ጋሞ ዱቡሻ

  • Home
  • ጋሞ ዱቡሻ

ጋሞ ዱቡሻ Our page is dedicated to foster a "One Gamo."

We aim to share insightful information and engaging content through seminars, research, and publications, all designed to develop a cohesive ideology that aligns with the interests of the Gamo community.

18/08/2025
አሁን ባለው ሁኔታ የጋሞ ብሄረሰብ የፖለቲካ አቅም ከሞላ ጎደል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል። ከዚህ ቀደም የጋሞ ፖለቲካ የተቀናጁና ተተኪ ፖለቲከኞችን  በማፍራት ባሕል የተቃኘ አልነበረም:: ዛሬ...
17/08/2025

አሁን ባለው ሁኔታ የጋሞ ብሄረሰብ የፖለቲካ አቅም ከሞላ ጎደል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል። ከዚህ ቀደም የጋሞ ፖለቲካ የተቀናጁና ተተኪ ፖለቲከኞችን በማፍራት ባሕል የተቃኘ አልነበረም:: ዛሬ ላይ ይህ አዝማሚያ በመቀየሩ የብሔሩ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ጥቅም በሌሎች ተፅዕኖ ስር የመውደቅ ልማዱን እየቀየረ መጥቷል:: የበቁ እና ተናባቢ ፖለቲከኞችን የማብዛቱ አካሄድ ብዙ ውጤቶች አፍርቷል:: ለአብነት ያህል የፖለቲካ ተሰሚነታችን እየጨመረ መጥቷል:: በዚህም የተነሳ በዞን; በክልል እና በፌዴራል መንግስት የሚደመጡ ፖለቲከኞችን ማፍራት ችለናል; በብቃትመደራደር እና በፖለቲካው መድረክ ላይ የበለጠ ስምና ክብር አግኝተናል::
የበቁ እና ተናባቢ ፖለቲከኞችን የማብዛቱ አካሄድ ጥቅሙ በዚህ ብቻ የሚበቃ አይደለም:: በተለይም ተግዳሮቶችን መቋቋም የሚችል ሕብረት እንዲኖረን የተጫወተው ሚና ቀላል የሚባል አይደለም:: በጋሞ ሕዝብ ላይ በተለይም አዲሱ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተቋቋመ በሇላ የተነዙ እና እየተነዙ ያሉ ክሶች ሰሚ ያጡት የሁሉም ሕብረት ስለተፈጠረ እንጂ በተዓምር ምክንያት አይደለም::
በመሆኑም አሁንም በተወሳሰበው ክልላዊ እና ሀገራዊ ሁኔታ ውስጥ የቡድን ግቦችን ለማሳካት የሚወሰደው አካሄድ የፖለቲካ ብስለት እና ውጤታማነትን የሚጠይቅ እንደመሆኑ መጠን እንደብሔር ተተኪን ማዘጋጀት እና ጠንካራ አጠቃላይ የፖለቲካ ግንባርን መፍጠር በሚያስችሉ ስራዎች ላይ በሰፊው መስራት ያስፈልጋል:: አንድ መሪ ቢወገድ ወይም ከሥልጣን ቢነሳ፣ ለመተካት ዝግጁ የሆኑ ሰዎች ልኖሩን ይገባል፣ ይህም ቀጣይነትን ያረጋግጣል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክትየአርባምንጭ በተፈጥሮ ስሪቷ ውብ ናት። በከተማዋ እየተካሄዱ ያሉ የልማት ሥራዎች በቅርቡ በጎበኘንበት ወቅት የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክትን ተመ...
16/08/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የአርባምንጭ በተፈጥሮ ስሪቷ ውብ ናት።
በከተማዋ እየተካሄዱ ያሉ የልማት ሥራዎች በቅርቡ በጎበኘንበት ወቅት የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክትን ተመልክተናል። ይኽ ሥራ በመጠነ ርዕዩ ግዙፍ በመሆኑ አርባምንጭ ታላላቅ ጉባኤዎችን እንድታስተናገድ ያስችላታል። ከዚህ ቀደም ከነበረን ምልከታ ሰፋ ብሎ የተከናወነው የኩልፎ ወንዝ ዳርቻ ልማት ለከተማዋ ልዩ መልኮች ተጨማሪ ገጽታ ፈጥሯል።

ወደ አርባምንጭ ጫካ አዳዲስ የመግቢያ መንገዶች የተሠሩ ሲሆን ለተራሮቹ፣ ለውሃው እና ለከባቢው ደኖች መዳረሻ በር ሆነዋል። እነዚህና ሌሎች ከአዲስ አበባ ውጪ ባሉ ብዙ ከተሞች ያየናቸው መሻሻሎች የተለያዩ አማራጮች እንዳሉን የሚያሳዩ ያልተጠቀምንባቸውን አቅሞቻችንንም የሚገልጡ ናቸው። ይኽ እድገት በጋራ ጥረቶቻችን ታላላቅ ነገሮችን እንደምናሳካ የሚያመለክት ግልጽ ምልክት ነው።

ከሁሉም ጋር ተስማምቶ መኖር በጣም ጥሩ ነገር ነው። ከአንድ ጎረቤት ጋር ትንሽ ነገር ቢፈጠር፣ እርስዎ ችግር ፈጣሪ ነዎት ማለት አይደለም። ከጥቂት  ጎረቤትዎ ጋርም አለመግባባት ቢፈጠር፣ እን...
12/08/2025

ከሁሉም ጋር ተስማምቶ መኖር በጣም ጥሩ ነገር ነው። ከአንድ ጎረቤት ጋር ትንሽ ነገር ቢፈጠር፣ እርስዎ ችግር ፈጣሪ ነዎት ማለት አይደለም። ከጥቂት ጎረቤትዎ ጋርም አለመግባባት ቢፈጠር፣ እንደተለመደ ሊታይ ይችላል። ሆኖም፣ ከሁሉም ወዳጆችዎ ጋር ካልተግባቡ፣ ችግሩ ያለው ከሌሎች ጋር ሳይሆን ከእርስዎ ጋር ነው።

Ajora
11/08/2025

Ajora

10/08/2025

ለግንዛቤዎ
የሙስና ወንጀል

የሙስና ወንጀል ከባድ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ የሚያስከትል ወንጀል ነው። ይህንን ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት በሀገራችን ወንጀሉን ለመከላከል ህግ ከማውጣ በተጨማሪ ተቋማትን በማቋቋምም ወንጀሉን ለመቆጣጠር ልዩ ልዩ ጥረቶች ሲያደርግ ቆይቷል። ከዚህም ባሻገር የወንጀሉ ፈጻሚዎችን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ እና የተወሰደውን የመንግሰት እና የህዝብ ሀብት ለማስመለስ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። በዚህ አጭር ጽሁፍም በሙስና ወንጀሎች አዋጅ 881/2007 የተካተቱ የሙስና ወንጀሎች ምንነትን እና የሚያስከትሉትን የህግ ተጠያቂነት በአጭሩ እንመለከታለን፡፡

የሙስና ወንጀል ምንነት
እንደ አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት የቃሉ መሰረት ግእዝ ሲሆን ትርጉሙም ጥፋት፣ መበስበስ፣ መፍረስ፣ በመጥፎ ድርጊት መተዳደር ማለት ነው፡፡ በሌላ በኩል እንደ ታዋቂው አለማቀፍ ድርጅት ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ትርጉም ሙስና በአደራ የተሰጠን ስልጣን ለግል ጥቅም ማዋል ማለት ነው፡፡ ብላክስ ሎው የህግ መዝገበ ቃላትም ሙስና ከህጋዊ ሀላፊነት እና ከሌሎች ሰዎች ጥቅም በመጻረር ጥቅም ለማግኘት በማሰብ የሚፈጸም ድርጊት ነው በማለት ትርጉም ሰጥተውታል፡፡

የአገራችን ህግ ለሙስና ወንጀል መቋቋም መሰረታዊ የሆኑ ነጥቦችንም በማመልክት ስለ ሙስና ምንነት ያመለከተ ሲሆን ይሄውም በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 መሰረት ሙስና ወንጀል የሀሳብ፣ የህግ እና የድርጊት ፍሬ ነገሮችን ደንግጎ ይገኛል፡፡ የሀሳብ ክፍሉን ያየን እንደሆነ በአዋጁ ወንጀሎቹን የሚያቋቁሙ አንቀጾች ወንጀሉ የሚፈጸምበትን አላማ ሲገልጹ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት ወይም ሌላውን ሰው ለመጉዳት የሚፈጸሙ መሆናቸውን ይደነግጋሉ፡፡ በአዋጅ ቁጥር 881/07 አንቀጽ 3 ላይ ይሄው ተድንግጎ ይገኛል፡፡ የሙስና ተግባር መነሻው በቅጥርም ይሁን በሹመት የተገኘ መንግስታዊ ወይም ህዝባዊ ሀላፊነት ሲሆን ይህም የአዋጁ ዋነኛ ትኩረት ስለመሆኑ ከልዩ ልዩ ድንጋጌዎቹ መረዳት ይቻላል። ከዚህ ጋር ተያይዞ በአዋጁ አንቀጽ 4(2) ላይ የሙስና ወንጀልን አስመልክቶ ሰፋ ያለ ትርጉም እናገኛለን። በዚህም “ማንኛውም የመንግስት ወይም መንግስታዊ ድርጅት ሰራተኛ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የማይገባውን ጥቅም ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው መብት ወይም ጥቅም ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ በተሰጠው ሀላፊነት ወይም ተግባር ማድረግ የሚገባውን እንዳያደርግ ወይም ማድረግ የማይገባውን እንዲያደርግ ከሌላ ሰው ላይ ጥቅም የተቀበለ ወይም የጠየቀ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ጥቅም ለማስገኘት የተሰጠውን ስልጣን ወይም የህዝብ አደራ ያለአግባብ የተገለገለበት እንደሆነ፣ ጥቅም ለራሱ ለማገኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው መብት ወይም ጥቅም ላይ ጉዳት እንዲደርስ ለማድረግ በማሰብ ለመንግስት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ የማይገባ ጥቅም ለመስጠት ቃል የገባ፣ ያቀረበ፣ የሰጠ ወይም ለማቅረብ የተስማማ እንደሆነ ወይም በአግባቡ ለተፈጸመ ወይም በአግባቡ ለወደፊቱ ለሚፈጸም የመንግስት መስሪያ ቤት ወይም የመንግስት የልማት ድርጅት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሥራ የማይገባ ጥቅም ለማንኛውም ሰው የሰጠ ወይም ከማንኛውም የመንግስት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ የተቀበለ እንደሆነ በሙስና ወንጀል ፈፃሚነት ተጠያቂ ይሆናል” በማለት ሰፊ የወንጀል ድርጊቶችን አካቷል። ከዚህም እንደምንረዳው በሙስና ወንጀል ተጠያቂ ለመሆን ፈፃሚው የመንግሰት ሰራተኛ፣ የመንግሰት የልማት ድርጅት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ ወይም ተሿሚ መሆን እንዳለበት ነው። ከመንግሰት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛነት ባለፈም ሌሎች ሰዎች ከነዚሁ ሰዎች ጋር በመተባበር በነዚሁ ድርጅቶች ላይ የሙስና ወንጀል ከፈጸሙም የሚጠየቁበት የህግ አግባብ እንዳለ ከአዋጁ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች የምንረዳው ነው፡፡

የሙስና ወንጀል አይነቶች
በአዋጅ 881/2007 በርካታ የሙስና ወንጀል ተግባራት የተካተቱ ሲሆን ለዚህ አጭር ጽሁፍ ዓላማ ሲባል የተወሰኑትን ብቻ ለማሳያነት በሚከተለው አግባብ በአጭሩ እንመለከታለን።

በስልጣንን አላግባብ መጠቀም የሙስና ወንጀል

የተሰጠን የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ስልጣን አላግባብ መጠቀምን አስመልክቶ ህጉ የሚከተሉትን ዝርዝር ክልከላዎችን በግልጽ አስፍሯል። በዚህም “ማንኛውም የመንግስት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው ጥቅም ወይም መብት ላይ ጉዳት እዲደርስ ለማድረግ በማሰብ፣
• የተሰጠውን ሹመት፣ ስልጣን ወይም ሀላፊነት በግልጽ ተግባር ወይም በግድፈት ያለአግባብ የተገለገለበት እንደሆነ፣
• በግልፅ ከተሰጠው ስልጣን ወይም ሀላፊነት አሳልፎ የሠራ እንደሆነ ወይም
• ስልጣኑ ወይም ሀላፊነቱ የማይፈቅድለትን ጉዳይ በተለይም ስልጣን ወይም ሀላፊነት ሳይኖረው ወይም ከሥራው ከታገድ፣ ከተዛወረ፣ ከተሻረ ወይም ስልጣኑን ወይም ሀላፊነቱን ከተወ በኋላ የሰራበት እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ ከእንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እስራትና ከሶስት ሺ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአስር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራትና ከአስር ሺ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እንደሚቀጣ ተመላክቷል። ይህ እንዳለ ሆኖ የተፈጸመው ወንጀል ያደረሰው የጉዳት መጠን፣ የወንጀል ፈፃሚው ሀላፊነት ወይም በድርጊቱ የተገኘው ጥቅም ግምት ውስጥ ገብቶ እንደወንጀሉ ክብደት ቅጣቱ ከሰባት እስከ አስራ አምስት ዓመት እስራት እና ከአስር ሺ እስከ አንድ መቶ ሺ ብር በሚደርስ መቀጮ ያስቀጣል፡፡

እነዚህ ግምት ውስጥ የሚገቡ ነገሮች በተደራረቡ ጊዜ እንደነገሩ ሁኔታ የእስራት ቅጣቱ እስከ ሀያ አምስት ዓመት የገንዘብ መቀጮው ደግሞ እስከ ሁለት መቶ ሺ ብር ሊደርስ ይችላል።

ጉቦ መቀበል (Bribery)

ሌላኛው በመንግስት ወይም በህዝባዊ ድርጅቶች ሰራተኞች የሚፈጸም የሙስና ወንጀል ጉቦ መቀበል ሲሆን በአዋጅ 881/07 አንቀጽ 10 ላይ ወንጀሉን የሚያቋቁሙ ፍሬ ነገሮች ተዘርዝረዋል። በዚህም “ማንኛውም የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ በሀላፊነቱ ወይም በሥራ ግዴታው ማድረግ የማይገባውን ለማድረግ ወይም ማድረግ የሚገባውን ላለማድረግ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ጥቅም እንዲሰጥ የጠየቀ፣ የተቀበለ ወይም የተስፋ ቃል የተቀበለ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እስራትና ከሶስት ሺ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአስር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራትና ከአርባ ሺ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል።

እዚህም ላይ የወንጀል ፈፃሚው ሀላፊነት ወይም የስልጣን ደረጃ፣ ዓላማ፣ የተገኘው ጥቅም ከፍተኛነት ወይም የደረሰው ጉዳት ከፍተኛነት ግምት ውስጥ ገብቶ የእስር ቅጣቱ ከሰባት እስከ አስራ አምስት ዓመት ጽኑ እስራት ከፍ ሊል ይችላል። በተጨማሪም የገንዘብ ቅጣቱ እንዲሁ ከአስር ሺ እስከ መቶ ሺ ሊደርስ እንደሚችል ተመላክቷል። እንዲሁም እነዚህ ግምት ውስጥ የሚገቡ ነገሮች በተደራረቡ ጊዜ ቅጣቱ እስከ ሀያ አምስት ዓመት ጽኑ አስራት እና እስከ ሁለት መቶ ሺ ብር መቀጮ ድረስ ከፍ ሊል ይችላል።

የማይገባ ጥቅም መቀበል (Acceptance of Undue advantage)

በአዋጅ ቁጥር 881/07 አንቀጽ 11 መሰረት ማንኛውም የመንግስት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ በተሰጠው ሀላፊነት መሰረት ማድረግ የሚገባውን ተግባር ለማከናወን ሲል ይህንኑ ተግባር ከመፈጸሙ በፊት ወይም ከፈጸመ በኋላ ጥቅም እንዲሰጠው የጠየቀ፣ ያገኘ ወይም የተስፋ ቃል የተቀበለ እንደሆነ እንደነገሩ ሁኔታ ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እስራትና ከሶስት ሺ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከሰባት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራትና ከሃያ ሺ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል። እንዲሁም በተፈጸመው ወንጀል የተገኘው ጥቅም ከፍተኛነት፣ የጥፋተኛው የኋላፊነት ወይም የስልጣን ደረጃ የወንጀሉን አፈፃጸም ከባድ አድርጎት እንደሆነ የእስር ቅጣቱ ከአምስት እስከ አስራ አምስት ዓመት የሚደርስ ጽኑ እስራትና ከአምስት ሺ በማያንስ ስልሳ ሺ ብር በማይልጥ የገንዘብ መቀጮ የሚቀጣ ይሆናል።

ሥራን በማይመች ሁኔታ መምራት
በዚህ የሙስና ወንጀል ዘርፍ የሚወድቁት ድርጊቶች ደግሞ በአዋጅ ቁጥር 881/07 አንቀጽ 13 ስር እንደተመላከተው ማንኛውም የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በማሰብ ስልጣኑን ወይም ሀላፊነቱን ተጠቅሞ
• በንግድ ወይም በሌላ ሥራ፣ በግዢ ወይም በሽያጭ ወይም ከሚያከናውነው ሥራ ጋር በተያያዘ በማናቸውንም የሥራ ግንኙነት ማንኛውም ጥቅም የወሰደ ወይም ይህንን ጥቅም የሚያገኝበትን ውል የተዋዋለ ወይም ሌላ ዘዴ የፈጠረ
• አግባብ ባለው ባለስልጣን ከተወሰነው በላይ ዋጋ የእቃ ማቅረብ ውል፣ የሥራ መቋረጥ፣ ወይም ማናቸውንም የሥራ ውል የተዋዋለ ወይም በውል ከተመለከተው ዕቃ ወይም አገልግሎት ውጭ የተቀበለ እንደሆነ እንዲሁም
• በሥራው ምክንያት በአደራ የተቀበለውን ወይም ሊጠብቀውና ሊከላከለው የሚገባውን የመንግስት መስሪያ ቤት፣ የልማት ድርጅት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ጥቅም የሚጎዳ ተግባር በማናቸውም ዘዴ የፈጸመ እንደሆነ
እንደነገሩ ሁኔታ ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እስራትና ከሶስት ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ወይም ከአስር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራትና ከመቶ ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ የሚቀጣ ይሆናል። የጥፋተኛው ሀላፊነት ወይም የስልጣን ደረጃ፣ ግዴታው የተጣሰበት ዓላማ፣ የተገኘው ጥቅም ከፍተኛነት ወይም የደረሰው ጉዳት ከፍተኛነት ግምት ውስጥ ገብቶ ቅጣቱ ከሰባት አመት እስከ አስራ አምስት አመት የሚደርስ ፅኑ እስራት እና ከአስር ሺ ብር በማያንስ እና ከሁለት መቶ ሺ የማይበልጥ መቀጮ ሊደርስ ይችላል፡፡ እንዲሁም እነዚህ ግምት ውስጥ የሚገቡ ነገሮች በተደራረቡ ጊዜ ቅጣቱ ከአስር አመት እስከ እስከ ሀያ አምስት ዓመት ጽኑ አስራት እና ከሀያ ሺ ብር እስከ አራት መቶ ሺ ብር የሚደርስ መቀጮ ይሆናል።

ከባድ እምነት ማጉደል
እምነት መጉደል አስቀድሞ የተሰጠን አምነት አለአግባብ መጠቀምን ያመለክታል፡፡ በዚህም ከባድ እምነት ማጉደል ሲባል በአዋጅ 881/07 አንቀጽ 31 መሰረት ያልተገባ ብልጽግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ የመንግሰት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ ለአንድ ለተወሰነ አገልግሎት ወይም በአደራ የተሰጠውን ዋጋ ያለውን እቃ ወይም ገንዘብ በሙሉ ወይም በከፊል ለራሱ ማድረግ፣ ለሌላ ሰው ማድረግ፣ መውሰድ መሰወር፣ ለራሱ ወይ ለሌላ ሰው አገልግሎት ማዋል እና መሰል ድርጊቶችን መፈጸም ሲሆን ከሶስት እስከ ሰባት አመት ጽኑ እስራት እና ከአስር ሺ ብር እስከ ሀምሳ ሺ ብር መቀጮ እንደሚያስቀጣ ደንግጎ ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል የተገኘው ጥቅም ከፍተኛነት፣የጥፋተኛው የስልጣን ደረጃ፣የደረሰው ጉዳት መጠን ከፍተኛነት እየታየ ቅጣቱ ከሰባት እስከ ሀያ አምስት አመት ጽኑ እስራት እና ከሀምሳ እስከ አንድ መቶ ሺህ ብር መቀጮ ድረስ ሊቀጣ ይችላል።

ከባድ አታላይነት

በአዋጁ አንቀጽ 32 መሰረት ማንኛውም የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ ተገቢ ያልሆነን ብልጽግና ለራሱ ማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ አሳሳች የሆኑ ነገሮችን በመናገር፣ የራሱን ማንነት በመሰወር፣ መግለጽ የሚገባውን ነገር በመደበቅ ወይም የሌላውን ሰው የተሳሳተ እምነት ወይም ግምት በመጠቅም፣ በማድረግም ሆነ ባለማድረግ ሌላውን ሰው በማታለል የተታለለው ሰው የራሱን ወይም የሌላውን ሰው የንብረት ጥቅም የሚጎዳ ድርጊት እንዲፈጽም ያደረገው ከሆነ ከሶስት እስከ አስር አመት በሚድርስ ጽኑ እስራት ይቀጣል፡፡ በሌላ በኩል የተገኘው ጥቅም ከፍተኛነት፣ የጥፋተኛው የስልጣን ደረጃ፣ የደረሰው ጉዳት መጠን ከፍተኛነት እየታየ ቅጣቱ ከአምስት እስከ አስራ አምስት አመት ጽኑ እስራት እና ከአስር እስከ አንድ መቶ ሺህ ብር መቀጮ ሊቀጣ ይችላል።

ማጠቃለያ

በጥቅሉ የሙስና ወንጀል ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሶስተኛ ሰው ለማስገኘት ታስቦ በመንግስት፣ በመንግስት የልማት ድርጅት እና በህዝባዊ ድርጅቶች ላይ የሚፈጸም ወንጀል ሲሆን በመንግስት እና ህዝብ ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርስ ወንጀል ነው፡፡ በመሆኑም ወንጀሉን ለመከላከልና ተፈፅሞም ሲገኝ አጥፊዎችን ለህግ በማቅረብ ረገድ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል፡፡

06/08/2025

ድንገተኛ የልብ ሕመም እና መከላከያ መንገዱ

የልብ ህመም በተለያየ መንገድ እንደሚመጣ የሚናገሩት የ'Heart Attack Ethiopia ዋና ስራ አስኪያጅና የውስጥ ደዌ ሀኪም ዶክተር ኦፕስኔት መርዕድ፣ በዋነኛነት በደም ግፊት አማካኝነት እንደሚከሰት ይገልፃሉ፡፡

ደምግ ግፊት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተለመደ የጤና እክል ነው ያሉት ዶክተር ኦፕሲኔት፣ በአፍሪካ 50 በመቶ የሚሆነው ማህበረሰብ የዚህ ችግር ተጠቂ መሆኑን ይናገራሉ፡፡

ከእነዚህ ውስጥ ችግሩ እንዳለባቸው የሚያውቁት 27 በመቶ የሚሆኑት ብቻ መሆናቸውን ያብራራሉ፡፡

ከእነዚህ ውስጥም ደግሞ መድሃኒት የሚወስዱት 18 በመቶ የሚሆኑት ብቻ እንደሆኑ ይገልፃሉ፡፡
ሌላው ለድንገተኛ የልብ ህመም መንስዔ የሚሆኑት ኮሌስትሮል፣ ስኳር አብዝቶ መጠቀም፣ ጮማ ስጋ ማብዛት፣ ነጭ ዳቦ፣ ፓስታ አብዝቶ መጠቀም እና ስፖርታዊ እንቅስቃሴ አለማድረግ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ድንገተኛ የልብ ህመምን ለመከላከልና ህይወትን ለማዳን፣ ወቅቱን የጠበቀ ቅድመ ጤና ምርመራ መለመድ እንዳለበት ዶክተር ኦፕሲኔት ይመክራሉ።

በኢትዮጵያ ለመከላከል ሳይሆን ለመታከም ወደ ጤና ተቋማት መሄድ የተለመደ መሆኑን ጠቅሰው፣ በሰለጠነው ዓለም ቅድመ መከላከል ላይ በትኩረት እንሚሰራ አስረድተዋል።

ቅድመ- ጤና ምርመራ፣ ተጓዳኝ ህመሞችን በወቅቱ መታከም፣ አትክልትና ፍራፍሬን መመገብ እንዲሁም ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ ትኩረት መስጠት ድንገተኛ የልብ ህመምን ለመከላከል ሁነኛ መፍትሔ መሆኑን አስምረውበታል።

04/08/2025

"The same one who mistreated you will end up needing you.
That’s how life humbles people. The very person who once dismissed your presence, overlooked your efforts, and made you feel like you were too much—will one day find themselves in a place where they miss the very energy they pushed away. They’ll remember the way you loved without conditions, supported without being asked, and stayed loyal even when they gave you every reason to walk away.

But by then, you won’t be the same. You’ll have grown tired of breaking yourself into pieces to build others. You’ll have outgrown the need to chase validation from someone who couldn’t even see your value when you were right in front of them. You’ll realize you were never asking for too much—you were just asking the wrong person.

And when they return, it won’t be out of love. It’ll be out of lack. Lack of care, peace, and real connection—the kind you brought so naturally. But your healing will have taught you the difference between being needed and being respected. You’ll smile, not with bitterness, but with clarity.

Because sometimes the apology never comes. Sometimes the closure is in your own growth. And sometimes the most powerful move is walking away and letting them sit with the silence they created.

They’ll need you. But you won’t need them.

03/08/2025

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጋሞ ዱቡሻ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share