05/02/2024
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል
*******************
የኢፌዴሪ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ በነገው ዕለት ይካሄዳል።
በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 55 (17) በተቀመጠውና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት ስነምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 መሠረት፥ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች የሚሰጡትን መልስና ማብራሪያ የሚያዳምጥ ይሆናል።
በዚሁ መሠረት፥ ምክር ቤቱ በነገው ዕለት በሚያካሂደው 14ኛው መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምክር ቤት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።