11/05/2024
መሳተፍ እንደመታከም ነው!
ለፅዱ ኢትዮጵያ ሁሉም የበኩሉን በማድረግ ለማህበረሰብ ጤናን ያበርክት!
ፅዱ ኢትዮጵያ በትንሽ ጥረት ብዙ ጤናን፣ ንፁህ ሃገርን የማግኘት ንቅናቄ ነው። የፅዳት ባህላችንሰ እናውቃለን! ይህ የፅዳት ባህላችን እርስበርስ የበሽታ ምንጮች እንድንሆን አድርጎናል። ስለዚህ ሁላችንም ተጠያቂነት አለብን! ሽታን የሚጠየፍ አፍንጫ እያለን ፅዱ ኢትዮጵያን የማይደግፍ አዕምሮ ሊኖረን አይችልም። የበኩላችንን የምናደርገው ለጋራ ጤናችን ነው። ለጋራ ጤናችን በጋራ የምንረባረብበት ግንቦት 4 ነገ 50 ሚሊየን በአንድ ጀንበር ለመሰብሰብ ዲጂታል ቴሌቶን ተዘጋጅቷል። መሳተፍ እንደመታከም ነው!
#ፅዱኢትዮጵያ