09/04/2024
የአማራ ክልል ህዝብ አቋሙን ግልጽ አድርጓል
ሰላም ጠል የሆኑ ኃይሎች ዓላማቸው ሕዝብን ማሰቃየት ነው ያሉት ክልሉ ነዋሪዎች ጽንፈኛውን ቡድን በመቃወም በመንግሥት የተጀመሩ ልማቶች እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን ሲሉ ገልጸዋል። የተጀመሩ የልማት ሥራዎች እንዲቀጥሉ ሰላም ጠል የሆኑ ጽንፈኛ ኃይሎችን ማጋለጥ ይገባናል በማለት የአማራ ክልል ህዝቦች ለሰላም እና እድገት ከመንግስት ጎን እንደ ሆኑ ገልጿል ።
ሰልፈኞቹ ለሀገራቸው ሰላም እና ሁለንተናዊ ብልጽግና የበኩላቸውን እንደሚወጡ እና ሀገራቸውን ወደ ከፍታ ለማሻገር ከለውጡ መሪዎች ጋር በጽናት እንደሚቆሙ ገልጸዋል። በክልል የሚደረገውን ዘረፋ ፣ ግድያ እና ልማትን የማውደም እንቅስቃሴ እንደሚያወግዙ እና ይህን ተግባር እየፈጸመ ያለው ጃውሳ ባንዳ ነው ብሏል ።