Amhara Prosperity Party supporters /የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎች ገፅ/

  • Home
  • Amhara Prosperity Party supporters /የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎች ገፅ/

Amhara Prosperity Party supporters /የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎች ገፅ/ It hosts news and analysis on the current situation in Amhara and Ethiopia.

"ማዕድን የመበልጸጊያ ዘርፍ ነው!" አቶ ኃይሌ አበበ~~~~የማዕድን ሀብቱ አንዱ የመበልጸጊያ ዘርፍ ነው። በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ፕሮጀክት የሆነውና በቀን 130ሺ ኩንታል የማምረት አቅም ያለ...
15/03/2023

"ማዕድን የመበልጸጊያ ዘርፍ ነው!" አቶ ኃይሌ አበበ
~~~~
የማዕድን ሀብቱ አንዱ የመበልጸጊያ ዘርፍ ነው። በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ፕሮጀክት የሆነውና በቀን 130ሺ ኩንታል የማምረት አቅም ያለው የለሚ እንሳሮ ስሚንቶ ፋብሪካ በሚቀጥለው ዓመት ታህሳስ ወር ላይ ምርት ማምረት ይጀምራል፡፡

በክልላችን በአምስት ዘርፎች የሚካተቱ 40 የማዕድን አይነቶች ተገኝተዋል፡፡ የነበረው ሥርዓት አማራ ክልል ያለውን የማዕድን ሀብት በግልጽ እንዲታወቅ አለመፈለጉ፣ ዘርፉን ለማልማት የአደረጃጀት፣ የቴክኖሎጂ እና የክህሎት ችግሮች የነበሩት ነው፡፡

የክልላችን የማዕድን ዘርፉ አዲስ እና እምቅ ሃብት ባለቤት ነው፡፡ በክልሉ ከፍተኛ የድንጋይ ከሰል ማዕድን ክምችት አለ። በተሰራው የስነ ምድር ጥናት መሠረት ክልሉ 14 በመቶ የማዕድን የክምችት ባለቤት መሆኑ ተረጋግጧል።

ያለውን የማዕድን ክምችት ማልማት ከተቻለ ኢትዮጵያ 7መቶ 50 ሚሊዬን ዶላር ወጪ አድርጋ ወደ ሀገር ውስጥ የምታስገባውን የድንጋይ ከሰልን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ይችላል፡፡

ዘርፉ የትኩረት ማዕከል አድርጎ ከሚሰራባቸው መካከል አንደኛው የስራ ዕድል ፈጠራ ነው። እስካሁን ባለው ሁኔታ ለ23 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል። በዚህ ዓመት ብቻ በማዕድን ልማት ዘርፍ 56 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር በእቅድ ይዘን እየሰራን እንገኛለን።
አቶ ኃይሌ አበበ
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ማዕድን ቢሮ ኃላፊ

በአድዋ ላይ ጉራማይሌ የሆነ አተያይ  ይዘን  በዝርዝር ምዕራፎች  መስማማት አይሆንልንም፦ አቶ መልካሙ ተሾመ - የምዕ/ጎጃም ዞን ዋና አስተደዳዳሪ::የአድዋ ድል ግዘፍ ነስቶ  በዓለም አደባባ...
02/03/2023

በአድዋ ላይ ጉራማይሌ የሆነ አተያይ ይዘን በዝርዝር ምዕራፎች መስማማት አይሆንልንም፦ አቶ መልካሙ ተሾመ - የምዕ/ጎጃም ዞን ዋና አስተደዳዳሪ::

የአድዋ ድል ግዘፍ ነስቶ በዓለም አደባባይ ተገዳዳሪ የሌለው የብርሃን ጮራ፣ የእኩልነት ማህተም፣ የነጻነት ቀንዲል ሆኖ ከመገለጡ አስቀድሞ በእነ አጤ ምኒልክ አዕምሮ ውስጥ የተቀመረ ረቂቅ ሀሳብ ነበር። አድዋን የወለደው እነ አጤ ምኒልክ ቅኝ ግዛትን የተጠየፉበት ጥልቀት ነው። አድዋ የታሰበበት ርቅቀት፤ በአድዋ ተራሮች ከተገማሸሩ ጀግንነቶችም የሚበልጥ ነው። ከተጨባጩ የአድዋ ድል የሚበልጡ እልፍ አድዋዎች በእነሱ ልቡና ውስጥ ነበሩ። ከ127 ዓመታት በፊት የካቲት 23 ቀን 1988 ዓ/ም የቅኝ ገዥዉን እብሪት አስተንፍሶ ካሳየን የእነ አጤ ምኒልክ ጀግንነት፣ አርበኝነት እና አገር ወዳድነት ጀርባ እቡይነትን ወደ ጥልቅ ጉድጓድ የሚጥሉ መልከ-ብዙ አድዋዎች በውስጣቸው ነበር።

በአድዋ ጀግኖች አባቶቻችን እና በአሁናዊው የህሊናም ሆነ የነባራዊ ሁኔታችን መካከል ያለው ልዩነት ሆን ተብሎ በተለጠጠ የድርሰት ዓለም እንጅ በእውኑ ያለ ወይም ሊኖር የሚችል አይመስልም።

በአድዋ ተራሮች ከተገለጠው አጤ ምኒልክ በፊትና በኋላ ስላሉት አጤ ምኒልኮች በጥሞና ማሰብ ያስፈልገናል። አጤ ምኒልክ የአድዋ ድልን ካበጀበት ጀግንነቱ ፤ ለምን አድዋ እንደሆነ የተረዳበት ጥበቡ ይበልጣል። የየካቲት 23 ድል ድንገቴ አይደለም፤ በፊቱም በኋላውም እሱን ያማጡ፤ እሱኑ ተንከባክበው የበለጠ አድዋ ሊያዋልዱ የቃተቱ፣ ያሰላሰሉ አጤ ምኒልኮች አሉ። ( እምዬ ምኒልክ በተለይ ከአድዋ ድል በኋላ ኢትዮዽያን ለማስዘመን ያደረጉትን ጥረት ልብ ይሏል)።

በገሃድ ከተገለጠው የዚያ ዘመን ጀግንነት ይልቅ የዚያን ዘመኑ ገዥ መንፈስ፣ የእነ አጤ ምኒልክ ፍልስምና ይገዝፋል።

ወደ የተሟላ መለወጥ ለመሄድ አድዋን እና ከአድዋ ጀርባ የተነጠፉትን ግዙፍ እሳቤዎች በቅጡ መረዳት አስፈላጊ ይሆናል። እኩልነት፣ ነጻነት፣ አርበኝነት፣ ጀግንነት፣ ማንነት፣ የጦር ሳይንስ፣ ፍትሃዊነት፣ ዲፕሎማሲ ፣ አንድነት ወዘተ ሁሉ የታላቁ መጽሃፍ አድዋ ምዕራፎች ናቸው። በአድዋ ላይ ጉራማይሌ የሆነ አተያይ ይዘን በዝርዝር ምዕራፎች መስማማት አይሆንልንም። አድዋ የጋራችን ትውስታ ( Collective Memory)፣ የሁላችንም እደርስበት ( Aspiration) ነው።

እንኳን ለ127 ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ።

 #የአማራ ክልል  #ማዕድን ልማት ቢሮ እንደ ሀገር ከሁሉም ክልሎች ቀዳሚ በመሆን የዕውቅና ሰርተፍኬት ማግኘት ችሏል!!የአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ በመዋቅሩና በዘርፉ የተሠማሩ አ...
22/11/2022

#የአማራ ክልል #ማዕድን ልማት ቢሮ እንደ ሀገር ከሁሉም ክልሎች ቀዳሚ በመሆን የዕውቅና ሰርተፍኬት ማግኘት ችሏል!!

የአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ በመዋቅሩና በዘርፉ የተሠማሩ አካላት በትብብርና በቅንጅት እያደረጉት ያለው የማዕድን የንቅናቄ ጉዞ አስደናቂ መሆኑ ተመሠከረለት። በዛሬው ዕለት በ12/03/15 ዓ/ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል በተካሄደው የአድናቆትና የዕውቅና ሥነ-ሥርዓት ላይ ክልላችን በማዕድን ዘርፍ እያሳየ ላለው ከፍተኛ ጥረት እንደ ሀገር ከሁሉም ክልሎች ቀዳሚውን ተርታ በመያዝ የመጀመርያውን የምስጋና እና የዕውቅና ሰርተፍኬት ከክቡር ሚኒስቴሩ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ሊቀበል ችሏል።
ይኽ ዓይነቱ ውጤት የተገኘው የሁላችንም ጥረት ነው ያሉት የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ኃይሌ አበበ በቀጣይ ጊዜያትም የበለጠ ርብርብ በማድረግ በተግባር ማዕድን ዓይነተኛ ከድህነት መውጫ መንገድ እንዲሁም የክልላችን አማራጭ የኢኮኖሚ መንገድ በእውነትም የክልሉ የንጋት ተሥፋ መሆኑን ለማረጋገጥ ተግተን በቅንነትና በቁርጠኝነት ማገልገል ይገባናል ብለዋል።

በድጋሚ ለመላ የማዕድን ቤተሠቦች እንኳን ደሥ አላችሁ!!!

በታሪክ የመጀመሪያው የማዕድን ንቅናቄ በአማራ ...የአማራ ክልል በኢትዮጵያ ደረጃ ቀዳሚ የሆነን ውድና እጅግ በመጠኑም ብዙ ማዕድን በውስጡ የያዘ ቢሆንም ይህ ውድ ሀብታችንና ዘርፉ የሚገባውን...
25/10/2022

በታሪክ የመጀመሪያው የማዕድን ንቅናቄ በአማራ ...

የአማራ ክልል በኢትዮጵያ ደረጃ ቀዳሚ የሆነን ውድና እጅግ በመጠኑም ብዙ ማዕድን በውስጡ የያዘ ቢሆንም ይህ ውድ ሀብታችንና ዘርፉ የሚገባውን ያክል ትኩረት ባለማግኘቱ ብሎም እስትራቴጂካሊ አስቦ አማራን ብሎም ኢትዮጵያን ሊያሻግር የሚችለውን ሀብት እናውቀው ዘንድ ያደረገን ሊደርሽፕ ባለመኖሩ ፀጋችንን ሳናውቀው ኖረን ነበር::

ዛሬ ግን በታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን አይን ገላጭ የምስራችና የተግባር እርምጃ መነሻ መሰረት በመጣል የክልሉ ማዕድን ቢሮ ታሪክ ጀምሮልናል።

እናመሰግናለን !!

ዶ/ር ይልቃል ከፋለ
አቶ ግርማ የሽጥላ
አቶ ሀይሌ አበበ
እና ወንድማችን ክቡር ምኒስተር
ኢንጅነር ታከለ ኡማ

‹‹ስንዴችንን እንጂ ሉዓላዊነታችንን ለጨረታ አናቀርብም››ኢትዮጵያ ሀገራችን ምድረ-ቀደምት ነች ሲባል ከብርቅየነት መገለጫዎቿ እኩል፣ የሥነ-መንግሥት ታሪኳ አንዱ መገለጫዋ ሆኖ ይጠቀሳል፡፡ አ...
23/10/2022

‹‹ስንዴችንን እንጂ ሉዓላዊነታችንን ለጨረታ አናቀርብም››

ኢትዮጵያ ሀገራችን ምድረ-ቀደምት ነች ሲባል ከብርቅየነት መገለጫዎቿ እኩል፣ የሥነ-መንግሥት ታሪኳ አንዱ መገለጫዋ ሆኖ ይጠቀሳል፡፡ አንዳንዶች እንደሀገር ሳይታወቁ፣ ኢትዮጵያውያን በሀገር በቀል ዕውቀት የራሳቸውን መንግሥት አዋቅረው በባህላዊ ሥርዓት ነፃ ሀገርና ነፃ ሕዝቦች ሆነው ኑረዋል፡፡ በራሳችን መገበያያ ገንዘብ፤ በራሳችን የውስጥ አስተዳደር፤ በራሳችን ፍልስፍና እንደሀገር ቁመን ለሌሎች አስተምረናል፡፡

ከፍትሐ-ነገሥት እስከ ገዳ ሥርዓት፤ ከአክሱም እስከ ኡጋዴን ጫፍ፤ ከአባይ እስከ ግቤ፤ ከአዋሽ እስከ ኦሞ፤ ከባሮ እስከ ገናሌ በብዝሃ ባህል ባጌጠ አብሮነት በጎሳ መሪዎችና በሀገር ሽማግሌዎች ለሺህ ዘመናት አብሮነትን አዳብረናል፡፡ የኢትዮጵያ የዳበረ የሥነ-መንግሥት ታሪክ ከመሪዎቿ ብልህነት፣ ከሕዝቦቿ ጥንካሬ የሚመነጭ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራችን የውስጥ ችግሮቿን ለመፍታትም ሆነ ቀጠናዊ አብሮነትን በመፍጠር ረገድ ለሌሎች የሚተርፍ ለዘመናት የዳበረ የውጥ አቅም አላት፡፡

የሺህ ዘመናት የነጻነት ታሪክ ያላት ኢትዮጵያ ሀገራችን፣ ሉአላዊነቷን በልጆቿ ኩራት፣ ጀግንነትና መስዋዕትነት አስከብራ ኑራለች፡፡ ዛሬም ይህ ኢትዮጵያዊ ኩራት፣ ጀግንነትና የመስዋዕትነት ወኔ በአዲሱ ትውልድ ላይ ቀጥሏል፡፡

ባለፉት ሁለት ቀናት በመላ ሀገራችን የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ‹‹ለኢትዮጵያ እቆማለ፤ ድምጼን አሰማለሁ! የውጭ ጣልቃ ገብነትን እቃወማለሁ!!›› በሚል መሪ ቃል፣ ኢትዮጵያ ያጋጠማትን የውስጥ ችግር በራሷ የመፍታት አቅም እንዳላት፣ ሕዝቧ የትኛውንም የውጭ ጣልቃ ገብነት እንደማይቀበል በኢትዮጵያዊ ጨዋነት፣ በሚያምር ሕብረ-ብሔራዊነት አሳውቋል፡፡

ከሰሞኑ በተካሄደው ሀገር አቀፍ ሰልፍ የምንረዳው እውነታ ኢትዮጵያዊያን በአንድ መቆም እስከቻልን ድረስ የትኛውንም ሀገራዊ ችግር እንደምንሻገር፣ በሕብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነት ዘላቂ ሠላማችንና ብልጽግናችን ማረጋገጥ እንደምንችል ነው፡፡

ዘላለማዊ ክብርና ሞገስ የማይሞት ታሪክ በመስራት ላይ ላለው የኢትዮጵያ ጥምር ጦር ይሁንና አሸባሪው ህወሓት ታሪክ የሚሆንበት ምዕራፍ ላይ ደርሰናል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔር ብሄረሰቦች ውህድ ማንነት ውጤት የሆነው የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን የሀገረ-መንግሥቱ የመጨረሻ ምሽግ መሆኑን በተግባር በማስመስከር ላይ ይገኛል፡፡

የአሸባሪው ቡድን የቁም እስረኛ ሆኖ የኖረው የትግራይ ሕዝብ በኢትዮጵያ ብሔር ብሄረሰቦች የጋራ መስዋዕትነት ነፃ በሙውጣት ላይ ይገኛል፡፡ የትግራይ ሕዝብ በሽብር ቡድኑ ውስጥ ያሉ ቀሪ የታሪክ ተሸናፊ ባንዳዎችን ከወንድሞቹ መላ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ያለምህረት በመታገል ወደመቃብር ሊያወርዳቸው ይገባል፡፡

በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው የባንዳዎች ጀንበር ሲጠልቅ፤ የኢትዮጵያ ብልጽግና እየቀረበ ስለመምጣቱ ነው፡፡

የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት፣ ሉዓላዊነትና የፖለቲካ ነፃነትን የመጠበቅ ሕገ-መንግሥታዊ፣ ሞራላዊና ታሪካዊ ኃፊነት ያለበት በሕዝብ የተመረጠው የኢትዮጵያ መንግሥት ነው፡፡

ስለሆነም የኢትዮጵያን ሉአላዊነት የሚጋፉ የትኞቹንም ውሳኔዎችንም ሆነ በውስጥ ጉዳያችን ገብተን እንወስንባችሁ ለሚሉን የውጭ ኃይሎች መርህ አልባ የጣልቃ ገብነት ፍላጎታቸውን ልንቀበል አንችልም፡፡ በእናት ሀገራችን ኢትዮጵያ የሉአላዊነት ጉዳይ አንደራደርም!!

የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲና ትግበራ ትብብርን፣ የጋራ ጥቅምን እና ሉዓላዊነትን በማስከበር እና በማክበር ላይ የተመሠረተ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁንና ለሦስተኛ ጊዜ ኢትዮጵያን ለመውጋት በተነሳው በአሸባሪው ህወሓት ላይ ሕግ የማስከበር እርምጃ ከተጀመረ ወዲህ የሀገራችን ኢትዮጵያን ሉአላዊነት በሚጋፋ መልኩ የውጭ ኃይሎች ካለፈው የቀጠለ ጫናና ተጽዕኖ ለማሳደር እያደረጉ ያሉት በቀቢጸ ተስፋ ላይ የተንጠለጠለ ሙከራ ሊሳካ እንደማይችል፣ ይልቁንስ መንግሥት በትግራይ ክልል የሚገኙ ዜጎቹን ለመታደግ እና ሕገመንግሥታዊ ግዴታውን ለመወጣት ከሚያደርገው ጥረት ጎን በመሰለፍ በመርህ ላይ የተመሰረተ አጋርነታቸውን ሊያሳዩ ይገባል፡፡

በትግራይ ያለው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ፈረንጆቹ ‹war on terror› እንደሚሉት በሽብር ላይ የተከፈተ ጦርነት ነው!! ይህ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ወሳኝ ተልዕኮ በመሆኑ ቀጠናዊ ሰላምና መረጋጋትን የሚሹ ሁሉ ከኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ጎን ሊሰለፉ ይገባል፡፡ ከዚህ ውጭ በውስጥ ጉዳያችን ጣልቃ ልግባ ለሚል የትኛውም የውጭ ኃይል ምላሻችን፡- ስንዴችንን እንጂ ሉዓላዊነታችንን ለጨረታ አይቀርብም!!

በኢትዮጵያ ብሔር ብሄረሰቦች የጋራ መስዋዕትነት የትግራይ ሕዝብ ከአሸባሪው ሕወሓት እገታ ነፃ ይወጣል!!

ኢትዮጵያዊነት አሸናፊ ማንነት!!!

'ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ'' እንደተባለው ሁሉ እንደ ህዝብ በአንድነት መደራጀት በመቻላችን የተደቀኑብንን ፈተናዎች በድል እየተወጣን እንገኛለን። አሸባሪው ህውሃት በጀመረው ጦርነት ከመላ...
20/10/2022

'ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ'' እንደተባለው ሁሉ እንደ ህዝብ በአንድነት መደራጀት በመቻላችን የተደቀኑብንን ፈተናዎች በድል እየተወጣን እንገኛለን።

አሸባሪው ህውሃት በጀመረው ጦርነት ከመላው ህዝባችን ጋር መግባባታችን፣ የማያሻማ አቋም መያዝ በመቻላችን እና አመራሮቻችንም በግልጽ የስነ ምግባር መመሪያ እንዲመሩ ማድረግ በመቻላችን ተገደን የገባንበትን የመከላከል ጦርነት አሸባሪው ትህነግ ያሰበውን እንዳያሳካ ማድረግ ችለናል።

'' ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ '' እንደተባለው ሁሉ መላ ህዝባችን በአንድነት በመደራጀት የውስጥ እና የውጭ የዘመናት ጠላቶቻችንን በሁሉም አቅጣጫ መመከት እየቻልን ነው።

ካልተደራጀ ሚሊዮን የተደራጀ ሺ ያሸንፋል፤ እንደ አገር ስክነት በተሞላበት መልኩ መደራጀት መቻላችን የጠላትን ወረራ መመከትና መከላከል እንድንችል እያደረገን ነው። ለዚህ ስኬት ህዝቡ በሀብቱ በእውቀቱ በጉልበቱ የቻለውን ሁሉ እያበረከተ በመሆኑ ዘላለማዊ ክብር ይገባዋል።

የነበረውን ችግር በነበረው አሰራር ለመፍታት አልሰራንም። መቀየር የምንፈልጋቸውን ሁኔታዎች በአዲስ መንገድ በአዲስ አሰራር ለመፍታት ሰርተናል።

ታታሪው ህዝባችንም ለጥምር ጦሩ የሚያደርገው ድጋፍ በአንደኛው ዙር እና በሁለተኛው ዙር ጦርነት እንደተደረገው ሁሉ አሁን ተገደን በገባንበት በሶስተኛው ዙር ጦርነትም እንደ ክልል እንደ ዞን እንደ ወረዳ እየተደረገ ያለው ድጋፍ ህዝባችንን እንድናመሰግን ብቻ ሳይሆን ከዚህ በበለጠ ሰርተን እንድንክሰው የሚያስገድድ ተግባር ነው። ይህም በመሆኑ በሁሉም ደረጃ ለሚገኙ አስፈፃሚ አካላት እና ለመላው ህዝብ ምስጋና ይገባቸዋል።

ወረራው በጦርነቱ ምክንያት አርሶ አደራችን የግብርና ልማት ስራውን እንዳይከውን በማስገደድ በድህነት አንገታችን ደፍተን እንድንኖርና ሉዓላዊነታችንን እንድናጣ የሚያደርገው የአሸባሪው ትህነግና አጋሮቹ የኢኮኖሚ ሴራ በስራ ወዳድ አርሶ አደሮች፣ በግብርናው ሴክተር ባለሙያዎችና በመላ አመራሩ ርብርብ ምርትና ምርታማነትን የሚጨምርና ስራ በመከወን የብልጽግና ራዕይን የሚያሳኩ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን መስራት ችለናል፡፡

ድል የሚገኘው በመስዋዕትነት ነው ለድል የተከፈለው መስዋዕትነት ደግሞ በታሪክ መዛግብታችን አስፍረነዋል ለዚህ ድል መሰዋእትነት የከፈለው ህዝባችንን በሁሉ ዓቀፍ አገልግሎት ለመካስ በቂ የስራ ስምሪት እና መመሪያ ወስደን በአንድነት ልናገለግል ይገባል። መላው ህዝባችንም ተገደን የገባንበትን የመከላከል ጦርነት በድል እንድናጠናቅቅ ህዝባዊ ደጀንነቱን አጠናክሮ ይቀጥል ዘንድ ጥሪ አቀርባለሁ።

አቶ ግርማ የሽጥላ
በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኋላፊ

"ለኢትዮጵያ እቆማለሁ፤ ድምፄን አሰማለሁ"በሚል መሪ ቃል በመጪው ቅዳሜና እሑድ በመላ ሀገሪቱ ምድር አንቀጥቅጥ  ሰልፍ ሊደረግ ነው። የሰልፉ አስተባባሪዎች ለድሬቲዩብ እንደተናገሩት የሰልፉ ዋ...
19/10/2022

"ለኢትዮጵያ እቆማለሁ፤ ድምፄን አሰማለሁ"በሚል መሪ ቃል በመጪው ቅዳሜና እሑድ በመላ ሀገሪቱ ምድር አንቀጥቅጥ ሰልፍ ሊደረግ ነው።

የሰልፉ አስተባባሪዎች ለድሬቲዩብ እንደተናገሩት የሰልፉ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ ላይ የሚደረጉ የውጭ ጫናዎችን መቃወም ነው።

ኢትዮጵያውያን ሰልፉን እንዲቀላቀሉና በሰላማዊ መንገድ የውጭ ጣልቃ ገብነትን እንዲቃወሙ አስተባባሪዎቹ ጥሪ አቅርበዋል።
ፎቶ:- ፋይል

በትግራይ ህፃናት ሳይቀሩ ለጦር ያሰለፈው ህወሓት የአለም አቀፍ ሕጎችን በመተላለፍ  በጦር ወንጀል ሊጠየቅ ይገባዋል።
19/10/2022

በትግራይ ህፃናት ሳይቀሩ ለጦር ያሰለፈው ህወሓት የአለም አቀፍ ሕጎችን በመተላለፍ በጦር ወንጀል ሊጠየቅ ይገባዋል።

ሰራዊታችን ሽሬን ሲቆጣጠር የተገኘው የህወሓት ገመና‼️😭በሀገር መከላከያ ሰራዊታችን የሚመራው ጥምር ጦር ሽሬን እና አካባቢዋን ከተቆጠጠረ በኋለ የሚታዩ እና የሚሰሙት ነገሮች እጅግ ዘግናኝ ና...
18/10/2022

ሰራዊታችን ሽሬን ሲቆጣጠር የተገኘው የህወሓት ገመና‼️😭

በሀገር መከላከያ ሰራዊታችን የሚመራው ጥምር ጦር ሽሬን እና አካባቢዋን ከተቆጠጠረ በኋለ የሚታዩ እና የሚሰሙት ነገሮች እጅግ ዘግናኝ ናቸው‼️ በሽሬ ከተማ ወጣቶች ዘንድ በተወደደው #ሀጎስ ገ/ህይወት የሚመሩ ለአካባቢ ተቆርቋሪ ነን ባዮች እስከመቼ ነው ህወሓትን እያልን የምናልቀው በሚልና ወጣቱ ወደ ጦር ግንባር እንዳይሄድና እናት አባቶቹን እየተንቀባከበ ቀዬው ብቻ እንዲጠብቅ ሲያነሳሱ እና ህወሓትን ልክ አይደለችም እያለው ማህበረሰቡን እያነሳሱ መሆኑን ህወሓት ስትረዳ 83 ወጣቶችን ከሽረ ከተማ ወጣ ብሎ ባለ አካባቢ በጅምላ ገድሎ በጅምላ የቀበረበት ስፍራ ተገኝቷል‼️😭😭😭

ወጣት #ሀጎስ ገ/ህይወትን ግን ወዳልታወቀ ቦታ ይዘውት ሄደዋል እንጂ እነሱ የተገደለ ዕለት አብሯቸው አልሄደም ብለው የዐይን እማኞች መስክረዋል‼️😭

ምን አይነት አረመኔነት ነው❓ 83 ወጣቶችን በጅምላ መረሸን😭😭

ለመላው የእስልም እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1497ኛው የመውሊድ  በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩ በዚህ ታላቅ በዓል ዋዜማ በሱማሌ ክልል ተገኝተን ለተደረገልን ደማቅ አቀባበ...
07/10/2022

ለመላው የእስልም እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1497ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩ በዚህ ታላቅ በዓል ዋዜማ በሱማሌ ክልል ተገኝተን ለተደረገልን ደማቅ አቀባበል ልባዊ ምስጋናየን አቀርባለሁ።

የነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) መውሊድ በዓል የአሏህ እዝነትና ቸርነት ያደረበት የሰላም፣የፍቅርና የአብሮነት ይሆንልን ዘንድ እመኛለሁ።

መልካም በዓል!!
ዒድ ሙባረክ !!

ግርማ የሽጥላ
በአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኋላፊ

‹‹ፅኑና የማይደፈር የመከላከያ ተቋም ግንባታችን የኢትዮጵያ ህልውና ዋስትና ነው ››                      ክቡር አቶ ግርማ የሺጥላ                        •~•~• ...
04/10/2022

‹‹ፅኑና የማይደፈር የመከላከያ ተቋም ግንባታችን የኢትዮጵያ ህልውና ዋስትና ነው ››
ክቡር አቶ ግርማ የሺጥላ
•~•~•
በብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ አባልና የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ግርማ የሺጥላ ባስተላለፉት መልእክት ‹‹ በኢትዮጵያ ደመኛ ጠላቶች ላኪነት ሀገረ-መንግሥቱን የማፍረስ የጥፋት ተልዕኮ ይዞ የተሰለፈው ጥንተ-ጠላት ትሕነግ ከነአስተሳሰቡ ላይነሳ የሚቀበረው ፅኑና የማይደፈር የመከላከያ ተቋም ግንባታችንን አጠናክረን ስንቀጥል ነው›› ብለዋል፡፡

ጠላት ትናትን በገዥነት ዘመኑ አማራን ከሀገር ግንባታ ተሳትፎው ለመነጠል ከተጠቀመባቸው መንገዶች አንድ ከሀገር መከላከያ ተሳትፎ ማራቅ ፣ የነበሩትን ነባር አባላትና አመራሮች ከሚና ውጭ ማድረግ፣ በማንነታቸው ማሰርና ማሳደድ እንደነበርም አቶ ግርማ አስታዉሰዋል ። ዛሬም ለይቶለት የእናት ጡት ነካሽነቱን ለዓለም ካሳየ በኋላም በአንድ ጎን ሀገር እየወጋ በሌላ ጎን ደግሞ አማራ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ተሳትፎ እንዲርቅ በቅጥረኞቹ በኩል የሐሰት ፕሮፖጋንዳ ቢነዛም፣ ጥንተ-ጠላቱን ጠንቅቆ የሚያውቀው ሕዝባችን በአስደማሚ ሁኔታ ለሠራዊቱ ያለውን ክብር በተሳትፎ በማረጋገጥ ላይ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል ።

አቶ ግርማ በተጨማሪም ‹‹ የህልውና ስጋት ያለበት ህዝብ ጠንካራ ሀገራዊ የየመከላከያ ተቋም በመገንባት ካልሆነ በስተቀር የዳር ተመልካች በመሆን የሚሻገረው ፈተና እንደሌለ ሕዝባችን ገብቶታል፤ በዚህም አባቶች በምርቃት፣ እናቶች በእልልታ፣ ልጆቻቸውን ሸኝተዋል ብለዋል ።
ወጣቶች በአርበኝነት መንፈስ ታላቁን የሀገረ-መንግሥቱን ዘብ በመቀላቀል ላይ ናቸው ፤ ኢትዮጵያን በማሻገር በትግላችሁ የማይሞት ታሪክ ለመስራት የተሰለፉ ወጣቶች ፅኑና የማይደፈር የመከላከያ ተቋም በመገንባት የኢትዮጵያን ህልውና እንደሚያጸኑ በመግለጽ ወጣቶቻችን በኢትዮጵያ ደመኛ ጠላቶች መቃብር ላይ የማይሞት ታሪክ ይሰራሉ ሲሉ ክቡር አቶ ግርማ ተናግረዋል ፡፡
‹‹ሞትና ውርደት ለኢትዮጵያ ደመኞች ፤ ዘላለማዊ ክብርና ሞገስ ለሀገረ-መንግሥቱ ዘብ!! ››
•~•~•
"ለሀገር ክብር በትግል እናብር "
"ቃላችንን ፈፅመን ከፍታው ላይ እንገናኝ"
~~~

በቅንነት እና በሀቀኝነት ሀገርንና ህዝብን እስካገለገልክ ድረስ ከየትኛውም ዓይነት አቅጣጫ የሚመጣን ጦር ማርከህ፣ዘላቂ የብረት አጥር ትገነባበታለህ!አቶ ግርማ የሺጥላ ምንጊዜም ለሀቅና ለእውነ...
29/09/2022

በቅንነት እና በሀቀኝነት ሀገርንና ህዝብን እስካገለገልክ ድረስ ከየትኛውም ዓይነት አቅጣጫ የሚመጣን ጦር ማርከህ፣ዘላቂ የብረት አጥር ትገነባበታለህ!

አቶ ግርማ የሺጥላ ምንጊዜም ለሀቅና ለእውነት በፅናት የቆመ፣ከራሱ በፊት የህዝብን ጥቅምና ክብር የሚያስቀድም፣እርስ በርስ ከመገዳደልና ከመዋረድ እንመካከርንና እንነጋገርን የሚያስቀድም፣በስሜትና በግለፍተኝነት ሳይሆን በመቻቻልና በመማማር የሚያምን የዘመኑ ጥበበኛ መሪ ነው!

ድል ለሀቀኞቻችን!🙏🙏🙏

"ግባ በለው" ከእነዚህ ምርኮኞች መካከል በስተቀኝ ያለው ኮሎኔል ጉዑሽ የሚባል ሲሆን የአሸባሪው ቡድን ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ነው። እናም እነዚህ ታጣቂዎች በዋግ ግንባር ሀሙሲት በነበረው ...
08/09/2022

"ግባ በለው"

ከእነዚህ ምርኮኞች መካከል በስተቀኝ ያለው ኮሎኔል ጉዑሽ የሚባል ሲሆን የአሸባሪው ቡድን ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ነው።

እናም እነዚህ ታጣቂዎች በዋግ ግንባር ሀሙሲት በነበረው ውጊያ በጥምር ጦሩ የተማረኩ ናቸው።

በመጨረሻ ኑዛዜው ጡረታ የሚያስወጣኝ አጣሁ እያለ የሚያማርረው ጌታቸው እንዲህ የሚል አስቂኝ ነገር ተናገረ!ሰሞኑን የተገኘውን ምስጢራዊ ሰነድ ሲያስተባብል ”እኛ ጋር መብራት ስሌለለ በኮምፒተር...
06/09/2022

በመጨረሻ ኑዛዜው ጡረታ የሚያስወጣኝ አጣሁ እያለ የሚያማርረው ጌታቸው እንዲህ የሚል አስቂኝ ነገር ተናገረ!
ሰሞኑን የተገኘውን ምስጢራዊ ሰነድ ሲያስተባብል ”እኛ ጋር መብራት ስሌለለ በኮምፒተር አንጽፍም፣ ጽሁፋችን ሁሉ የእጅ ጽሁፍ ነው” አለ፡፡ እፊቱ ላይ የተገተረው ካሜራ በኤሌክትሪክ እንደሚሠራ እንኳ ረስቶት፡፡

አግማስ ጫኔ

A Man of his wordአቶ ግርማ የሽጥላ ደፋርና የመርህ ሰው ናቸው፣ በውሳኔያቸው የሚፀኑ ትንታግ፣  ላመኑበት ሁሉ ግንባራቸውን የሚሰጡ ደፋር መሪ፣ ማዕበል የማያናውጣቸው የብረት አጥር፣...
27/08/2022

A Man of his word

አቶ ግርማ የሽጥላ ደፋርና የመርህ ሰው ናቸው፣ በውሳኔያቸው የሚፀኑ ትንታግ፣ ላመኑበት ሁሉ ግንባራቸውን የሚሰጡ ደፋር መሪ፣ ማዕበል የማያናውጣቸው የብረት አጥር፣ የአባቶቻችንን ጥበበኛነት የወረሱ ዕውነተኛ የአባቶቻቸው ልጅ፣ የሚናገሩትን የሚተገብሩና በቃላቸው የሚገኙ መሪ በመሆናቸው አንዳንዶቹ A Man of his word ይሏቸዋል።

አቶ ግርማ የሽጥላ ውሳኔን ከጥሩ ድፍረት ጋር አጣምረው ሲወስኑ መባልን የማይፈሩ ተወዳጅ መሪ ናቸው። አቶ ግርማ እኛ ጥረት ካደረግን የማንለውጠው ነገር አይኖርምና ከልባችን ሰርተን ወደ ከፍታው እንውጣ በሚል መርህ ህዝብን ለማበልፀግ የሚሰሩ መሪም ናቸው።

አቶ ግርማ ነገን ከፍ የተሻለ በማድረግና የህዝብን ከፍታ ለሜብሰር የሚተጉ ስክነትን የተላበሱና በቁርጠኝነት እየሰሩ ከሚገኙ የአማራ መሪዎች አንዱ መሆናቸው ለጠላት ተላላኪዎች የተመቸ አልሆነም።

ከሰሞኑ ስማቸውን ለማጠልሸት እየተሯሯጡ የሚገኙ ጭር ሲል አልወድምን ተነቅቶባችኋልና እረፉ ለማለት ነው።

ቄስ የሚገድል፣ የቄስ ሚስት የሚደፍር ክፉ የወለድሽ የትግራይ እናት ሆይ!ገዳም የሚዘርፍ፣ መናኝ የሚደፍር የወለድሽ የትግራይ እናት ሆይ!ቤተ ክርስትያንና መስጊድ የሚያቃጥል እርጉም የወለድሽ ...
25/08/2022

ቄስ የሚገድል፣ የቄስ ሚስት የሚደፍር ክፉ የወለድሽ የትግራይ እናት ሆይ!

ገዳም የሚዘርፍ፣ መናኝ የሚደፍር የወለድሽ የትግራይ እናት ሆይ!

ቤተ ክርስትያንና መስጊድ የሚያቃጥል እርጉም የወለድሽ የትግራይ እናት ሆይ!

በክፉ ልጅሽ ምክንያት መከራሽ ገና ነው! ገና!

የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው ሲሉ ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) አስታወቁ። => "የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው"=>...
12/06/2022

የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው ሲሉ ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) አስታወቁ።

=> "የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው"

=> "የሕግ ማስከበር ዘመቻው የአማራን ህዝብ አንድነት ለማጠናከር ያለመ ነው"

የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ(ዶ.ር) ከጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ጋር እየመከሩ ነው።

የጎንደር ከተማን ሰላምና እድገት ለማረጋገጥ መሰራት ስላለባቸው ጉዳዮች የጋራ አቋም ለመያዝ ያለመ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ያለው።

ጎንደር የስልጣኔያችን ምልክት፤ የሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ሐብቶች መናገሻ የኾነች የዓለም መዳረሻ ከተማ መኾኗን ያነሱት ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ገጽታዋን ለማጠልሸት በሐይማኖትና በብሔር ሽፋን ግጭት እንዲቀሰቀስ የሚሰሩ ሐይሎች መበራከታቸውን ገልጸዋል።

በቅርቡ በጎንደር ከተማ የተከሰተው ግጭትም የሕዝቡን ማኅበራዊ እሴት የማይመጥን አሳዛኝ ድርጊት ነው፤ ማንም ይሁን ማን ጥፋተኞች መወገዝ አለባቸው፤ አጥፊዎች ለህግ ቀርበው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው በተደረገው ጥረት ሕዝቡ ያሳየው ትብብርም የሚመሰገን ነው ብለዋል።

በአካባቢው በአማራና በቅማንት ሕዝብ መካከል ግጭት ተከስቶ ሕዝቡ እንዲደሳቆል የሚያደርጉትንና ለዘመናት በአብሮነት የኖረውን የክርስትናና እስልምና ሃይማኖት ተከታዮችን ለመለያዬት በተለየዩ ጊዜያት ግጭት ቀስቅሰው ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት የሚያደርሱ አካላትን በጋራ ልንታገላቸው ይገባል ነው ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ።

የሰው ታላቅነት የሚመዘነው ከውድቀት መነሳት በመቻል በመኾኑ ከዚህ በፊት የተፈጠሩትን ግጭቶች ምክንያታቸውን በመለየት ለመፍትሔዎቻቸውና ለቀጣይ አብሮነታችን የጋራ አቅጣጫ ማስቀመጥ ይኖርብናል ነው ያሉት።

"አንዳችን ለአንዳችን አስፈላጊ መሆናችንን በመገንዘብ ሐይማኖትን ሽፋን በማድረግ ግጭት የሚቀሰቅሱ አካላትን አጋልጠን ለህግ ማቅረብ አለብን፤ ከዚህ በኋላ የጎንደርን ሰላም ለማናጋት የሚሰሩትን አምርረን ልንታገላቸው ይገባል " በማለት ነው ያሳሰቡት ዶክተር ይልቃል።

በቅርቡ የሕዝብን ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ የተጀመረው የህግ ማስከበር ስራ የነበሩ ስጋቶችን በመቀነስ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ርእሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል።

የህግ ማስከበር ዘመቻው የአማራ ሕዝብን አንድነት ለማጠናከር ያለመ ነው ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው ብለዋል።

አንድ ስንኾንና ስንጠናከር ሌሎች ያደምጡናል፤ ከተፈረካከስን ግን ተደማጭነታችን ይቀንሳል ሲሉም ለነዋሪዎች የአንድነት ጥሪ አቅርበዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል።

አምራች ኢንዱስትሪዎች ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት መፋጠን የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ለማጠናከር መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል  አምራች ኢንዱስትሪዎች ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት መፋጠን የሚያደ...
11/06/2022

አምራች ኢንዱስትሪዎች ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት መፋጠን የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ለማጠናከር መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል

አምራች ኢንዱስትሪዎች ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት መፋጠን የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ለማጠናከር መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የኢፌድሪ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ተናገሩ፡፡

በጎንደር ከተማ የሚገኘው የዳሽን ቢራ ፋብሪካ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ውጪ ያካሄደው የማስፋፊያ ፕሮጀክት ተጠናቆ ዛሬ ለምረቃ በቅቷል፡፡

በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ የተገኙት ሚኒስትሩ እንደተናገሩት አምራች ኢንዱስትሪዎች ለሀገሪቱ ልማት መፋጠንና ለዜጎች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር በኩል ኢኮኖሚያዊ ድርሻቸውና ተሳትፎአቸው የላቀ ነው፡፡

የዳሽን ቢራ ፋብሪካ በአማራ ክልል መቋቋሙ ለዜጎች ሰፊ የስራ እድል ከመፍጠር ባሻገር በማህበራዊ ልማትና በስፖርቱ ዘርፍ እያደረገ ያለው ድጋፍና ተሳትፎ ትልቅ ግምት የሚሰጠው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች መስፋፋትና መጠናከር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሩ የዳሽን ቢራ ፋብሪካ የከተማና የገጠሩን ኢኮኖሚያዊ ትስስር በማጠናከር ረገድ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ትልቅ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በአማራ ክልል የኢንቨስትመንት ፈር ቀዳጅ ኮሆኑ አምራች ኢንዱስትሪዎች ዳሽን ቢራ ግንባር ቀደም መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፍአለ ናቸው፡፡

ዳሽን ቢራ የክልሉን ልማት በመደገፍ በኩል ባለፉት አመታት ፋና ወጊ የልማት ተግባራት ማከናወኑን የጠቆሙት ርእሰ መስተዳድሩ የክልሉ መንግስት ለፋብሪካው መጠናከር የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግራዋል፡፡

ፋብሪካው የክልሉን አርሶአደሮች የቢራ ገብስ ምርት በመጠቀም የአርሶአደሩ ህይወት እንዲቀየር በማድረግ በኩል ላለፉት አመታት ሰፊ ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ ማድረጉንም ገልጸዋል፡፡

የፋብሪካው አመታዊ የቢራ ገብስ ግብአት ፍላጎት ከፍተኛ በመሆኑ ፋብሪካው የሚፈልገውን የግብርና ግብአት በበቂ መጠን አርሶአደሩ አምርቶ እንዲያቀርብ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል፡፡

ከውጪ የሚገባውን የቢራ ገብስ በሀገር ውስጥ እንደሚረት በማድረግ በኩል የተሻሻሉ የቢራ ገብስ ዝርያዎችን በምርምር በማፍለቅ ለአርሶአደሩ በማቅረብ በኩል የግብርና ምርምር ተቋማት በትኩረት እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡

በ591 ሚሊዮን ብር ወጪ ፋብሪካዊ ያካሄደው የማስፋፊያ ፕሮጀክት አመታዊ የቢራ ማምረት አቅሙን ከ800ሺ ሄክቶ ሊትር ወደ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክቶ ሊትር የሚያሳድገው ነው፡፡

በፋብሪካው የማስፋፊያ ፕሮጀክት ምረቃ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አገኘው ተሻገርን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የፋብሪካው የፕሮጀክት ማስፋፊያ እንዲሳካ ድጋፍ ላደረጉ አካላት የእውቅና ምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን የፋብሪካው የምርት እንቅስቃሴም በእንግዶች ተጎብኝቷል፡፡

"...ተመትቼ ነበር፣ በሂሊኮፕተር ነው ወደሕክምና የወሰዱኝ። አሉ የተባለ ዶክተሮች ናቸው ተዘጋጅተው የጠበቁኝ። ከላይ ጀምሮ ውጪ ሃገር (የፈለገው ሃገር) ሄዶ ይታከም ተብሎ ሄጄ ታክሜአለሁ።...
22/05/2022

"...ተመትቼ ነበር፣ በሂሊኮፕተር ነው ወደሕክምና የወሰዱኝ። አሉ የተባለ ዶክተሮች ናቸው ተዘጋጅተው የጠበቁኝ። ከላይ ጀምሮ ውጪ ሃገር (የፈለገው ሃገር) ሄዶ ይታከም ተብሎ ሄጄ ታክሜአለሁ። ምቴ (የተመታሁት) ከባድ ነበር። ፊቴ ላይ ነበር ጉዳቱ፤ አሁን ድኜ ወደ ሥራዬ ተመልሻለሁ።"
ብ/ጄ/ል ሻምበል በየነ

ዛሬ ግንቦት 14 ቀን 2014 ዓ.ም በመከላከያ ቴሌቪዥን ከሰጡት ቃለምልልስ የተወሰደ።

የአማራ ክልል መንግሥት ሕግ የማስከበር ሙሉ አቅም አለው” ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር)የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) በወቅታዊ ጉዳዮች መግለጫ ሰጥተዋል። ...
18/05/2022

የአማራ ክልል መንግሥት ሕግ የማስከበር ሙሉ አቅም አለው” ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር)

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) በወቅታዊ ጉዳዮች መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የአማራና የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት ወያኔና የወያኔ ፈረሶች ናቸው ብለዋል። በግንባር አካባቢ የወያኔ ፈረስ ኾነው የሚያገለግሉትን ኃይል አዘጋጅተን እየተፋለምን ነው ሲሉ ገልጸዋል።

የአማራ ክልል የፀጥታ ምክር ቤት በዝርዝር አጥንቶ ክልሉን ለማዳከም የሚሠሩ ጠላቶች መኖራቸውን አረጋግጧል ብለዋል። የውስጥ ጠላቶችን ለመዋጋት የውስጥ አንድነታችንን ማጠናከር አለብን ነው ያሉት። የኅብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ የመግባት እንቅስቃሴ ችግር ውስጥ እየወደቀ መኾኑንም ተናግረዋል። ውስጡን እያዳከመና እየከፋፈለ የሚገኝ ኃይል እንዳለም አረጋግጠናል ነው ያሉት።

ሕገወጥ ተኩስ በአጭር ካልተቀጨ በስተቀር ለኅብረተሰቡ ስጋት ይኾናልም ነው ያሉት። የልማት እንቅስቃሴዎች በሰላማዊ ሁኔታ እንዳይከናወኑ እየተደረገ መኾኑን መገንዘባቸውንም ተናግረዋል።

የኮንትሮባንድ ንግድም ፈታኝ እየሆነ መምጣቱንም ገልጸዋል። አንዳንዱ ሕገ ወጥ ንግድ በጦር መሳሪያ ጭምር እየታገዘ መኾኑንም ጠቁመዋል።

በታጠቁ ኃይሎች ምክንያት የመንግሥት አቅጣጫዎች እንዳይተገበሩ የሚያደርጉ መፈጠራቸውንም ተናግረዋል።

ሃይማኖትን ሰበብ በማድረግ እርስ በርስ በማጋደል ክልሉ የፀጥታ ስጋት ውስጥ እንዲቆይ የሚያደርጉ ሁኔታዎች መገኘታቸውን አመላክተዋል። ይህም ለውጭ ጠላት ተገላጭ እንዲኾን እያደረገ መኾኑንም መገምገማቸውንም ጠቁመዋል።

በየደረጃው ያለ አመራር እየተሳተፈበት የሕግ ማስከበር ሥራው እየተከናወነ መኾኑንም አስታውቀዋል። እየተወሰደ ያለው የሕግ ማስከበር ሥራ ጅማሮው አበረታች መኾኑንም አንስተዋል።

ሕገ ወጥ የመሬት ወረራን በማስለቀቅ እና ሕጋዊ ለማድረግ እየተሠራ መኾኑንም ገልጸዋል። የሕግ ማስከበር ሥራው አስፈላጊና ስኬታማ እንደሚኾን ተናግረዋል።

ሕግ የማስከበር ሥራችንን አጠናክረን እንቀጥላለንም ብለዋል። የአማራን ሕዝብ ሰላምና ደኅንነት ለመጠበቅ እንሠራለን ነው ያሉት።

እርስ በርሱ የተከፋፈለ ሕዝብ ለጠላት ተጋላጭ መኾኑንም አንስተዋል። ሕግ የማስከበሩ ሥራ የመንግሥትን ኃላፊነት የሚያረጋግጥ እና ሕዝብን የመታደግ መኾኑንም አስታውቀዋል። ወጣቶች ከመንግሥት ጋር በመኾን ለሕግ ማስከበሩ ሥራ እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ተጠርጣሪዎችን እየያዙና በውይይት ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ሥራ እንደሚሠራም አንስተዋል።ያለ አግባብ የተያዙ ሰዎች ካሉ አጣሪ ኮሚቴው እያጣራ አፋጣኝ መፍትሔ ይሰጣልም ነው ያሉት። ጥፋተኞች ግን በሕግ አግባብ ሊቀጡ ይገባል ነው ያሉት። ከክልሉ ውጭ ተይዘው ጠፉ የሚባሉት ትክክል አይደለም መስተካከል አለበትም ብለዋል። የተፈጠረ ስህተት ካለም መታረም አለበት ነው ያሉት።

የክልሉ መንግሥት ሕግ ለማስከበርና ሙሉ አቅም አለው ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ ሕገወጦችንና ሥርዐት አልበኞችን የመቆጣጠር አቅም አለው ነው ያሉት። እየተወሰደ ያለውን የሕግ ማስከበር ሥራ ኅብረተሰቡ ከአሉባልታ ተቆጥቦ በጥንቃቄ እንዲመረምረውም አሳስበዋል።

የጦር ነጋሪት እየጎሰመ ያለውን ጠላት በመከላከያ ሠራዊት፣ በልዩ ኃይል፣ በሚሊሻና በፋኖ ሕዝባችን ደጀን አድርገን እንመክታለን ነው ያሉት።

ሕዝቡ እንዲከፋፈል ዘመቻ እንደተከፈተበትም ተናግረዋል። ሕዝቡ ተከፋፍሎ እንዲዳከም እየተደረገ ነው፤ ሕዝቡ ይሄን መገንዘብ አለበት ነው ያሉት።

መንግሥት እያደረገ ያለው ሕገወጦችንና ሥርዐት አልበኞችን መቆጣጠር እንጂ ሌላ ዓላማ የለውምም ብለዋል። ሕገ ወጦች ተጠያቂ መኾን አለባቸው፤ ያላጠፋ ነጻ ይኾናልም ነው ያሉት። “በሕገወጦች ላይ ያለ ምኅረት እርምጃ መውሰድ አለብን፤ ይህ የመንግሥት ተግባር ነው” ብለዋል።

“የአማራ ክልል መንግሥት የጦር መሳሪያ አያስፈታም፤ የክልሉ መንግሥት ፋኖን የሚያዋክብ አይደለም፣ ፋኖዎችን አመሰግነናል፣ ሸልመናል፣ ነገር ግን በፋኖ ስም የሚነግዱ አሉ፤ በነጻነት እና የአማራ የክብር ስም በኾነው ፋኖ እየተንጠላጠሉ ሕገ ወጥ ተግባር ለመፈጸም የሚፈልጉ አሉ፤ ሕግ ስናስከብር ፋኖ ነው የሚባለው ውሸት ነው፣ እኛ ሕገወጦችን እንጂ ፋኖዎችን የመንካት ዓላማ የለንምም” ነው ያሉት። ዓላማችን የዜጎችን ሰላምና አንድነት ጠብቀን የጋራ ጠላታችን በጋራ መጠበቅ ነው ብለዋል።

የመንግሥትን ሥራ የሚገዳደር ኃይል ሊኖር አይችልምም ብለዋል። ሕዝቡ ከፀጥታ መዋቅር ጎን እንዲሰለፍም ጥሪ አቅርበዋል። ሰላምና ደኅንነታችን በራሳችን እንገባ፣ ይህን የማድረግ አቅም አለንም ብለዋል። ማርኮ የያዘ ሰው መሣሪያውን አይነጠቅም፣ ነገር ግን ማስመዝገብ አለበትም ብለዋል።

መሳሪያውን ለችግር ጊዜ እንዲጠቀምበት የሚያደርግ ስልጠና እንሰጣለን ፣ መሳሪያ ያላቸው እንዲያስመዝግቡ ጥሪ እናቀርባለን ነው ያሉት።

በተጀመረው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ጥሩ ለውጥ መገኘቱን የገለጹት ርእሰ መሥተዳድሩ በቅርቡ ከተኩስ ድምፅ ነጻ የኾኑ ከተሞችን እንፈጥራለንም ብለዋል። ከሕግ ማስከበሩ በተቃራኒ የቆሙት ኹሉ ለአማራ ሕዝብ የማያስቡ መዃናቸውንም አንስተዋል።

ለአማራ ሕዝብ ተቆርቋሪ የኾነ ለሕዝብ ሰላምና ደኅንነት መሥራት እንደሚገባውም አንስተዋል። የተያዙ ግለሰቦችን በአግባቡ እንይዛለንም ብለዋል። ኅብረተሰቡ ሕገወጦችን እያወጣ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል።

ሰላምን ለማስከበር በሰላማዊ መንገድ እንሠራለን፣ ከአቅም በላይ ሲኾን እርምጃ እንወስዳለንም ነው ያሉት።

"ህዝቡ በየደረጃው ላነሳቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ኃላፊነት ወስደን እየሰራን ነው" አቶ ግርማ የሽጥላህዝቡ በየደረጃው ላነሳቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ኃላፊነት ወስደ...
05/04/2022

"ህዝቡ በየደረጃው ላነሳቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ኃላፊነት ወስደን እየሰራን ነው" አቶ ግርማ የሽጥላ

ህዝቡ በየደረጃው ላነሳቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ኃላፊነት ወስደን እየሰራን ነው ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና በአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሽጥላ ገለፁ።

የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚና በአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሽጥላ እንደገለፁት ፓርቲያችን በመጀመሪያውና በታሪካዊው ጉባኤው የተለያዩ ሀገራዊ ውሳኔዎችን ማሳለፉን አስታውሰው የውሳኔ ሃሳቦችንም ከክልል እስከ ቀበሌ ድረስ ከመላው ሕዝብ ጋር ውይይት አድርገናል ሲሉ ገልፀዋል፡፡

አቶ ግርማ አክለውም በፓርቲችን ከፍተኛ አመራሮች በተመራው የህዝብ ውይይት መድረክ በርካታ ጥያቄዎች እና ተጨባጭ ችግሮች ተነስተዋል ያሉ ሲሆን በተነሱ አስተያየቶችና ችግሮች ላይ ህዝቡ፣ ፓርቲው እና በየደረጃው ያለው የመንግስት መዋቅር የየድርሻቸውን ኃላፊነት ወስደው የተነሱ ችግሮችን ለመፍታት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ መግባባት እንደተፈጠረም አቶ ግርማ ገልፀዋል፡፡

የአማራ ብልጽግና ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሽጥላ አክለው እንደገለፁት ህዝቡ ያነሳቸውን ጥያቄዎችና ተጨባጭ ችግሮች መፍታት፣ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ፣ ተጠያቂነትን ማዕከል ያደረገ የፓርቲ እና የመንግስት አመራሮችን የማስፈጸም ብቃት ከፍታ በማረጋገጥ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፓርቲያችን ተግቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

ህዝቡ በየደረጃው ላነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየሰራን ነው ያሉት አቶ ግርማ ስራውን ውጤታማ ለማድረግም ከሚያዝያ 1 እስከ ሰኔ 30 2014 ዓ.ም የሚቆይ የዘጠና ቀናት የአጭር ጊዜ ዕቅድ እንደተቀመጥም ገልፀዋል።

ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከላይ እስከ ታች በየደረጃው የሚገኙ ፈጻሚ አካላት በሙሉ አቅማቸው ወደ ተጨባጭ ተግባራዊ ምላሽ እና የሕብረተሰብ ተሳትፎ፣ ተጠቃሚነት እና እርካታን ለማረጋገጥ እንደሚንቀሳቀሱ ገልጸዋል ።

በመጨረሻም የፓርቲያችን መዋቅር ከላይ እስከ ታች በጥብቅ ዲሲፕሊንና መርህ እየተመራ የህዝብ አስተያየት ወደ ተግባር እየተቀየሩና ጥያቄዎቹም እየተመለሱለት ስለመሆኑም በየጊዜው የመፈተሸ ስራ ተናክሮ እንደሚሰራ አቶ ግርማ የሽጥላ ተናግረዋል፡፡

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

"ወንድሞቻችንን ለመቀበል ዝግጅት አጠናቀናል" የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ነዋሪዎች  የአማራ ሕዝብ ትግል ፍሬ አፍርቶ ዛሬ ላይ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ሲናፍቀውና ሲመኘው የነበረውን ማ...
01/04/2022

"ወንድሞቻችንን ለመቀበል ዝግጅት አጠናቀናል" የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ነዋሪዎች

የአማራ ሕዝብ ትግል ፍሬ አፍርቶ ዛሬ ላይ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ሲናፍቀውና ሲመኘው የነበረውን ማንነቱን ተላብሶ፣ ነጻነቱን ተጎናፅፎ የትግል ጊዜ አጋሩን በሁሉም ቦታ ተገኝተው ስለ ከፈሉት መስዋእትነት አመሥግነዋል።

በቅርቡ ለሚካሄደው "አማራን እንወቅ" ኹለተኛ ምዕራፍ መርሐ ግብር የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን የክት ልብሷን ለብሳ፣ የነጻነት ካባዋን ተጎናጽፋ እጆቿን ዘርግታ ልጆቿን ለመቀበል ዝግጁ ኾናለች።

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ያነጋገራቸው የሑመራ ከተማ ነዋሪዎች የወንድሞቻቸውን መምጣት በጉጉት እንደሚጠብቁት ገልጸዋል።

የሰላም ኢትዮጵያ ሆቴል ባለቤት የኾኑት ወይዘሮ ስሜነሽ ሞላ ለአሚኮ በሰጡት አስተያየት ስለ ነጻነታችን የታገሉ፣ የሕይወት መስዋእትነትን የከፈሉ ልጆቻችን ናቸውና በራችን ከፍተን ልንቀበላቸው ዝግጁ ነን ነው ያሉት።

ሌላኛው ከአሚኮ ጋር ቆይታ ያደረጉት ባለሃብት አድምጠው ሰረበ የታገሉላትን ምድር ለማየት በመምጣታቸው አባት ልጁን እንደሚናፍቅው እኛም በፍፁም ፍቅር ልንቀበላቸው ዝግጁ ነን ብለዋል።

ከፍተኛ መስዋእትነት የከፈሉባትን ምድር ለማየት መምጣታቸው አንድነታችን የማይነጣጠልና ለጠላት የማንበገር መኾናችንን ማረጋገጫ ነው ሲሉ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

የሚመጡ እንግዶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ ዝግጅት ማጠናቀቁን የሑመራ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኀላፊ እና የዝግጅት ኮሚቴው አስተባባሪ አቶ ተስፋሁን አበበ ገልጸዋል።

ከመላው የአማራ ክልል ዞኖች የተውጣጡ ከ600 በላይ እንግዶች "ወልቃይት የትግላችን መነሻ፣ የአንድነታችን ማሳያ፣ የነጻነታችን ዓርማ አማራን እንወቅ " መርሐ ግብር ላይ ተሳታፊ እንደሚኾኑና በመርሐ ግብሩም የወልቃይት ጠገዴን አማራዊ ባሕል ለማሳወቅ ዝግጅት መጠናቀቁን አቶ ተስፋሁን አስታውቀዋል።

አሚኮ

" ወልቃይት የትግላችን መነሻ ፣ የአንድነታችን ማሳያ ፣ የነፃነታችን አርማ ""አማራን እንወቅ "መርሐ-ግብር ምእራፍ ሁለት በቅርቡ እንደሚካሄድ ተገለፀ። በፕሮግራሙም ከመላው አማራ የተወከሉ ...
28/03/2022

" ወልቃይት የትግላችን መነሻ ፣ የአንድነታችን ማሳያ ፣ የነፃነታችን አርማ "

"አማራን እንወቅ "መርሐ-ግብር ምእራፍ ሁለት በቅርቡ እንደሚካሄድ ተገለፀ።

በፕሮግራሙም ከመላው አማራ የተወከሉ ከ600 በላይ ወጣቶች፣ ምሁራን፣ ማህበራዊ አንቂዎች፣ ሴቶች፣ መንግስት ሰራተኞች፣ ባለሀብቶች እና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ።

መርሐግብሩን አስመልክቶ የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት መግለጫ ሰጥቷል።

የሊግ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ ወጣት አብይ አበባው እንደገለፁት በትሕነግ የግዞት ዘመን ተወልዶ የማያውቀው ማንነት ተጭኖበት ያደገው የወልቃይት ጠገዴ አማራ ወጣት ትውልድ በሌሎች የአማራ አካባቢዎች ያለውን ባህል ፣ ዕሴት እና አማራዊ ትውፊት እንዲያውቁ ለማድረግ በቅርቡ ከወልቃይት ጠገዴ አማራ የተወከሉ ከ300 በላይ ወጣቶች በመላው አማራ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እና የትውውቅ መርሐግብር ተዘጋጅቶ እንደነበረ ወጣት አብይ አስታውሰዋል።

ኃላፊው አክለውም በዚህ ጉብኝትም የወልቃይት፣ ጠገዴና ሰቲት ሁመራ የአዲሱ ትውልድ አማራ ወጣቶች ከአፓርታይድ በከፋ አገዛዝ ተነፍገው የኖሩትን አማራዊ / ኢትዮጵያዊ ማንነት እና ጣዕምን እንዲያጣጥሙ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ለወልቃይት አማራ ወጣቶችም የአማራ ህዝብ አኩሪ ማንነት፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ትውፊት እና የአኗኗር ዘይቤዎችን ማስተዋወቅ ተችሏል ብለዋል።

በተጨማሪም የወልቃይት ጠገዴና ሰቲት ሁመራ ወጣቶች በትህነግ የግፍ አገዛዝ ሲደርስባቸው የነበረውን ግፍ እና በደል ለሌላው የአማራ ህዝብ የማጋራት እድልን ያገኙ ሲሆን ወጣቶቹ በትሕነግ የጭቆና አገዛዝ ዘመን የተጎዳውን የወልቃይት አማራ ወገናችንን ስነ ልቦና ማደስ እና ማህበራዊ እረፍት ለመስጠት ተችሏል።

የዚህ መርሐ- ግብር ቀጣይ ክፍል የሆነው " ወልቃይት የትግላችን መነሻ፣ የአንድነታችን ማሳያ፣ የነፃነታችን አርማ"
፤ "አማራን እንወቅ" መርሐ-ግብር ምእራፍ ሁለት በቅርቡ እንደሚካሄድ ወጣት አብይ የጠቆሙ ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ከመላው አማራ ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉ ከ 600 በላይ ተሳታፊዎች ይገኛሉ ብለዋል።

የ"አማራን እንወቅ " መርሐ-ግብር ምዕራፍ ሁለት መሠረታዊ አላማም የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ሰቲት ሁመራ ዞንን ማስጎብኘት እና ከወልቃይት አማራዎች ጋር የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነ ኃላፊው ተናግረዋል።

መጋቢት 19 /2014 ዓ.ም
----
" ወልቃይት የትግላችን መነሻ ፣ የአንድነታችን ማሳያ ፣ የነፃነታችን አርማ "
---

APP

እናስተውል!!የኤርትራ ሠራዊትና የአማራ ልዩ ሃይል በጋራ እየጨፈሩ የሚያሳይ በሚል በብዛት ሲሰራጭ የዋለው ቪዲዮ (Video) ሃሰተኛ ሲሆን ዋነኛ ዓላማውም “የአማራ ልዩ ሃይል ከኤርትራ ሠራዊ...
28/03/2022

እናስተውል!!

የኤርትራ ሠራዊትና የአማራ ልዩ ሃይል በጋራ እየጨፈሩ የሚያሳይ በሚል በብዛት ሲሰራጭ የዋለው ቪዲዮ (Video) ሃሰተኛ ሲሆን ዋነኛ ዓላማውም “የአማራ ልዩ ሃይል ከኤርትራ ሠራዊት ጋር በመተባበር የትግራይን ሕዝብ ከበባ ውስጥ አስገብተው ለከፋ ጉዳት ዳርገውታል” የሚለውን የጁንታውን ክስ እውነት በማስመሰል H.R. 6600 እንዲጸድቅ ግፊት ማድረግ ነው!!

ስለዚህ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ህዝባችንን ለሚጎዳ ፕሮፖጋንዳ ሰለባ ባንሆን እና ባንተባበር መልካም ነው።

የደጃዝማቸ ተድላ ጓሉ ሀገር የንጉስ ተክለሀይማኖት መናገሻ የቀድሞዋ መንቆረር የአሁኗ ደብረማርቆስ ከተማ ወጣቱን ከንቲባ ሹማለች።ወጣቱ ከንቲባ ይትባረክ አወቀ በተቀዳሚ ከንቲባነት ሹመት የተሰ...
21/03/2022

የደጃዝማቸ ተድላ ጓሉ ሀገር የንጉስ ተክለሀይማኖት መናገሻ የቀድሞዋ መንቆረር የአሁኗ ደብረማርቆስ ከተማ ወጣቱን ከንቲባ ሹማለች።

ወጣቱ ከንቲባ ይትባረክ አወቀ በተቀዳሚ ከንቲባነት ሹመት የተሰጣቸው ከማማዋ በቅርቡ ወደ ሪጅዮፓሊታንት ከተማነት ማደጓን ተከትሎ ነው።

ከተማዋ ወደ ሪጅዮፓሊታንትነት ደረጃ ማደግ ከፍተኛ የልማት እድል ይዞላት የመጣ ሲሆን ይህንን እድል በአግባቡ በመምራት የከተማዋን ነዋሪወች የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል ውጤታማ አመራር በመስጠት በኩል ደግሞ ወጣቱ ከንቲባ እና ካቢኔው ከፍተኛ እምነት ተጥሎባቸዋል።

መልካም የስራ ዘመን ወንድማችን።

"በሸኔ መንገድ እየሄደን ሸኔን አናሸንፈውም። " ጋዜጠኛ Fasil Yenealem የዛሬው የጋይንት ድርጊት በሁሉም አማራ ሊወገዝ ይገባል።
08/02/2022

"በሸኔ መንገድ እየሄደን ሸኔን አናሸንፈውም። "

ጋዜጠኛ Fasil Yenealem

የዛሬው የጋይንት ድርጊት በሁሉም አማራ ሊወገዝ ይገባል።

ደቡብ ጎንደር ዞን እስረኛ ለማስፈታት ከሞከሩ መካከል 16ቱ ተገደሉ ተባለበአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን እስረኛ ለማስፈታት የሞከሩ 16 ሰዎች መገደላቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የደ...
08/02/2022

ደቡብ ጎንደር ዞን እስረኛ ለማስፈታት ከሞከሩ መካከል 16ቱ ተገደሉ ተባለ

በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን እስረኛ ለማስፈታት የሞከሩ 16 ሰዎች መገደላቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የደቡብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ጥላሁን ደጀኔ ከደቂቀዎች በፊት ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ትናንት ሌሊት 8 ሰዓት ሲሆን ነፋስ መውጫ ማረሚያ ቤትና ሌሎች ሁለት ፖሊስ ጣቢያዎች እስረኛ ለማስፈታት ከሞከሩት ዘራፊ ካሏቸው ታጣቂዎች መካከል 16ቱ ሲገደሉ 20 ተማርከዋል ፡፡

ዘራፊ ያሏቸው አካላት ከተለያዩ አጎራባች ዞኖች የተሰባሰቡ እንደነበሩም ምክትል አስተዳዳሪው አመልክተዋል፡፡ ከመንግስት በኩል 3 የፀጥታ አካላት መቁሰላቸውን የተናገሩት አቶ ጥላሁን፣ ከማረሚያ ቤት ወጥተው ከነበሩት ታራሚዎች መካከል 65ቱ በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳና በደቡብ ጎንደር ዞን ጋይንት ወረዳ በተውጣጡ ጥምር የፀጥታ አካላት ቅንጅት በያሉበት ተይዘው ተመልሰዋልም ብለዋል፡፡

የባህር ዳር ወልዲያ መስመር ለተወሰነም ጊዜ ቢሆን ዛሬ ተቋርጦ እንደነበር ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ታጣቂዎቹ በ3 ተለያዩ መኪናዎች የመጡ እንደነበሩና ተሸከርካሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለዋልም ነው ሉት

ዘገባ፤ ዓለምነው መኮንን_DW_ ከባህርዳር

አባቶቻችን የሰጡንን ያስረከቡንን ሰንደቅ ጠብቀን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሚጠብቅ ሃይል ያስፈልጋል።የተሰጠህን ዕድል በመጠቀም ወደ ልዩ ሀይል ተቀላቀል!!!
04/02/2022

አባቶቻችን የሰጡንን ያስረከቡንን ሰንደቅ ጠብቀን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሚጠብቅ ሃይል ያስፈልጋል።

የተሰጠህን ዕድል በመጠቀም ወደ ልዩ ሀይል ተቀላቀል!!!

ይተማል እንጂ ነበልባል ጎበዝ፣ከጠላቱ ጋር ጦር የሚማዘዝ፣እሳት ጨብጦ እሳት የሚይዝ።አያስደፍርም ሀገር እናቱን፣ይሰዋል እንጂ ክብር ህይወቱን።የአማራ ልዩ ሀይልን ይቀላቀሉ
04/02/2022

ይተማል እንጂ ነበልባል ጎበዝ፣
ከጠላቱ ጋር ጦር የሚማዘዝ፣
እሳት ጨብጦ እሳት የሚይዝ።
አያስደፍርም ሀገር እናቱን፣
ይሰዋል እንጂ ክብር ህይወቱን።

የአማራ ልዩ ሀይልን ይቀላቀሉ

የአማራ ልዩሀይልን መቀላቀል በተግባር ተቆርቋሪነትን አንዱ ማሳያ ነው! ወቅቱ በሁለንተናዊ መንገድ ሀይላችን የምናጠናክርበት ሲሆን ልዩሀይላችን ማጠናከርና መቀላቀል ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው...
04/02/2022

የአማራ ልዩሀይልን መቀላቀል በተግባር ተቆርቋሪነትን አንዱ ማሳያ ነው!

ወቅቱ በሁለንተናዊ መንገድ ሀይላችን የምናጠናክርበት ሲሆን ልዩሀይላችን ማጠናከርና መቀላቀል ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው!

ስለሆነም መስፈርቱን የምናሟላ የአማራ ወጣቶች ዛሬው በመመዝገብ ለአማራ ህዝብ በተግባር ጠበቃ እንሁን!

በመጨረሻም ከወጭ ቀሪ 300.000 ወጣት እንዳለቀባቸው አምነዋል።
01/02/2022

በመጨረሻም ከወጭ ቀሪ 300.000 ወጣት እንዳለቀባቸው አምነዋል።

11ኛ ዙር የአማራ ልዩ ምዝገባና ምልመላ ስራ ተጀመረ።አማራው የተጋረጠበትን አደጋ ለመመከትና ክብሩን አስጠብቆ ለማስቀጠል ከተፈለገ አቅሙ የሚፈቅድላቸው ወጣቶች ሁሉ ልዩ ሀይላችንን መቀላቀል ...
27/01/2022

11ኛ ዙር የአማራ ልዩ ምዝገባና ምልመላ ስራ ተጀመረ።

አማራው የተጋረጠበትን አደጋ ለመመከትና ክብሩን አስጠብቆ ለማስቀጠል ከተፈለገ አቅሙ የሚፈቅድላቸው ወጣቶች ሁሉ ልዩ ሀይላችንን መቀላቀል ይጠበቅባቸዋል።

ስለሆነም ሁሉም አማራ 11ኛው የአማራ ልዩ ሀይል ምዝገባና ምልመላ የበኩሉን አስተዋፅኦ በማበርከት በጠላቶቻችን የሚፈራ በወዳጆቻችን ደግሞ የሚከበር ሀይል እንድንገነባ መስራት ይኖርበታል።

አማራነት ያሸነፋል!
ኢትዮጵያዊነት ይለመልማል!

"እኔ የመጣሁት የአማራን ህዝብ ጥቅም ለማስጠበቅ ነው ! ከጀርባየ ምንም አይነት ሸፍጥ ሆነ ሴራ የለም ! አላማየ የአማራን ህዝብ ጥቅም ማስከበር የኢትዮጵያን አንድነት ማስቀጠል ብቻ ነው!ሁላ...
16/01/2022

"እኔ የመጣሁት የአማራን ህዝብ ጥቅም ለማስጠበቅ ነው ! ከጀርባየ ምንም አይነት ሸፍጥ ሆነ ሴራ የለም !

አላማየ የአማራን ህዝብ ጥቅም ማስከበር የኢትዮጵያን አንድነት ማስቀጠል ብቻ ነው!

ሁላችሁም ከጎኔ ልትቆሙ ይገባል!

ፋኖ ለአማራ ህዝብ ጥቅም የታገለ ሀገርን ያዳነ ሀይል ነው!

እኔ ፋኖን የማፍረስ አላማ በፍፁም የለኝም እኔም ለህዝቤና ለሀገሬ ፋኖ ነኝ !

በፋኖ ስም የሚዘርፈውን ህግ የሚጥሰውን ከፋኖ ጋር በአንድነት ታግለን ፋኖን ይዘን ጠላታችን እስከመጨረሻው እንመክታለን"

የአማራ ክልል ፕሬዘዳንት አቶ ይልቃል ከፋለ!

በአላማ፣በእቅድና በመርህ የሚመራ ትግል ለምን አልኖረንም?እኛ የእየለት አጀንዳ ሲወረወርልን ያችን እንደ ቁርስ፣ምሳና እራት ስናኝክ ነው የምንውለው! እስኪ ራሳችን እንጠይቅ ከእለታዊ አጀንዳ ...
14/01/2022

በአላማ፣በእቅድና በመርህ የሚመራ ትግል ለምን አልኖረንም?

እኛ የእየለት አጀንዳ ሲወረወርልን ያችን እንደ ቁርስ፣ምሳና እራት ስናኝክ ነው የምንውለው! እስኪ ራሳችን እንጠይቅ ከእለታዊ አጀንዳ ወጥተን እናውቃለን ወይ? አንድ አጀንዳ ሳያልቅ በነጋታው ሌላ አጀንዳ አይደለም ወይ የሚወረወርልን? እስኪ ራሳችን እንጠይቅ በየቀኑ የተወረወሩ አጀንዳዎችን ዞር ብለን እናስታውሳቸዋለን ወይ?

አማራ በአላማ፣በእቅድና በመርህ የሚመራ ትግል የለውም! መነሻና መዳረሻውን አያውቅም! ዝም ብሎ ሰዎች ባዘጋጁለት አረንቋ ውስጥ ገብቶ ከመዳከር ውጭ ሌላ አያውቅም! በእውነቱ አጀንዳ ከሌለ ይጨንቀናል! አጀንዳ ሲወረወር ብቻ react ማድረግ እንጅ ወደ ኋላ ሄደን ወደፊት ለመንደርደር የሚያስችለንን momentum አንፈጥርም!

We just don't know the way out of this never-ending trap!

ፎቶ :-የዋግ ቆንጆ ህፃን

 #መረጃ ስለ ፋኖ❗️የአማራ ክልል መንግስት በህልውና ዘመቻ ስምሪት ተሰጥቷቸው ከነበሩ ፋኖ መሪዎች ጋር የመጀመሪያ ዙር ውይይት በባህር ዳር ከተማ እንደሚያካሂድ መረጃ ደርሶናል፡፡ መድረኩም ...
14/01/2022

#መረጃ ስለ ፋኖ❗️

የአማራ ክልል መንግስት በህልውና ዘመቻ ስምሪት ተሰጥቷቸው ከነበሩ ፋኖ መሪዎች ጋር የመጀመሪያ ዙር ውይይት በባህር ዳር ከተማ እንደሚያካሂድ መረጃ ደርሶናል፡፡

መድረኩም በቀጣይ የክልሉን የፀጥታ መዋቅር የበለጠ በማጠናከር የህዝባችንን ህልውና ለማስጠበቅ መከናወን ስለሚኖርባቸው ሁነኛ አጀንዳዎች በመምከር ላይ የሚያተኩር ይሆናል፡፡

ከጠላት ባልተናነሰ መንገድ የተለያዩ ከፋፋይና ስሁት አጀንዳዎችን በማራገብ የአማራን ህዝብ አንድነት ለማዳከም መሞከር ግን ጉንጭ ከማልፋት ውጭ ረብየለሽ ነው።

አማራ በጊዜውም ያለጊዜውም ፅና!

ትንሽ ቆሎ ይዘህ ከአሻሮ ተጠጋ ነው ጉዳዩ!የሰነድ ሽፋን ስዕል አሳይቶ ስለሰነድ ማውራት!ግን የማስተዋል ጥበባችንን ማን ወሰደብን?🤔"አሳፋሪው የብልፅግና ሰነድ የምትል አዲስ አጀንዳ ተከፍታለ...
13/01/2022

ትንሽ ቆሎ ይዘህ ከአሻሮ ተጠጋ ነው ጉዳዩ!

የሰነድ ሽፋን ስዕል አሳይቶ ስለሰነድ ማውራት!

ግን የማስተዋል ጥበባችንን ማን ወሰደብን?🤔

"አሳፋሪው የብልፅግና ሰነድ የምትል አዲስ አጀንዳ ተከፍታለች" የሰነዱን ከበር በመለጠፍ ነው ህዝቡን ለማወዛገብ እየተሞከረ ያለው።

እዉነተኛው ሰነድ 64 ገፅ ሲሆን የአማራን ተጋድሎ የፋኖን ጀግንነት ጭምር በአግባቡ የሚመሰክር የህዝቡን ጀግንነትና ደጀንነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ እንዲያውም የአማራን ህዝብ "ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሁሌ ሲደማ ይኖራል" በማለት ከትግራይ ጋር በመጎራበቱ እየገጠመው ያለውን ችግር በአግባቡ በመዘርዘር ጭምር የሚጀምር ሰነድ ነው።

አሁንም የቀጣዩን ትግልም እንዴት መጠናቀቅ እንዳለበት በአግባቡ ያስቀምጥና ያሉ ችግሮችን ደግሞ ለቅሞ ለማረም በሚጠቅም መንገድ ያስቀምጣል። ይህ ደግሞ የግድ መሆን ያለበት ነው።

ይሄን መነሻ አድርገዉ ሁሉም ክልሎች ከየራሳቸዉ ተነስተዉ ሰነዱን በስልጠና መለክ ተጠቅመዉበታል።

የአማራ ክልልም ከራሱ አንፃር አዳብሮ ስልጠና እየሰጠበት ነዉ። ዛሬ እየዞረ የዋለዉ ሰነድ ግን በደቡብ ሐዋሳ የተሰጠ መሆኑ ተደርሶበታል።

ሐዋሳወች የአማራን ተጋድሎ አለማንሳታቸዉ በእጅጉ ሁላችንንም አስገርሟል።

ለሁሉም እዉነቱ ሌላ ነዉ። የአማራ ብልፅግናም በጉዳዩ ዙሪያ በቂ መረጃ ይሰጥበታል ብለን እንጠብቃለን።

ሌላኛውና ይህንን ሁሉ ጥርጣሬ የሚያከሽፈው ጉዳይ ደግሞ የአማራ ክልል መንግስት በሁለት ዙር የተከፈለውን ከፋኖ መሪወች ጋር የሚደረግ ውይይት ነገ በባህርዳር ከተማ የሚጀመር መሆኑ ነው።

ይልቅ ሁሉም አማራ በየ እለቱ በሚሰጡት አጀንዳወች ሳይደናገር ለጠላቶች በሩን ሳይከፍት አንድነቱን ማጠናከር ላይ ብንሰራና ማህበረሰብ አንቂው፣ ሙሁሩ ፣ፓለቲከኛው
እንደ ዘመን አመጣሽ ፊኛ ስሜት የሚወጥርውና የሚያስተነፍስው ሳይሆን እንደ አባቶቹ ዘመን የማይሽረው የጥበብ ብልሀትና እውቀት መሰደሪያ ማህደርን ቢመስል መልካም ነው።

/ቢክስ መልካሙ/

የተረጋገጠ መረጃ!!!/share/ከውስጥ አዋቂዎች በደረሰን የተረጋገጠ  መረጃ መሰረት የአማራ ክልል መንግስት ትጥቅ ሊያስፈታ ነው የሚለው መረጃ ፍፁም ሃሰትና ሆን ተብሎ የአማራን አንድነት ለ...
13/01/2022

የተረጋገጠ መረጃ!!!
/share/

ከውስጥ አዋቂዎች በደረሰን የተረጋገጠ መረጃ መሰረት የአማራ ክልል መንግስት ትጥቅ ሊያስፈታ ነው የሚለው መረጃ ፍፁም ሃሰትና ሆን ተብሎ የአማራን አንድነት ለማዳከም የተለቀቀ መረጃ መሆኑን ደርሰንበታል፡፡

እንዲያውም ቀጣይነት ላለው የህልውና ዘመቻ የፀጥታ ሃይሉን የበለጠ ማጠናከር የክልሉ መንግስት ዋነኛ ትኩረት ሆኖ እንደሚቀጥል ከሰሞኑ ከነበሩ መድረኮች የደረሱን መረጃዎች ያረጋግጣሉ፡፡ ስለሆነም ህዝባችን ጠላት የሚሰጠንን አጀንዳ እየተቀበልን ለፀረ አንድነት ኃይሎች ተባባሪ መሆን የለብንም፡፡

ነውረኛ ከፋፋዩችን ማጋለጣችንን ቀጥለናል!የባለፈው ዘመን የፖለቲካ ግልሙትና ሊቅ ነን ባዮችና የዚህ ዘመን ባንዳ የስልጣን ጥመኞች ወቅታዊ ያልተቀደሰ ጋብቻ ፈጥረው ሰሞኑን የውሸት አጀንዳን በ...
12/01/2022

ነውረኛ ከፋፋዩችን ማጋለጣችንን ቀጥለናል!

የባለፈው ዘመን የፖለቲካ ግልሙትና ሊቅ ነን ባዮችና የዚህ ዘመን ባንዳ የስልጣን ጥመኞች ወቅታዊ ያልተቀደሰ ጋብቻ ፈጥረው ሰሞኑን የውሸት አጀንዳን በመፈብረክ ሀገራዊ ቀውስ ለመፍጠር መላላጥ ይዘዋል። ሴራቸው ያልተገለጠለት እስኪገባው ድረስ እኛም እውነቱን እየቆረጥን ሀሰተኞችን ከታገል ወደኋላ አንልም።

ስምን እንደፈለጉ እየተዋሱ በመጠቀም ምስኪኑን የማህበረሰብ ክፍል ለማደናገርና ድብቁን የመከፋፈል ሴራቸውን ካላጋለጥን መከራችን የከፋ ይሆናል። አስተዋዩ ህዝባችን እውነቱን ይረዳ ዘንድ እየተከታተልን እናጋልጣለን ከዛም እውነቱን መመዘን የሱ ይሆናል።

ጀግና በስራ ላይ ሰነፍ በወሬ ላይ ነው!!አቶ አማረ አለሙ የሀገርን ህልውና የሚታደጉትን ጀግኖቹን በማሰልጠን ላይ ነው።ደመላሸ ብርጌድ የተባለውን በሁመራ በባከር ጀግኖች የአማራ ልዩ ኃይልን ...
12/01/2022

ጀግና በስራ ላይ ሰነፍ በወሬ ላይ ነው!!

አቶ አማረ አለሙ የሀገርን ህልውና የሚታደጉትን ጀግኖቹን በማሰልጠን ላይ ነው።

ደመላሸ ብርጌድ የተባለውን በሁመራ በባከር ጀግኖች የአማራ ልዩ ኃይልን አሰልጥኖ በማስረቅ በሰቆጣ ግንባር ድል ተጎናፅፈዋል።

በሁለተኛው ዙር ደግሞ ነብሮ ብርጌድ የተባለውን የአማራ ልዩ ኃይል አሰልጥኖ በማስመረቅ በጋሽና ግንባር ታሪክ ሰርተዋል።

በሦስተኛ ደረጃ ነበልባ ብርጌድ የተባለውን ልዩ ሃይል አሰልጥኖ በማስመረቅ ወልቃይት ግንባር ላይ ታሪክ መስራታቸውን ቀጥለዋል።

ከመከረም እስከ አሁኗ ዕለት ድረስ ሠራዊቱን በማሰልጠን እና ግንባሮች በማጠናከር የራሱን ታሪካዊ አሻራ በማሳረፍ ላይ ነው።

ወንድማችን አማረ አለሙ እጥፍ ክብርና ምስጋና ይገባኃል።

ጀግናው በስራ ላይ ነው! ሰነፎች እስካሁን በወሬ ላይ ናቸው።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Prosperity Party supporters /የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎች ገፅ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share