08/12/2023
ሕዳር 30 የሚካሄድ ሰልፍ የለም!!
በሰልፍ ስም ሁከት እና ትርምስን አልመው እየሰሩ መሆኑን አስቀድመን ተናግረናል። አማራ ክልልን እንደ ኮሎምቦ፤ አዲስ አበባን እንደ ሲሪላንካ ሲል የነበረ ጃውሳ አማራ ክልልን ሰላም ነስቶ፣ ከልማት አስተጓጉሎ ያልተሳካለትን አዲስ አበባን የትርምስ ሜዳ የማድረግ ውጥኑን ዳግም በመከለስ በሰላማዊ ሰልፍ ስም እየተንቀሳቀሰ ነው።
በሰላማዊ መንገድ እንታገላለን በሚሉ ጭምብላሞች ስም ሰልፍ እየጠራ፣ በከተማ ውጊያ የሰለጠኑ #ጃውሳዎችን በሕቡዕ አስታጥቆ ወደ አዲስ አበባ በማስገባት በአማራ ክልል የዞን ከተሞች ሞክሮ ያልተሳካለትን አይነት ውጊያ ለመክፈት እየተንቀሳቀሰ ስለመሆኑ፤ የደህንነት እና የፀጥታ የጋራ ግብረ ኀይል ዛሬ በተለያዩ የከተማው ክፍሎች የተቆጣጠራቸው የጦር መሣሪያዎች እና ግለሰቦች ማሳያ ናቸው። መንግስት አሁንም ክትትሉን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። የአዲስ አበባ ህዝብም ከተማውን ከዘራፊዎች እና አመጽ ቀስቃሾች በንቃት ሊጠብቅ ይገባል።