደናግጠው ሲመለከቱ ነ...
22/04/2024

ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ከዩኒቨርስቲው ፊት ለፊት በተለምዶ "ፍየል ገበያ" አካባቢ አንድ ወጣት ሞቶ ተገኝቷል።

የሟችን ማንነት ማወቅ ያልቻሉት በአካባቢው ላይ የነበሩ ሰዎች ተደናግጠው ሲመለከቱ ነበር።

በአካባቢዉ የተፈጠረውን ግርግር ተከትሎ ቦታው ላይ የደረሰው የከተማው ፖሊስ ቦታው የገበያ ግርግር ያለበት ከመሆኑ የተነሳ አስክሬኑን ፎቶ ከሚያነሱ ግለሰቦች ሲጠብቅ ነበር።

በስፍራዉ የተገኙ የአካባቢዉ ሰዎች ግራ በሚያጋባ ሁኔታ ድንገት ሞቶ እንዳዩትና ከዚህ በፊት አይተዉት እንደማያውቁ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ስለሁኔታዉ የጠየቅናቸዉ በቦታዉ የደረሱ የፖሊስ ቡድን አባላት በበኩላቸዉ ጉዳዩን የማጣራት ስራ እንደተጀመረ በመግለፅ ለጊዜዉ ለህዝብ የሚሰጥ መረጃ እንደሌላቸው ገልጸዋል።

ሟች የዩኒቨርስቲ ተማሪ እንዳልነበር የተረጋገጠ ሲሆን በሟች አስክሬን ላይ ጉዳት ስለማይታይ የሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ተወስዶ ከተመረመረ በኋላ ለተጨማሪ ምርመራ ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ መወሰኑን ገልጿል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዘርፌ ወንድማገኝ ለአምስት ዓመታት ከአትሌቲክስ ታገደች:: የ21 ዓመቷ የመካከለኛ ርቀት አትሌት ለአምስት ዓመታት መታገዷን የገለጠው አትሌቲክስ ኢንቴግሪቲ ዩኒት የተባለው...
22/04/2024

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዘርፌ ወንድማገኝ ለአምስት ዓመታት ከአትሌቲክስ ታገደች::

የ21 ዓመቷ የመካከለኛ ርቀት አትሌት ለአምስት ዓመታት መታገዷን የገለጠው አትሌቲክስ ኢንቴግሪቲ ዩኒት የተባለው ተቋም ነው።

ተቋሙ በቀድሞው ትዊተር በአሁኑ ኤክስ ሰሌዳው ላይ በለጠፈው መግለጫ አትሌቷ ምርመራ ከተደረገላት በኋላ ቅጣት ማስተላለፉን አሳውቋል።

የዓለም አትሌቲክስ አካል የሆነው ይህ ተቋም ባወጣው መግለጫ፣ አትሌቷ ሁለት የተከለከሉ ንጥረ-ነገሮችን መውሰዷን አምናለች ብሏል።

ዘርፌ፤ ቴስቶስቴሮን የተባለውን እና ኢፒኦ የተሰኘውን አትሌቶች በደማቸው ውስጥ የበለጠ ኦክሲጅን እንዲኖር የሚያደርግ ንጥረ ነገር መውሰዷን አምናለች።

ዘርፌ በቶኪዮ ኦሊምፒክስ በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ስምንተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ይታወሳል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

ሶስት አይነ ስውር መንታ ልጆች ያለ አባት እያሳደገች ያለች እናት። ይህቺን ጀግና እናት ተዋወቋት። ትዕግስት በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪ አግኝታለች ...
22/04/2024

ሶስት አይነ ስውር መንታ ልጆች ያለ አባት እያሳደገች ያለች እናት። ይህቺን ጀግና እናት ተዋወቋት።

ትዕግስት በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪ አግኝታለች ትዳር መስርታ ልጆች ለማግኘት ወሰኑ፣ ሶስት ልጆች እርጉዝ መሆኗን አወቀች፣ ሶስቱም ልጆች ተወለዱ። የመወለጇ ጊዜ ወቅት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማስተርስ ዲግሪ ትምህርቷን ባጠናቀቀችበት ወቅት ነበር ትምህርቷን አጠናቃ ተመርቃለች።

የተወዱት ልጆች አንደርወይት ነበሩ አያድጉም የሚል ጭንቀት ነበረብኝ ራሴን ሁላ ለማጥፋት ወስኜ ነበር ስትል በሰይፉ በኢቢኤስ ላይ ስትናገር ፋስት መረጃ ተመልክቷል። በተጨማሪም ሶስቱም አይነ ስውር መሆናቸውን አወቅን እንዲሁም ወንዱ የኦቲዝም ተጠቂ ነበር ትላለች ትዕግስት።

ባለቤቴ በልጆቹ እንደዚህ መሆን በጣም ይጨነቅ ነበር በጭንቀት ታመመ በአጭር ጊዜ ህመም ህይወቱ አለፈ ትላለች። ከዛ በኋላ ያለው ከባድ ነበር ለእኔ እዚህ መድረስ የእናቴ፣ የቤተሰቤ ጥንካሬ ትልቅ አስተዋጾ አለው ብላለች።

በአሁኑ ወቅት ሙሉ ጊዜዋን ስራ አቁማ ልጆቿን በማሳደግ ላይ ትገኛለች። ህክምና ካገኙ የማየት ተስፋ እንዳላቸው ተነግሯል። ኮሚቴ ተቋቁሞ ገቢ እየተሰበሰበ ይገኛል የፋስት መረጃ ቤተሰብም ኮሚቴው አካውንቶችን ይፋ እንዳደረግ የምትችሉትን ድጋፍ በማድረግ የትዕግስትን ጫና በአጭር ጊዜ እንደምናቀል ጥርጥር የለውም።

ይህን መረጃ ላይክ፣ ሼር በማድረግ ሁሉም ጋር እንዲደርስ ያድርጉ ከትዕግስት ጎን መሆናችንን እናሳይ 🙏፡፡


_
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

በመዲናዋ የሰራተኛ ምደባን በመቃወም ስራ ያልገቡ ሰራተኞች ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ ጥሪ ቀረበ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተደረገውን የመንግስት ሰራተኞች ምዘና ተከትሎ የተከናወነ...
22/04/2024

በመዲናዋ የሰራተኛ ምደባን በመቃወም ስራ ያልገቡ ሰራተኞች ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ ጥሪ ቀረበ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተደረገውን የመንግስት ሰራተኞች ምዘና ተከትሎ የተከናወነውን የሰራተኛ ምደባ በመቃወምና በሌሎች ግላዊ የጥቅም ጥያቄዎች ምክንያት ስራ ያልገቡ ሰራተኞች ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ የከተማው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት አስተዳደር ቢሮ ጥሪ አቅርቧል፡፡

ሰራተኞች ባስመዘገቡት ውጤት መሰረት የስራ ድልድል መደረጉንና ሰራተኞች በተቻለ መጠን በሚኖሩበት ወረዳ እና ክፍለ ከተማ አካባቢ እንዲመደቡ መደረጉን የከተማዋ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት አስተዳደር ቢሮ የስራ አመራር ዘርፍ ሀላፊ አቶ መላኩ ጉራቻ ተናግረዋል፡

ምደባው ከተከናወነ በኋላ በሁሉም ክፍለ ከተማ አገልግሎቶች ሳይቋረጡ እንዲሰጡ እየተደረገ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፤ በዚህ ሁኔታ ግን መመሪያውን በመቃወም እና በሌሎች ምክንያቶች ወደ ስራ ገበታቸው ያልተመለሱ ሰራተኞች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡

አሁንም በምደባው ላይ ቅሬታ እየቀረበ በመሆኑ ወደ ስራ ገበታቸው ያልተመለሱ ሰራተኞችን ሙሉ ቁጥር አሁን ላይ ማወቅ እንደማይቻል አመላክተዋል፡፡

በስራ ምደባው 3ሺ 266 ሰራተኞች ከነበሩበት ደረጃ ዝቅ ሳይደረጉ፤ ወደ ሌላ ቦታ በማዘዋወር መመደባቸውን ሃላፊው አስታውቀዋል፡፡


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የቦክስ ውድድር  ቤተልሔም ወልዴ  ለኢትዮጵያ የነሐስ ሜዳልያ አስገኝታለች።  _____ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የ...
20/04/2024

በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የቦክስ ውድድር ቤተልሔም ወልዴ ለኢትዮጵያ የነሐስ ሜዳልያ አስገኝታለች።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

ቲክቶክሩ  ማጅራት መቺ !!  ከ3 ወር በፊት አንድ ኢትዮጵያውያን ወገናችን ከሞተር ላይ ወድቆ ከወገቡ በታች እግሩ ይጎዳል:: ይህን አጋጣሚ በመጠቀም በቲክቶክ ስሙ Akirsh ከ363 ሺህ በ...
20/04/2024

ቲክቶክሩ ማጅራት መቺ !!

ከ3 ወር በፊት አንድ ኢትዮጵያውያን ወገናችን ከሞተር ላይ ወድቆ ከወገቡ በታች እግሩ ይጎዳል::

ይህን አጋጣሚ በመጠቀም በቲክቶክ ስሙ Akirsh ከ363 ሺህ በላይ followers ያለው ልጅ ከጎደኞቹ ጋር በመሆን በቲክቶክ ለተጎዳው ልጅ ማሳከሚያ ገንዘብ ማሰባሰብ ይጀመራል ።

ገንዘቡም ኢትዮጵያውያን:ከውስጥም ከውጪም የለገሱ ሲሆን ፤ በልጅ ስም ያሰባሰብኩትን ገንዘብ ልጁ መዳን ስለማይችል ወደ 350 ሺህ ብር ሰይጣን አሳስቶኝ አጥፍቼዋለው ብሎ በቪዲዮ አምኗል::

ይህ ከህግ አንፃር ራስ ላይ መመስክር ስለሆነ ሌሎችን እንዲማሩበት እንዲሁም በዚህ ቲክቶክ በሚባል አፕ ብዙ የማጭበርብር ዘዴ እየቀጠለ ነው ። ይሄን ልጅ በቁጥጥር ስር ውሎ የወስደውን ገንዘብ ና ባጠፉው ጥፋት ልክ እርምጃ እንዲወስድበት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለሚመለከተው አካል በትህትና ያሳውቃል::
ፊስቡክ ላይ ፖስቱ በደንብ እንዲሸራሸር .. ሼር ፣ ላይክ ኮሜንት አድርጉት።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

በጀርመን የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ምዕምናን ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ። በጀርመን የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ምዕምናን በፍራንክፈርት ከተማ ...
20/04/2024

በጀርመን የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ምዕምናን ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ።

በጀርመን የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ምዕምናን በፍራንክፈርት ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።

በሰልፉ ላይ በተለያዩ የጀርመን ከተሞች የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት አባቶች እና ምዕምናን እንዲሁም ሌሎች የሌላ እምነት ተከታዮች መሳተፋቸውን፤ በጀርመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ካሕናት መራዊ ተበጀ ለዶይቼ ቬለ አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ በተለይ ባለፉት “ስድስት ዓመታት ውስጥ የተደረገው ግፍ፣ ሰቆቃ፣ ጩኸት፣ የገዳማት መደፈር፣ የመናንያን መነኮሳት መሞት፣ የሕዝቦች መፈናቀል፣ በሀገሪቱ ላይ የሚደርሰው እና የሚታየው ቀውስ ሁሉ” ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንዳስገደዳቸው ሊቀ ካሕናት መራዊ ተበጀ ተናግረዋል።

ሊቀ ካሕናት መራዊ ተበጀ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ውስጥ በሚገኘው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የተፈጸመውን የመነኮሳት ግድያ በምሳሌነት ጠቅሰዋል።

“በደብረ ኤልያስ የተደረገው፣ በሌሎቹም ቦታዎች የተደረገው ጥፋት እና እልቂት እጅግ እያስቆጨን፣ እጅግም እያናደደን፣ ብሶታችንም ከዕለት ወደ ዕለት እየበዛ፣ እየከፋ በመሔዱ እነሆ ድምጻችንን እናሰማለን” ሲሉ ተናግረዋል።

በፍራንክፈርት ከተማ በተካሄደው በዚህ ሰልፍ ላይም "በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ካህናትና ምዕምናን ላይ የሚደረገው ማዋከብ እና ግድያ ይቁም!"፣ "ቤተክርስቲያን ላይ ግልጽ የጥፋት ቅስቀሳ የሚያደርጉ ሰዎች ተጠያቂ ይሁኑ" የሚሉና ሌሎች መፈክሮች ተስተውለዋል።

በወራት በፊት የካቲት 12 /2016 የጥንታዊው እና በታሪካዊው ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አራት መነኮሳት በግፍ መገደላቸውና ይህም ግድያ በ " ሸኔ ታጣቂዎች" መፈፀሙን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገልጻ ነበር።

በወቅቱ ከገዳሙ ከተወሰዱት 5 መነኮሳት ውስጥ አንድ መነኩሴ ሳይገደሉ በሕይወት ተርፈው ወደ ገዳሙ የተመለሱ ሲሆን፤ ከሟቾቹ ጋር የነበሩት እኚህ መነኩሴ ግድያውን ፈጽሟል ከተባለው ታጣቂ ቡድኑ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው ተደርሶበት በቁጥጥር ሥር መዋላቸው መገለጹም ይታወሳል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

ኢትዮጲያዊቷ አትሌት ከ10 ዓመታት በፊት ያሸነፈችበትን የቦስተን ማራቶን 100 ሺ ዶላር እስካሁን ድረስ አልተሰጣትም። የ36 ዓመቷ ኢትዮጲያዊቷ አትሌት ብዙነሽ ዲባ የረጅም ርቀት አትሌት ስት...
20/04/2024

ኢትዮጲያዊቷ አትሌት ከ10 ዓመታት በፊት ያሸነፈችበትን የቦስተን ማራቶን 100 ሺ ዶላር እስካሁን ድረስ አልተሰጣትም።

የ36 ዓመቷ ኢትዮጲያዊቷ አትሌት ብዙነሽ ዲባ የረጅም ርቀት አትሌት ስትሆን እኤአ በ2014 በቦስተን ማራቶን ብታሸንፍም በአሸናፊነቷ ሊሰጣት ይገባ የነበረው 100 ሺ ዶላር እስካሁን እንዳልተሰጣት ከሲቢኤስኒውስ ኒውዮርክ ጋር ባደረገችው ቆይታ ተናግራለች።

በወቅቱ በውድድሩ ብዙነሽ ዲባ ሁለተኛ ወጥታ የነበረ ቢሆንም አንደኛ የወጣችው አትሌት ውድድሩ ከተደረገ ከሁለት ዓመት በኃላ በ2016 በዶፒንግ አበረታች መድኃኒት በመውሰድ ያገኘችው ውጤት ተሰርዞ አንደኝነቱን አትሌት ብዙነሽ ዲባ አግኝታለች። ኑሮዋን በአሜሪካ ያደረገችው አትሌቷ የሁለት ልጆች እናት ስትሆን ዳግም ወደ ልምምድ መመለሷን ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል።

አትሌቷ በካሊፎርኒያ ዓለም አቀፍ ማራቶን፣ በሳንዲያጎ ማራቶን፣ በሎስ አንጀለስ ማራቶን፣ በግራንድ ማ ማራቶን፣ በቦስተን ማራቶን እና በቲዊን ሲቲ ታ ማራቶን አሸናፊ ነች። በኒውዮርክ ሲቲ ማራቶን ሶስት ጊዜ ምርጥ አስር ሆና አጠናቃለች።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

" ስጋት ፈጥሮብናል " - ኤምባሲዎቹ ሰሞነኛውን የሰሜን ኢትዮጵያን ጉዳይ አስመልክቶ በአዲስ አበባ የሚገኙት ፦- የካናዳ፣- የፈረንሳይ፣- የጀርመን፣- የጣሊያን፣- የጃፓን፣ - የእንግሊዝ እ...
20/04/2024

" ስጋት ፈጥሮብናል " - ኤምባሲዎቹ

ሰሞነኛውን የሰሜን ኢትዮጵያን ጉዳይ አስመልክቶ በአዲስ አበባ የሚገኙት ፦
- የካናዳ፣
- የፈረንሳይ፣
- የጀርመን፣
- የጣሊያን፣
- የጃፓን፣
- የእንግሊዝ እና የአሜሪካ ኤምባሲዎች የጋራ አጭር መግለጫ አውጥተዋል።

በዚህም ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ " #አወዛጋቢ " በሆኑት አካባቢዎች ከሰሞኑን የተፈጠረው ግጭት " ስጋት ፈጥሮብናል " ብለዋል።

ሁሉም ወገኖች የታጣቂ ኃይሎች ትጥቅ ማስፈታት ፣ ብተና እና መልሶ ማቋቋም / / እንዲሁም ተፈናቃዮችን #በሰላም ወደ ነበሩበት መመለስ ላይ አበክረው መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

" ውጥረቱ እንዲረግብ እና ጥበቃ እንዲደረግላቸው እናሳስባለን " ብለዋል።

በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የተወሳሰቡ የፖለቲካና የጸጥታ ቀውሶችን ለመፍታት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ ውይይት ማድረግ ብቸኛው መንገድ ነው ብለዋል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

29 ሺሕ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን ተገለጸ። ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት፤ 29 ሺሕ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካ...
20/04/2024

29 ሺሕ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን ተገለጸ።

ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት፤ 29 ሺሕ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት (ኦቻ) አስታውቋል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት (ኦቻ) ትናንት ሚያዝያ 11/2016 ባወጣው ሪፖርት፤ በግጭቱ ምክንያት የተፈናቀሉት ዜጎች በቆቦ፣ ሰሜን ወሎ እና ሰቆጣ ከተማ በሚገኙ መጠለያዎች ላይ ተጠልለው እንደሚገኙ ገልጿል፡፡

ከተፈናቀሉት 29 ሺሕ ዜጎች ውስጥ 70 በመቶዎቹ ሕጻናት እና ሴቶች ሲሆኑ፤ ቀሪዎቹ አዛውንቶች እና ታዳጊዎች ናቸው ያለው ሪፖርቱ፤ ከአጠቃላይ ተፈናቃዮች ውስጥ 23 ሺሕ የሚሆኑት ቆቦ ቀሪዎቹ 5 ሺሕ 980 የሚሆኑት ደግሞ ሰቆጣ ከተማ ተጠልለው እንደሚገኙ ገልጿል።

በአካባቢው ያለው ሁኔታ አሁንም ያልተረጋጋ በመሆኑ ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ ይችላሉ ያለው ጽ/ቤቱ፤ አሁን ላይ ለተፈናቃሉ ዜጎች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ሕይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።

ነገር ግን ለተፈናቃዮቹ የሚቀርበው የምግብ እና ውሃ እጥረት አሳሳቢ መሆኑን በመግለጽ፤ ተፈናቃዮቹ አፋጣኝ የነፍስ አድን እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው አመላክቷል።

በተጨማሪም ለጋሽ አገራትና አጋር ተቋማት የሚያደርጉት ድጋፍ ውስን በመሆኑ፤ አሁን ላይ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ ለተጎዱ ተፈናቃዮች የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል።

ኦቻ ለተፈናቃዮቹ በተለይም መጠለያ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎችና የሕክምና አገልግሎት በአፋጣኝ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ያሳሰበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ አደጋ መከላከል እና ዝግጁነት ኮሚሽን ሰራተኞች ጉዳዩን ለመከታተል ሚያዚያ 11 ቀን 2016 ወደ ስፍራው ማቅናታቸውንም ገልጿል፡፡

ባሳለፍነው ሳምንት የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱባቸው የራያ አካባቢ ዳግም ግጭት መቀስቀሱ የሚታወስ ሲሆን፤ በዚህም ግጭት የህወሃት ታጣቂዎች ወደ ራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መምጣታቸውን ተከትሎ፤ የአካባቢው ነዋሪዎች ቤታቸውን ጥለው ለመሰደድ መገደዳቸው ተገልጿል፡፡

የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎም፤ የአማራ ክልል መንግሥት "ህወሕት ለአራተኛ ጊዜ ወረራ ፈጽሞብኛል" ሲል ወቅሷል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ፤ በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፣ "ክሥተቱ በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ወይም በህወሓት አልያም በትግራይ እና በአማራ ክልሎች መካከል የተፈጠረ ግጭት አይደለም" ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የፌደራሉ መንግሥት በበኩሉ የይገባኛል ጥያቄ በሚነሣባቸው በእነዚህ አካባቢዎች ባለው ወቅታዊ ሁኔታ፤ ሁሉም ወገኖች ለፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት እንዲገዙና ከተንኳሽ ተግባራት እንዲቆጠቡ የጠየቀ ሲሆን፤ ሁሉም ወገኖች ካለፈው ግጭት ትምህርት መውሰድ እንዳለባቸው አሳስቧል።


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

"በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ነገ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉና በከፊል ይቋረጣል" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ በኤሌክትሪክ ጥ...
20/04/2024

"በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ነገ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉና በከፊል ይቋረጣል" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

በአዲስ አበባ ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ በኤሌክትሪክ ጥገና ሥራ ምክንያት ነገ ከጠዋቱ 3:00 እስከ ቀኑ 10:00 ድረስ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉና በከፊል እንደሚቋረጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።

በዚህም መሠረት ነገ ሚያዚያ 13 ቀን 2016 ከጠዋቱ 3:00 እስከ ቀኑ 10:00 ሰዓት ድረስ፤ በአዲስ አበባ ከተማ ፈጥኖ ደራሽ፣ ኮልፌ ኮምርሄንሲቭ ት/ቤት፣ ዱ ሆቴል፣ ታይዋን ገበያ፣ ኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል፣ እህል በረንዳ፣ አውቶብስ ተራ፣ አዲስ ከተማ ት/ቤት፣ ገነሜ ት/ቤት፣ አማኔኤል ቤ/ክ፣ ሰብስቴሽን አካባቢ፣ መሳለሚያ፣ እሳት አደጋ፣ ሳንባ ነቀርሳ፣ አበበ ቢቂላ ስታዲየም፣ ታይዋን፣ ሆላንድ ኤምባሲ፣ አማኑኤል ቤ/ክ፣ አማኑኤል ሆስፒታል፣ ሻወል ደማ ት/ቤት፣ ብርጭቆ፣ አስኮ 40/60 ኮንዶሚኒየም፣ ፊሊጶስ ቤ/ክ፣ እስላም መቃብር፣ ሎሚ ሜዳ፣ ጠሮ መስጊድ፣ ቀራንዮ መድህንዓለም ቤ/ክ፣ ቤተል ሆስፒታል፣ ቤተል እሳት አደጋ፣ ጦር ኃይሎች ሆስፒታል፣ መኮንኖች ክበብ፣ ገዳመ ኢየሱስ፣ ወይብላ ማርያም፣ አውጉስታ፣ አንፎ፣ ወይራ ሰፈር፣ ወይራ ኮንዶሚኒየም፣ ሞቢል፣ ራሺያ ካምፕ፣ ተዘንአ ሆስፒታል፣ ሙስና ሰፈር እና አካባቢዎቻቸው የጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉና በከፊል እንደሚቋረጥ ተገልጿል፡፡

በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚገኙ ደንበኞች ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አገልግሎቱ አሳስቧል፡፡


_____
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፤ የእፍታ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይቀላቀሉ! መረጃዎችን ለሌሎች ያጋሩ ሀሳብ አስተያየትዎን ይስጡ።

በ1500 ሜትር ታሪክ 3ኛውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አትሌት ጉድፍ ፀጋዬ አሸነፈችአትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ በዋንዳ ዳይመንድ ሊግ 3 ደቂቃ ከ50 ሰከንድ ከ30 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ሶስተኛው...
20/04/2024

በ1500 ሜትር ታሪክ 3ኛውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አትሌት ጉድፍ ፀጋዬ አሸነፈች

አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ በዋንዳ ዳይመንድ ሊግ 3 ደቂቃ ከ50 ሰከንድ ከ30 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ሶስተኛውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ በ1500 ሜትር ውድድር አሸንፋለች።

 #ዝቋላ በወራት በፊት የጥንታዊው እና በታሪካዊው ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አራት መነኮሳት  በግፍ መገደላቸው ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስ...
20/04/2024

#ዝቋላ

በወራት በፊት የጥንታዊው እና በታሪካዊው ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አራት መነኮሳት በግፍ መገደላቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ግድያው በ " ሸኔ ታጣቂዎች " መፈፀሙን መግለጿም አይዘነጋም።

በወቅቱ አንድ የገዳሙ መነኩሴ ከሟቾቹ ጋር የነበሩ ዱካቸው መጥፋቱም ሲገለጽ እንደነበር ይታወሳል።

እኚሁ መነኩሴ ግድያውን ፈጽሟል ከተባለው ታጣቂ ቡድኑ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው ተደርሶባቸው በእስር ቤት እንዳሉ ተሳምቷል።

ይህ የተሰማው ከቀናት በፊት በመንግስታዊ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች በዝቋላ ገዳም በታጣቂዎች ስለሚደርሰው ግፍን በተመለከተ በተሰራጨ አንድ ፕሮግራም ላይ የገዳሙ አባቶች ሲናገሩ ነው።

በወቅቱ ምን ሆነ ?

የካቲት 12 /2016 ዓ/ም ከገዳሙ ከተወሰዱት እና በኃላም ለምምክር ተብለው ከተጠሩት 5 መነኮሳት አንድ መነኩሴ ሳይገደሉ በህይወት ተርፈው ወደ ገዳሙ ተመልሰዋል።

አባ ገ/ኢየሱስ ፀጋዬ ፦

" መጀመሪያውኑ መረጃውን የሚሰጥ ከኛ ውስጥ አደራጅተዋል። እነሱ ናቸው የኛን እያንዳንዱን መረጃ የሚሰጧቸው።

ይሄን እኛ አናውቅም በወቅቱ ፤ አሁንም ቢሆን ሀገር መከላከያ መጥቶ መረጃው እንዲህ እንዲህ ነው ብሎ ስልካቸውን ጠልፎ ያለውን መረጃ ከእንቅስቃሴያቸው አኳያ ነው ያወጣልን እንጂ ውስጡን አናውቅም።

እንደኛው ቆብ ያደርጋሉ፤ መናኝ ናቸው።

እነሱ ተርፈው የመጡት አባት የምንጠራጠራቸው መከላከያው በትክክል መረጃ አግኝቶባቸዋል።

እሳቸው ወደ ማታ መጡ ተባሉ ግን የሸኛቸው ሸኔ ነው እስከ ግማሽ መንገድ ከመጡ በኃላ በራቸውን ዘግተው በውጭ አስቆልፈው ተቀምጠዋል።

ማታ 2 ሰዓት ላይ ሀገር መከላከያ ሰራዊት መጡ እኚያን በአስቸኳይ መያዝ ስለነበረባቸው የት ነው ያሉት አሉ ? ሄደው ከቤታቸው ሲፈለጉ ጠፉ በውጭ ተቆልፏል ከዛ በሩ ይሰበር ተብሎ በሩን መከላከያዎቹ ሰብረው አገኟቸው በቁጥጥር ስር አዋሏቸው።

ከዛ መከላከያው እኛን የማረጋጋት ስራ ነው የሰራው። እርግጠኛ ሆኜ ምናገረው በወቅቱ ሀገር መከላከያ ባይመጣ አናድርም ነበር።

አሁንም በየጫካው ተሰማርተው ጥበቃ እያደረጉ ነው። "

አባ ተ/መድህን ገ/መስቀል ፦

" ገንዘባችንን ፣ መሳሪያዎቻችንን በመውሰድ ባላቸው ሲስተም ከውስጣችንም ሳይቀር ከነሱ ጋር የተዋሃደ ኃይል ያለውን ንብረታችንን ሁሉ እስከማጣት ደርሰናል። መከላከያ ኃይል በመረጃ ነው ሊያወጣቸው የቻለው። "

ገረመው ይርጋ (የሉበን ጩቃላ ወረዳ ሚሊሻ) ፦

" ይሄን ሁሉ ሲያደርጉ ብቻቸውን አይደለም። የራሳቸውን ሰው ከቤተክርስቲያን ውስጥ አሰማርተው ይህ ስራ ሲሰራ ነበር። ከህዝቡም ከነዋሪው አደራጅተው ያንን ስራ ይሰራ ነበር።

መጨረሻ ላይ እነዛ አባቶች ታግተው ሄደው አባቶችም መስእዋትነት ከፈሉ።

እነዛም ተመሳጥረው የነበሩት በጣም አደገኛ የተባለው ተይዟል። በቁጥጥር ስር የዋሉም አሉ። "

ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ፤ " ድሮም የሚጎዳው የውስጥ አዋቂ ነው " ብለዋል።

" የቀረቡ መስለው ፣ አብረው የመነኑ መስለው ፣ አብረው ከገዳሙ ሰዎች ጋር በደባልነት በአስመሳይነት የሚኖሩ እንደነበሩ ጭላንጭሎች ነበሩ ይሄን ሁላችንም እናውቃለን " ሲሉ ገልጸዋል።

በዚሁ በቀረበው ፕሮግራም ላይ የገዳሙ አባቶች ፥ ታጣቂዎቹ ከውስጥ ባላቸው ሰዎች አማካኝነት እያንዳድኑ ንብረት የት እንደሚቀመጥ በማወቅ በተደጋጋሚ ጊዜ ዝርፊያ ሲፈጽሙ እንደከረሙ ተናግረዋል።

ይህንን ለፀጥታ ኃይል ካሳወቁ ቤተክርስቲያኗን ጭምር በቦምብ እንደሚያወድሙ ሲዝቱ እንደነበር ገልጸዋል።

#ዝቋላገዳም2016

@እፍታ መረጃ

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Efita Mereja እፍታ መረጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share