25/08/2023
ኢትዮጵያ የBRICS አባል በመሆኗ ከምታገኛቸው ጥቅሞች መካከል በጥቂቱ እንደሚከተለው ልዘርዝር:-
👉በሰሜኑ ጦርነት ወቅት የነበረውን አይነት የምዕራባውያን #ጫናን ለመቋቋም ይረዳታል።
👉አባል ሀገራቱ ከዶላር ውጪ የመገበያያ ገንዘብ የማሳተም እቅድ ስላላቸው ከዶላር ጥገኝነት ነፃ ለመወጣት ይረዳታል።
👉ከአባል ሀገራቱ ቀጥተኛ የኢንቨስትመንት እድሎችን ታገኛለች። ይሄም በኢኮኖሚ ያላትን ተፅዕኖ በእጅጉኑ ይጨምራል።
👉ከአባል ሀገራቱ ብድሮችን በቅናሽ የወለድ መጠን ወይም በዜሮ የወለድ ስሌት ለማግኘት ትልቅ እድል ይፈጥርላታል።
👉የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በማሳደግ ዜጎች የባህል እና የእውቀት ልውውጥ እንዲያደርጉ እድል ይሰጣል።
👉አብዛኛው አባል ሀገር በቴክኖሎጂ የተራቀቀ እውቀት ባለቤት በመሆናቸው ይሄንን የቴክኖሎጂ እውቀት ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ከፍተኛ እድል ይፈጥራል!
ከላይ የዘረዘርኳቸው እና የመሳሰሉት ጥቅሞች ያሉትን የዲፕሎማሲ ስራ ነው እንግዲ ያሳካነው!! እንኳን ደስ አለን ለሀገር ወዳድ ህዝቦች በሙሉ!!!
#ጃውሳ