Abrhm chora

Abrhm chora Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Abrhm chora, Digital creator, .

ከእብደት ውጣ!!፨፨፨////////፨፨፨እብደት አስተሳሰብ ውሱንነት ጋር ብቻ የሚገናኝ ጉዳይ አይደለም። አብዛኛው የዓለማችን ሰው እብደቱን ባለማወቁ ሙሉ በሙለ የሚያስብና እንዳላበደ ያምናል። ...
12/10/2023

ከእብደት ውጣ!!
፨፨፨////////፨፨፨
እብደት አስተሳሰብ ውሱንነት ጋር ብቻ የሚገናኝ ጉዳይ አይደለም። አብዛኛው የዓለማችን ሰው እብደቱን ባለማወቁ ሙሉ በሙለ የሚያስብና እንዳላበደ ያምናል። እውነታው ግን እያንዳንዱ ሰው ይብዛም ይነስም በየጊዜው በእብደት ውስጥ ያልፋል፤ ምንነቱ በማይታወቅ የአስተሳሰብ ውልብታ ይመታል፤ በቅጡ እንኳን ሊረዳውና ሊገልፀው የማይችለው ሁኔታ ውስጥ እራሱን ያገኛል። ማድረግ ያለበትን ነገር ሳያደርግ መጠበቅ የሌለበትን ውጤት በጉጉት ይጠብቃል። አንድ ከአንድ ደረጃ ወደሌላኛው ደረጃ የማለፉ ጉዳይ አጠራጣሪ የሆነ ተማሪ ስሙን ከሰቃዮቹ ተርታ ሲፈልግ ብንመለከት ከእርሱ የባሰ እብድና ግራ የተጋባ ሳው እንደሌለ እናስባለን። ነገር ግን የብዙዎቻችን ህይወት ከእርሱ የተለየ አይደለም። የማይመጥነንን ውጤት በመጠበቅ እድሜ ዘመናችንን የምንፈጅ ሰዎች ጥቂቶች አይደለንም።

አዎ! ጀግናዬ..! ከእብደት ውጣ! እራስህን እያወክ እራስህን አታስጨንቅ፤ በገዛ ፍቃድህ እራስህን ጫና ውስጥ አትክተት፤ ያልዘራሀውን ለማጨድ፣ ያልተከልከውን ለመቁረጥና ያንተ ያልሆነውን ለመብላት አትሯሯጥ። ሰጥቶ የመቀበልን ምድራዊ ህግ አክብር፣ ታግሎ የማሸነፍን መርህ ተከተል፣ ዋጋ ከፍሎ ለውጤት የመብቃትን ህግ ፈፅም። ላንተ ሲሆን የሚቀየር ምድራዊ አሰራር የለም። የምርም ጥበብ እንደታደለው፣ ማስተዋል እንደተሰጠው፣ ልቡም በብረሃን እንደተሞላ ሰው የምታስብ ከሆነ በምንም መንገድ ቁጭ ብለህ በሰዎች ላብ ማትረፍን የምታስብ፣ ያለስራህ ሙገሳን የምትጠብቅ፣ በጥፋትህ አድናቆትን የምትመኝ ሰው አትሆንም። ዛሬ ያለስራህ ብትደነቅ ነገ በስራህ እንደምትዋረድ አስታውስ።

አዎ! ዘወትር ተመሳሳይ ተግባር እየፈፀምክ የተለየ ውጤት መጠበቅ አቁም፤ ሁሌም አንድ ቦታ እየተገኘህ የህልምህን መሳካት አትመኝ፤ እራስህን አሳንሰህ እየተመለከትክ ሰዎች ከፍ እንዲያደርጉህ አትጠብቅ። ዓለም በልብህ የያዝከውን፣ በአዕምርህ የሚመላለሰውን፣ በእምነትህ የሚታየውንና በልማድህ የሚገለጠውን ያንኑ እንደምትሰጥህ እወቅ። የቤቱ ዋንኛ ችግር እራሱ ሆኖ፣ ለውድቀቱና ስህተቱ ተጠያቂው እራሱ ሆኖ፣ ደስታ ለማጣቱ ምክንያት እራሱ ሆኖ ሳለ ለእራሱ ቤት መፍትሔ ፍለጋ ሃገሩን እንደሚያስስ፣ ለውድቀቱ፣ ለስህተቱና ለወረደ ህይወቱ ውጫዊውን አካል እንደሚወቅስና ለደስታው ብሎ እራሱን አደጋ ላይ እንደሚጥል ሰው በእብደት ጎዳና ላይ እየተመላለሰ ያለ ሰው አለን? በፍፁም። እብደትህን አቁምና እራስህን ተረዳ፣ የዓለምን አሰራር ተገንዘብ፣ የምድርን ህግ እወቅ፣ ሃላፊነትህን በአግባቡ ስትወጣ የሚገባህ ነገር በእጅህ እንደሚገባ እመን።
ሰናይ ቀንይሁንልን! 🌘🌒💫✨
አብርሃም 🤜🤜🫷🫷

 !!የሕዝባችን ደሞክራሲ መብት  #በ21ኛው ክፍለ ዘመን!በህገ-መንግሥቱ ላይ ካስቀመጣቸው መሠረታዊ መርሆዎች የሕዝባችን ራሱን በራሱ  #የማስተዳደርና  #የመወሰን መብት እንደተጠበቀ መሆኑ ለ...
04/10/2023

!!

የሕዝባችን ደሞክራሲ መብት #በ21ኛው ክፍለ ዘመን!

በህገ-መንግሥቱ ላይ ካስቀመጣቸው መሠረታዊ መርሆዎች የሕዝባችን ራሱን በራሱ #የማስተዳደርና #የመወሰን መብት እንደተጠበቀ መሆኑ ለሁሉም ግልጽ ነው፡፡

ያም ሆነ ይህ! /የወ/ው/አከባቢ ሕዝብ #የስቆቃ ህይወት ለዘመናት እየኖረ ከዛሬ ነገ ይሻላል የሚል የትዕግስቱን ጥልቀት በታላቅነት መንፈስ ብዙ አመታትን አሳይቷል፡፡

ይህ #ሕዝብ ትናንት ለጎፋ ምድር እጅግ ቀላል የማይባል ተጽዕኖ ፈጣሪና አጥንቱን ከስክሰው፣ ደሙን አፍሰው፣ ዳር ድንበሩን አስከብረው፣ለጎፋ ምድር ትልቅ ዋጋ የከፈለው #ሕዝብ መሆኑ በታሪክ የማይረሳና የማይካድ ሀቅ ነው፡፡

ሆኖ ግን #ሕዝባችን ለዘመናት #የስቆቃ ህይወት እየገፋ መኖሩን ሰው ሆኖ ለተፈጠረ ፈጠሩ ብዙ ማስረዳት ጊዜን ማባከን ይሆንብናል፡፡

#በ21ኛው ክፍሌ ዘመን የሰው ልጅ ብዙ ርቀት በሄደበት #ሕዝባችን፦

1ኛ. #መንገድ ፣
2ኛ. #መብራት፣
3ኛ. #ውሃ፣
4ኛ. /ር_እጦት፣
5ኛ. /ር_እጦት፣
6ኛ. ፣
በአጠቃላይ ሙሉ በሙሉ መሠረተ-ልማት ጭምር በሌለበት ለዘመናት መኖራቸው #ገርሞኛል፡፡

ዛሬም ይህ #ሕዝባችን እንደ ትላንትናው በጨለማና #በስቆቃ ውስጥ ኖሮ፣ በቃሬዛ መመላለስ፣ድፍሪስ ውሃ መጠጣቱ፣በኩራዝ ጨለማውን እያበሩ መኖሩ፣መጥፎ ጊዜውን እንደ መልካም አጋጣሚ የሚቆጠሩ #ሕዝብ እንደሆነ ይታውቃል፡፡

#ሕዝባችን ለዘመናት በጭቆናና አረቆ ውስጥ መቆየቱ ታሪካዊ ስህተት ብቻ ሳይሆን ታሪካዊ ይቅር የማይለው ነው፡፡

ይህ ትውልድ፦
#በአንድነት፣
#በአብሮነት፣
#በፍቅር፣
#በሠላም፣
#በመደጋገፍ፣
#በመቻቻል፣
#በመተጋገዝ፣
ታሪክ ሰርተው #በሕዝባችን ላይ ተደቅኖ ለዘመናት የኖረውን ቀንበር ከትከሻችን አሽቀንጥረን ለመጣል ብሩህ ተስፋ የሚያይበት ጊዜው አሁን ነው፤ ሩቅም አይደለም!!

ነው!!!

03/10/2023
03/10/2023

14.2K likes, 72 comments. “part[9]የሚተካሽ ጠፋ...🥺”

ለእነዚህ ነገሮች ብቻ ክብር ስጣቸው!!••••••••••••••••••••••••••••••••••••••➦ ሦስት ዓይነት ሰዎችን አክብር !!!     ✅ የዕውቀት ባለቤቶችን     ✅ ቤተሰብህን  ...
03/10/2023

ለእነዚህ ነገሮች ብቻ ክብር ስጣቸው!!
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

➦ ሦስት ዓይነት ሰዎችን አክብር !!!
✅ የዕውቀት ባለቤቶችን
✅ ቤተሰብህን
✅ አዛዉንቶችን
➦ ሦስት ነገሮች ይኑሩህ !!!
✅ ታማኝነት
✅ እምነት
✅ መልካም ስራ
➦ ራስህን ከሦስት ነገሮች አርቅ !!!
✅ ሰዎችን ከመናቅ
✅ ከማጭበርበር
✅ ከብድር
➦ ሦስት ነገሮችን ተቆጣጠር !!!
✅ ምላስህን
✅ ቁጣህን
✅ ስሜትህን
➦ ከሦስት ነገሮች ራስህን ጠብቅ !!!
✅ ከመጥፎ ስራ
✅ ሰዎችን ከማማት
✅ ከምቀኝነት
➦ ሦስት ነገሮችን ፈልግ !!!
✅ ️ዕዉቀትን
✅ ጥሩ ስነ-ምግባርን
✅ ታዛዥነትን
➦ ሦስት ነገሮችን ንጹህ አድርግ !!!
✅ ሰዉነትህን
✅ ልብስህን
✅ ንግግርህን
➦ ሦስት ነገሮችን አስታዉስ !!!
✅ ሞትን
✅ ሰዎች የዋሉልህን ዉለታ
✅ ሰዎች የሰጡህን ምክር
ወይደ ውርኪ ወረዳ!!

"መንገድ፣መብራት፣ውሃ፣በአጠቃላይ የመሠረተ ልማት እና የወረዳ መዋቅር ጥያቄ ምላሽ እንጠብቃለን!!          ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖🔜ሀገራዊ ለውጥ ከመጣ ወድህ የህዝቦቿ፣እኩልነት የሀብት ...
02/10/2023

"መንገድ፣መብራት፣ውሃ፣በአጠቃላይ የመሠረተ ልማት እና የወረዳ መዋቅር ጥያቄ ምላሽ እንጠብቃለን!!
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
🔜ሀገራዊ ለውጥ ከመጣ ወድህ የህዝቦቿ፣እኩልነት የሀብት ክፍፍል ፍታሃዊነት፣የህዝቦች መስተሳሰር፣
የጋራ ልማት ተጠቃሚነት፣የመፈቃቀር፣በአንድነት
ከህገ-መንግሥት ሳይፃረሩ የመደራጀት ዕድል ከመቸውም ጊዜ የሰፋ ሆኖ መጥቷል፡፡

🔜ይህ ሁኔታ ለአንድ ሀገር ትርጉም ሰጭ የዕድገት፣
የብልጽግና፣የዲሞክራሲ ልዕልነት እንድጎላ ያደርጋል፡፡

🔜በዚህ ውስጥ የሚታቀፉ ህዝቦች የመፈቃቀር፣
የመተባበር፣በጋራ ሆነው የሀገር ሉዐላዊነት ለማስከበር እና የማክበር፣የብሔር ብሔረሰቦች የሆነውን ሀገር በጋራ በማልማት፣በጋራ በመወሰን፣የድርሻቸውን እንዲወጣ ያስደርጋል፡፡

🔜በተቃራኒ የሀገር ዕድገት በውስን ሰዎች እጅ እንዳሌ መስሏቸው በመዋደድ ፋንታ መጥላትን፤
በመደገፍ ፋንታ መቃወም፤በመስማማት ፋንታ ችላ ማለትን፤በእውነት ፋንታ ውሸትን፤በመቅረብ ፋንታ
መራቅን፤በገሀድ ከመናገር ፋንታ በድብቅ መናገር የቡድን ዓላማ በማንፀባረቅ፣የወል እውነቶችን በማጥፋት የሚሠሩ ኃይሎች ከድርጊታቸው መቆጠብ አለባቸው፡፡

ይህ ዓይነት ድርግት ወይም ተግባር ለዘመናት ከመቆየቱ የተነሳ ሀገር ሆነ አከባቢ ለታለመለት መልካም ዓለማ ሳይደርስ መቆየቱ በአንፃራዊ ግልጽ ቢሆንም
አሁን ግን ቆሚ ብለን ማሰብ፣ለመልካም ነገር በአንድነት መቆም፣ከመጥፎ ድርጊት መውጣት ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም ባይ ነኝ፡፡

🔜የህዝቦችን አንድነት፣እኩልነት፣የጋራ የሆኑ እሴቶች፣ባህላዊ ወግን ለሚመጣው ትውልድ
በማፍራት እና ለጠቃሚ ዓላማ፣የሀገራዊ ስሜት የሚኖር ዜጋ እንድፈጠር ቢያደርግ መልካም ነው፡፡

🔜አንድነት ለዓለም፣ለአህጉር፣ለሀገር እንድሁም ለአንድ አከባቢ የማይቀር ግደታውን አውቀው መኖር ብልህነት ነው፡፡

🔜 ወይደ ውርኪ ወረዳ!
=>ላይማ ፃላ ከተማ!!

አስደሳች ዜና ቀጥታ ከሶዶ_ ዲላ የትራንስፖርት ስምሪት ተጀመረአዲሱ መስመር ታሪፍ 179 ብር ከ50 ሳንቲም ነው።እነሆ ከባለ ሰባት በር መግቢያና መውጫ ከተማ አንዱ የሆነው ከወላይታ ሶዶ ጌዲ...
02/10/2023

አስደሳች ዜና
ቀጥታ ከሶዶ_ ዲላ የትራንስፖርት ስምሪት ተጀመረ

አዲሱ መስመር ታሪፍ 179 ብር ከ50 ሳንቲም ነው።

እነሆ ከባለ ሰባት በር መግቢያና መውጫ ከተማ አንዱ የሆነው ከወላይታ ሶዶ ጌዲኦ ዞን ዲላ ከተማን በቀጥታ የሚያገናኝ መንገድ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ከዚህም ቀደም ከሶዶ ሀዋሳ ከዛም ዲላ ይደረግ በነበረው ጉዞ የሚያጋጥሙ መጉላላቶችን ይቀንሳል የተባለለት አዲሱ መስመር 179.50 ሳንቲም ብር ታሪፍ ተቆርጦለታል።

መነሻውን ከመናኅሪያ አድርጎ ሶዶ በአዋሳ መስመር በሞሮቾ በሚወስደው መንገድ ከዛሬ ጀምሮ ለህዝብ አገልግሎት ወይም ትራንስፖርት ለመስጠት የተከፈተው መንገድ 168 ኪሎሜትር ይረዝማል።

ይህም ከዚህ ቀደም በ3 የተለያየ ተሽከርካሪ የሚደረገውን ጉዞ አንድ ያደረገና ርቀት የሚቀንስ መንከራትን የሚያስቀር በመሆኑ ወደ ዲላ ከተማ ከዎላይታ ሶዶ በቀጥታ መጓዝ መጠቀም ይችላሉ ።

ለዘገባው ጥንቅር የዎላይታ ሶዶ ከተማ ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ታጠቅ ምትኩ መረጃዎች በመስጠት የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።

የዎላይታ ሶዶ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ነው የዘገበው ።

Wolaita!!!!

ዳንኤል 6¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯³ ዳንኤልም መልካም መንፈስ ስላለው ከአለቆችና ከመሳፍንት በለጠ፤ ንጉሡም በመንግሥቱ ሁሉ ላይ ይሾመው ዘንድ አሰበ።⁴ የዚያን ጊዜም አለቆችና መሳፍንቱ ስለ መንግሥቱ...
02/10/2023

ዳንኤል 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ ዳንኤልም መልካም መንፈስ ስላለው ከአለቆችና ከመሳፍንት በለጠ፤ ንጉሡም በመንግሥቱ ሁሉ ላይ ይሾመው ዘንድ አሰበ።
⁴ የዚያን ጊዜም አለቆችና መሳፍንቱ ስለ መንግሥቱ በዳንኤል ላይ ሰበብ ይፈልጉ ነበር፤ ነገር ግን የታመነ ነበረና፥ ስሕተትና በደልም አልተገኘበትምና በእርሱ ላይ ሰበብና በደል ያገኙበት ዘንድ አልቻሉም።

አቶ አብራሃም ዞራ በደ/ጎፋ ወረዳ እያለ ምን ሠራና ነው? እና እንተን ያረገውን እንደት ኤረስተህ ነው የወደቁ የዞን አመራሮችን የምትደግፈው ያላችሁኝ ሁለት ሰዋች አንድ ነገር ልንገራችሁ ""ቱም ሞርኬ ማድሰስ"" ገስ ኑ አስ!!! ከግል ጉዳይ ባለፈ አስቡ የግል ጉዳየን በግል እንፈታለን። አቶ አብራሃም ዞራ እንደነሱ ደካማ አስተሳሰብ ባለበትና በመንደርተኝነት የምታጠር ብሆን #ከጽዳት እስኬ #ተሾሚ የውርክ ልጅ ማድረግ ይችል #ነበር ግን በመንደርተኝነት ኮሮጆ ያልተካተተ በመሆኑ ሰውን በሥራና በሥራ ይመዝናል ለዝህም እናንተው ምስክር ናችሁ።በወረዳ እያለ ምን ሠራ ለምትለኝ በወቅቱ የራሱን ሥራ አሰፈጻምና ካብነን አሳምኖ ከሠራቸው ሥራዋች ጥቅቱን ላስቃኝህ
1ኛ= ለፃንጋ ወርጭና ሻሌ ህዝብ የድሃ ድሃ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍል የልማታዊ ሴፍትነት ታቅፈው በምግብ ለሥራና በቀጥታ ተረጅነት ተጠቃም እንድሆኑ ማድረግ
2ኛ=ለኡባ ባርኤኤ ሰሎ ጋጫ ባንዳ መንገድ 12.08 ኪሎ ሜት በማስከፈት ኮረት እንዲነጠፍ መደረጉ
3ኛ=ከዶርማሌ ማጋዛ 3.5 ኪሎ ሜትር መንገድ ከፈታ ስራ መሠራቱ
4ኛ=የሎጤ ታዳጊ ማዘጋጃ የመጀሪያ ቦኖ መሠራቱ
የሎጤ ማዘጋጃ መብራት እንዲገባ ጥናት መደረጉ (አሁን መብራት እንዲገባ የተደረገው በዚያ ጥናት መሆኑ
5ኛ= ለዘመናት አስተዋሽ ያልነበረው የላይማ ማዕከል አምቡላንስ በማስወሰን አገልግሎት ማዕከል ላይ እንዲያገለግል መደረጉ
6ኛ=የቦርዳ ሀይስኩል በማስወሰን ከቦርዳ ዛንጋ ሄደው የሚማሩ ተማሪዎች በቅርበት እንዲማሩ በማስፈቀድ ስራ እንዲጀመር መደረጉ።
7ኛ=የኡባ ሀይስኩል፣ የውርኪ ሀይስኩል፣ የዛንጋ እና ውርኪ ጤና ጣቢያ እንደወረዳ ማስወሰኑ (ግንባታ ሂዴት ላይ ያለ እና አገልግሎት የጀመረ
8ኛ=ግንባታው የተቋረጠው የፃንጋ ጤና ጣቢያ ግንባታ እንደገና እንዲጀመር በጀት በመመደብ ስራ የተጀመረበት
9ኛ=ከጣይና ላይማ 21 ኪሎ ሜትር መንገድ ከሳሊኒ ማሽን በማስተባበር የተጠገነ መሆኑ
እነዚህ በአንድ ዓመት ውስጥ በወረዳ ውስጥ የተሰሩ ውስን ስራዎች ናቸው። የምታነጻጽሩ ሰዋች እስት ከለውጡ ወድህ ደ/ጎፋን ካስተዳደሩ አካላት ኤከል ኤሄን ሰርቶል ብለህ ግለጽልኝ? ስለ አብራሃም የቀረውን ቀጥሉበት!!!

ብዙ ሰዎች የቆሻሻ መኪኖች ናቸው። ቆሻሻውን ተሸክመውም የሚያራግፉበት  ቦታ ይፈልጋሉ። አንተ ግን ቆሻሻ መጣያቸው አትሁን!። ፈገግ ብለህ ምንም እንዳልተፈጠረ ቆጥረህ ነገሩን አሳልፈህ፦👉ለክፋ...
02/10/2023

ብዙ ሰዎች የቆሻሻ መኪኖች ናቸው። ቆሻሻውን ተሸክመውም የሚያራግፉበት ቦታ ይፈልጋሉ። አንተ ግን ቆሻሻ መጣያቸው አትሁን!። ፈገግ ብለህ ምንም እንዳልተፈጠረ ቆጥረህ ነገሩን አሳልፈህ፦
👉ለክፋታቸው በጎነትን፣
👉ለስድባቸው መልካም ምኞትን፣
👉ለርግማናቸው ምርቃትን፣
👉ለቁጣቸው ፈገግታን፣
👉ለትዕቢታቸው ትህትናን፣ መልስላቸውና ቆሻሻቸውን ይዘው እንዲመለሱ አድርጋቸው።
በጭራሽ አንተ ላይ ማራገፍ የለባቸውም!!
✍️ትዝፍት ይሆናል!!

የጎፋ እና የኦይዳ ህዝቦች የዘመን መለወጫ በዓልን በሣውላ ከተማ ለማክበር ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ሣውላ ፣ መስከረም 14 ፣ 2016 ዓ.ም በነገው ዕለት የጎፋ ጋዜ ማስቃላ እ...
02/10/2023

የጎፋ እና የኦይዳ ህዝቦች የዘመን መለወጫ በዓልን በሣውላ ከተማ ለማክበር ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
ሣውላ ፣ መስከረም 14 ፣ 2016 ዓ.ም በነገው ዕለት የጎፋ ጋዜ ማስቃላ እና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላ የዘመን መለወጫ በዓል በሣውላ ከተማ በድምቀት ይከበራል።

በዋዜማው ወጣቶች የጋዜ ጭፈራ በከተማው እየተጫወቱ በዓሉን እያደመቁት ይገኛል።

የጎፋ እና ኦይዳ ህዝቦች የዘመን መለወጫ የሆነው የጎፋ '' ጋዜ ማስቃላ '' እና የኦይዳ ''ዮኦ ማስቃላ '' በዓል በሲምፖዝየም እና በአደባባይ የፆምፔ ኬሶ ሥነ-ስርዓት በሣውላ ከተማ ይከበራል።

YOO! YOO! MASQQALA

Daanaw Daana!!

02/10/2023

ህዝብን መናቅ የምያስከፍለው ዋጋ ከፍ ያለ ነውና!!!
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°

አካባቢን (ሕዝብን) መናቅ መቆም አለበት። የመዋቅር ጥያቄ ሕዝባዊ መሠረት ያለው የመብት ጥያቀ እንጅ የግለሰብ አይደለም።

በወይዴ ውርኪ መፈጠር ወይም መገኘት ኃጥአት አይደለም። ከወይዴ ውርኪ የተገኘ ሰው ዋና አስተዳደር /ዋና ፖርት አመራር መሆን የለበትም፣ እንዴት ወይዴ ውርኪ ይመራናል። እኛ ካልሆንን በቀር ሌላ ለምን በማለት የአካባቢ ተወላጆች ላይ ከፍ ያለ ጥላቻ መስራት ተገቢነት የለውም።

ከእኛ አካባቢ ካልሆነ ከዚያኛው አካባቢ የተገኘ ሰው ለምን በምል አካባቢን ከአካባቢ ለማጋጨት በሬ ወለድ ወሬ በመፍጠር የአካባቢ ተወላጆችን የማሳዳድ ዘመቻ መቆም አለበት። በተደራጀ መንገድ በግልጽ በቡድን በማደም እና በስውር በማህበራዊ ትስስር ገጽ የአካባቢውን ተወላጆችን የማሳደድ ሸፍጥ ልቆም ይገባል።

ይህ በአንድ አካባቢ በስውር ታቅዶ በተቀናጀ እና በተደራጀ መንገድ የሚሰራው የጥላቻ ፖለቲካ ለአካባቢው ካለ የቆዬ ጥላቻ የሚመነጭ እና ህዝብን በመናቅ የሚደረግ የሴራ ፖለቲካ በመሆኑ የማሳደድ እና የመግፋት የሴራ ፖለቲካ መቆም አለበት።

በወይዴ ውርኪ አካባቢ ያለው የመዋቅር ጥያቄ የህዝቡ መሠረታዊ ጥያቀ እና የመልማት ጥያቀ ነው። የመዋቅር ጥያቀ የመመለስ ኃላፊነት ያለበት በአዋጅ ስልጣን የተሰጠው የክልሉ መንግስት ነው። ወይዴ ውርኪ በመዋቅር ለመደራጀት ጥያቀ ያቀረበው የመጠየቅ መብቱ ህገ መንግስታዊ መብት ስለሆነ እንጅ ውለታ እንዲዋልለት ችሮታ አልጠየቀም። የመመለስ ያለመመለስም ኃላፊነት ያለው የማድረግ ስልጣን ያለው አካል እንጅ አንድ መንደር አይደለም።

አንድ መንደር ተነስቶ "ጥያቀው የእነ እንትና ጥያቀ ነው" እየተባለ ሕዝብን በመናቅ የሚደረገው የንቀት አካሄድ ትርፉ አሉታዊ ብሆን እንጅ ሌላ አይሆንም። ትላንት ክልል ከተመሠረተ በሁዋላ የሚመሠረተው ክልል ጥያቀውን ይመልሳል አሁንም ክልል በለሌበት መመለስ አንችልም በማለት የምርጫ ልፈለፋ ስደረግለት ልማት ምን እንደሆነ በአይኑ ሳያይ አምኖ የመረጠን ሕዝብን በመናቅ ምን አያመጡም ብሎ ሜዳ ላይ መፎከር ግልጽ ንቀት እና ጥላቻ ነው። በሌላ በኩል በአደባባይ ጥያቀያችሁ ተገቢ ነው ከክልል ምስረታ በሁዋላ አዲሱ ክልል ይመልሳል ብሎ የይምረጡኝ በተሰበከበት ማግስት ጥያቀው የእነ እንትና ነው መባሉ በሰበቡ ግለሰቦችን ለመግፋት የሚደረግ ሴራ ነው።

እነሱ እና እኛ የምለው ንጽጽር መድረሻው ዬት እንደሆነ እና ዬት እንደምያደርስ አብረን የምናዬው ይሆናል። ጥላቻ ትርፉ መለያዬት እና መቃቃር ከመፍጠር ውጭ ትርፍ የለውም። የጥላቻ አካሄድን የጀመራችሁት የሰፈራችሁ ቡድን የበላይ እንዲሆን ከሆነ ቡድን ለእግር ኳስ ወይም ለገና ጫዋታ ቢቻ መሆኑን እንዲትገነዘቡ ይሁን። በዚህ ሁሉ ግን ህዝብ መከበር አለበት። ሕዝብን መናቅ የሚያስከፍለው ዋጋ ከፍ ያለ ነውና!!!!

02/10/2023

የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በመሆን የጎፋ እና የኦይዳ ሕዝቦችን የማገልገል ዕድል በማግኘቴ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡

ይህንንም ታላቅ ኃላፊነት በእምነት የሰጠኝን መሪዉን ፓርቲ ብልፅግና እና የክልሉን መንግሥት እንዲሁም ከግምቴ በላይ በፍቅር የተቀበለኝን የዞኑን ሕዝብ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡

ባልተቆጠበ ጥረት እጅ ለእጅ ተያይዘን ለሕዝባችን ዕድገትና ብልፅግና እንተጋለን !!

ፈጣሪ ይርዳን !!

02/10/2023

ታይ!!
#እስከዛሬ ድረሰ ስለሰዎች መጥፎነት አላወራሁም፤ነገር ግን አሁን የሰዉ ደምፅ አልወደድኩትም እና ውሻ አንበሳ ላይ መጮሁ እንጂ ለሌ ነገር የመድረክ አቅም የለሁም እና እናንተ አሁን ስለአንበሳው የሌለ ነገር በማውራት እንዴ ውሻ ድምፅቹን ከፍ እያደረጋቹ እንደሆነ ሰማው ግን የእናንተ ንግግር ከውሻ ጮሁት በላይ እንዳለሆነ ልታዉቅ ይገባል ይድረስ ገለቴ👈👈

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abrhm chora posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share