05/11/2023
ህብረ ብሔራዊ ሀገራዊ አንድነትን ማጠናከር ለሀገረ መንግስት ግንባታዉ ከፍተኛ ፋይዳ ኣለዉ።
ህብረ ብሔራዊ ሀገራዊ አንድነት እየተጠናከረ ሊሄድ የሚችለው ደግሞ የብሔር ማንነት እና ህብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያዊ አንድነት ሚዛናቸዉን ጠብቀው ሲጓዙ ነዉ።
የብሔር፣የቋንቋ፣የባህል፣የሃይማኖት፣የፖለቲካ አመለካከት ወዘተ..ብዝሃነት በገነባት ኢትዮጵያ ሚዛናዊነትን ያረጋገጠ ፣ከፅንፈኛ አስተሳሰብ እና ተግባር የተጠበቀ የፖለቲካ እሳቤን ባህል ማድረግ ኢትዮጵያን ለማፅናት መሠረት ነዉ።
ፅንፈኛ አስተሳሰብ እና ድርጊት ሚዛናዊነትን በማዛባት፣አካታችነትን በማሳሳት ወደ አግላይነት ያሸጋግራል ።
አግላይነት ወደ ጠቅላይነት በማምራት ብዝሃነትን ለመቀበል፣ለማክበር እና ለማስተናገድ ተግዳሮት ይሆናል።በዚህም መነሻ ህብረ ብሄራዊ ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር ጠንካራ ሀገረ መንግስት የመገንባቱን ዕድል ይፈትነዋል።
ብልጽግና ፓርቲ የብሔር ማንነት እና ህብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያዊ አንድነት ሚዛናቸዉን ጠብቀዉ እንዲራመዱ በማድረግ በሂደቱም ጠንካራ አገረ መንግስት መገንባትን መሠረት አድርጎ እየሠራ ይገኛል ።
ኢትዮጵያ ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን የምትመች፣ ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ያበበባት አገር እንድትሆን ብልጽግና ተግቶ ይሠራል ።
ሚዛናዊ የፖለቲካ እይታ መርህ ሁሉንም ብዝሃነቶች የማስተናገድ የመሀል የፖለቲካ አስተሳሰብና ተግባር ነዉ።
ፅንፈኝነት ኢትዮጵያን ከማዳከም ያለፈ ዉጤት እንደማያስገኝ ከዚህ በፊት የፈተኑንን ችግሮች ዞር ብሎ በማየት መገንዘብ እንችላለን። የዘርፈ ብዙ ፀጋዎች ሀገር ኢትዮጵያ ሚዛናዊ የፖለቲካ እይታ መርህን እና ሙሉዕ እይታን በማጠናከር የለዉጥ ጉዞዋን እንድታፋጥን የዜግነት አደራ አለብንና የየበኩላችንን እናበርክት ።