Bahir Dar wikileak BW

  • Home
  • Bahir Dar wikileak BW

Bahir Dar wikileak BW Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Bahir Dar wikileak BW, Digital creator, .

18/01/2024

የድል ዜና

ከደምበጫ ወደ ገሊላ ለማቅናት አስቦ የተንቀሳቀሰው ሰው በላው አራዊት ሰራዊት፣ ሮቢት ላይ በይርሳው ደምስ በሚመሩት ፋኖዎቻችን በደረሰበት ድንገተኛ መብረቃዊ ጥቃት የጉዞ እቅዱን ሰርዞ 3 ፖትሮል ሙሉ አስክሬኑን ይዞ ወደመጣበት መፈርጠጡ ተሰማ።

ይህ አራዊት ሰራዊት ገሊላ ሳይደርስ ሮቢት ላይ ሰው ለገበያ በሚሰበሰብበት ቦታ ቀድሞ ተኩስ የከፈተ ቢሆንም ፋኖዎቻችን ከየት መጡ ሳይባል አስክሬን አድርገውታል።

በተጨማሪም ከደምበጫ በ5 ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘዋ የጨረቃ ከተማም ፋኖዎቻችን ሰርገው በመግባት ህዝብን 2 የአገዛዙን ሰዎች ይዘው መሄዳቸው ታውቋል።

16/01/2024

አዴቶች በርቱ

13/01/2024

ብልጽግና በህወሀቱ ጦርነት በሁለት አመት ውስጥ ከጣለው የድሮን ብዛት ይልቅ አማራ ክልል ላይ በስድስት ወር ውስጥ የጣለው በሶስት እጥፍ ይበልጣል ።

ገራሚው ጉዳይ የትግራይ ዲያስፖራዎች ጉዳዩን ለአለም ለማስረዳት የሄዱበትን ያህል ርቀት አማራው ዲያስፖራ 1/4ኛ አለመሞከሩ ነው ።
ክልሉ በየቀኑ በድሮን እየተጨፈጨፈ ነው ድምጽ የሚያሰማ ግን ማንም የለም ።
ምን ይሻላችኋል ግን ዲያስፖራዎች ?

ብፅዑ አቡነ አብርሃም መግለጫ ሰጥተዋል !በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ፩. ቤተ ክርስቲያን የራሷ ነፃነት አላት፪. ያም ይኽንን አድርጊ ይሄም ይኽንን አድርጊ ስላላት እየተጎች የተባ...
12/01/2024

ብፅዑ አቡነ አብርሃም መግለጫ ሰጥተዋል !
በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች

፩. ቤተ ክርስቲያን የራሷ ነፃነት አላት

፪. ያም ይኽንን አድርጊ ይሄም ይኽንን አድርጊ ስላላት እየተጎች የተባለችውን የምታስተናግድ አትኾንም አይደለችምም።

፫. ማንም ይኽን አድርጊ እያለ ሊጎትታት አይችልም። ነገር ይኽንን በሉ ይኽንን ካላደረጋችሁ የሚባል መያዣ ነገር ቤተ ክርስቲያን አስተናግዳም አታውቅም። ወደፊትም አታስተናግድም። ወደፊትም የመጣውን በጸጋ ከምትቀበል ውጭ። ይኽንን አድርጊ ስልሽ ብቻ ነው የምታደርጊው የሚለው አስተሳሰብ ጨርሶ የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ይነካል።

፬. መንግሥት በዓለ ጥምቀትን ለማክበር ቅድመ ኹኔታ ማስቀመጡን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ በመግለጫቸው ጠቁመዋል። [የአቡነ ቄርሎስን እና የአቡነ ሉቃስን] አቋም በበዓሉ እንድታወግዝ መንግሥት አቋም ይዟል።

፭. መንግሥት አኩራፊ ሊኾን አይገባውም። ይኼንን ካላልሽ እንዲህ አላደርግም ማለት አይገባም።

፮. ሱሪ በአንገት አውጣው የሚባል ነገር ቤተ ክርስቲያን አትሸከምም

፯. መኪና ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ሲገባ የማይፈትሹ ሲወጣ የሚፈትሹ የመንግሥት ጥበቃዎች አሉ። የሚገባ መኪና አይፈተሽም የሚወጣ መኪና ይፈተሻል። ምንድን ነው የተፈለገው? ከቤተ ክርስቲያንስ ምንድን ነው የሚወጣው? መድፍ ነው? መሣሪያ ነው?

እኛ መሪዎቹ የማናውቀው ፈታሽ አቁሞ መፈተሽ ድፍረት ነው። የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕልውና መፈታተን ነው።

፰. መደፋፈሩ በዝቷል። መንግሥት ቤተ ክርስቲያኒቱን ደፍሯታል። አልፎ ይሔዳል። ቤተ ክርስቲያንን መድፈር አደጋ ነው። ለሃይማኖቱ የማይሞት የለም።

አዛዣችን በዝቷል። ላዘዘን ኹሉ አጎንብሰን እንችላለን እንዴ? ሃይማኖታችን ከሚፈቅደው ውጭ። በሉ የተባልነውን ኹሉ ማለት እንችላለን እንዴ? ለእኔ አድርግ የሚለኝ ሃይማኖቴ ብቻ ነው። ማስፈራሪያ አይገዛንም። ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ በለው።

፱. በየሔድንበት በየቢሮው ደሞ ለኦርቶዶክስ? እየተባልን ነው። ቢያንስ አይኾንም እንኳ [የአባት ነው] አትቁም ያሉት ለማኝ አትቁም ነው። ያንን ያንን ያርሙ።

እዚህ እኛው ቤት አድር ብዬው ቅጥረኛው ስለሚበዛ ነው። የድፍረት ኃጢአት በዝቷል። ድፍረት የቤቱን ሰው ገዝቷል የውጭውንም ሰው ገዝቷል። የማትደፈረውንም ቤተ ክርስቲያን እያስደፈረ ይመጣል። አኹን የቀረው በሉ ውጡ ብሎ የመረካከብ ሥራ ነው ይኽች ቤተ ክርስቲያን የቀራት። ይኽንን ደግሞ ቆሞ የሚያይ የለም።

የጎጠኝነቱ ምንጩ ቤተ ክህነቱ ኾኗል። ከሃይማኖቴ ቋንቋዬ ይበልጣል የሚሉ ሰዎች የተነሡበት ጊዜ ነው። ስወለድ ቋንቋዬን ይዤ ነው የተወለድኹት ሃይማኖት በኋላ ነው የመጣ ነው የሚሉ ካህናት የተፈጠሩበት ወቅት ነው።

፲. ከሃይማኖቴ ጋር የእኔ ነፍስ ትወጣለች። በሃይማኖት አንደራደርም።

አንበርክኬ ልግዛ የሚለው ይቁም

ለመጨረሻው ጸዋት ወ መከራ ራሳችንን እናዘጋጅ!

 #መረጃ ጎንደር ከተማ እና አካባቢዋ የድል ዜና የጭልጋ ወረዳ የብልጽግና አመራሮች ወደ ጫንድባ ከተማ ግብር ለመሰብሰብ ሲሄዱ ባልታወቁ ሀይሎች ተመትተዋል፡፡ በዚህም 1ኛ የጭልጋ ወረዳ  የፀ...
12/01/2024

#መረጃ ጎንደር ከተማ እና አካባቢዋ

የድል ዜና
የጭልጋ ወረዳ የብልጽግና አመራሮች ወደ ጫንድባ ከተማ ግብር ለመሰብሰብ ሲሄዱ ባልታወቁ ሀይሎች ተመትተዋል፡፡ በዚህም 1ኛ የጭልጋ ወረዳ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ
2ኛ የወረዳው የገቢዎች ቢሮ ም/ሀላፊ፤
3ኛ ስማቸው እና ሀላፊነታቸው በውል ያልታወቁ አራት አመራሮች እርምጃ የተወሰደባቸው ሲሆን ሁለቱ ደግሞ ታፍነው ተወስደዋል።

👉 ሰሞኑን በጎንደር እና አካባቢዋ ባለው ውጊያ የጠላት ሀይል በንፁሀን ላይ ጭፍጨፋ ፈፅሟል። ንብረት አውድሟል።

1ኛ የጎንደር ከተማ የንፁሀን ሞት 13 ደርሷል።
2ኛ ሰባት ደረጃቸውን የጠበቁ ቀበሌ 18 አካባቢ የሚገኙ ቤቶች በከባድ መሳሪያ ተመትተዋል ።
3ኛ በከባድ መሳሪያ የተመቱ ቤተክርስቲያናት አሉ፡፡
4ኛ በጎንደር ጣቁሳ ወረዳ በኩራባስ ቀበሌ ሰውድባ ጊዮርጊስ አጠቃላይ የቤተክርስቲያን ንብረት ተዘርፏል።
የቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት ተሰብሮ 500 ብር ካሽ ተውስዷል። የቤተክርስቲያን ጥበቃ ላይ የነበሩ ግለሰቦች ተደብድበው ሶስት ክላሽ መሳሪያቸው ተውስዷል።

በጎንደር ከተማ እና በአካቢው ላይ ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም ትራንስፖርት ቆሟል፡፡ የንግድ ሱቆች ተዘግተዋል።
Misganew Andualem

እርምጃ ተወስዶባቸዋል !ባለፉት ሳምንታት ባህር ዳር ከተማ እና አካባቢው   የሚንቀሳቀሱ  ብልጽግና ያደራጃቸው ዘራፊ ቡድኖች በተለይም የመከላከያ ካምፑን (መኮድ) ተገን በማድረግ ባለሀብቶችን...
11/01/2024

እርምጃ ተወስዶባቸዋል !

ባለፉት ሳምንታት ባህር ዳር ከተማ እና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ ብልጽግና ያደራጃቸው ዘራፊ ቡድኖች በተለይም የመከላከያ ካምፑን (መኮድ) ተገን በማድረግ ባለሀብቶችን እና የባለሀብት ልጆችን እንዲሁም የግል ተቋማት ስራ አስኪያጆችን አግተው ገንዘብ ይቀበላሉ። ።የጎጃም ዕዝ ፋኖ የእህል እንቅስቃሴን በተመለከተ የሰጠውን መግለጫ ለራሳቸው ጥቅም በሚጠቅም መልኩ በቀጠናው ውስጥ ከአካባቢ አካባቢ የሚደረግን እንቅስቃሴ መኪኖችን በማገት ገንዘብ ይቀበላሉ። ሆኖም እንዚህ ዘራፊ ቡድኖች ከእዚህ ድርጊታቸው እንዲታቀቡ ተደጋጋሚ በስልክ የማግባባት ሙከራ ተደርጓል ። ሽማግሌዎችም ተልከው ሂደቱ ውጤት አላመጣም። ቡድኑም እገታውን እና ስም ማጠልሸቱን ገፍቶበት ሂዷል ። ተመክረው ተዘክረው አልሰማ ያሉ እነዚህ ዘራፊዎች በጎጃም ዕዝ የባህር ዳር ፋኖ በፋኖ አማኑኤል ሞላ የሚመራው ደጉ በላይ ሻለቃ በወሰደው የአጸፋ እርምጃ የቡድኑ መሪን ጨምሮ አራቱ ዘራፊዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ሲሆን ሶስቱ ተኩስ በመክፈታቸው እርምጃ እንደተወሰደባቸው ፋኖ ኢንጅነር ማንችሎት ነግሮኛል። በቁጥጥር ስር የዋሉ ዘራፊዎች ማንነት ቪዲዮው እንደደረሰ ይወጣል።

Tesfaye W/Silase

11/01/2024

አንድ አስቸኳይ መረጃ፣ 2 ደግሞ የድል ዜናዎች

1. አሁን ከ30 ደቂቃ በፊት ከመኮድ የወጡ ሁለት ኦራል ሙሉ ወታደርና አንድ ዙ 23 የጫነ ፒካፕ ወደ ጎንደር መስመር በፍጥነት እያመሩ እንደሆነ ታውቋል፤ ክትትል ይድረግ፤ መረጃ አድርሱን። የወገን ጦር መረጃው ይኑራችሁ።

2. ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ሻለቃ ደብረብርሃን ዙሪያ ጎሼባዶ ታላቅ ጀብዱ መፈጸሟን አዶናይ አበበ ያጋራን መረጃ ያስረዳል። ሻለቃዋ ዙ23 እና ታንክ አንጋግቶ የመጣውን አራዊት ሰራዊት በሽምቅ ጉዳት እንዳደረሱበትና ቀሪውን ወደ መጣበት ማስፈርጠጣቸውን ታውቋል።

3. ዛሬ ሌሊት ሊነጋጋ ሲል በሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ ሙጃ ከተማ ጥቃት ለመፈፀም አቅደው የተንቀሳቀሱ ሚሊሻና ፖሊሶች ሟል ወደምትባል ቀበሌ ያመራሉ። ሆኖም ግን መረጃው ቀድሞ የደረሳቸው ፍም እሳቶቹ የግዳን ፋኖዎች ከነመኪናው ቀድመው ወደ አመድነት እንደቀየሯቸው ታውቋል።

11/01/2024

የብልጽግና ሚስጥራዊ ስብሰባ መረጃ!

የዐብይ አህመድ አገዛዝ ከሰሞኑ በበርካታ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጉ ይታወቃል።

ስለ ትግራይ እና አማራ የቀረቡ ሃሳቦች በብልጽግና ስብሰባ ላይ የቀረበው ሀሳብ በፋኖ የደህንነት መዋቅር ተመንትፎ ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰው!

1ኛ. በምክክር ኮሚሽን በኩል በቶሎ በፌደራል መንግስቱ ጣልቃ ገብነት እርቅ ይደርግ በክልል መንግስታት መካከል መግባባት በመፍጠር እና የተቋረጡ የንግድ እና መሰል ተግባራትን በክልል መንግስታት ደረጃ መስራት። ይሄን ማድረጋችን የትግራይ ሃይሎች ከፋኖ ጋር ጥምረት እንዳይፍጥር ያደርጋል። አወዛጋቢ ቦታዎች በፌደራል ቁጥጥር ስር የተዳደራሉ።

2ኛ. የትግራይ ሃይሎችን ከፌደራል መንግስቱ መካከል ያለውን አለመግባባት በማርገብ ከህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የፌደራል ስልጣን በመስጠት ውጥረቱን በማላላት ጊዜ መግዛት አለብን። በተጨማሪም የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች ሪፎርም ላይ ስለሆነ የሚመጡት አመራሮች በአማራ ሃይሎች በኩል በቀላሉ ተቀባይነት ሊያገኙ ይችላሉና ለእኛ ጥሩ ነው።

3ኛ. በጀነራል ብርሃኑ በቀለ አማካኝነት ማይጠብሪ ላይ እንዲበተን የተደረጉ የሚሊሻ አባላት ወደ ማይጠብሪ መልሶ ማስገባት እና የብሄር ዘውግ ያለው ግጭት ማስነሳት አለብን። በተመሳሳይ በሰሜን ጎንደር ያሉ የትግራይ ዘር ሃረግ ያላቸው ላይ ተመሳሳት ግጭት ማስነሳት አለብን።

4ኛ. በሱማሊያ እና ኤርትራ መሪነት ጦርነት ሊኖር እንደሚችል መጠቆም ያስፈልጋል። ትግራይንም በዚህ ምክንያት ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ መክተት አለብን።

አማራ ክልልን በተመለከተ!

1ኛ. ለሚሊሻ እና አድማ ብተና የውጊያ አበል መጨመር

2ኛ. የፋኖ ሃይሎች ወደ ድርድር እንዲመጡ ማድረግ። ለዚህም ከፍተኛ የማዳከም ስራ በመስራት ተስፋቸው ድርድር እንዲሆን ማድረግ።

3ኛ. የሚሊሻ እና አድማብተና እና ከወረዳ በታች ያሉ አባላት እንዳይከዱ ከህዝብ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲነጠሉ ማድረግ እና ህዝቡ እንዳይሸሽጋቸው ማድረግ።

4ኛ. ስለድሮን አሁን ካላቸው እውቀት የተለየ እና የተሳሳተ እነሱን አደጋ ላይ የሚያጋልጥ መረጃ ማስተጋባት

5ኛ. የካቲት 1 ሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪ እንዲቀበሉ ማድረግ (ከዚህ በፊት ጥር 1 ላይ እንጀምራለን ብለው የነበረ ያልተሳካላቸው)

6ኛ. የጥር 3 ኦፕሬሽን የተሳካ እንዲሆን ለሚሊሻ እና አድማብተና ደሞዝ ቅድሚያ መስጠት።

ይቀጥላል...

11/01/2024

ቀድመህ አጋልጥ - የአገዛዙ የፀጥታ አመራሮች ስልጠና!

ለሚሊሽያና ለአድማብተና አመራሮች "የህግ ማስከበር ስልጠና" በሚል በባህርዳር ከተማ ለማድረግ ታስቦ የነበረ ቢሆንም፣ በባህርዳር ከተማ ያለው ነባራዊ ሁኔታ ስልጠናውን ለማድረግ የሚያስችል አለመሆኑን የአገዛዙ ሰዎች ገምግመው ቦታዎቹ ሊቀየሩ እንደቻሉ የባህርዳር ዊክሊክስ ምንጮች ይገልፃሉ።

በዚህም መሰረት ከነገ ጀምሮ፦

▪︎የጎጃም ቀጠና - በደብረ ማርቆስ ከተማ
▪︎የጎንደር ቀጠና - በጎንደር ከተማ
▪︎የቤተአማራ ወሎ ቀጠና - ደሴ ከተማ
▪︎የከሚሴ ዞንና ሸዋ ቀጠና - በደብረ ብርሃን ከተማ

ስልጠና የአገዛዙ የፀጥታ አመራሮች ስልጠና እንደሚጀመር ታውቋል። ይህ መረጃ ለወገን ኃይል መድረስ ይኖርበታልና ይዛመት።

10/01/2024

የታሪክ ነገር ይገርማል!
===============
በስራ አጋጣሚ ከሶማሌዎች ጋ ተቀራርቦ የማውራት እድል ነበረን። ከየት ነህ? ከየት ናችሁ ተባብለን እንድንጠያየቅ የሚያደርግ ነገር በመካከላችን አልነበረም። እነሱ ከሶማሊያ እኛ ከኢትዮጵያ እንደሆንን በ appearance ~ ብቻ እንተዋወቃለን። እነሱ ግን አልፈው ይጠይቃሉ። በወያኔ ጊዜ ~ ኢትዬጵያዊ ሆነህ ምንድን ነህ ይሉ ነበር። ከቁጣቸው የሚያተርፍህ ያኔ ኦሮሞ ነኝ ያልክ ከሆነ ብቻ ነበር። ትግሬ ነኝ ካልክ መለስ ዜናዊ የሚባል አረመኔ በአሜሪካ ዶላር ተሸጦ በህዝባችን ላይ የሰራውን ግፍ መቼም ቢሆን የምንረሳው ጉዳይ እንዳልሆነ እንድታቀው ይሉ ነበር። አማራ ነኝ ካልክ እናንተ ሙስሊምን የበደላችሁ ~ عدو الإسلام ~ ይሉሀል። አረብኛው ሲነበብ ~ ዓዱውል ኢስላም ~ የሚል ሲሆን ትርጉሙ ~ የእስልምና ጠላቶች ~ ማለት ነው።

እንዴት እንደዚያ ልትሉ ቻላችሁ ካልካቸው በኦሮሞ ኦንጋውያን ታጋዬች በኩል ሁሉንም ነገር እንደሚያውቁ ይነግሩሀል። ስለ አማራ የተፈበረከው የኦነግ ታሪክ በሀገራችን ፖለቲካ ውስጥ የምንናቆርበት ብቻ ሳይሆን ድንበር ዘለልም ጭምር ነበር። ኦሮሞ ማለት ሙስሊም ማለት ሲሆን አማራ ማለት ክርስቲያን ማለት እንደሆነ ሶማሌዎች ከኦነግ ላይ የጠጡትን ወልጋዳ ትርክት አይናቸውን ሳያርገበግቡ ይነግሩሀል።

በዚህ አይነት ንግግራችንና ውይይታችን መካከል አይ እኔ እኮ መሀመድ ሀሰን ነው የምባለው። በብሄሬ አማራ ነኝ፣በሀይማኖቴ ሙስሊም ነኝ ስላቸው ~ They were dead sure and መልሳቸው ~ you can't be ~ የሚል ነበር።

እኔም ~ with basic common sense simple logic ~ ጥያቄዮን አስከትላለሁ። አሁን እናንተ ለኔ እንደ ህዝብ ሱማሌያውን መሆናችሁንና በእምነት እስልምናን እንደምትከተሉ ነገራችሁኝ።

Then,
Do you think it would be right or wrong, or rationally correct for me to say, that while you are a Somali you can't be a Muslim?

Sure they would pose for a moment of processing followed by a moment of silence.

ውይይታችን ይቀጥልና ነገር ግን እነኚያ የአማራ አፄዎች የእስልምና ጠላትና ጨቋኝ ነበሩ ይላሉ። እንደ ወያኔዎችና እንደ ኦነጋውያን በገገማው እኛ ብቻ የምንለውን ስማን የሚሉትን ትተን በ reason, በ logic, በ common sense and በባለሙያተኛ የታሪክ ተመራማሪ ፀሀፊዎች ፅሁፍ መረዳት የሚችሉትን እንዲህ ብለን አናስረዳ ነበር።

አፄ ቴዎድሮስ ~ በእርግጥ አማራ ነበሩ። አፄ ዪሀንስ ትግሬ ነበሩ። አፄ ሚኒሊክ አማራ ነበሩ። አፄ ሀይለስላሴ ከአማራ፣ከኦሮሞና ከጉራጌ ዘር የተገኙ ነበሩ። ይሄን instant brainstorming ከሰጠን በኋላ ~ የበለጠ እውቀት እንዲኖራቸው ሊያደርጓቸው የሚችሉ የታሪክ መዛግብት reference አክለንላቸው የአፄዎቹ የማንነት ስብጥር እንዲህ በሆነበት እውነታ ውስጥ የአፄዎቹ የአገዛዝ ዘመን የአማራ ብቻ ነበር ማለት ይቻል ነበር ወይ? ብለን ጥያቄ ስናቀርብላቸው ~ we saw them in a state of stupefaction and wandering. We saw them in awe.

በሰአቱ በዚህ እስከ hair-splitting በሚባል ደረጃ ወርደን ነገሮችን ለማስረዳት የምንሞክር የነበረው በየትኛውም በሰው ልጅ በተቋቋመ መንግስት ስር ሊፈጠርና ሊደርስ የሚችለውን የመንግስታዊ አስተዳደር እንከንና እክል ለመሸፋፋን ሳይሆን ካለ አግባብ በበአማራ ህዝብ ላይ ይዘራ የነበረው ውሸት እንደ አማራነታችን በጣም ይረብሽን ስለነበር ነበር። ምክኒያቱም የውልደት ማንነትና ቋንቋ የፖለቲካችን መሰረት የቆመበት የዚህ ዘመን እውነታ በሆነበት አለም ሰማያዊ በሆነው እምነት አንዱን ፃድቅ አንዱን ወንጀለኛ ተደርጎ ይቀርብ የነበረው ትርክት ከመሰረቱ ልክ አልነበረም።

Fast forward
===========
ከመለስ ዜናዊ የሶማሊያ ዘመቻ በኋላ በአጠቃላይ ለኢትዮጵያውያን በተለይ ደግሞ ለትግሬዎች የነበረው አመለካከት መልካም አልነበረም። ዛሬ አብይ አህመድ በ ill advised ፖለቲካና ከፋኖዎቻችን የትግል ተፅእኖ ለመውጣት በተቀመረው የእውር በድንብሩ ጉዞ በአንድ ወቅት የአማራን ህዝብ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የጦስ በሬ አድርጎ በፖለቲካውም፣በታሪኩም ሆነ በሀይማኖት ያቀርብ የነበረው የኦነጋውያን ትርክት ባርቋል። በወልጋዳ ትርክት መሬት ለመሬት ሲጎተት የነበረው የአማራ ህዝብ ስም ምንም እንኳ ጥፋትን በህዝባችን ላይ ያመጣ መሆኑ ባይካድም የህዝባችንን እውነት ደብቆ ማቆየት አልተቻለም። ጊዜ ማን ምን እንደሆነ ፈልቅቆ እያሳየን ነው።

ዛሬ በአብይ አህመድ እብደትና በኦዴፓዎች ማንአለብኝነት ~ the page of a history book is turned into another chapter of an unfortunate reckoning.
=========
Only the truth shall set you

source :Mohammed Hassen

  ፦ የመንዝ ላሎ ወረዳ የአገዛዙ መዋቅር ሙሉ በሙሉ ፈረሰ!▪︎የመንዝ ላሎ ወረዳ 52 የብልጽግና አገዛዝ የፖለቲካና የፀጥታ አመራሮች ታህሳስ 28/2016 ዓ.ም ለሸዋ መንዝ ላሎ ሰበር ፋኖ ...
10/01/2024

፦ የመንዝ ላሎ ወረዳ የአገዛዙ መዋቅር ሙሉ በሙሉ ፈረሰ!

▪︎የመንዝ ላሎ ወረዳ 52 የብልጽግና አገዛዝ የፖለቲካና የፀጥታ አመራሮች ታህሳስ 28/2016 ዓ.ም ለሸዋ መንዝ ላሎ ሰበር ፋኖ በፃፉት ደብዳቤ መሰረት የወረዳውን የአገዛዙ መዋቅር ሙሉበሙሉ በፈቃዳቸው አፍርሰው፣ ፋኖን በይፋ መቀላቀላቸውን ገልጸዋል። የደብዳቤው ሙሉ ይዘት ቀጥሎ ቀርቧል።

👉 "እኛ ከዚህ በታች ስማችን የተዘረዘረው የሰሜን ሸዋ ዞን የመንዝ ላሎ ምድር ወረዳ የብልጽግና አመራር የነበርን፣ የፖሊስ አባል የነበርንና የሚሊሻ አባል የነበርን፣ (ቀደም ሲል) በነበረን ስልጣንና ኃላፊነት አገዛዙን በማመንና ለአገዛዙ በመታመን ከአገዛዙ የሚሰጠንን ተልዕኮ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ስንፈፅምና ስናስፈፅም የቆየን ሲሆን፣ አሁን ግን የአማራ ህዝብ ግፍና በደል ስላሳሰበንና የመንግሥትን ሴራ ስለተረዳነው የአማራ ፋኖ እያደረገ ያለውን የህልውና ትግል ከዛሬ ጀምሮ #የተቀላቀልን መሆኑን በፊርማችን እናረጋግጣለን።

ስም ዝርዝር… ኃላፊነት…
ከሰላምታ ጋር"

አስተያየት፦ በነገራችን ላይ በሰሜን ሸዋ ብዙ ወረዳዎች አገዛዙን በተመሳሳይ እያስወገዱ በራሳቸው እየተመሩ ይገኛሉ። አራዊት ሰራዊቱም ወደ ወረዳዎቹ ሲገባ እምሽክ ስለሚል ሰልችቶት አሁን ነፃ ቀጠና እየሆኑ ይገኛል። ለአብነት ያህል መርሐቤቴን፣ ሚዳና ወረሞንና የመንዝ ወረዳዎችን መጥቀስ ይቻላል። የመንዝ ላሎን ወረዳን ለየት የሚያደርገው ግን የአገዛዙ የፖለቲካና የፀጥታ አመራሮች በይፋና በፈቃዳቸው ፋኖን መቀላቀላቸው ነው። ለዚህም ታላቅ ታላቅ አድናቆታችንን መግለጽ እንፈልጋለን።

10/01/2024

~ ዛሬ ሌሊት በመንዝ መሐል ሜዳ በአሸባሪው አገዛዝ ወታደሮች ካምፕ ላይ በተደረገ ድንገተኛ ኦፕሬሽን ከ 40 በላይ ወራሪ ሲደመሰስ በርካቶች ቆስለዋል።

ድል ለህዝባችን!

10/01/2024

~ ባለ ስልጣናት ተሸኝተዋል!

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ ጫንድባ አካባቢ እርጎ ሜዳ በተባለ ልዩ ቦታ በተጣለ ደፈጣ በአምቡላንስ ሲጓጓዙ የነበሩ ሠባት የአሸባሪው አገዛዝ ባለስልጣናት ላይ እርምጃ ተወስዷል።

የወረዳው የሠላምና ደህንነት ሀላፊ፣ የፖሊስ ኮማንደርና የገቢዎች ሀላፊን ጨምሮ ሠባቱም ሆድ አደር አመራሮች እስከወዲያኛው ተሸኝተዋል።

ድል ለህዝባችን!

ሰበር መረጃ - ከባህር ዳር በጎጃም ዕዝ የባህር ዳር ፋኖ ስር ሁለት ሻምበሎች ታሪካዊ ስያሜን ይዘው መመስረታቸው ታውቋል።1. አንሻ ሰይድ ሻምበል - በጀግናዋ እህታችን ፋኖ ህይወት ጌራ የሚ...
10/01/2024

ሰበር መረጃ - ከባህር ዳር

በጎጃም ዕዝ የባህር ዳር ፋኖ ስር ሁለት ሻምበሎች ታሪካዊ ስያሜን ይዘው መመስረታቸው ታውቋል።

1. አንሻ ሰይድ ሻምበል - በጀግናዋ እህታችን ፋኖ ህይወት ጌራ የሚመራው ይሆናል። ይህ ሻምበል ስያሜውን በወለጋ ክልል ቤተሰቦቿን የኦነግ ታጣቂዎች በማጨፍጨፍ ላይ እያሉ እራሷን ለማትረፍ "ወላሂ ሁለተኛ አማራ አልሆንም፤ አትግደሉኝ" በማለት በተማፀነችው ህጻን አንሻ ሰይድ የተሰየመ መሆኑ ታውቋል።

"አንሻ ሰይድ የትግላችን ቃል ኪዳን ሆና፣ ታናናሾቿ በማንነታቸው ኮርተውና ተከብረው የሚኖሩባትን ለሁሉም እኩል የሆነችን ሃገር ለመፍጠር እንታገላለን" ሲሉ የሻምበሏ አባላት ተናግረዋል።

2. ታዲዮስ ታንቱ ሻምበል - ይህም ሻምበል በጎጃም ዕዝ የባህር ዳር ፋኖ ስር የተመሰረተ ሲሆን በቅርቡ ወደ ሻለቃ እንደሚያድግም ተነግሯል። ይህ ሻምበሉ ስያሜውን የወሰደውም ለእውነት ታምነው በእርጅና እድሜያቸው መስዕዋትነት እየከፈሉ ካሉት የወላይታው አንጋፋ ጋዜጠኛና የታሪክ ምሁር ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ ስም እንደሆነ ታውቋል። ፋኖዎቻችን በአጋጣሚውም "ለጋሽ ታዲዮስ ታንቱ እጅግ እጅግ ታላቅ አክብሮት አለን" ሲሉ ለሚዲያዎች የላኩት መልዕክት ያስረዳል።

በዚሁ አጋጣሚ በሌሎች አካባቢዎች ያላችሁም ፋኖዎቻችን እነዚህንና መሰል ትልቅ ትርጉም ያላቸውን ስያሜዎች እንድትጠቀሙ ጥሪ እናቀርባለን። ዝቅ ያደረጓቸውን፣ በታሪክ ውስጥ ተገቢና ጉልህ ስፍራ ሰጥተን ከፍ አድርገን እናሳያቸው!

10/01/2024

ቡሬ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ያሉ ወታደራዊ አዛዦች ከእንቅልፋቸው ሲነቁ ጓዶቻቸው ከእነ ትጥቃቸው ከጠፉባቸው፣ ከእኛ ጋር እንደሆኑ ንገሯቸው።

በርካታ የሰራዊቱ አባላት በመክዳት የቡሬ ዳሞት ፋኖ ብርጌድ ነጻ ቀጠና ወደሆነ አካባቢ በሰላም መድረሳቸውን ስናበስር በደስታ ነው። በፋኖዎቻችንም ወገናዊ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

እነዚህ ወንድሞቻችን ብሬን ጨምሮ ከእነሙሉ ትጥቃቸው ለፋኖዎቻችን እጃቸውን የሰጡ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ አንድ የመቶ አለቃ አዛዥ ይገኝበታል። በተመሳሳይ የአራዊት ሰራዊቱ ዋና የህክምና ባለሙያም በዚሁ ቀጠና ለአባይ ብርጌድ እጁን መስጠቱ ታውቋል።

09/01/2024

የግንዛቤ ማስጨበጫ መረጃ ለፋኖዎቻችን

1. ለጥቃት ወይም ቅኝት የሚላክ ድሮንን እንዲበር የተሞላበትን ከፍታ ማወቅ በጥንቃቄና ቀላሉ ድሮኑን ለመምታት ያግዛል። ስለዚህ ያለንን መሳሪያ የሚሸፍነውን ርቀት እና የድሮኑን ከፍታ ታሳቢ አድርጎ መምታት ይቻላል። ከanti-drone ባሻገር የድሮኑ ከፍታ ማወቅ ትልቁ ጥቅሙ ከተቻለ lock አድርጎ በዙ-23 መምታትም ሊመታ እንደሚችል የአየር ኃይል ምንጮቻችን ያደረሱን መረጃ ያስረዳል።

2. ከአማኑኤል ጀምሮ እስከ ፍኖተሰላም እና በሸዋ ደግሞ ጀማ ወንዝ አካባቢ የድሮን ቅኝቶች እንዳሉ ታውቋል። ጥንቃቄ ይደረግ!

3. ሶስተኛው መረጃችን ደግሞ ፋኖዎቻችን polygraph የሚባልን የምርኮኞች ስምሪት (ውሸት ካለም) ለማወቅ የሚያግዝ ወታደራዊ ማሽን በብዛት ማስገባት መቻላቸው እጅግ መልካም የሚባል ዜና ነው። ከእንግዲህ ስምሪት ወስዶ የሚማረክ አራዊት ሰራዊት ካለ፣ ግንባሩ ላይ ፈርዶ ይሆናል ማለት ነው። አንዱ polygraph 300 ዶላር ብቻ በመሆኑ በቀላሉና በብዛት ማግኘት ተችሏል።

09/01/2024

ከጎጃም ዕዝ ፋኖ የተሰጠ መግለጫ

ፋኖነት ቅንጦት ሳይሆን የአማራ ህዝብ ፍትህ በተጓደለበት፣ ነፃነቱ በተገፈፈበት፣ ጠላት አገሩንና ሀይማኖቱን ሊያረክስ በመጣበት እና የመኖርና ያለመኖር የህልውና ትግል በገጠመው ጊዜ ለክብሩ ለማንነቱ ለሀይማኖቱ ሲል በአንድነት የሚነሳበት እሴቱ ነው። በመሆኑም አማራ በአንድነት በተነሳበት በዚህ ጊዜ በተለይም በጎጃም ፈር ቀዳጅ ሆኖ በየወረዳው የተበታተነውን ትግል አንድ አድርጎ አራት ኪሎ ትንሳዔውን ለማክበር በጎጃም ቀጠና ዕዝ ከተመሰረተ ቅርብ ጊዜ ቢሆንም ጥሩ ውጤትን እያስመዘገበ ይገኛል።

ስለሆነም የጎጃም ዕዝ ባደረገው 4ተኛው አስቸኳይ የስራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ በተለያዩ የትግሉ ቀዳሚ በሆኑ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ከተወያዬ በኋላ የሚከተለውን ባለ ሁለት ነጥብ የአቋም መግለጫ በመስጠት ሌሎችን አጀንዳዎች በይበልጥ የማሰቢያ ጊዜ አስቀምጧል።

1ኛ.የዲያስፖራ ክንፉ በአማራ ህዝብ ትግል ውስጥ ከሀሳብ እስከ ፋይናንስ በማገዝ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ይታወቃል። በመሆኑም በጎጃም ዕዝ ፋኖ በውጭ የሚገኙ የአማራ ተወላጆችን እና ሌሎች የፋኖን እንቅስቃሴ ደጋፊዎች ለማስተባበር እና የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ በማሰብ በዕዙ ስራ አስፈፃሚ ሰፊ ውይይት ከተደረገ በኋላ የውጭ ማህበረሰባችንን እንዲያስተባብሩና አስቸኳይ የሃብት አሰባሳቢ ኮሚቴ (Emergency Fund Rise Committee) ያዋቀረ ሲሆን በኮሚቴው በኩል ለሁለት ሳምንታት ውይይቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል። ኮሚቴውም ዘጠኝ አባላት ያሉት ሲሆን ጋዜጠኛ ተስፋዬ ወልደስላሴን ሰብሳቢ አድርጎ መርጧል።
ስለሆነም በውጭ የምትኖሩ የአማራ ባለሀብቶች፣ የማህበረሰብ አንቂዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ዩቲዩበሮች፣ ቲክታከሮችና በሁሉም የሚዲያ ፕላትፎርሞች ውስጥ ያላችሁና የፋኖን የህልውና ትግል የምትደግፉ ወገኖቻችን ትብብራችሁን የምንጠይቅ መሆኑን እየገለጽን እናንተ በምትሳተፉባቸው ሚዲያዎች ያሉትን አድማጭ-ተመልካቾቻችሁን፣ አድናቂዎቻችሁንና ደጋፊዎቻችሁን ግንዛቤ በመፍጠር ጥር አስር ለሚጀመረው ዘመቻ የበኩላችሁን አሻራ እንድታሳርፉ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

2ተኛ.ሐሰተኛ በቃሉ፣ ስደተኛ በቅሉ ይታወቃሉ እንዲል ብሂሉ የፋሽስታዊ አገዛዙ ክልል ብሎ ባስቀመጠው በረት/ክልል/ ውስጥ ሰላም ያለ ለማስመሰልና ተማሪዋችን የፕሮፖጋንዳው/የፖለቲካው ሚዛን ማስጠበቂያ ቀብድ በማድረግ የስርዓቱ ስልጣን አስጠባቂ የሆነውን የትምህርት ስርዓት በመጠቀም በአማራ ክልል* ውስጥ የሚገኙ ዩንቨርስቲዎች በከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር በኩል በተደረጉ ጫናዎችና በምንጣፍ ጎታች የዩኒቨርሲቲ ፕሪዝዳንቶች አማካኝነት የተለያዩ ዩንቨርስቲዎች ለተማሪዎቻቸው ጥሪ ማድረጋቸው ይታወቃል።
ነገር ግን በክልሉ ውስጥ የአማራ ህዝብ ለህልውናው (ለነጻነት፣ ለእኩልነትና ፍትሃዊነት) እልህ አስጨራሽ ትግል ከጨፍጫፊውና ፋሽስታዊው አገዛዝ ጋር እያደረገ ይገኛል። በዚህ ትግልም አመርቂ ውጤቶችን በማስመዝገብ የጨፍጫፊውን አገዛዝ እያፈራረሰው ይገኛል።
ስለሆነም ውድ ተማሪዎች ትምህርት ለአማራ ልጅ በዚህ ሰዓት ቅንጦት ሆኖበት ከክርስቲያን እስከ ሙስሊሙ፣ ከህጻናት እስከ ሽማግሌውና ከአርሶ አደር እስከ መንግስት ሰራተኛው/ምሁራን/የአያቶቹን ታሪክ በመድገም በዱር በገደሉና በፀሃይ በብርዱ ለህልውናው በከፍተኛ ደረጃ እየተዋደቀ በሚገኝበት በዚህ ሰዓት የተማሪዎችን እንቅስቃሴ መሰረት በማድረግ መፈርጠጥ ልምዱ የሆነው ጨፍጫፊው ቡድን በፋኖ ላይ ጥቃት ለመሰንዘርና በሚወሰደው የአጻፋ እርምጃ በሚደርስ ጉዳት ፋኖ በንፁሀን ተማሪዋች ላይ ጥቃት ፈጸመ በማለት ፕሮፖጋንዳ ለመንዛት እየሰራ እንደሆ መታወቁ የአደባባይ ሚስጥር ሁኗል።
ስለሆነም የፋሽስታዊ አገዛዙን ጥሪ ተቀብለው በሚመጡ ተማሪዋች ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ሃላፊነቱን መንግስት ነኝ የሚለው ጨፍጫፊው ቡድንና እራሳችሁ ተማሪዎች የምትወስዱ መሆኑን እንድታውቁ በአፅዕኖት እናሳስባለን።

ድል ለተገፋው የአማራ ህዝብ!
ድል ለፋኖ!

ጎጃም ዕዝ ፋኖ!
ታህሳስ 30/2016 ዓ.ም

09/01/2024

አብይ አህመድን ግንባራቸው መሬት እስኪበሳ ድረስ እየሰገዱ ወንበሩን ያመቻቹ ሰዎች አሁን ደግሞ ለጃዋር መስገድ፣ መንከባለል እና መንደባለል ጀምረዋል፡፡ አሁንስ ድጋሚ ልታስጨርሱን እድል የላችሁም፡፡ እድሜ ለፋኖ!

09/01/2024

በፍኖተሰላምና አካባቢው ዛሬ የተሰራው ጀብዱ!

▪︎ከፍኖተሰላም በቅርብ ርቀት ላይ ወዳሉት
መንዝና ገራይ አካባቢዎች አራዊት ሰራዊቱ በ3 አቅጣጫዎች ለመክበብና ጥቃት ለመሰንዘር እንዳሰበ የፋኖ የደህንነት መዋቅር መረጃ ደርሶበታል። ፋኖዎቻችን የእራሳቸውን እቅድ ነድፈው ይጠብቁ ጀመር።

▪︎አራዊት ሰራዊቱም በጠዋቱ ወደ ሁለቱ ቀበሌዎች ተንቀሳቀሰ፤ ሚሊሽያም ሆነ አድማ ብተና አብረውት የሉም። በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ግን ፋኖዎቻችን በእራሷ በፍኖተሰላም ከተማ ውስጥ በቀረው ኃይል ላይ ከ3 አቅጣጫዎች ጥቃት ከፈቱ።

ወዲያውም፦

1) በባዕታ ቤተክርስቲያን አካባቢ ከ10 በላይ አራዊት ሰራዊት አስክሬን ሲሆን ከ15 ላይ ደግሞ ቁስለኛ ሆኗል። ሌሎች ደግሞ ቀጠሉ…

2) በገወቻ ስላሴ መውጫ ከ40 በላይ ሚሊሻ እና አድማ ብተና ተደመሰሰ። ቀጠሉ…

3) በመምህራን ኮሌጅ አካባቢ ደግሞ በርካታ አራዊት ሰራዊት፣ ሚሊሽያና አድማ ብተና ሲደመሰስ፣ ቀላል የማይባል ቁስለኛም እንደተመዘገበ ታውቋል።

▪︎ፋኖዎቻችን ይህን ጥቃት ፈፅመውም ከድልድዮ (ከፍርን ከላህ ወንዝ) ማዶ ያለውን የከተማውን ግማሽ ክፍል በቅፅበት ውስጥ ተቆጣጥረዋል።

▪︎ይህ እየሆነ እያለ ወደ መንዝ እና ገራይ የተንቀሳቀሰው ሰራዊት ወደ ቀበሌዎቹ እየደረሰ ነበር። ቢሆንም ግን ገና ሳይረጋጋ ቦታ ይዘው የነበሩት ፋኖዎቻችን ተኩስ ሲከፍቱበት ያን ያክል የአፀፋ ምላሽ ሳይሰጥ በፋኖ ወዳልተያዘው የከተማዋ ክፍል ሲሮጥ መግባቱ ታውቋል።

▪︎በነገራችን ላይ አራዊት ሰራዊቱ ሚሊሽያና አድማ ብተና አብረው ከሌሉ የመዋጋት ድፍረትም ሞራልም እንደሌለው ይነገራል፤ አብረው ሲኖሩ ግን ከፊት እያሰለ የእሳት እራት እያደረጋቸውና ሲሸሹ ደግሞ እራሱም እየጠበሳቸው እንዳለ የሚታወቅ ነው።

እምባ አባሾቻችን ፋኖዎች "አንሻ ሰይድ ብርጌድ" ተብሎ የሚጠራ መመስረታቸውን ስንሰማ:–"The absence of the will to live is, alas, not sufficient to make...
09/01/2024

እምባ አባሾቻችን ፋኖዎች "አንሻ ሰይድ ብርጌድ" ተብሎ የሚጠራ መመስረታቸውን ስንሰማ:–
"The absence of the will to live is, alas, not sufficient to make one want to die."

የሚለው ጥቅስ ለምን ትዝ እንደሚለን አማራ በመሆናችን እኛ ብቻ ነን የምናቀው!

09/01/2024

በእንጅባራ ወታደራዊ ካምፕ ምን ተፈጠረ?

ታህሳስ 29 ከምሽቱ 3:00 እስከ ሌሊት 6:00 አካባቢ በእንጅባራ ከተማ ካምፕ ውስጥ የነበረ አራዊት ሰራዊት እርስበርሱ ሲለባለብ እንዳደረ ታውቋል። በዚህ ለሰዓታት በቀጠለው የተኩስ ልውውጥ በርካቶች እንዳለቁ ተገምቷል። በርካታ የሰራዊቱ አባላትም መክዳታቸው የታወቀ ሲሆን እንደምርጫቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲገናኙ የሚመቻችላቸው መሆኑን ከወገን ኃይል በኩል ተሰምቷል።

በሌላ በኩል ደግሞ በአዲስ አበባ 6 ኪሎ አካባቢ ለጊዜው ምክንያቱን ያላወቅነው የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ተነግሯል። ያው ነገሮች ወደ መቋጫቸው ሲቃረቡ ይህን መሰል ነገሮች የሚጠበቁ ናቸው። በመጨረሻዋ ሰዓትም የጨቅላውን ግንባር በእርሳስ የሚፈትን ዳዊት ይወለዳል።

09/01/2024

የአማራ ብሄርተኝነት እናት የሆነችው መስከረም አበራ ጃዋርን መሐመድ ኢትዮዽያ ኢትዮዽያ ያስባለው እና tone of speech እንዲለወጥ ያደረገው እሱ እንደነገረን ታስሮ ETVን ስለተከታተለ ሳይሆን ከታች በተዘረዘሩት ሶስት ምክንያቶች እንደሆነ
ከአመት በፊት ገልፃ ነበር

1️⃣የኦሮሞ ፖለቲካ በውስጡ ብዙ ስንጥቃቶች በመፈጠራቸው እነዚህን ችግሮች ሳይፈቱ ስለ ኦሮሞ ሪፐብሊክ ማሰብ ለኦሮሞውም አደገኛ ስለሆነ ግዜ መግዛት እና ያላለቁ ስራዎችን በኢትዮዽያ ውስጥ ሆኖ መስራት ግዴታ መሆኑን መገንዘቡ፤

2️⃣የአማራ ብሔርተኝነት በከፍተኛ ደረጃ ማደግ እና ብሔርተኝነቱ ደግሞ በትጥቅ ትግል መታገዙ እንዲሁም የአማራ ብሔርተኛ thought of clarity ላይ መድረስ በኢትዮዽያዊነት ሽፋን አማራውን ማታለል የማይቻልበት ደረጃ መደረሱ፤ አማራው ለአማራነቱ ቅድሚያ ሰቶ ከኦሮሞ ጋር ፍጥጫ ውስጥ እንደሚገባ ስለገባው፤

3️⃣በአሁኑ ወቅት የኦሮሞ ፖለቲካ በምዕራባዊያን ዘንድ ተበዳይ ሳይሆን የአናሳዎችን መብት እና ህልውና የማያከብር በሚል እየታየበት ያለበት ሁኔታ
እስከዛሬ ከሚታይበት “የተበዳይነት “እይታ ወቶ የጨፍጫፊነት እና የአፈናቃይነት ምስል መጎናፀፉ ጃዋርን እረፍት እንደነሳው እና እንዳሳሰበው መስኪ ትገልፃለች።

09/01/2024

ባህር ዳር

ትላንት ረፋድ ባህር ዳር ወረዳ ፍ/ቤት ላይ ባልታወቁ ኃይሎች በተጣለ ቦንብ የፍርሃት ቆፈን የሚጋልበው የብልፅግና ካድሬ ዛሬ ፍርድ ቤቶች ዝግ እንዲሆኑ አድርጓል። በርካታ ቁጥር ያለው ፖሊስ ዛሬ ሙሉዓለም አዳራሽ ግቢ ውስጥ ተሰብስበው እንዲቀመጡ ተደርጓል። ሚኒሻ ተልካሻ , ሰላም አስከባሪ እና አድማ ብተና ዋና ዋና መንገዶችን በእግር እየዞሩ ይታያል። ዘንድሮ ቁርጥ ነው !!
ተሰፉየ ወ/ስላሴ

08/01/2024

ይህን ሴራና የጭፍጨፋ ዕቅድ ቀድመህ አጋልጥ!

በሽመልስ አብዲሳ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ከ250 በላይ የኦሮሞ ታጣቂዎችን ከአካባቢው ባንዳዎች ጋር በማጣመር በቡሬና ቁጭ አቅራቢያ ባሉት ቦቆጣቦ እና ሶንቶም ቀበሌዎች አስታጥቆና አስርጎ ማስገባቱን የኦሮሚያ ክልል ምንጮቻችን ያደረሱን መረጃ ያስረዳል።

ይህ ታጣቂ ኃይል በኦሮሚያ ክልል የሚፈፀመውን ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ተቀጥያ የሆነ ስምሪት እንደወሰደ ተነግሯል። በነገራችን ከወር በፊት በተመሳሳይ ከኦሮሚያ ክልል ወደ ሰንቶም በገቡ ታጣቂዎች ምክንያት በርካታ ሺዎች ወደ ቂጭና ሌሎች አካባቢዎች መፈናቀላቸው የሚታወስ ነው።

ሙሉ በሙሉ? 🤔 ጉድህን ተመልከት ያገሬ ስው?ሆን ተብሎ የተሰራጨ ነጭ ውሸት ወይስ የተለመደ ማደንዘዣ?
05/01/2024

ሙሉ በሙሉ? 🤔

ጉድህን ተመልከት ያገሬ ስው?ሆን ተብሎ የተሰራጨ ነጭ ውሸት ወይስ የተለመደ ማደንዘዣ?

04/01/2024

በጎጃም ፋኖ ዕዝ ሶስተኛ ክፍለ ጦር ስር
የአባይ ሸለቆ ብርጌድ
በመቶ አለቃ አያሌው ይርሳው መሪነት እና
በውጭ ግንኙነት አስተባባሪው ውባለ ተገኘ ፊት አውራሪነት ዛሬ መርጡለማርያም ዙሪያ አራት ቦታዎች ላይ ደረቅ ወንዝ ,ድቦ,ጎረፍ እና መርጡለማርያም ከተማ ከባድ ትንቅንቅ ተደርጎ ጠላት ክፉኛ ተመቷል። ፋኖ ጠንካራ ትግል በማድረጉ የጠላት ጦር አስክሬኖቹን ማንሳት ሳይችል በመፈርጠጡ የወገን ጦር በአማራዊ ክብር እንዲቀበሩ አድርጓል ።
በውጊያው ሂደት አራተኛ ሻምበል ለልዩ ኦፕሬሽን መርጡለማርያም ከተማን ተቆጣጥሮ አስፈላጊውን ኦፕሬሽን ከሰራ በኋላ ከከተማው ወጥቶ ገዥ ቦታ ይዞ ተቀምጧል ።

ድል ለፋኖ !!

ሰበር የጀብድ ዜናበ50 አለቃ ወንድሙ ማሩ  የሚመራው💪 የላስታ አውራጃ ብ/ጄኔራል አሳምነው ፅጌ  #ክፍለጦር በዛሬው  #ዕለት ማለትም ታህሳስ 14 ቀን 2016 ዓም ከጧቱ 3:00 በአንድ ሲኖ...
24/12/2023

ሰበር የጀብድ ዜና

በ50 አለቃ ወንድሙ ማሩ የሚመራው💪

የላስታ አውራጃ ብ/ጄኔራል አሳምነው ፅጌ #ክፍለጦር በዛሬው #ዕለት ማለትም ታህሳስ 14 ቀን 2016 ዓም ከጧቱ 3:00 በአንድ ሲኖ ትራክ፣ በሁለት ኦራል እና በአንድ Iveco ትራክ ሙሉ ተጭኖ ከላሊበላ ወደ ቡግና ሲጓዝ የነበረ የጠላት አብይ ጦር ልዩ ቦታው ገንጅ የተባለውን ቦታ አለፍ ብሎ "መስኮይ" ከምትባል ቦታ በነበልባሎቹ የጀግናው የአሳምነው ፅጌ ልጆች በተፈፀመ መብረቃዊ የደፈጣ ጥቃት በአራቱም ከባድ መኪኖች ላይ ተጭኖ የነበረው ግዑዛን የጠላት አብይ ጦር ሙሉ ለሙሉ መደምሰስ ሲቻል መኪኖቹ ሲቃጠሉ የተወሰኑ ዘመናዊ የነፍስ ወከፍ እና የቡድን መሳሪያዎችን ማግኘት ተችሏል።

አሁን በዚህ ስዓት ተጨማሪ እሬሳ አንሽ ኃይል በማምጣት እሬሳውን ሲለቅም ገዥ ቦታዎቻችንን ይዘን እያየነው ነው ብለዋል።

መንገሻ ፈንታው የክልሉ ኮሙኒኬሽን "ፋኖን ከገባበት ገብቶ መከላከያችን ይበቀለዋል" ብሎ በዛተው ዛቻ መሰረት ህዳር 19/2016ዓም በድሮን ጥቃት ወገኖቻችንን መጨፍጨፉ ይታወቃል። ይህ የዛሬው በጠላት ላይ የተፈፀመው የደፈጣ ጥቃት ከ120 በላይ ቲማትምን ስናፈርጠው ለድሮን ጥቃቱ የተሰጠ መልስ መሆኑን ደም መላሾቹ የጀግናው የአሳምነው ፅጌ ልጆች ገልፀዋል።

አሳምነውዊዝም ብቸኛ የመዳኛ መንገዳችን ነው!!!!

24/12/2023

አስቸኳይ ነው!

በትናንትው ዕለት (ቅዳሜ ታህሳስ 13) ከሰኔ ማርያም ወደ እስቴ የተመለሰው አራዊት ሠራዊት፣ ዛሬ ወደ አንዳቤት ጃራ ገዶ ለመግባት ጉዞ ላይ እንዳለ ለወገን ኃይል አስቸኳይ መልዕክት ይድረስ።

24/12/2023

በጤና ተቋም ላይ የድሮን ጥቃት ተፈፅሞ፤ የተቋሙ ባለቤት፣ የጤና ባለሙያዎችና ታካሚዎች በቦንብ ጋይተው ሚዲያዎች ሁሉ ዝም!!! የሐኪሞች ማህበር ፀጥ፣ የአለም የጤና ድርጅት ባልሰማ ባላየ አለፈ!!!
ብቸኛው መዳኛችን #ፋኖነት ብቻ ነው

መተከል ላይ 207 ወገኖቻችን በሰዓታት ልዩነት በግፍ ተጨፍጭፈው በዶዘር በጅምላ ከተቀበሩ 3 ዓመት ሆነ፤   ያንጊዜ የምንጮኸው በተለምዶ ከክልሉ ውጭ ኗሪ ለሚባለው አማራ ነበር። ዛሬ አማራ ...
24/12/2023

መተከል ላይ 207 ወገኖቻችን በሰዓታት ልዩነት በግፍ ተጨፍጭፈው በዶዘር በጅምላ ከተቀበሩ 3 ዓመት ሆነ፤ ያንጊዜ የምንጮኸው በተለምዶ ከክልሉ ውጭ ኗሪ ለሚባለው አማራ ነበር። ዛሬ አማራ ባለበት የኢትዮጵያ ክፍል ሁሉ እስርና ሞት ከፊቱ አለ። መዳኛችን የጀመርነው መንገድ ብቻ ነው፤ ፅናት ለወገን ሃይሎች!

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahir Dar wikileak BW posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share