Wetatu Alegn

Wetatu Alegn Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Wetatu Alegn, Digital creator, .

17/04/2024

ስለ ሰላም እንዘምራለን፤ ደግሞም እንሰራለን!

የዴሞክራሲ ምህዳሩን በማስፋት ሲንከባለሉ የመጡ እና በየጊዜው ቅርፃቸውን የሚቀያይሩ ሳንግባባ ያደርንባቸውን አገራዊ ጉዳዮች ጭምር ህዝባችንን በማሳተፍ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት በመስጠት አገራዊ አንደነታችንን በማይናወጥ መሰረት ላይ ለመገንባት ከለውጡ ጀምሮ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።

በእሳት ተፈትኖ ነጥሮ እየወጣ ያለው የለውጡ መሪ መንግስታችን እና ፓርቲያችን "ኢትዮጵያ አበቃላት" ያስባለውን ከውጭም ከውስጥም የተደቀነባትን ምናልባትም በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ውስብስብ ፈተና ህዝቡን ከጎኑ አሰልፎ እንደ ጉም ከመግፈፉ በተጨማሪ የቆመለትን ኢትዮጵያን የማበልፀግ ዓላማ ለአፍታም ሳይገታ አጠናክሮ አስቀጥሏል።

በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያን መለወጥ የማይመኙ፣ በልፅጋ ማየት የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ ፀረ-ሰላም ሀይሎች ፍላጎታቸው የሚሳካው እርስ በእርስ ስንጣላ እንጅ ስንፋቀር ባለመሆኑ 24 ሰዓት በታዛቢነት ከዳር ሆነው የሚመለከቱትን የጦርነት ፊሽካ መንፋታቸውንና ከእሳት ላይ ቤንዚን ማርከፍከፋቸውን አላቆሙም።

ኢትዮጵያዊያን የጦርነትን እና የግጭትን አስከፊነት በየጊዜው የህይወት መስዋዕትነት እና የንብረት ውድመት ውድ ዋጋ እያስከፈለን እያለፍንበት ያለ የአስከፊ ታሪካችን ገፅታ ጭምር እንጂ ከርቀት የምንሰማው ጉዳይ አይደለም።

የግጭት አትራፊዎች ያልተቋረጠ የገቢ ምንጭ በሬ ወለደ የሚሉ የሀሰት ወሬዎች በመሆናቸው ሳያረጋግጡና ሳያመዛዝኑ የሚያዳምጡ ግለሰቦችን ወደ እኩይ መረባቸው ለማስገባት ጠዋት ማታ ያሰራጫሉ።

ከሀሰተኛ መረጃዎች ራስን መጠበቅ እንዲሁም በዘመኑ የሚዲያ አማራጮች ውሸታቸውን ማጋለጥም ከእያንዳንዳችን ይጠበቃል።

የአገር ዋልታ የሆነው መከላከያ ሰራዊታችን እና ሌላውም የፀጥታ ሀይላችን አስተማማኝ ሰላማችንን ለማረጋገጥ ለሚወስዳቸው አጥፊዎችን ወደ ህግ የማቅረብና ህግን የማስከበር እርምጃዎች እንደተለመደው ደጀንነታችንና ድጋፋችንን ማጠናከርም ይገባል።

የግጭት አትራፊዎች ስለሰላም ማውራትን፣ ስለሰላም ነገሮችን በትዕግስት ማለፍን እንዲሁም የሀይማኖት አባቶችን የሰላም ምክር እንደ ሞኝነት ቢቆጥሩትም የኢትዮጵያን አስተማማኝ ሰላም ለማረጋገጥ እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልፅግናዋን እውን ለማድረግ ቆርጠን በመነሳታችን ዛሬም ሆነ ነገ ስለ ሰላም እንዘምራለን፤ ደግሞም እንሰራለን!

17/04/2024

በኮሪደር ልማት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት ተደርገዋል::

በኮሪደር ልማት ምክንያት ከመጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከ4 ኪሎ እስከ ፒያሳ ያለው መስመር የራስ መኮንን ድልድይ እየተሰራ በመሆኑ ተዘግቶ የነበረው መንገድ በከፊል ክፍት ተደርገዋል፡፡

በዚህም መሰረት፡-

• ከደጃች ውቤ በአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ

• ከባሻወልዴ ችሎት በቱሪስት ሆቴል ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

• ከዳኑ ሆስፒታል እስከ ቱሪስት ሆቴል በመውጣት ወደ ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

•ከአራዳ መስተዳደር ወደ ዳኑ ሆስፒታል መውረጃ በአንድ አቅጣጫ ብቻ አሽከርካሪዎች መጠቀም የሚችሉ እና ልዩ ልዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ በመሆኑ ለአጭር ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪን አቁሞ መሄድ ፍፁም ክልክል መሆኑን አሽከርካሪዎች ተገንዝበው የትራፊክ ምልክትና ማመላከቻዎች አክብረው እራሳቸውንና ሌሎችን ከትራፊክ አደጋ እየጠበቁ መንገዱን መጠቀም እንደሚችሉ እናስታውቃለን::

17/04/2024
14/04/2024

ሰላማችንን በመጠበቅና ጽንፈኝነትን በጋራ በመታገል የሀገራችንን ብልፅግና እውን እናድርግ!

ሰላምን እውን የማድረግም ሆነ ሰላምን የማጣት ወሳኙ እኛው ራሳችን ነን። ዛሬ በእጃችን ያለው ሰላም ነገም በአስተማማኝ ደረጃ ሊቀጥል የሚችለው ሁሉም ለሰላም ተግቶ ሲሰራና ሰላምን የሚያፈርሱ ነገሮችን ያለ ምህረት ሲታገል ብቻ ነው፡፡

ሰላምን ከሚያደፈርሱ ነገሮች አንዱ ደግም ጽንፈኝነት ነው። ጽንፈኝነት ከመደመር ሳንካዎች ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ሲሆን የራስን ፍላጎት በሌሎች ላይ የመጫን ወይም የማስገደድ አባዜ የተጠናወተው ጫፍ የሚይዝ የኋላቀርነት መገለጫ ነው፡፡

መነሻው በተናጠል ፍላጎቷቶች ላይ የሚመሰረትና የሌሎችን መስተጋብሮች ለመቀበል የሚቸገር ነው።

ኢትዮጵያ ደግም ብዝሃ ሀሳብ፣ ብዝሃ ባህል፣ ብዝሃ ቋንቋና ብዝሃ ሃይማኖት ባለቤት ናት።

በመሆኑም የአዲሱ የብልፅግና እሳቤ መሰረት የሚያደርገው የመደመር ትውልድ አስተሳሰብ ትርክቱ የትስስር ትርክት፣ የአብሮነት ትስስር ነው፤ በማናቸውም የፖለቲካ፣ ማህበራዊ፣ የሀገር ደህንነትና ውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች እኔም፣ እኛም፣ በአጠቃላይ ሁላችንም በጋራ መጠቀም አለብን ማለት መቻል አለብን።

በመሆኑም ከጽንፈኝነት በመራቅ፣ ሰላማችንን መጠበቅ እና መንከባከብ አማራጭ የሌለው የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ነው።

እኛ ኢትዮጵያዊያን ሀገራችን ሰላም ከሆነች የምንናፍቀውን ብልጽግና በአጭር ጊዜ እውን ከማድረግ የሚከለክለን ምድራዊ ሀይል አይኖርም።

ሰላማችንን በመጠበቅና ጽንፈኝነትን በጋራ በመከላከል የሀገራችንን ብልፅግና እውን እናድርግ!

14/04/2024

ሰላም፣ ይቅርታ እና ፍቅር ዕሴቶቻችን ናቸው፡፡ በፍቅር መደመርና በይቅርታ መሻገር ዋናው መርሐችን ነው፡፡ ታሪካዊ ስብራቶችን መጠገንና ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ማጽናት ራእያችን ነው፡፡ መደመር መንገዳችን፣ ብልጽግና መዳረሻችን ነው፡፡

እነዚህ ዕሴቶች በለውጥ ዘመን የሚገጥሙንን ተግዳሮቶች የምንወጣባቸውና እስከቀጣዩ መዳረሻ የምንዳረስባቸው ናቸው፡፡ ያም መዳረሻ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና ነው፡፡

የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

12/04/2024
12/04/2024

በፅንፈኛው የፋኖ አመራርና አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱን ፖሊስ ገለፀ፡፡

የሽብር ተግባር ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የፅንፈኛው አመራርና አንድ የቡድኑ አባል ላይ እርምጃ መውሰዱንና አንደኛውን ደግሞ መቆጣጠሩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

የፅንፈኛው ቡድን አባላት የሆኑት ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣ አቤኔዜር ጋሻው አባተ እና ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ በከተማችን አዲስ አበባ የሽበር ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ ይዘው እየተንቃሰቀሱ መሆኑን የፀጥታ አካላት ክትትል ሲያደርግባቸው መቆየቱ ተጠቅሷል።

አሸባሪዎቹ የሽብር ተግባራቸውን ሳይፈፅሙ በቁጥጥር ስር ለማዋል የፖሊስ አባላት እንቅስቃሴ እያደረጉ ባለበት ሁኔታ ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሚሊኒዬም አዳራሽ አካባቢ ፅንፈኞች እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ ባለመሆናቸውና ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው የፅንፈኛው ፋኖ መሪ ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት ፅንፈኛው ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ በተኩስ ልውውጡ መሃል መገደሉን ፖሊስ ገልጿል።።

አቤኔዘር ጋሻው አባተ የተባለው የቡድኑ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉንም አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ፅንፈኞቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገ እንቅስቃሴ ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ሲቆስሉ አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ግለሰብ ፅንፈኞቹ በመኪናቸው እንዲጭኗቸው ቢያስገድዷቸውም ግለሰቡ አልተባበር በማለታቸው በፅንፈኛው አባላት መገደላቸውን የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ በቀጣይ የደረሰበት ዝርዝር መረጃ አሳውቃለሁ ብሏል።

12/04/2024

የተቀናጀ ልማት

ዛሬ ዕለተ አርብ ሚያዝያ 04/2016 ዓ.ም ምሽት ይጠብቁ።

05/04/2024

ብልፅግና - የአሁኑም የመጪውም ትውልድ ፓርቲ !

ኢትዮጵያችን የበርካታ ብሄር ብሄረሰቦች ማንነት፣ ቋንቋ፣ እምነት፣ ባህል ህብርም መገኛም ናት፤ እጅግ በጣም ሰፊ ብዝሃነት ያለባት ድንቅ ሀገር ናት።

የብዝሃነት ፀጋዋ ነገ ሁለንተናዊ ብልፅግና የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት የሚያስጎመጅ ሰናይ ዕድል እንጂ፣ ስጋቷ ሊሆን በፍፁም አይገባም።

መሪ ፓርቲያችን ብልፅግናም ይህንን መልካም ዕድል በመጠቀም በአንድ በኩል ብዝሃነታችንን በአግባቡ የሚያስተናግድበትን ፣በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራዊ አንድነታችንን የሚያረጋግጥበትን እውነተኛ ህብረ ብሄራዊ ፌደራላዊ ስርዓት ለመገንባት እየሰራ ይገኛል።

ይህ ደግሞ ዛሬን ለማለፍ ብቻ ሳይሆን የነገውን ሰላምና አንድነት፣ እኩልነትና ብልፅግና ሰምረውልን እንደ አገርና ህዝብ ለመኖር ያስችለናል፤ ለዚህም ነው ብልፅግና - የአሁኑም የመጪውም ትውልድ ፓርቲ ነው የምንለው።

05/04/2024

መንግሥት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ሰላም ለማስፈን የተቀናጀ ርምጃ በመውሰዱ ክልሎቹ ወደ አንጻራዊ ሰላም ተመልሰዋል፡- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

መንግሥት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ሰላም ለማስፈን የተቀናጀ ርምጃ በመውሰዱ ክልሎቹ ወደ አንጻራዊ ሰላም እና መረጋጋት መመለሳቸውን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፣ መንግሥት ያሉ ችግሮችን በሰላም እና በድርድር ለመፍታት ምንጊዜም ዝግጁ የነበረ ቢሆንም የሰላም አማራጩ ተቀባይነት በማጣቱ ሕግ በሚፈቅድለት አግባብ ሕግ ወደ ማስከበር ርምጃ ገብቶ ሲሠራ መቆየቱን ሚነስትሩ ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት በአብዛኞቹ የአገሪቱ አካባቢዎች አንጻራዊ ሰላም እና መረጋጋት መፈጠሩን ጠቁመው፣ ይህንንም ይበልጥ ማጽናት ይገባል ብለዋል።

በአማራ ክልል የተጀመረው ሕግ የማስከበር ሥራ ውጤታማነቱን ጠብቆ እየቀጠለ መሆኑን ያስረዱት ዶክተር ለገሰ፣ በክልሉ ሕግ የማስከበር ርምጃውን ተከትሎ ክልሉ ከሞላ ጎደል ወደ ሰላም እና መረጋጋት የመጣበት ሁኔታ ተፈጥሯ ብለዋል።

ክልሉን መልሶ የማደራጀት እና አቅሙን የመገንባት ሥራ እየተሠራ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።

የክልሉን የጸጥታ ኃይል መልሶ በማደራጀት እና ሥልጠና በመስጠት የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ እየተሠራ ነው ብለዋል።

በአደናጋሪ መረጃ ተወናብደው የነበሩ ከ12 ሺህ በላይ ግለሰቦች የቀረበላቸውን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ተሃድሶ ወስደው ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀላቀል ሰላማዊ ኑሮ መጀመራቸውንም አንሥተዋል።

በልዩ ልዩ ምክንያ አኩርፈው እና ተበትነው የነበሩ ከ10 ሺህ በላይ የቀድሞ የክሉሉ ልዩ ኃይል አባላት በተደረገላቸው ጥሪ መሠረት ተሃድሶ ወስደው የክልሉን ሰላም ለመጠበቅ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የክልሉ አመራር የሕዝቡን ሰላም እና ጥያቄ ለመመለስ እየሠራ እንደሚገኝም ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ጽንፈኛ ኃይሉ አሁን ላይ በየመንደሩ እና ሰፈሩ በመሰማራት መንገድ በመዝጋት በዘረፋ ወንጀል ላይ መሰማራቱን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይህ ኃይል የክልሉ አርሶ አደር ማዳበሪያ ጭምር እንዳይደርሰው እያደረገ ነው ብለዋል።

በኦሮሚያ ክልል በሚንቀሳቀሰው የአሸባሪው ሸኔ ቡድን ላይም እየተወሰደ ያለው ርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን ያነሱት ዶክተር ለገሰ፣ የሽብር ቡድኑ በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች ላይ መከላከያ ሠራዊት በወሰደው መጠነ ሰፊ ርምጃ ውጤት መገኘቱን አውስተዋል።

የመከላከያ ሠራዊት አሸባሪው ቡድን ሲጠቀምባቸው የነበሩ ዋሻዎች፣ ጫካ እና የተለያዩ ይዞታዎች መቆጣጠሩን ተናግረዋል።

በመሆኑም አሁን ላይ አሻባሪው ቡድን ይንቀሳቀስባቸው በነበሩ አካባቢዎች የሰላሙ ሁኔታ እየጎለበተ መምጣቱንም አስረድተዋል።

በዚህም የኦሮሚያ ክልል ለልማት እና ለመልካም አስተዳደር ሥራ የተመቸ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል።

ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ የማድረግ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ያነሱት ሚኒስትሩ፣ ይህም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል መንግሥታት የተቀናጀ ጥረት እየተከናወነ መሆኑን አውስተዋል።

ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል የተካሄዱ የድጋፍ ሰልፎች ሕዝቡ ለመረጠው መንግሥት፣ ለተገኙ ውጤቶች እና የልማት ትሩፋቶች ቀጣይነት ድጋፉን እና ዝግጁነቱን የገለጸበት እንደነበር ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በመግለጫቸው አንሥተዋል።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

05/04/2024
05/04/2024
28/03/2024

አዲስ አበባ በጋራ ጥረታችን እንደ ስሟ በሚታይ በሚዳሰስ ልማት ትፈካለች!

የሁላችንም ቤት የሆነችው አዲስ አበባ የሚመጥናትም የሚገባትም ብልፅግና በመሆኑ ዕድሜ ያረጁና ያፈጁ ሰፈሮቿ እየታደሱ፣ አዳዲስ ህንፃዎችም በግሉ ዘርፍ እና በመንግስት በፍጥነትና በጥራት እንዲጠናቀቁ ግልፅ አሰራር ተዘርግቶ እየተሰራ ይገኛል።

በበርካታ ሰፈሮች በቆርቆሮ አጥር ታፍኖ የቆየውን ውበቷን በልማት እጆቻችን በመግለጥ ማራኪ የአይን ማረፊያ ማድረግ ጀምረናል።

በለውጡ አመራር መሪነት አዲስ አበባን እንደ ስሟ ዉብ፣ ጽዱና ለኗሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የተጀመረዉ የኮሪደር ልማት የመንገድ አካፋዮችን ማስዋብ ፣ የመንገድ ዳር መብራት፣ አረንጓዴ ልማት፣ እስታንዳርዱን የጠበቀ የመኪና ፣ የብስክሌት ና የእግረኛ መንገድ፣ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ የሆነ መንገድ እና ለጤና ተስማሚና ጽዱ አከባቢ ለመፍጠር ወዘተ ... ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገንም ታሳቢ በማድረግ እየተከናወነ ሲሆን አበረታች ስራዎች ተጀማምረዋል።

አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ከተማ የሆነችው አዲስ አበባችን የነዋሪዎቿን ህይወት በሚያሻሻል መልኩ ጎስቋላ ሰፈሮቿ እየታደሱ ተወዳዳሪነቷና ተመራጭነቷ በእጅጉ ጨምሯል።

በቅርቡ የተመረቀው የአድዋ ድል መታሰቢያ ጨምሮ ታላላቅ አገራዊ ፕሮጀክቶች ከልማት ፋይዳቸው ባሻገር የኢትዮጵያ ታሪክ ለዓለም ከፍ ብሎ እንዲታይ ጉልህ ሚና እያበረከቱ ይገኛሉ።

አዲስ አበባ በስም ብቻ ሳይሆን በሚታይ በሚዳሰስ ልማት መፍካት እንደሚገባት በማመን ፓርቲያችን፣ ህዝባችንና መንግስታችን ከተማዋን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ 24 ሰዓት ስራ ላይ ናቸው።

28/03/2024
28/03/2024

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wetatu Alegn posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share