Genet Ketema

Genet Ketema Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Genet Ketema, Digital creator, .

05/05/2024

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!

በክርስትና አስተምሮት በክርስቶስ ትንሳኤ ጥላቻ በፍቅር፣ ጨለማ በብርሃን፣ ልዩትነት በአብሮነት ድል ተነስተዋል፤ ሁላችንም ኢትዮጵያዊ አንድነታችንንና ህብረታችንን የሚሸረሽሩ አጀንዳዎችን፣ ጉስቁልናን እና ድህነትን ድል በመንሳት ህብረ ብሔራዊ አብሮነታችንን እና አንድነታችንን ከፍ በማድረግ በዓሉን ልናከብር ይገባል።

በዓሉንም እርስ በርስ በመተሳሰብ፣ በመደጋገፍ፣ ፍቅርንና አብሮነትን ይበልጥ በሚያጎለብት መልኩ በህብረት ልናከብር ይገባል፡፡

መልካም የትንሰኤ በዓል!
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት
ሀላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ

05/05/2024
05/05/2024

እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ ! አደረሰን!

ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለማዳን እራሱን ዝቅ ሲያደርግ እራስ ወዳዶች ማስተዋል ተስኗቸው ስለነበር ፣ አንዳንዶችም ባለማወቅ እራሳቸው ተሳስተው ብዙዎችንም አስተዋል።

ሆኖም በትንሳኤው ብርሃን ከስቅለት በኋላ ፋሲካ ፣ ከጨለማ በኋላ ብርሃን ፣ከሞት በኋላ ሕይወት ሆኖ እውነቱ ተገልጧል።

ኢትዮጵያም ከኋላቀርነት ፣ ከድህነት ፣ ከጥላቻ ፣ ከመጠላለፍ ተላቃ የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን ጉዞ ስትጀምርም አንዳንዶች በብዙሀኑ ውርደት ላይ የነበሩበትን ምቾት የሚያጡ ስለመሰላቸው ፣ አንዳንዶች ደግሞ በጥቂቶች ተታለው ጉዞዋን ለማደናቀፉ ብዙ እንቅፋቶችን ደቅነዋል።

እውነትን በውሸት ለመሸፈን የሚሞክሩ ሀይሎች ከቅርብም ከሩቅም ፣ ከውስጥም ከውጪም መሰናክል ለመፍጠር የሚቻላቸውን ሁሉ ቢያደርጉም በትንሳኤው ብርሃን ከስቅለት በኋላ ፋሲካ እንደሆነ ሁሉ ፓርቲያችን በተከተለው ፣ መንግስታችን በሚተገብረው ትክክለኛ አቅጣጫ የኢትዮጵያ ትንሳኤም ሩቅ አይሆንም።

ኢትዮጵያ ለዘመናት ተብትቧት የቆየውን የዘረኝነት እና የፅንፈኝነት ገመድ እየበጣጠሰች እህትማችነትን ፣ ወንድማዎችነትን እና አብሮነትን እየገነባች መዳረሻዋ ወደ ሆነው ብልፅግና እና ልዕልና በመደመር መንገድ ትገሰግሳለች።

በከተማችን እየተከበሩ ያሉ አገራዊ እና ሀይማኖታዊ በዓላትም በብዝሀነታችን የደመቀ አንድነታችን እያጠናከሩ ይገኛሉ።

ህዝበ ክርስቲያኑም ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ከጨለማ ወደ ብርሀን ለመውሰድ የመስዋዕት በግ ሆኖ ያበራውን የትንሳኤ በዓል እንደወትሮው ሁሉ ያለው ለሌለው በማካፈል በመተሳሰብ በአብሮነት በፍቅር እንድታሳልፉ መልዕክታችንን እያስተላለፍን በዓሉ የሰላም የፍስሀ ይሁንላችሁ እንላለን።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት

05/05/2024
05/05/2024

"ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሠላምና በጤና አደረሳችሁ ፥ አደረሰን!

የትንሳኤን በአል ስናከብር ሃይማኖታዊ አስተምህሮቱ በሚፈቅደው መልኩ በወንድማማችነት እና እህትማማችነት እሳቤ ተደጋግፈን ፣ ለተቸገሩ ወገኖቻችንን ያለንን በፍቅር አካፍለን ማሳለፍ ይገባናል!"

:- አቶ አለማየሁ እጅጉ
በብልጽግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት ምክትል እና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ

05/05/2024

"መላው የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለትንሣዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! እንኳን አደረሰን!

የፋሲካ በአል ኢትዮጵያዊ መተሳሰብ እና መደጋገፍ የሚነግስበት በዓል እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ!"

አቶ ይመር ከበደ
በብልጽግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ

05/05/2024
05/05/2024

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!

ውድ የክርስትና እምነት ተከታዮች በዓሉን ስናከብር በወንድማማችነት እና በእህትማማችነት በመተሳሰብ፣ በመደጋገፍ፣ ፍቅርንና አብሮነትን ይበልጥ በሚያጎለብት መልኩ በህብረት ልናከብር ይገባል፡፡

እኛ ኢትዮጵያዊያን የቀደምት አባቶቻችንና እናቶቻችንን የመደጋገፍና የመተጋገዝ አኩሪ ባህል በዚህኛውም ትውልድ በማስቀጠል ጧሪና ደጋፊ የሌላቸውን አረጋዊያንና ህፃናትን እንዲሁም ተቸግረው ያሉ ወገኖቻችንን በመደገፍና በመንከባከብ በዓሉን በአብሮነት ስናከብረው አንድነታችንን በማጠንከር ፅኑ መሠረት የምንጥልበት መልካም አጋጣሚ ይሆናልና በአሉን ስናከብር ያለንን እያካፈልን በአብሮነት እንድናከብረው ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።

መልካም የትንሰኤ በዓል!

አቶ ሙሉጌታ ጉልማ
በብልፅግና ፓርቲ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ

25/04/2024

ብልጸግና አሰባሳቢ ትርክትን በመቅረፅ የበለጸገች ኢትዮጵያ ይገነባል!

ሀገራችን ኢትዮጵያን የአሁኑንና የመጪውን ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስከብር አስተማማኝ መሰረት ዛሬ ላይ በመገንባት ሰላም፣ ዴሞክራሲ፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ የዜጎች ክብር፣ ፍትሕ እና የጋራ ብልጽግና የተረጋገጠባት ሀገር መሆን ይኖርባታል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ የጥንታዊ ስልጣኔና የቀደመ ሀገረ-መንግስት ባለቤት ብትሆንም አሰባሳቢ የሆነ ሀገራዊ ትርክት መገንባት ባለመቻሏ ትርክቶቿ በስርዓታት ፖለቲካ ፍላጎት ላይ ብቻ የተንጠለጠሉ ሆነው በመቆየታቸው ስርዓታት በወጡ እና በወረዱ ቁጥር የሚገለባበጡ ነጠላ ትርክቶች ገዥ እየሆኑባት የሀገረ-መንግስት ግንባታ ተግባሯን ያለ ተቃርኖ ለማስቀጠል አልታደለችም። በአንፃሩ የአሜሪካን፣ የቻይናን የፈረንሳይን ሀገራዊ ገዥ ትርክቶች የሚነግሩን ስርዓቶች ቢቀያየሩም ገዥ ሀገራዊ ትርክታቸው መሰረቱ ሀገረ-መንግስቱ ላይ በመገንባቱ በየወቅቱ የሚነሱ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች አይለዋወጥም።

ሀገራት ህዝባቸውን ከየት እንደተነሱና ወዴት እንደሚደርሱ በአሰባሳቢ ገዥ ትርክት በመገንባት ከአስተዳደራዊ ወሰናቸው አልፈው በዓለም ላይ የበላይነታቸውን ቅቡልነት አረጋግጠዋል።
የዓለማችን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሚዘውሩት የትርክት የበላይነት በያዙ ሀገራት እና ተቋማት ፍላጎት ነው። እነዚህ ሀገራትም ይሁኑ ተቋማት የትርክታቸውን የበላይነት ለማስጠበቅ ሁሉንም ዓይነት ሀይል የማስጠበቂያ አማራጮችን ይጠቀማሉ።

ትርክት ቻይናን ከወደቀችበት አንስቶ የዓለም ተፆዕኖ ፈጣሪ ሀገር አድርጎ ከፊት አስቀምጧታል። ትርክት ሶሪያ ከዓለም ቀደምት ሀገርነት ወደ ፍርስራሽነት ቀይሩታል። ትርክት ኢትዮጵያን ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲነገር የሚኖረውን በቅኝ-ገዥዎች ቅኝ ያለመገዛት ታሪክ እንዲትሰራ አስችሏታል።

ትርክት በህዝብ ውስጥ ለጋራ ዓላማና ራዕይ በአብሮነት በማነሳሳትን በአርበኝነት እንዲፈፅሙ የሚያንቀሳቅስ ታላቅ ሀይል መሆኑን በመረዳት ብልጽግና ፓርቲ በተራራቀ ዋልታ የሚገኙትን የሀገራችን ትርክቶች ወደ አሰባሳቢ ገዥ ትርክት ለማምጣት በህብረ-ብሄራዊ አንድነትና ወንድማማችነት ላይ የተመሰረት ብሄራዊ አርበኝነት የሀገራችን ገዥ ትርክት እንዲሆን እየሰራ ይገኛል።

ብልፅግና በህብረ-ብሄራዊ አንድነትና ወንድማማችነት ላይ የተመሰረተው ብሄራዊ አርበኝነት የሀገራችንን ያልፈውን የጉዞ ምዕራፍ ፣ የዛሬን ነባራዊ ሁኔታ እና የነገን መዳራሻ የምንመለከትበት የጋር አሰባሳቢ ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው ብሎ ያምናል።

በህብረ-ብሄራዊ አንድነትና ወንድማማችነት ላይ የተመሰረተው ብሄራዊ አርበኝነት ገዥ ትርክት የትላንቱን ኢትዮጵያ ህዝቦች ታሪክ መሰረት አድርጎ የዛሬውን አስተሳስሮ ነገን ማመልከት የሚችል የህዝባችንን ዋና ዋና የጋራ እሴቶችን፣ ፍላጎቶችንና ግቦችን የሚያሳካና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ያደርጋል።

ፓርቲያችን ህዝባችን የጋራ ታሪክ ያለው፣ ብዙ ትላንቶችን በጋራ የተሻገረ አሁን ስንቅ ልናደርጋቸው የሚገቡ አያሌ ታሪኮችን እንዳሉት ያምናል።

በዚሁ አግባብ ብልፅግና በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ አማካይነት ነባር የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት፣ ታሪካዊ እሴቶችን አውጥቶ በማበልፅግ እና በማህበራዊ ካፒታላችንን በመጠቀምና በእነዚህ ላይ እሴቶችን በመጨመር ለነገ ብልጽግናችን በሚሆን መንገድ ማልማት በሰፊው ቀጥሏል።

ከትላንት የተሻለ ሀገራችንንና ህዝቡቿን የሚጠቅም ታሪክ እንድሰራ፣ የትውልዶችን ድካም በማረም ለትወልድ የበለፅገች ሀገር ለማስረከብ እንትጋ። ስለዚህ ትርክታችን ያለፈውን ብቻ ሳይሆን የዛሬን ዕድል እና የገነን ተስፋ ታሳቢ ያደረገ መሆን አለበት።

25/04/2024

ሁለንተናዊ ብልጽግና ማለት ምን ማለት ነዉ?

ብልጽግና ምሉዕ የሆነ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ፣ የሀገር ደህንነትና ውጭ ግንኙነት ልህቀት ውጤት ነው፡፡ ከፖለቲካው አንጻር ብልጽግና መካከለኛና አካታች የፖለቲካ እይታን ይከተላል፡፡

ከዚህ አንጻር ሲታይ ብልጽግና በቀኝና በግራ ዋልታዎች መካከል ሚዛን በመበጠበቅ በመደመር እሳቤ የተቃኘ የተረጋጋ የፖለቲካ ሀይሎች አሰላለፍና መስተጋብር የሰፈነበት ምህዳር የበለጸገ ፖለቲካ ማሳያ ነው፡፡ ሁሉም ማንነቶችና ፍላጎቶች እውቅናና ክብር አግኝተው የሚደመጡበት፣ ህግና ስርዓት የሰፈነበት አውድ ነው።
ቅቡልነት የተጎናፀፈ ሀገረ መንግሥት የተረጋገጠበት ነው። ፍትህና ርትህ እውን የሆነበት፤ የኢትዮጵያ ህዝቦች ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነት የሰፈነበት ነው፡፡

በሌላ በኩል ሁለንተናዊ ብልፅግና የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ እውን የሆነበት ነው፡፡ ሁለንተናዊ የግብርናና ኢንዱስትሪ ልማትና ዕድገት የተሰናሰለበት ነው፡፡ ገቢ ምርቶች በብዛትና በጥራት የተተኩበት፣ የኤክስፖርት ምርቶችም በዚያው ልክ በብዛትና በጥራት የተመረቱበትና የውጭ ምንዛሬን ማሳደግ የተቻለበት፣ ለሰፊ የተማረ የሰው ኃይል ዘላቂና አስተማማኝ የስራ ዕድል መፍጠር የተቻለበት ነው፡፡

ብልጽግና ፓርቲ የኢኮኖሚ ሽግግርን ለማፋጠን የግብርናና ኢንዱስትሪ ዘርፉን ትስስር የሚያጠናክርና ሀገራችንን በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ቀዳሚ ማዕከል እንድትሆን የሚያስችሉ ስራዎችን በስፋት እየሰራ የሚገኘውም ከዚሁ እሳቤ በመነሳት ነው፡፡

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Genet Ketema posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share