05/05/2024
በሀገራችን እና በመላው ዓለም የምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሠላም አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ።
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ኃጢአት የከፈለው መስዋዕትነት የጥላቻና የክፋትን ምዕራፍ ዘግቶ፤ የፍቅር፣ የእርቅና የሠላም መርሆዎችን፣ እንዲሁም የዘላለምን ሕይወት መንገድን በማብሰር ይቅርታ የአሸናፊዎች መንገድ መሆኑን ነፍሱን በመስቀል ላይ በመስጠት ፍቅር በተጨባጭ አረጋግጧል።
እኛም ዛሬ የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሳኤ ስናከብር ሁል ጊዜ ሠላም፣ ይቅርታ፣ ምህረት እና ልባዊ መተሳሰብ የእለት ተእለት የህይወታችን መርሆ መሆን እንዳለበት ልብ ልንል ይገባል።
መልካም በዓል
አቶ ፍቃዱ ተሠማ
በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኋላፊ