Hanii toofik

Hanii toofik Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hanii toofik, Digital creator, .

25/03/2025

በለውጡ ዓመታት የሐረርን የታሪክ ልክ እና የመስህብ ሃብቶች የገለጡ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል

ሐረር፤መጋቢት 16/2017(ሐክመኮ)፡- በለውጡ ዓመታት የሐረርን የታሪክ ልክ እና የመስህብ ሃብቶች የገለጡ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ ገለጹ።

በክልሉ ባለፉት ሰባት ዓመታት በከተማ ልማት ዘርፍ የተከናወኑ የልማት ስራዎችንና የተመዘገቡ ስኬቶቸን እንዲሁም ቀጣይ እቅዶችን በማስመልከት አቶ ሙክታር ሳሊህ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም ከለውጡ በፊት የከተማ ፕላንን መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የነበሩ ችግሮችን በማስታወስ በተለይም ህገ-ወጥ ግንባታና የመሬት ወረራ በስፋት ይስተዋሉ ነበር ብለዋል።

በመሆኑም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ሀረር ከተማ በፕላን እንድትመራ ማድረግን ጨምሮ የከተማዋን የታሪክ ልክ የሚመጥኑ የልማት ስራዎችን በማከናወን የተሳካ ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት።

በለውጡ ሰባት ዓመታት የሐረርን የታሪክ ልክ እና የመስህብ ሃብቶች የገለጡ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ስለመከናወናቸውም ጠቅሰዋል።

የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበት የነበረውን የጀጎል የአለም አቀፍ ቅርስ በማደስ ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችል ትልቅ አሻራ ያረፈበት ስራ መከናወኑንም ለአብነት አንስተዋል።

በከተማው በኮሪደር ልማት የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችንና መናፈሻዎችን በመገንባት የከተማዋ የውበት መገለጫና ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ ማድረግ መቻሉንም እንዲሁ።

እንደ አጠቃላይ በለውጡ ሰባት ዓመታት የነበሩ ቅርሶችን በማደስና በመጠበቅ የሀገር ሃብት ሆነው እንዲቀጥሉ በማድረግ በኩል የሚታይ ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት።

በክልሉ ለተመዘገበው ተጨባጭ ውጤት የአመራር ቁርጠኝነት የህዝቡ እገዛና ትብብር ታክሎበት የተገኘ ስኬት መሆኑን አንስተዋል።

በቀጣይም ሐረርን የማስዋብ፣ ልማቷን የማስቀጠልና የህዝቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ አረጋግጠዋል።

25/03/2025

በለውጡ ዓመታት የሐረርን የታሪክ ልክ እና የመስህብ ሃብቶች የገለጡ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል
****************
(ኢ ፕ ድ)

በለውጡ ዓመታት የሐረርን የታሪክ ልክ እና የመስህብ ሃብቶች የገለጡ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ ገለጹ።

በክልሉ ባለፉት ሰባት ዓመታት በከተማ ልማት ዘርፍ የተከናወኑ የልማት ስራዎችንና የተመዘገቡ ስኬቶቸን እንዲሁም ቀጣይ እቅዶችን በማስመልከት አቶ ሙክታር ሳሊህ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም ከለውጡ በፊት የከተማ ፕላንን መሰረት ያደረጉ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የነበሩ ችግሮችን በማስታወስ በተለይም ህገ-ወጥ ግንባታና የመሬት ወረራ በስፋት ይስተዋሉ ነበር ብለዋል።

በመሆኑም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ሀረር ከተማ በፕላን እንድትመራ ማድረግን ጨምሮ የከተማዋን የታሪክ ልክ የሚመጥኑ የልማት ስራዎችን በማከናወን የተሳካ ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት።

በለውጡ ሰባት ዓመታት የሐረርን የታሪክ ልክ እና የመስህብ ሃብቶች የገለጡ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ስለመከናወናቸውም ጠቅሰዋል።

የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበት የነበረውን የጀጎል የአለም አቀፍ ቅርስ በማደስ ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ የሚያስችል ትልቅ አሻራ ያረፈበት ስራ መከናወኑንም ለአብነት አንስተዋል።

በከተማው በኮሪደር ልማት የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችንና መናፈሻዎችን በመገንባት የከተማዋ የውበት መገለጫና ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ ማድረግ መቻሉንም እንዲሁ።

እንደ አጠቃላይ በለውጡ ሰባት ዓመታት የነበሩ ቅርሶችን በማደስና በመጠበቅ የሀገር ሃብት ሆነው እንዲቀጥሉ በማድረግ በኩል የሚታይ ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት።

በክልሉ ለተመዘገበው ተጨባጭ ውጤት የአመራር ቁርጠኝነት የህዝቡ እገዛና ትብብር ታክሎበት የተገኘ ስኬት መሆኑን አንስተዋል።

በቀጣይም ሐረርን የማስዋብ፣ ልማቷን የማስቀጠልና የህዝቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ አረጋግጠዋል ሲል የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

መጋቢት 16 ቀን 2017 ዓም

25/03/2025
25/03/2025
25/03/2025
24/03/2025
24/03/2025

በለውጡ ዓመታት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ውጤታማ ስራ ተከናውኗል።

በሐረሪ ክልል በለውጡ ዓመታት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ውጤታማ ስራ መከናወኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ልማት ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር ተናገሩ።

የክልሉ ምክትል ርዕስ መስተዳድር እና የግብርና ልማት ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር በክልሉ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት በግብርና ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን በተመለከተ ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

ወይዘሮ ሮዛ ኡመር እንደገለጹት ከለውጡ ዓመታት ቀደም ሲል በክልሉ የተሻሻለ የግብርና አሰራንር ባልተከተለ መንገድ የሚከናወኑ ምርትና ምርታማነትን የማጎልበት ስራዎች ውጤታማ ሳይሆኑ መቅረታቸውን አንስተዋል።

በክልሉባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት በመስኖ ልማት፣በሌማት ትሩፋት፣በአዝዕርት ሰብል እንስሳት ሃብት ልማትና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

በክልሉ ከተማና ገጠር ወረዳዎች በሌማት ትሩፋት በእንስሳት ተዋጽዎና በአትክልትና ፍራፍሬ የተከናወኑ ስራዎች ህብረተሰቡ፣ አምራቹና ሸማቹ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝ አስችሏል ብለዋል።

በገጠር በመስኖ ልማት የሚከናወኑ ስራዎችም ምርትና ምርታማነት እንዲጎለብትና የአርሶ አደሩ ምግብ ዋስትናን እንዲረጋገጥ ከማስቻሉም ባለፈ ምርቱን በቀጥታ ለከተማው ማህበረሰብ በማቅረብ የዋጋ ንረትን እንዲረጋጋ ከፍተኛ እገዛ ማድረጉንም ተናግረዋል።

በበልግና መኽር እርሻ ረገድ የዝናብ እጥረትን ተቋቁመው በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡ የበቆሎና የማሽላ እርሻ ስራዎች በእጥፍ ማደጉንና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ይበልጥ እያረጋገጠ መምጣቱን ተናግረዋል።

በክልሉ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና እንክብካቤ የተከናወኑ ስራዎችም አርሶ አደሩ የከርሰ ምድር ውሃን በቅርበት እንዲያገኝ በማስቻሉ አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት ተላቆ ምርትና ምርታማነት እንዲጎለብት አስችሏል ብለዋል።

በክልሉ በለውጡ አመታት በተከናወኑ የግብርና ስራዎች ምርትና ምርታማነትን በማጎልበት ምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ በሰፍትኔት የሚረዱ ዜጎች ቁጥር በየዓመቱ እንዲቀንስ እያስቻለ እንደሚገኝ አክለዋል።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hanii toofik posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share