06/05/2024
መላው የክርስትና ሀይማኖት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሠላምና በጤና አደረሰን ፣ አደረሳችሁ ።
የክርስትና አስተምህሮት እንደሚያስረዳን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ህይወቱን የሰጠው ስለ ሰው ልጅ ፍፁም ፍቅር ነዉ። እኛም አርዓያውን ተከትለን በፍቅር እንድንኖር እና መስጠትን የህይወታችን አካል እንድናደርግ ነው ።
ስለሆነም የፋሲካ በዓል የመስዋዕትነት፣የይቅርታ ፣ የመተሳሰብና የመደጋገፍ በአጠቃላይ ውብ የሆኑትን ኢትዮጵያዊ እሴቶቻችን ይበልጥ ከሚያጎሉና ከሚያደምቁ በዓላት መካከል ዋነኞቹ ነው።
በመሆኑም ይህን ታላቅ ሐይማኖታዊ በዓል ስናከብር በተለመደው የመተጋገዝና የመረዳዳት እንዲሁም የአብሮነት መንፈስ እንዲሆን ጥሪ አቀርባለሁ ።ንፁህ ሆነን እንደተፈጠርነው ሁሉ በንፅህናና በቅንነት መኖር እና ህዝባችንን ከልብ ማገልገል ይጠበቅብናል።
በድጋሚ መልካም የትንሳኤ በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ።
አቶ መገርሳ ገላና
በብልፅግና ፓርቲ የየካ ክ/ከተማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ