ጋሞ ዱቡሻ

  • Home
  • ጋሞ ዱቡሻ

ጋሞ ዱቡሻ Our page is dedicated to foster a "One Gamo."

We aim to share insightful information and engaging content through seminars, research, and publications, all designed to develop a cohesive ideology that aligns with the interests of the Gamo community.

ጋሞ በ42 'ደሬ'ዎች[federated units) የምኖር አንድ ሕዝብ ነው
12/10/2025

ጋሞ በ42 'ደሬ'ዎች[federated units) የምኖር አንድ ሕዝብ ነው

ፈቃድ ያላቸው የግልና የመንግስት ሚድያዎች ጭምር የጋሞን ሕልውና የማሳነስ ስልታዊ እንቅስቃሴ በይፋ እያገዙ በሕግ ደረጃ ያላቸውን ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የጋሞ ዞን መንግስት በኢትዮጵያ ደረጃ ...
29/09/2025

ፈቃድ ያላቸው የግልና የመንግስት ሚድያዎች ጭምር የጋሞን ሕልውና የማሳነስ ስልታዊ እንቅስቃሴ በይፋ እያገዙ በሕግ ደረጃ ያላቸውን ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የጋሞ ዞን መንግስት በኢትዮጵያ ደረጃ ያለውን የተሻለ አስቻይ የሕግ ማዕቀፍ ወደመጠቀም መሸጋገር አለበት::

 #ለአርባምንጭ አለም አቀፍ ስታዲዬም  " 6111 Ok " ባለ አራት ዲጅት የገቢ ማሰባሰቢያ ቁጥር ተከፈተ*****የደቡብ ኢትዮጲያ ክልላዊ መንግስት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ለአርባምን...
22/09/2025

#ለአርባምንጭ አለም አቀፍ ስታዲዬም " 6111 Ok " ባለ አራት ዲጅት የገቢ ማሰባሰቢያ ቁጥር ተከፈተ
*****
የደቡብ ኢትዮጲያ ክልላዊ መንግስት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ለአርባምንጭ አለም አቀፍ ስታዲዬም " 6111 Ok " ባለ አራት ዲጅት የገቢ ማሰባሰቢያ ቁጥርን በመክፈት አስጀምሯል

"የአርባ ምንጭ አለም አቀፍ ስታዲዬም የእኔ ነው ! "

" 6111 Ok " በማለት ስታዲዬማይችንን አብረን እንገንባ !

እንኳን አደረሳችሁ! እንኳንም ደስ አላችሁ !
#ሀባ ማስቃላ ...... ዮዮዮ

ስንት ዓመት ትምህርት ሚንስቴርን መርቶ ምንም ውጤት ያላመጣ ይልቁንም በየዓመቱ ተመሳሳይ ድስኩር የምነግረን እርሱ ልጠየቅ ይገባል:: ስልጣኑንም የተዳመረ ውጤት ማሳካት ለሚችል ማስረከብ አለበ...
15/09/2025

ስንት ዓመት ትምህርት ሚንስቴርን መርቶ ምንም ውጤት ያላመጣ ይልቁንም በየዓመቱ ተመሳሳይ ድስኩር የምነግረን እርሱ ልጠየቅ ይገባል:: ስልጣኑንም የተዳመረ ውጤት ማሳካት ለሚችል ማስረከብ አለበት::

15/09/2025

ትምህርት ሚንስቴር በትውልዱ ላይ የያዘው ዓላማ ግልፅ አይደለም::

15/09/2025

በኢትዮጵያ ዘንድሮ ከ5285,882 የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መሀል ያለፉት 48,920፣ የወደቁት ደግሞ 536,962 ሆነዋል። በሌላ አገላለፅ 91.6% ተማሪዎች ወድቀው 8.4% ብቻ አልፈዋል ነው።

ይህ የትምህርት ስርዐቱን የሚመሩት አካላት በተደጋጋሚ የኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት የወደቀ ነው የሚለውን ለማሳየት ብቻ በማለም እያደረጉት የመጣ አደገኛ ልምምድ ነው:: ልምምዱ የተማሪዎችን እያደገ የሚሄድ ልጅነታቸውን; የሐገሪቱ የትምህርት መሠረተ ልማት ያሳደረባቸውን ውስንነት ታሳቢ ሳያደርግ የሚገታ; ወለጆችን ጥረት የማይመለከት እንዲሁም ከአመታት በሇላ ሐገሪቱን የሚቀበል enlighted ትውልድ የማያስቀር አደገኛ ልምምድ መሆኑን ለመመልከትና ለመገምገም አይፈልጉም:: በመሆኑም የትምህርት ስርዓቱ የግል ፍላጎትን ብቻ እንጂ ሰፊ ዓላማ ባላቸው አመራሮች እየተመራ አለመሆኑን እነዚህ ልምምዶች እያስመለከቱን ይገኛሉ:: በትምህርት መሠረተ ልማቱ ላይ እዚህ ግባ የሚባል investment ሳይደረግ ውጤቱን መገምገም ጥፋት ብቻ እንጂ ዓላማው ግልፅ አይሆንም::
የትምህርት ሚንስቴር በተከታታይ ዓመታት ልያሳዬን እየሞከረ ያለው ትውልድ ለማብቃት የተወጣውን የራሱን ሀላፊነት ሳይሆን''' ትውልዱ ላይ ታይቷል'' ያለውን ጉድለት ብቻ እየሆነ መጥቷል::


የመማር ማስተማር ግብዓቶች እጥረት ማለትም በብዙ የሀገሪቱ ክፍሎች የመማሪያ መፃህፍት፣ ላብራቶሪዎች እና ቤተ-መጻሕፍት እጥረት አለ። ታዲያስ ተማሪዎች ያለ በቂ ግብዓት እንዴት ውጤታማ ሊሆኑ ይችላሉ?

ከመሰረተ ልማት አንፃር ትምህርት ቤቶች ለትምህርት ምቹ ናቸው ወይ? በክፍል ውስጥ የተማሪዎች ቁጥር መጨናነቅ፣ የንፅህና መጠበቂያ ስፍራዎች እጥረት እና ሌሎች መሰረተ ልማታዊ ችግሮች በውጤቱ ላይ የራሳቸውን አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳረፋቸው አይቀርም። ለዚህም ነው አሁን ''አለፉ" ከተባሉትም ያለፉት ከሺህ በላይ የመንግስት ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ሳያሳልፉ በተሻለ አፈፃፀም የግል ትምህርት ቤቶችና የመንግስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች ልያሳልፉ የቻሉት::

በእውነቱ ትምህርቱን የሚመሩ ግለሰቦች በትውልዱ ላይ ከፍተኛ ሥነ-ልቦናዊ ጉዳት እያስከተሉ ከመሆናቸውም ባለፌ እያስከተሉት ያለው ማህበራዊ ቀውስ ቀላል አይደለም:: ይህ ውድቀት በተማሪዎችና በቤተሰቦቻቸው መካከል ከፍተኛ ውጥረት ይፈጥራል። ወላጆች ለልጆቻቸው የወደፊት እጣ ፈንታ ስጋት ሊገባቸው ይችላል።

በመሆኑም ይህ የፈተና ውጤት ከመንግስት እና ከትምህርት አመራሮች ትልቅ ኃላፊነትን ይጠይቃል። ተማሪዎቹ በብዛት የወደቁት ለምንድን ነው? የሚለው ጥያቄ በግልፅና በሙያዊ መንገድ መመለስ አለበት።

መንግስት የችግሩን መንስኤ እና ዘላቂ መፍትሄ መቀየስ ያስፈልጋል። ይህ ማለት በትምህርት መሰረተ ልማትና ጥራት ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ማድረግ ማለት ነው። በተለይም የተማሪ ምዘና በፈተና ብቻ ከመታጠር ይልቅ ተለዋዋጭነት ያለው የትምህርት ስርዓት መከተል ያስፈልጋል:: ፈተናው ብቻ የተማሪዎችን ዕውቀት መመዘኛ መሆን የለበትም። የትምህርት ስርዓቱ የተማሪዎችን የችሎታና የፍላጎት ልዩነት ከግምት ውስጥ ያስገባ መሆን አለበት። ምክንያቱም
ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች በየዓመቱ ወድቀው የትምህርት ምህዳሩን ለቀው መውጣታቸው የራሱ የሆነ የሀገር የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄን ያስነሳል።

ይህ ውጤት የትምህርት ስርዓቱን የውድቀት ማሳያ ብቻ ሳይሆን፣ በሐገር መፃዕ ዕድል ላይ የተቃጣ ትልቅ አደጋ እንደሆነ ማሰብ ይገባል። አለበለዚያ፣ በአመታት በኋላ ሀገርን የሚመራ ብሩህ ትውልድ የማጣት አደጋ ያንዣብብብናል።

የሕዳሴው ግድብ፡ በኃይለ ሥላሴ የታሰበ፣ በመለስ ዜናዊ የተጀመረ፣ በአብይ አህመድ የተጠናቀቀ
28/08/2025

የሕዳሴው ግድብ፡ በኃይለ ሥላሴ የታሰበ፣ በመለስ ዜናዊ የተጀመረ፣ በአብይ አህመድ የተጠናቀቀ

27/08/2025

እዚያ ማዶ--ይሰማል ወይ?!

በቁጥር የበዙ ግለሰቦች እና ቡድኖች የፖለቲካውን መስክ ለመቆጣጠር እና የተወሰኑ አላማዎችን ለማራመድ ዲጂታል መድረኮችን እየተጠቀሙ እንደሆነ የሶሻል ሚድያ ስልቶች ትንተና ያሳያል:: ይህ ትን...
26/08/2025

በቁጥር የበዙ ግለሰቦች እና ቡድኖች የፖለቲካውን መስክ ለመቆጣጠር እና የተወሰኑ አላማዎችን ለማራመድ ዲጂታል መድረኮችን እየተጠቀሙ እንደሆነ የሶሻል ሚድያ ስልቶች ትንተና ያሳያል:: ይህ ትንተና ከሐገር አቀፍ እስከ አካባቢያዊ ፍላጎት ያላቸውን ማሕበራዊ ሚድያን መሠረት ያደረጉ የፕሮፓጋንዳ ማሰራጫዎችን የዳሰሰ ሲሆን የአብዛኛዎቹ ገፆች ፕሮፓጋንዳ ለማሰራጨት የሚጠቀሙበት ስልታዊ እና ዘዴያዊ አቀራረብ በጣም አሳሳቢ ገፅታ ያለው ሆኖ ታይቷል።
በሐገር አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ እና ብዙ ተከታይ ያሏቸው አንዳንድ ግለሰቦች እና በእነሱ የሚመሩ የማሕበራዊ ሚድያዎች ፕሮፓጋንዳ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ላይ ባለው ከፍተኛ ትኩረት የሚታወቅ ነው። ይዘቱ የእርሳቸውን እያንዳንዱን እንቅስቃሴ፣ ያለፈውን፣ የአሁኑን እና የወደፊቱን፣ እንዲሁም ስሜታቸውን እና ህዝባዊ እንቅስቃሴዎችን በተመለከቱ ማጣቀሻዎች የተሞላ ነው። ይህ ስልት የዘፈቀደ ትችት አይደለም፤ ይልቁንስ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ተቀባይነት ለመሸርሸር አልፎም በራሳቸው ፓርቲ ውስጥም ጭምር አለመተማመንን ለመፍጠር ነው።

የዎላይታ አንቂ ነን ባዮች ሚዲያ ገጾችም ተመሳሳይ የሆነ ነገር ግን ደግሞ የበለጠ አካባቢያዊ የሆነ ስልት ይጠቀማሉ:: ፕሮፓጋንዳውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር /ፕሬዝዳንት ላይ ያነጣጠረ ያደርጉታል። የገጾቹ ዋና ስልት በአካባቢያዊ፣ በአንድነት-አላማዊ፣ እና አግላይ አመለካከት ላይ የተመሰረተ ሆኖ የዎላይታ ፍላጎት በክልሉ ውስጥ ከሌሎች ሁሉ ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል የሚለውን ሀሳብ ያራምዳል። ይህ ትረካ በክልሉ ውስጥ ፍትሃዊ ልማት እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ያለውን እውነታ የሚያዛባ አስተሳሰብ ነው። የዎላይታ ህዝብ እንደተገለለ፣ እንደተረሳ እና ችላ እንደተባለ አድርጎ ያሳያል - ይህም ሆን ተብሎ የተፈጠረ እና አሳሳች አቀራረብ ነው።

የዎላይታ ሚዲያዎች ጥቃት በብቸኝነት በጋሞ ተወላጅ በሆኑ ጠንካራ አመራሮች በተለይም ደግሞ በክልሉ ፕሬዝዳንት ላይ ያተኩራል። ይህ ግላዊ እና ብዙ ጊዜ አጥላሽ የሆነ አቀራረብ ለፕሮፓጋንዳ ኃይለኛ መሳሪያ ነው። ይህም የሚከተሉትን ለማድረግ ያገለግላል፦

1. ስልጣን ላይ ያለውን ግለሰብ ህጋዊነት ማሳጣት፣ ይህም የሚመራውን አጠቃላይ አስተዳደር ለማፍረስ ቀላል ያደርገዋል።

2. የፖሊሲ ልዩነቶችን እንደ ግላዊ ክህደት ወይም የውጭ ቡድን (የጋሞ ብሄረሰብ) ጭቆና አድርጎ በማቅረብ የጎሳ ውጥረቶችን ማቀጣጠል።

3. የዎላይታ ህዝብ በክልሉ አስተዳደር ሰለባ እንደሆነ አድርጎ የሚያሳይ ግልጽ "እኛ እና እነሱ" ትረካ መፍጠር፣ ይህም ክልሉ በአንድ ብሄረሰብ ፍላጎት ቁጥጥር ስር ነው ብሎ ይከሳል።

18/08/2025
አሁን ባለው ሁኔታ የጋሞ ብሄረሰብ የፖለቲካ አቅም ከሞላ ጎደል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል። ከዚህ ቀደም የጋሞ ፖለቲካ የተቀናጁና ተተኪ ፖለቲከኞችን  በማፍራት ባሕል የተቃኘ አልነበረም:: ዛሬ...
17/08/2025

አሁን ባለው ሁኔታ የጋሞ ብሄረሰብ የፖለቲካ አቅም ከሞላ ጎደል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል። ከዚህ ቀደም የጋሞ ፖለቲካ የተቀናጁና ተተኪ ፖለቲከኞችን በማፍራት ባሕል የተቃኘ አልነበረም:: ዛሬ ላይ ይህ አዝማሚያ በመቀየሩ የብሔሩ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ጥቅም በሌሎች ተፅዕኖ ስር የመውደቅ ልማዱን እየቀየረ መጥቷል:: የበቁ እና ተናባቢ ፖለቲከኞችን የማብዛቱ አካሄድ ብዙ ውጤቶች አፍርቷል:: ለአብነት ያህል የፖለቲካ ተሰሚነታችን እየጨመረ መጥቷል:: በዚህም የተነሳ በዞን; በክልል እና በፌዴራል መንግስት የሚደመጡ ፖለቲከኞችን ማፍራት ችለናል; በብቃትመደራደር እና በፖለቲካው መድረክ ላይ የበለጠ ስምና ክብር አግኝተናል::
የበቁ እና ተናባቢ ፖለቲከኞችን የማብዛቱ አካሄድ ጥቅሙ በዚህ ብቻ የሚበቃ አይደለም:: በተለይም ተግዳሮቶችን መቋቋም የሚችል ሕብረት እንዲኖረን የተጫወተው ሚና ቀላል የሚባል አይደለም:: በጋሞ ሕዝብ ላይ በተለይም አዲሱ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተቋቋመ በሇላ የተነዙ እና እየተነዙ ያሉ ክሶች ሰሚ ያጡት የሁሉም ሕብረት ስለተፈጠረ እንጂ በተዓምር ምክንያት አይደለም::
በመሆኑም አሁንም በተወሳሰበው ክልላዊ እና ሀገራዊ ሁኔታ ውስጥ የቡድን ግቦችን ለማሳካት የሚወሰደው አካሄድ የፖለቲካ ብስለት እና ውጤታማነትን የሚጠይቅ እንደመሆኑ መጠን እንደብሔር ተተኪን ማዘጋጀት እና ጠንካራ አጠቃላይ የፖለቲካ ግንባርን መፍጠር በሚያስችሉ ስራዎች ላይ በሰፊው መስራት ያስፈልጋል:: አንድ መሪ ቢወገድ ወይም ከሥልጣን ቢነሳ፣ ለመተካት ዝግጁ የሆኑ ሰዎች ልኖሩን ይገባል፣ ይህም ቀጣይነትን ያረጋግጣል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክትየአርባምንጭ በተፈጥሮ ስሪቷ ውብ ናት። በከተማዋ እየተካሄዱ ያሉ የልማት ሥራዎች በቅርቡ በጎበኘንበት ወቅት የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክትን ተመ...
16/08/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የአርባምንጭ በተፈጥሮ ስሪቷ ውብ ናት።
በከተማዋ እየተካሄዱ ያሉ የልማት ሥራዎች በቅርቡ በጎበኘንበት ወቅት የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክትን ተመልክተናል። ይኽ ሥራ በመጠነ ርዕዩ ግዙፍ በመሆኑ አርባምንጭ ታላላቅ ጉባኤዎችን እንድታስተናገድ ያስችላታል። ከዚህ ቀደም ከነበረን ምልከታ ሰፋ ብሎ የተከናወነው የኩልፎ ወንዝ ዳርቻ ልማት ለከተማዋ ልዩ መልኮች ተጨማሪ ገጽታ ፈጥሯል።

ወደ አርባምንጭ ጫካ አዳዲስ የመግቢያ መንገዶች የተሠሩ ሲሆን ለተራሮቹ፣ ለውሃው እና ለከባቢው ደኖች መዳረሻ በር ሆነዋል። እነዚህና ሌሎች ከአዲስ አበባ ውጪ ባሉ ብዙ ከተሞች ያየናቸው መሻሻሎች የተለያዩ አማራጮች እንዳሉን የሚያሳዩ ያልተጠቀምንባቸውን አቅሞቻችንንም የሚገልጡ ናቸው። ይኽ እድገት በጋራ ጥረቶቻችን ታላላቅ ነገሮችን እንደምናሳካ የሚያመለክት ግልጽ ምልክት ነው።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጋሞ ዱቡሻ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share