12/03/2024
ወንድማችን አስቻለው ቡባ ከ EMS ጋር ባረገው ቆይታ የማረቆ ዘጠኝ ቀበሌ ወደ ማረቆ መካለል አለበት ሲል ተናግሯል
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ማረቆ ሊቢዶ ሚዲያ ኔትወርክ, News & Media Website, .
ወንድማችን አስቻለው ቡባ ከ EMS ጋር ባረገው ቆይታ የማረቆ ዘጠኝ ቀበሌ ወደ ማረቆ መካለል አለበት ሲል ተናግሯል
ከ ራጋ ማጋ የተወሰደ አገራችን ኢትዮጵያ በጣሊያን ወረራ ወቅት ነፃ እንድትወጣ የአንበሳውን ድርሻ
ከተወጡት ሀዲያ ካፈራቻቸው ጀግና ልጇ ፊት አውራሪ ጌጃ ገርቦ አንድ ነበር ከ
1888 በዓድዋ ጦርነት ከ 5000 በላይ ጦር ይዞ አድዋ ላይ ለነፃነት በርካታ ዋጋ
የከፈለ ጀግና ነው በ 1928 በሁለተኛው ዙር እስከ 1932 በማይጨው ጦርነት
የተከፈለ ጀግና የሀዲያ ተወላጅ ነው ጌጃ ገርቦ ጌጃ በወቅቱ ጦሩን ከሀዲያ ይዞ
አድዋ ድረስ እስኪደርስ የተለያየ ቦታ እረፍት ያረጉበት ቦታ በስሙ እስከ ዛሬ ድረስ
ይጠራል አዲስ አበባ መሄጃ አዋሽ ወንዝን እንዳለፉ ሬዲዮ ጣብያ
መቆጣጠርያው ጋ ጌጃ ሰፈር ይባላል እንደገና መሃል አዲስ አበባ በስተ ምስራቅ
ተክለሃይማኖት በስተ ምዕራብ አብነት በስተ ደቡብ ልደታ በስተ ሰሜን መርካቶ
ምዕራብ ሆቴለሰ ሞላ ማሩ ዙርያው ጋ ጌጃ ሰፈር ይባላል ጌጃ በርካታ ጦሩ
ያረፈበት ቦታ በስሙ ይጠራል አድዋ ማይጨው አከባቢም በስሙ ጌጃ ሰፈር
የሚባል አከባቢ እንዳለ የመረጃ ምንጮቻችን ያመለክታሉ ። ራጋ ማጋ ከማረቆ
ብሔረሰብ
ማረቆ ፋና በርበሬ
የማረቆ የባህል አልባሳት በአርቲስቶቻችን
ስመገናናው የማረቆ በርበሬ
እንኳን ወደ ማረቆ ብሔረሰብ በሰላም መጡ
ማረቆ ልዩ ወረዳ አርጎ ቀበሌ
እንኳን ወደ ማረቆ ልዩ ወረዳ በሰላም መጡ ብለናል
ወንድሜ እንኳን ለፋሲካ በዓል በሰላም አደረሰህ
1000357363172 በለጠ ሽፈራው ኩዬ:- ወንድማችን በለጠ ሽፈራው ኩዬ ይባላል ተወልዶ ያደገው ማይመሮ ወይም ኢመር ዋጮ 3 ተወልዶ ያደገው ወንድማችን በልጅነቱ በደረሰበት ህመም ተቋቅሞ እስከዛሬ ድረስ ህመሙን እየታገለ ተምሯል አሁን ላይ ግን በክራንች ትንሽ ቦታ ስንቀሳቀስ ያመኛል ሲል ተናገሯል ወደ ህክምና ባቀናበት ወቅት ዶክተሮች መጓጓዣ ሶስት እግር ሞተር ሳይክል ተጠቀም ብለውት የመላው ኢትዮጵያን ህዝብ ትብብር እየጠየቀ ይገኛል ወንድማችን በለጠ ሽፈራው ኩዬ ከሰላምታ ጋር
አሉላ በዐድዋ ጦርነት
የኢጣሊያ ወታደሮች ምፅዋ ከደረሱበት ዕለት ጀምሮ ራስ አሉላ የፈሩትና
አስቀድመው ሲከላከሉት የነበረው ጉዳይ እየገፋ መጣና ዐድዋ ላይ ትልቁን ጦርነት
አስነሳ።
ከኢጣሊያኖች ጋር በሰላም ለመኖር ታላቅ ተስፋና እምነት የነበራቸው አፄ ምኒልክ
ዝነኛውን የውጫሌን ውል ሲፈራረሙ አስራ ሰባተኛው አንቀጽ አከራካሪ ብቻም
ሳይሆን ጦርነትንም አስከተለ። ያ ጣጠኛ አንቀጽ የሚለውም"የኢትዮጵያ ንጉሰ
ነገስት ከአውሮፓ ነገስታት ለሚፈልጉት ማንኛውም ጉዳይ በኢጣሊያ መንግስት
አጋዥነት መላላክ ይቻላቸዋል "ነበር የሚለው።ይህም አንቀጵ በአማርኛው ቋንቋ"
ፈቃዱ የሆነ እንደሆነ "የሚል ቃል ያለው ሲሆን በኢጣሊያን ቋንቋ ደግሞ
"ይገባዋል"የሚል የግዴታ መንፈስ ያዘለ ኑሮ ሁለቱም ሳይጣጣሙ ቀሩ።
ራስ አሉላ ግን የውሉን ነገር እንደሰሙ " ክንዳችን እስካልጠነከረ ፈረንጅን
በወረቀት ለመከላከል እንዴት ይሆናል "ብለው ነበር።የፈሩት አልቀረም ከምኒልክ
ጋር ሆነው ለጦርነቱ ተሰለፉ ።በጀነራል ባራቲዬሪ አዝማችነት ሃያ ሺህ ወታደሮች
አሰልፎ ከስድሳ በላይ መድፍ አስጭኖ ከአስመራ ተነስቶ ትግራይ የገባው
የኢጣሊያን ጦር በመጀመርያ አንባላጌ ቀጥሎ መቀሌ ላይ ከቆየ ቦኋላ እንደገና
ሃይሉን ጨምሮ በአራት ጀነራሎች አዋጊነት መድቦ ወደፊት ገሰገሰ።
አፄ ምኒልክም በራሳቸው አዝማችነት ከእቴጌ ጣይቱ ጀምሮ በአንድ ንጉሥ፣
በሰባት ራሶች፣ በአንድ ዋግ ስዩምና በአንድ ፊታውራሪ አዋጊነት ከሰባ ሺህ በላይ
ጦር አሰልፈው ወደ ዐድዋ ገሰገሱ።
ሁለቱም ወገኖች ለጦርነት መሰለፋቸውን የተመለከቱት እውነተኛ ዜጎችም የየግል
ጠባቸውን ኩርፊያቸውን ጠብ እርግፍ እያደረጉ ወደ ወገኖቻቸው ጦር ተቀላቀሉ ።
ከነዚህም የቁርጥ ቀን ወገኖች መካከል ደጅ አዝማች በሐታ ሐጎስ ራስ ስብሃትና
ራስ ሐጎስ ተፈሪ ዋና ዋናዎቹ ነበሩ። በተለይም ደጅ አዝማች በሐታ ሐጎስ ቀደም
ብለው የኢጣሊያን ደጋፊ ሁነው በማገልገላቸው የአካለ ጉዛይ ገዥ ሁነው ነበር።
በዚህ ጊዜ በግዛታቸው የሚገኘውን ለም መሬት ተቆጥሮ እና ተከልሎ
ለኢጣሊያኖች እንዲሰጥ እንዲያደርጉ ታዘዙ ።ቀጥሎ ደግሞ በግዛታቸው ውስጥ
የሚገኙትን ቆነጃጅት እየመረጡ ለኢጣሊያውያን ወታደሮች እንዲሰጡ ታዘዙ በዚህ
ጊዜ ባሕታ ሐጎስ አሻፈረኝ ብለው ይነሳሉ።
ባለቤታቸውም "ምነው እነሱ ያዘዙህን ብትፈፅም "ይሏቸዋል ።
"እሺ እንግዲል በመጀመሪያ ያንቺን ልጆች ልስጣቸዋ?!" ይላሉ ባሕታ ሐጎስ ።
"እዋይ!ይሄማ አይሆንም !!"ይላሉ እናት
"ነገሩ ባንቺ ቤት ሲመጣ የእናትነትሽ ልብ ተነካ አይደል የሌሎችም እናቶች ልብ
እንዳንቺው እንደሚነካ አስቢ"ብለው በሐታ "የአገሬን ለም መሬትና የወገኖቼን
ቆነጃጅት ልጆች ለማንም ነጭ መርዘኛ እባብ አልሰጥም።"ብለው አሻፈረኝ ይላሉ
ወድያውኑ የበላይ ተቆጣጣሪያቸው የነበረው የኢጣሊያን መቶ አለቃን ራሳቸው
ጉሮሮውን አንቀው ይጥሉና በእግራቸው ረግጠው በጎራዴ ሲወጉት የመቶ
አለቃውም "ኢጣልያኮ ሃያል ናት"እያለ ሲጮህ በሐታም ጉሮሮውን እንደወጉት
"ኢትዮጵያም ከኢጣሊያ የበለጠች ሃያል ነች"ብለው ረሸኑት።ከዛ ቦኋላ ሐላይ
በተባለው ቀበሌ አካባቢ ከነበረው የኢጣልያ ጦር ገጥመው ከፍተኛ ጀብዱ
ፈፅመው በቆራጥነት ተሰው። ሕዝቡም
" ባሕታ ባሕታ ሰገነይቲ
አንበሳ ትውልድ ሰበይቲ
በሐንቲ ጠመንጃ ቀታል ምእቲ"
ትርጉሙም :-"የሰገነይቲው ጀግና ባሕታ
እናትህ አንበሳ ወልዳ አሳደገች ወይ አጥብታ!
በአንድ ጠመንጃ መቶዎች የምትመታ!"
የማሞ ውድነህ "አሉላ አባነጋ "መፅሐፍ የተወሰደ
የምር በኢትዮጵያዊነቴ እንድንኮራበት ከሚያደርጉኝ አንዱ
እንኳን ለ 127 የዓድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳቹ ።
ራጋ ማጋ
ጀግናን የምታፈራው ሀዲያ በርካቶች ጀግኖችን አፍርታለች ዛሬ ስለ አዲዋው እና
ስለ ማይጨው ጀግና አርበኛ ጌጃ ጋርቦ ጥቂት እንላለን ሙሉ ስሙ ጌጃ ገርቦ
ይባላል ትውልድ እና እድገቱ በሀዲያ ዞን ሚሻ ወረዳ ሲሆን ጌጃ እሱም እንደ
በዛብህ ጴጥሮስ በለጋ እድሜ ለእናት አገሩ ኢትዮጵያ የተዋደቀ ጀግና ነው ጣሊያን
ኢትዮጵያን ስትወር በወቅቱ ለመላው ኢትዮጵያ ጥሪ ቀርቦ አገራችንን ኢትዮጵያ
ጀግና ወጣቶች ያስፈልጓት ነበር በየ ቦታው ያሉ የጎበዝ አለቆች ተሰባስበው
ኢትዮጵያን ለመታደግ መላው ኢትዮጵያውያን ለመፋለም ቆርጠው ተነሱ በወቅቱ
አውሮፖውያን መላው አፍሪካን ለመቀራመት የባርያ ንግድ ወይም ቀኝ ግዛት
የሚለውን ፍልስፍናን በመከተል መላው አውሮፖ አፍሪካን ተቀራመቷት በወቅቱ
እናት አገራችን ኢትዮጵያ ቀኝ ግዛት ለመግዛት ጣሊያን በሰሜን በኩል ወደ
ኢትትዮጵያ ዘልቃ ገባች በወቅቱ ጌጃ የሚመራው ጦር ከሀዲያ ከከንባታ ከሊቢዶ
የተወጣጡ ጦር ከ 5000 በላይ ጦር ይዞ ጉዞውን ከሆሳና አድርጎ በጎጎቲ ጆሌ
ሶስት የሊቢዶን ጦር ይዞ ጉዞውን ኬላ ጢያ ሱተን ተሬ አዋሽ ጋ ለተወሰነ ቀን አዋሽ
ሬዲዮ ጣብያው ጋ ጌጃ ጀዌ የሚባለው ቦታ ካረፉ በዋላ ጉዞአቸውን ወደ አዲስ
አበባ በማድረግ ማላ ማሩ ተክለሃይማኖ ልደታ ማከሉን ያደረገው ጌጃ ሰፈር
የሚባለው ሰፈር የጌጃ ገርቦ ጦር ያረፈበት ስፍራ ነው ጌጃ በጣም ጀግና ጦረኛ
ነበር አትንኩኝ ባይ ነበር በከፍተኛ ደረጃ በእስፖርት ጌጃ ሰፈር የሰለጠኑ
ወታደሮቹን ይዞ አድዋ ደረሰ የጌጃ ጦር በከፍተኛ ደረጃ በመፋለም የአንበሳውን
ድርሻ ተወቷል በወቅቱ በከፍተኛ ከሚፈራው ጦር የሊቢዶ ጦር ከፍተኛ እንደነበር
የታሪክ ተመራማሪዎች ያስረዳሉ ጌጃ የጣሊያን ጦር ከበድ ብሎ ሲፋለመው
በወቅቱ የሊቢዶን ጦር አስገባ ብሎ ለምክትሉ ይናገር እንደነበር የታሪክ
ተመራማሪዎች ያስረዳሉ የጌጃን ጦር በከፍተኛ ደረጃ ስሙ ከፍ እንዲል ካደረገው
አይበገሬነቱ ነው ጌጃ በጣም ጀግና ብርቱ ስው ነበር ከ 40 ዓመት በዋላ በድጋሚ
የጣሊያን ጦር በማይጨው በኩል ኢትዮጵያን በንዴት በመውረር ጌጃ ዳግም
ማይጨው ላይ ተፋልሟል ። መረጃ ሙሉ ሰው ያረጋል ራጋ ማጋ የመረጃ ምንጭ ።
ለወልቂጤው የሰው ህይወት እንዲጠፋ መንሴ የሆኑት ጀንበር አብዶ ታረቀኝ ደግፌ ዳውድ ካሚል በህግ መጠየቅ አለባቸው ። የውሃውን ተቃውሞ ወደ ሌላ አቅጣጫ በመቀየራቸው የሰው ህይወት ሊያልፍ ችሏል ።
ማረቆ ሊቢዶ የበርካታ ቱባ ባህል ባለቤት
ማረቆ ሊቢዶ
ጀግናን የምታከብረው ማረቆ እንቁ ልጇን ዳሪን የጀግና አቀባበል እያደረገችለት ነው
ማረቆነት ወንጀል ሆኖበት ላለፉት በርካታ ዓመታት በግፍ የታሰረው ወንድማችን ዳሪ እንሴቦ ክእስር ተፈቷል እንኳን ደስ አለህ ወንድሜ
ጥር 29 ማረቆ ልዩ ወረዳ እንደ ችቦ ይለኮሳል
ማረቆ ልዩ ወረዳ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማረቆ ልዩ ወረዳ የጥምቀጥ በዓል አከባበር ።
እኛን የሚጠሉ እኛን አፋነው ክልል ለመሆን እኔ ብቻ ነኝ ጉልበተኛ የሚለውን
አካል ክንፉን መተን ጥለነዋል ። ማረቆ ማህፀነ ለምለም ምድር በእንቁ ልጆቿ
ታፍራ እና ተከብራ ከጥር 29 ጀምሮ አለምሽ ዛሬ ነው ዛሬ እንለታለን ጥር 29
ማረቆ ልዩ ወረዳ
እንሴኖ ያሚቼ መልካም የገና በዓል ከማረቆ ልዩ ወረዳ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችበሙሉ እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳቹ
ገናዲ
ብራዚላዊው ፔሌ ከዚ ዓለም በሞት ተለየ ነብስ ይማር
ራጋ ማጋ የማረቆ ብሔረሰብ የግጭት አፈታት በፋና ብሮድካስት የቀረበ
እድግ በሉልን የሜጤ ሊቢዶ ልጆቻችን ።
ሜጤ ሊቢዶ የመስኖ ልማት ተጠናክሮ ቀጥሏል የሚበረታታ ነው ሁሉም አርሷደር መበርታት አለበት ።
ለማንኛውም ከአዲስ አበባ መቀሌ የሚደረገው ጉዞ በግሌ በጣም ደስ ብሎኛል የትግራይ እናት በድጋሚ የጥይት ድምፅ መስማት የለባትም
Be the first to know and let us send you an email when ማረቆ ሊቢዶ ሚዲያ ኔትወርክ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.
Want your business to be the top-listed Media Company?