24/11/2022
፨፨በፈጣሪ እለምናችኋለሁ ሼር_ላይክ ይደረግ፨፨
በምስራቅ ወለጋ ዞን በስቡ ስሬ ወረዳ በስሬ ከተማ የተጠለሉ ወገኖቻችን ወደተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ከሔዱት ውጭ በከተማዋ የተጠለሉ 5970 ሰዎች ይገኛሉ።
እነዚህ በስሬ ከተማ በሸራ ውስጥ ወጥረው የሚኖሩ በብርድና በጸሐይ እየተሰቃዩ የሚገኙ ሲሆን በስሬ ከተማ በሚገኘው የአኗር መስጅድ አጠር ክልል ውስጥ ሸራ ወጥረው የሚኖሩ ከወረዳው ከተለያዩ ቀበሌዎች ተፈናቅለው ያለምንም ጠያቂ ከአንድ አመት በላይ የሆናቸው ናቸው።
ስለሆነም አጠቃላይ ማህበረሰቡን፣ በስሬ ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮችንና እርዳታውን ለህዝቡ በቅርበት ሊያደርሱልን የሚችሉትን በሙሉ ኢንተርቪው አድርገን ለእናንተ ይዘናል።
የስሬ መስጅድ ኢማም የሆኑት ሸህ ኡመር ሞላ በጣፋጭ አንደበታቸው ሁሉንም ተጎጂዎች ሰብስበው በቀጥታ መልዕክታቸውን አስተላልፏል።
ውድ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቼ በወለጋ የሚኖሩ አጠቃላይ ማህበረሰብ አለም ያሉበትን አውቆ፤ በተቻለው አቅም በአካል ተገኝቶ፣ መንግስትም እውነቱን ተገንዝቦ፣ አቅጣጫ ለማስያዝ አጉልዞ ጥያቄ ስራውን በኢፋ በቦታው ጥርት ባለቪድዮ፣ ጥርት ባለድምጽ፣ ይዞላችሁ ቀርቧል።
ይህንን በወለጋ አከባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ብሶት፣ ረሐብ፣ ሰቆቃ፣ ሞትና መፈናቀል ከመነሻው ጀምሮ አሁን እስካለበት ደረጃ እና በቀጣይ ማንኛውም ባለድርሻ አካላት ለመፍትሄው እንድዘጋጁ የሚያደርግ ይሆናል ብለን እናምናለን‼
ስለሆነም ማንኛውም ሰብዓዊ ፍጡር ከቀያቸው ለቀው፣ ተሰደው፣ የሚበሉት፣ የሚለብሱት አጥተው፣ በየሜዳው ለሚገኙት ጥርት ባለሁኔታ ሁሉም በተገኙበት፣ የሐይማኖት መሪዎች ባሉበት፣ የሐገር ሽማግሌዎች በተገኙበት ቀረፃ አድርገን፤ ማገዝ ለሚፈልጉ አካላት ግልፅ አሰራር ይዘን መጥተናል።
እንደዚህ አይነት ግልፅ ለሆነው አሰራር ፍቃደኛ ሆነው ችግሮቻቸውን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እንድደርስና መንግስትም ትኩረት እንድሰጥ የሚደርስባችሁን መከራና ስቃይ ተቋቁማችሁ ለቀረፃ የተባበራችሁን በሙሉ ክብረት ይስጥልን‼🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ቀረፃው በሁሉም አከባቢዎች ይቀጥላል..
ሙሉ ቪድዎውን በቴሌግራም ቻናላችን ያገኛሉ።
https://t.me/my_Angergutin_77