Smartmereja.net

  • Home
  • Smartmereja.net

Smartmereja.net Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Smartmereja.net, News & Media Website, .

የአራትኛ አመቷን ልደት ለማክበር ለልደቷ በተጠመቀ ጠላ በርሜል ዉስጥ የገባችው ታዳጊ ህይወቷ አለፈ!  በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ጥቅምት 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጎጀብ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቁጥር ሁለ...
28/10/2023

የአራትኛ አመቷን ልደት ለማክበር ለልደቷ በተጠመቀ ጠላ በርሜል ዉስጥ የገባችው ታዳጊ ህይወቷ አለፈ!


በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ጥቅምት 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጎጀብ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቁጥር ሁለት ተብሎ በሚጠራበት ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት የአራት አመቷ ህፃን ለልደቷ በተጠመቀ በጠላ በርሜል ዉስጥ ገብታ ህይወቷ ማለፋን ተገልፇል።

ም/ኢ/ር መሠረት ገለፃ ወላጆቿ የህፃኗን የአራተኛ አመት ልደት ለማክበር ጠላ መጠመቁን ለልደቷ የሚያስፈልጉ ዝግጆቶች መሠናዳቱን እና እናት ማልዳ ጠላዉን እያጣራች ሳለ ህፃኗ ከመኝታ ተነስታ እናቷ ወደምትሰራበት ቦታ እንደመጣች እና ወንበር ላይ ቆማ ወደ በርሜሉ ዝቅ ብላ እያየች እናት ወጣ ብላ እስክትመለስ ጠላ ዉስጥ ገብታ ህይወቷ እንዳለፈ አስረድተዋል።

አክለዉም በድንጋጤ እናት ብትጣራ ምላሽ በማጣቷ ወደስፍራዉ መጥታ ህፃኗን ከበርሜል ውስጥ ብታወጣትም ህይወቷ እንዳለፈ ፖሊስ ከስፍራዉ የነበሩ እማኞች አረጋግጫለሁ ብሏል።

የልደት ደስታዉ ወደለቅሶና ሀዘን መቀየሩን የጠቀሰዉ ፖሊስ የአራት አመቷ ህፃን ለአራተኛ አመቷን ልደት የተገዛላትን ልብስ ለብሳ፣ ጫማ፣ ሻማ ለኩሳ ከመንደሩ እኩዮቿ ጋር መልካም ልደት ሳትባል፣ ለወዳጅ ዘመድ ጥሪ የተጠመቀዉ ጠላ፣ ዳቦ፣ እንጀራ እና ወጥ ለሀዘንተኛ ማስተዛዘኛ መዋሉን ታዉቋል።

በመጨረሻም ፖሊስ ወላጆች የህፃናትን እንቅስቃሴ መከታተል እንዳለባቸዉ መልዕክቱን አስተላልፏል ሲል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን ዘገቧል።

«ምሳ ሰዓት ሲደርስ ከጊቢው ወጥቼ ምሳ እንደበላ ሰው ዞር ዞር ብዬ እመለሳለሁ፣ ደሞዜ 1700 ነው ከዛ ውስጥ 1400 ለቤት ኪራይ ከፍላለሁ» በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ የሚሰራ አ...
27/10/2023

«ምሳ ሰዓት ሲደርስ ከጊቢው ወጥቼ ምሳ እንደበላ ሰው ዞር ዞር ብዬ እመለሳለሁ፣ ደሞዜ 1700 ነው ከዛ ውስጥ 1400 ለቤት ኪራይ ከፍላለሁ»

በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ የሚሰራ አንድ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኛ በየጊዜው የምሳ ሰዓት ሲደርስ ስራውን አጠናቆ ለምሳ ሲወጣ እጁን በኪሱ ውስጥ ከቶ ከጊቢው ወጥቶ ሲሄድ እመለከታለው።

አንድ ቀን በተመሳሳይ ከጊቢ ወጥቶ የስራ ሰዓት ሲደርስ ሲመለስ አገኘሁትና ጠጋ ብዬ ጠየኩት።

ሁል ጊዜ ስመለከትህ ምሳ ሰዓት ከጊቢ ትወጣለህ ውጪ ነው ወይስ ቤትህ ሄደህ ነው ምሳ የምትበላው? በማለት ጠየኩት

''አይ አንቺ '' ብሎ ፈገግ አለ

የምሬን እኮ ነው አልኩት መልስ እየጠበኩ

''ዝም ብዬ ዞር ዞር ብዬ ነው የምመለሰው ያው ለሰዓት ማዳረሻ '' አለኝ

አልገባኝም አልኩት በድጋሚ

''አይ ታሪክዬ'' አለ በሀዘን ስሜት እየተዋጠ

ቀጠል አደረገና ''1700 ብር ነው የወር ደሞዜ ከዝች ደሞዜ ላይ የቆርቆሮ ቤት 1400 ብር ተከራይቼ ነው የምኖረው ታድያ በምሳ እቃ ምኑን ልቋጥር ፣ ከየትስ አምጥቼ ምግብ ቤት እገባለሁ ብለሽ ነው ያው ሰዓት እስኪደርስ ልደታ ቤተክርስቲያንን ተሳልሜ ትንሽ ቁጭ ብዬ ምሳ ተመግቤ እንደመጣ ሰው ዞር ዞር ብዬ ነው የምመለሰው'' አለኝ

''በቀን አንዴ ማታ ላይ ትንሽ ከተመገብን አይበዛብንም ብለሽ ነው ''

አለ በቀልድ መልክ እንዳልከፋው ለማስመሰል ፈገግ እያለ

ወዲያው ውስጤ በሀዘን ተሞላ ምነው ባልጠየኩት ብዬ እራሴን ወቀስኩኝ በዚህ መልኩ በተመሳሳይ ህይወት ውስጥ በፍርድ ቤቱ በድጋፍ ሰጪ ዘርፍ ላይ በሚከፈላቸው አነስተኛ ደሞዝ ህይወታቸውን እየገፉ ያሉ በርካቶች ናቸው። በዚህ ኑሮና በዚህ ደሞዝ ቤተሰብ የሚመሩ ህጻናት ልጆች ያሏቸውም ይገኛሉ።

የጠ /ሚ አብይ አህመድ ወደ ስልጣን መምጣትን ተከትሎ ለፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በኃላፊነት ተሹመው የነበሩት የቀድሞ የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊና ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሰለሞን አረዳ የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ችግራቸው ተረድተው '' ደሞዛችንን ያስተካክሉልን ይሆናል'' ብለው ተስፋ ያደረጉ ሰራተኞች በርካቶች ነበሩ።

ይሁንና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ደሞዝ በሚመለከት ምንም ማስተካከያ ሳይደረግ ሁለቱም ፕሬዝዳንቶች በገዛ ፍቃዳቸው ስራቸውን መልቀቃቸው ተሰማ።

ከዛ በኋላ ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህግ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር ነበሩ የተባሉት የቀድሞ ጠበቃ አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና ፣በዳኝነት ዘርፍ ላይ ለበርካታ ጊዜያት አገልግለዋል የተባሉት ወይዘሮ አበባ እምቢ አለ እንደ ቅደም ተከተላቸው ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ።

በጥር 15 ቀን 2015 ከቀድሞዎቹ ፕሬዝዳንቶች የስራ ኃላፊነት ርክክብ አድርገው ስራቸውን ጀመሩ ከዚህ በኋላ ደግሞ በድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ዘንድ ሌላ ተስፋ ተጫረ

ሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ/ ም ደግሞ ሌላኛው የፍርድቤቶች ሰራተኞችን ተስፋ የሰነቀ ፌሽታን የፈጠረ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 25ኛ መደበኛ ጉባዔው ላይ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሰራተኞች አስተዳደር ደንብ መፅደቁ ተሰማ ፣

ይህ ከተሰማ አሁን አምስት ወራት ተቆጠረ

ይሁንና ደንቡ ተግባራዊ ሆኖ ጠብ የሚል ነገር ይኖራል በሚል ተስፋ በተለመደው በኑሮ ጫና ውስጥ ሆነው የህይወታቸውን ውጣ ውረድ የሚገፉት ሰራተኞች ተግባራዊነቱን በተመናመነ ተስፋ እየተጠባበቁ ይገኛሉ።

ተስፋ የቆረጡት ደግሞ ስራቸውን እየለቀቁ የተሻለ እንጀራ ፍለጋ ላይ ተሰማርተዋል።

''ያም መጣ ይህ ለራሱ እንጂ ለኔ የሚያስብ የሚጠቅም የለም '' በማለት ፊታቸውን ወደ ፈጣሪ ያዞሩና ከነገ ዛሬ ይሻል ይሆን ብለው ፈጣሪያቸውን ተስፋ ያደረጉም አሉ።

ለማንኛውም የተቋማት መሪዎች በቤታችሁ ወይም በሆቴል ስትመገቡ፣ ስትዝናኑ፣ ውስኪም ስታፈሱ፣ በዝቅተኛ ደሞዝ የሚሰቃዩ ሰራተኞችን አስታውሱ እላለሁ።

በኔ በኩል አበቃሁ
ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
ሰላም ለሀገራችን ህዝብ ይሁን

“ግጭቱ ከቆመ ሁሉም ታጋቾች በቀናት ውስጥ ሊለቀቁ ይችላሉ” - የኳታር አደራዳሪበእስራኤል እና ሃማስ መካከል እየተደረገ ያለው ጦርነት ከቆመ በጋዛ ሰርጥ ታግተው የሚገኙ እስራኤላዊያን በቀናት...
27/10/2023

“ግጭቱ ከቆመ ሁሉም ታጋቾች በቀናት ውስጥ ሊለቀቁ ይችላሉ” - የኳታር አደራዳሪ

በእስራኤል እና ሃማስ መካከል እየተደረገ ያለው ጦርነት ከቆመ በጋዛ ሰርጥ ታግተው የሚገኙ እስራኤላዊያን በቀናት ውስጥ ሊለቀቁ እንደሚችሉ ታጋቾቹን የማስለቀቅ ንግግሩን እየመሩ ያሉት የኳታር አደራዳሪ ገልጸዋል፡፡

የእስራኤል የቦምብ ድብደባ እየጨመረ መምጣቱ ድርድሩን እንዳከበደባቸውም የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ እና ከፍተኛ አደራዳሪ ዶክተር ሞሐመድ አል ኩላይፊ ተናግረዋል፡፡

ሃማስ በእስራኤል ላይ ጥቃት በከፈተበት እለት ከ200 በላይ የእስራኤል እና የተለያዩ ሀገራት ዜጎችን ወደ ጋዛ ሰርጥ አግቶ መውሰዱ ይታወሳል፡፡

እስከ አሁን በተደረገው ድርድር አሜሪካዊት እናት ከነ ልጇ እና ሁለት እድሜያቸው የገፋ እስራኤላውያን ሴት አዛውንቶች ተለቀዋል።

ዶክተር ሞሐመድ “የእኛ ግብ ሁሉም ታጋቾች ነጻ እንዲወጡ ነው” ካሉ በኃላ ድርድሩ መልካም ውጤት እንዲያመጣ ጦርነቱ በአስቸኳይ መቆም እንዳለበት ማሳሰባቸውን ስካይ ኒውስ ዘግቧል፡፡

«ራሴን ለማጥፋት ሶስት ጊዜ አስቤ ነበር» ድምፃዊት ቬሮኒካ አዳነ  «እንደማንኛዉም ሰዉ ብዙ ችግር ዉስጥ አልፍያለዉ፣ የማያልፍ የሚመስሉ ጊዜያቶች አልፍያለዉ፣ መኖሬ ልክ አይደለም ብዬም አስ...
27/10/2023

«ራሴን ለማጥፋት ሶስት ጊዜ አስቤ ነበር» ድምፃዊት ቬሮኒካ አዳነ


«እንደማንኛዉም ሰዉ ብዙ ችግር ዉስጥ አልፍያለዉ፣ የማያልፍ የሚመስሉ ጊዜያቶች አልፍያለዉ፣ መኖሬ ልክ አይደለም ብዬም አስቤ አዉቃለዉ፣ ራሴን ለማጥፋትም ከአንድም ሁለት ሶስቴ ቁጭ ብዬ አስቤበትም አዉቃለዉ፣ ነገር ግን ራሴን አለማጥፋቴ በዛን ሰዓት ያልታየኝ የዛሬ ኑሮዬን እንድኖር አድርጎኛል።

ራስን ማጥፋት፣ ራስ ወዳድነት ነዉ፣ እኛ የምናስፈልጋቸዉን ሰዎች ለደቂቃም አለማሰብ ነዉ ልክ አይደለም ይሄንን ስፅፍ በደምብ አስቤበት ነዉ እና እባካቹ ህይወት የጨለመባችዉ መስሎ ከተሰማችዉ ያለሁበት ህይወት አይገባኝም ብላችዉ ከተሰማችዉ ፈተና ከተደራረበባችዉ ማርያምን እናንተ ትልቅ ቦታ ላይ ልደርሱ ነዉ፣ ይሄን ፈተና ብቻ እለፉት ፀልዩ እመኑኝ ሁሉም ያልፋል ነገ ትስቃላችሁ!»

ጫት ሲሰርቅ የተገኘው ግለሰብ ራሴን አጠፋለው ብሎ አንገቱ ላይ ከጠመጠመ በኋላ አመለጠ!  በማአከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን በጫት ስርቆት ወንጀል የተጠረጠረዉ ወጣት  በህብረተሰቡ  እጅ...
27/10/2023

ጫት ሲሰርቅ የተገኘው ግለሰብ ራሴን አጠፋለው ብሎ አንገቱ ላይ ከጠመጠመ በኋላ አመለጠ!


በማአከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን በጫት ስርቆት ወንጀል የተጠረጠረዉ ወጣት በህብረተሰቡ እጅ ከፍንጅ ከተያዘ በኋላ አንገቱ ላይ ሻርፕ አጥልቆ ታንቄ እራሴን አጠፋለሁ በማለት የሰዎችን የትኩረት አቅጣጫ አስቀይሮ ካመለጠ ከቀናት በኋላ በቁጥጥር ስር መዋሉ በዞኑ የዌራ ወረዳ ፖሊስ ገልጿል።

ተጠርጣሪ ጡምሶ ጎዲሌ ነዋርነቱ በዌራ ወረዳ የሶሪጌ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን በአይመሌ ቀበሌ ልዩ ስሙ መረጣ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ከአንድ ከግለሰብ መኖሪያ ቤት ጓሮ ማሳ ዉስጥ በመዝለቅ የጫት ስርቆት ሲፈፅም በአካባቢዉ ነዋሪዎች እጅ ከፍንጅ እንደተያዘና የያዦቹን ትኩረት የሚያስቀይር መላ ዘይዶ ማምለጡ ፖሊስ ገልጿል።

ክቡር የሆነዉ ሰዉ ህይወቱን ከሚያጣ እንደዉ የጫቱ ነገር ጥንቅር ብሎ በቀረብን በሚል ቁጭት የሟች አስክሬን ይመጣል ከመቼው ተገኝቶ ይመጣል በሚል እየተጠበቀ ነበር ወጣቱ በህይወት ኖሮ የተጠናወተዉ ሱስ ሊያስታግስ ወዲህ ወዲያ ሲያቅበዘበዝ በሰዎች እይታ ዉስጥ የገባዉ።

በወጣቱ አታላይነት የተገረሙተት ነዋሪዎች በአይነ ቁራኛ እየተከታተሉት ለፖሊስ ደዉለዉ ሞቷል የተባለዉ የጫት ቀበኛ አልሞተም በፍጥነት አባላት ይላኩልን ሲሉ በማሳወቃቸዉ የፖሊስ አባላትም ፈጥነዉ ከስፍራዉ በመገኘት በቁጥጥር ስር አዋሉት።

" እዉር ቢሸፍት እስከ ጓሮ ነዉ" እንዲሉ አይነት ሀገራዊ አባባል ሱሱን ለማስታገስና የዉስጡን ጥያቄ ለመመለስ ሲል በድፍረት አንድ ቀን ካልኮተኮተዉና ዉሃ ካላጠጣዉ ማሳ ዉስጥ ዘዉ ብሎ ገብቶ በፈፀመዉ ስህተት ህግ ፖሊስ በአፋጣኝ ምርመራ አጣርቶ ፍርድ ቤት ያቀርበዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ዘገባው የማዕካላዊ ኢትዮጵያ ፖሊስ ነው

የ16 ሚሊዮን ብር እድለኛ አፋልጉኝ   | 20 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው ይህ እጣ ባሳለፍነው ጷግሜ 2015 ዓም እጣው የወጣ ሲሆን 1820259 ደግሞ የመጀመሪያ እድለኛ ቁጥር እንደሆነ በወቅ...
27/10/2023

የ16 ሚሊዮን ብር እድለኛ አፋልጉኝ

| 20 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው ይህ እጣ ባሳለፍነው ጷግሜ 2015 ዓም እጣው የወጣ ሲሆን 1820259 ደግሞ የመጀመሪያ እድለኛ ቁጥር እንደሆነ በወቅቱ ተገልጿል።

የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድር ኮሙንኬሽን ዳይሬክተር አቶ ቴድሮስ ንዋይ እንዳሉት "ባሳለፍነው ጷግሜ ላይ የወጣው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ አሸናፊ እስካሁን አልመጣም" ብለዋል።

ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድሩ ይህን አሸናፊ እድለኛ እስከ ቀጣዩ የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ካልመጣ ወይም ካልመጣች ገንዘቡ ለመንግሥት ገቢ ይሆናልም ብለዋል።

20 ሚሊዮን ብር ከሚያሸልመው እጣ ቁጥር ውስጥ አንድ እጣ ያላው አንድ ሰው መጥቶ አራት ሚሊዮን ብሩን ወስዷል ያሉት አቶ ቴዎድሮስ 16 ሚሊዮን ብር የሚያሸልም ሶስት እጣዎች ያለው ወይም ያላት ሰው እስካሁን አልመጡም ሲሉም አክለዋል።

ሎተሪ እጣ ቆርጠው ቲኬቱን ደግመው እጣው ስለመውጣቱ እና አለመውጣቱን የማያረጋግጡ የሎተሪ ደንበኞች ስለሚኖሩ እጃቸው ላይ ያለውን ሎተሪ በድጋሚ እንዲያስተያዩም አቶ ቴድሮስ አሳስበዋል።

ከሶስት ዓመት በፊት አንድ የ20 ሚሊዮን ብር ሎተሪ ተሸላሚ ግለሰብ የሽልማት ጊዜው ሊያበቃ አምስት ቀናት ብቻ ሲቀረው መጥቶ እጁ ላይ በተገኘው ሶስት ሎተሪዎች መሰረት 16 ሚሊዮን ብሩን መውሰዱ ይታወሳል።

 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ ከሚማሩት ትምህርት ውጪ ወደ ተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ሔደው ለሚያደርጓቸው የተግባር ላይ ልምምዶች የሚደረግ ወጪ÷ ከምርቃት በኋላ በሚከፍሉት የወጪ...
27/10/2023



የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ ከሚማሩት ትምህርት ውጪ ወደ ተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ሔደው ለሚያደርጓቸው የተግባር ላይ ልምምዶች የሚደረግ ወጪ÷ ከምርቃት በኋላ በሚከፍሉት የወጪ መጋራት ውስጥ እንዲካተት ጥናት መጀመሩ ተገለጸ፡፡

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የወጪ መጋራት (Cost Sharing) መመርያ መሠረት ወደ መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተቀላቀሉ አዳዲስ ተማሪዎች÷ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ ተመርቀው እስኪወጡ ድረስ፣ መንግሥት ለምግብና ለመኝታ ያወጣውን ወጪ በሚገቡት ውል መሠረት ከምርቃት በኋላ ግዴታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተደንግጓል፡፡

ተማሪዎች ወደ ተግባር ልምምድ ሲወጡ ለሚቆዩባቸው ጊዜያት ለሚኖራቸው የተግባር ላይ ትምህርት፣ ከምረቃ በኋላ ከወጪ መጋራት ጋር ተደምሮ እንዲከፍሉ ለማድረግ የትምህርት ሚኒስቴር ዕቅድ መያዙንና ጥናት መጀመሩን፣ በትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ተሾመ ዳንኤል ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል፡፡

ሐሳቡ በጥናት ላይ መሆኑንና ዓላማውም ወደፊት ተማሪዎች የተግባር ላይ ልምምድን ትኩረት ሰጥተው እንዲማሩ ለማድረግ በማሰብ የታቀደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ይሁን እንጂ ለክፍያው የልማት አጋር ድርጅቶች ለትምህርት ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች ትስስር የሚመድቡት ገንዘብ ስለሚኖር፣ ከዚህ ገንዘብ ለወጪ መጋራት ሊከፈል የሚችልበት አሠራርም ሊዘረጋ እንደሚችልም አስረድተዋል፡፡

መረጃው የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

በውክልና መስተናገድ ማሻሻያ ተደረገበትበውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ አካል ጉዳተኛ የሆኑ ዜጐች በህመም ምክንያት መንቀሳቀስ ለማይችሉ በልዩ ሁኔታ በውክልና እንዲስተናገዱ ተፈቅዷልየመሬት...
30/10/2022

በውክልና መስተናገድ ማሻሻያ ተደረገበት

በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ አካል ጉዳተኛ የሆኑ ዜጐች በህመም ምክንያት መንቀሳቀስ ለማይችሉ በልዩ ሁኔታ በውክልና እንዲስተናገዱ ተፈቅዷል

የመሬት አገልግሎት በውክልና የሚሰጥበትን አግባብ ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ በተለያየ መንገድ እየተፈፀመ ያለውን ህገ ወጥ የቤትና ተያያዥ ሽያጭ ለመቆጣጠርና ስርአት ለማስያዝ ከመስከረም 11 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ማንኛውም መሬትና መሬት ነክ አገልግሎቶች የይዞታው ባለቤት በአካል ሳይቀርብ በውክልና እንዳይሰጥ በቁጥር አከዕ/03 04:110 በ01:5 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ መታገዱ ይታወታል።

ሆኖም በቀጣይ ህገ ወጥነትን በአሰራር ለመዘጋት የተጀመረው ሥራ እስኪጠናቀቅ ድረስ ህጋዊ ሆነው ውክልና መስጠት የግድ የሆነባቸው በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ አካል ጉዳተኛ የሆኑ ዜጐች በህመም ምክንያት መንቀሳቀስ ባለመቻላቸው በአካል መገኘት የማይችሉ ዜጐች የመስተንግዶ ጥያቄአቸውን ለመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቅርበው ህጋዊነታቸው እየተረጋገጠ በልዩ ሁኔታ በውክልና እንዲስተናገዱ መመሪያ ተላልፏል።

ቀጣሪዋን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድላ ተሰወረች•  ተጠርጣሪዋ በፖሊስ እየታደነች ነው ተብሏል  | ቦታው እዚህ አዲስ አበባ፣ አስኮ አዲሱ ሰፈር አካባቢ ነው፡፡ ትናንት ከቀኑ 5 ሰዓት ገደማ ሲሆን፤...
29/10/2022

ቀጣሪዋን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድላ ተሰወረች

• ተጠርጣሪዋ በፖሊስ እየታደነች ነው ተብሏል

| ቦታው እዚህ አዲስ አበባ፣ አስኮ አዲሱ ሰፈር አካባቢ ነው፡፡ ትናንት ከቀኑ 5 ሰዓት ገደማ ሲሆን፤ አንዲት የቤት ሠራተኛ ቀጣሪዋን በአሰቃቂ ሁኔታ፣ በቢላና በዘነዘና ገድላ መሰወሯን፣ ቤተሰቦቿ ለ #አዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡

ተጠርጣሪዋ በፖሊስ እየታደነች ነው ተብሏል፡፡

የቤት ሰራተኛዋ በሟች ወ/ሮ ፋሲካ ተሾመ ቤት ውስጥ ተቀጥራ ለአንድ ዓመት ከ6 ወር መሥራቷን የጠቆሙት ቤተሰቦቿ፤ እስካሁን ቀጣሪዋን የገደለችበት ምክንያት አለመታወቁን ነው የገለጹት፡፡

የ60 ዓመቷ ሟች ወ/ሮ ፋሲካ፣ የሁለት ልጆች እናት ሲሆኑ፤ በትናንትናው ዕለት ቤታቸው ውስጥ ብቻቸውን ሳሉ ነው በቤት ሰራተኛቸው በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት ተብሏል፡፡

ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን ከፈጸመች በኋላ እቃዎቿን ሸክፋና በሟች ላይ በር ዘግታ ከአካባቢው መሰወሯን ነ ው ቤተሰቦች የገለጹት፡፡

በምስሉ ላይ የምትታየውን ተጠርጣሪ ወንጀለኛ በየትም ቦታ ያየ ፣ ለፖሊስ በመጠቆም በቁጥጥር ሥር እንድትውል ይተባበር ዘንድ የሟች ቤተሰቦች ተማጽነዋል፡፡

29/10/2022
 #እንድታውቁትየኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የፌስቡክ ገጹ (ከ2.1 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያለው) ከቁጥጥሩ ውጭ መሆኑን አስታውቋል።አየር መንገዱ ፤ ደንበኞች እንዲሁም የገጹ ተከታታዮች በፌ...
29/10/2022

#እንድታውቁት

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የፌስቡክ ገጹ (ከ2.1 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያለው) ከቁጥጥሩ ውጭ መሆኑን አስታውቋል።

አየር መንገዱ ፤ ደንበኞች እንዲሁም የገጹ ተከታታዮች በፌስቡክ ገጹ የሚተላለፉ ማንኛውም መልዕክቶች የአየር መንገዱ አለመሆኑን ገልጿል፡፡

ችግሩን ለመፍታት በአሁኑ ሰዓት ከሜታ ኩባንያ ጋር እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።

TIKVAH-ETH

⚽️⚽️እየተሰፋ ነው 🥺 በቅድስ ጊዮርጊስ ና ፋሲል ጨዋታ ላይ የተከሰተመረቡ ተቀዶ በዳኛው በመርፌና ክር ከሰፋው በኋላ ጨዋታው ቀጥሏል::
26/10/2022

⚽️⚽️
እየተሰፋ ነው 🥺

በቅድስ ጊዮርጊስ ና ፋሲል ጨዋታ ላይ የተከሰተ

መረቡ ተቀዶ በዳኛው በመርፌና ክር ከሰፋው በኋላ ጨዋታው ቀጥሏል::

ወላይታ ድቻ የቀድሞው ሥራ አስኪያጁን ወደ ኃላፊነት አምጥቷል።በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2015 የውድድር ዘመን አጀማመራቸው ካላማሩ ክለቦች መካከል አንዱ ወላይታ ድቻ ይጠቀሳል፡፡...
25/10/2022

ወላይታ ድቻ የቀድሞው ሥራ አስኪያጁን ወደ ኃላፊነት አምጥቷል።

በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2015 የውድድር ዘመን አጀማመራቸው ካላማሩ ክለቦች መካከል አንዱ ወላይታ ድቻ ይጠቀሳል፡፡ ካደረጋቸው ሦስት ጨዋታዎች በሁለት አቻ እና በአንድ ሽንፈት በደረጃ ሰንጠረዡ 15ኛ ላይ ተቀምጦ የሚገኘው ክለቡ የቀድሞው ስራ አስኪያጁን ወደ መንበሩ በድጋሚ መልሷል፡፡

በቅርቡ የክለቡ ሥራ አስኪያጅ የነበሩትን አቶ ወንድሙ ሳሙኤልን ከቦታው ያነሳው በተለያዩ ጊዜያትም ሥራ አስኪያጆችን ሲለዋውጥ የሚታየው ወላይታ ድቻ በሊጉ እያስመዘገበ ካለው ውጤት እንዲሁም ደግሞ በአስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመድፈን በማሰብ በቦታው አዲስ ሹመት አስፈልጎታል። በዚህም ክለቡን ከምሰረታው ጀምሮ እስከ 2012 ድረስ በሥራ አስኪያጅነት እና በቡድን መሪነትም ጭምር ሲመሩ የነበሩትን እና በአሁኑ ሰዓት የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር የቦርድ አባል የሆኑትን አቶ አሰፋ ሆሲሶን በቀደመው የሥራ አስኪያጅነት ቦታ መመለሱን ለሶከር ኢትዮጵያ በላከው መረጃ አመላክቷል፡፡

25/10/2022
ወቅታዊው እና አሳሳቢው የወጣቱ የመድኃኒት ሱስ።ወጣቱ ትውልድ በአሁኑ ጊዜ አለአግባብ እየተጠቀመባቸው ከሚገኙ መድኃኒቶች ውስጥ ትራማዶል (Tramadol) አንዱ ሲሆን በተለይም የመድኃኒት ችር...
25/10/2022

ወቅታዊው እና አሳሳቢው የወጣቱ የመድኃኒት ሱስ።

ወጣቱ ትውልድ በአሁኑ ጊዜ አለአግባብ እየተጠቀመባቸው ከሚገኙ መድኃኒቶች ውስጥ ትራማዶል (Tramadol) አንዱ ሲሆን በተለይም የመድኃኒት ችርቻሮ ተቋማት በስፋት በሚገኙባቸው በከተሞች አካባቢ ችግሩ ጎልቶ የሚታይ ሲሆን ይህም ጉዳይ በወቅቱ ካልተቀጨ አሳሳቢ ወደ ሚባል ደረጃ ሊጨምር ይችላል፡፡

ከህክምና ዓላማ ውጪ ትራማዶልን የሚጠቀመው የወጣት ቁጥር ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ የመጣ ሲሆን ወጣቶች በቀጥታ ወደ መድኃኒት ችርቻሮ ተቋማት በመሄድ ትራማዶልን በቀላሉ እንዲገዙ ምክንያት ሆኗል፡፡

ትራማዶልን ከጤና ባለሙያ ትዕዛዝ ያለ ማዘዣ መውሰድ ወይም ከታዘዘ ጥንካሬ እና መጠን ብዙ ጊዜ መውሰድ ወይም ከተዘዘለን ጊዜ ገደብ ውጭ ለረጅም ጊዜ መውሰድ ለሱሰኝነት ያጋልጣል፡፡ የተለያዩ ጥናቶች ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ አገራት ትራማዶል አዕምሯዊ እና አከላዊ ሱስ እንደሚያስይዝ ያሳያሉ፡፡ስለዚህ በኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት አዋጅ ቁ.1112/2011 ናርኮቲክ መድኃኒት” ማለት በተባበሩት መንግሥታት በወጣው እና ኢትዮጵያ ባፀደቀችው የናርኮቲክ መድኃኒቶች ስምምነት መሠረት ቁጥጥር የሚደረግበት መድኃኒት ሆኖ በአስፈጻሚ አካሉ እንደ ናርኮቲክ መድኃኒትነት የተመደበ መድኃኒትን ማጠቃለሉን የሚገልፅ በመሆኑ ትራማዶል በናርኮቲክ መድኃኒትነት የተመደበ ነው፡፡
ትራማዶልን ከህክምና ዓላማ ውጪ መውሰድ ለከፍተኛ የጤና ጉዳት ያስከትላል። መድኃኒቱን ከሀኪም ትዕዛዝ ውጪና ያለአግባብ መጠቀም ዋናው ጉዳት መላመድና ሱሰኝነትን በማምጣት ለግለሰቡም ሆነ ለሀገር የሚያስከትለው ጉዳት እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ የኢትዮጵያ ምግብና መደኃኒት ባለስልጣን ክትትል ከሚደረግባቸው መደኃኒቶች መዘርዝር ውስጥ ተካትቷል። ከዚህ በተጨማሪም የምግብ ፍላጎት ማጣት፤ ከፍተኛ የራስ ምታት፤ የሰውነት ላብ፤ እረፍት ማጣት፤ እንቅልፍ ማጣት፤ የድካም ስሜት፤ ማስመለስ ሊያመጣ የሚችል ሲሆን በተለይ መድኃኒቱን መውሰድ ለማቆም መቸገር ከጤና አንጻር ሊከሰቱ የሚችሉ ጉዳቶች የማህበራዊ ቀውስና ለተለያዩ ወንጀሎች ተጋላጭ መሆን፤ ለድህነት እና ለተጓደለ ጤና መንስኤ ያጋልጣል፡፡

ትራማዶል የሚባለው መድኃኒት በመድኃኒት ችርቻሮ መሸጫ ተቋማት ላይ በዘፈቀደ እንዳይሸጥ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በተለያየ ጊዜ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን በመውሰድ በልዩ መድኃኒት ማዘዣ ብቻ እንዲሽጥ ለሁሉም የክልል ጤና ተቆጣጣሪዎች እንዲያውቁት በማድረግ ጥብቅ ክትትል እየተደረገ ይገኛል ፡፡

በመሆኑም ሁላችንም ትውልድን ለመታደግ ሕጉን ያላከበረ ተግባር ካስተዋሉ ለኢትዮጵያ ምግብና መደኃኒት ባለስልጣን በነፃ የስልክ መስመር 8482 እንዲያሳውቁ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ሞባይል ጠጋኙ ግለሰብ የ20 ሚሊዮን ብር አሸናፊ ሆነ፡፡ነዋሪነቱ አዲስ አበባ የሆነው  በእንቁጣጣሽ ሎተሪ 20 ሚሊዮን ብር አሸናፊ ሆኗል። አቶ ማትያስ ግርማ ዕድለኛ የሆነው ጳጉሜ 5 ቀን 2...
25/10/2022

ሞባይል ጠጋኙ ግለሰብ የ20 ሚሊዮን ብር አሸናፊ ሆነ፡፡

ነዋሪነቱ አዲስ አበባ የሆነው በእንቁጣጣሽ ሎተሪ 20 ሚሊዮን ብር አሸናፊ ሆኗል። አቶ ማትያስ ግርማ ዕድለኛ የሆነው ጳጉሜ 5 ቀን 2014 የወጣውን የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ነው።

የ40 ዓመቱ የ20 ሚሊዮን ብሩ ዕድለኛ በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ወረዳ 11 ነዋሪ ሲሆን ላለፉት 30 ያህል ቀናት ብሔራዊ ሎተሪ እድለኛውን ሲፈልግ ነበረ።

ሐዋሳ ፒያሳ 🚘 ዛሬ ጥዋት 3 ስአት አካባቢ ፒያሳ ሐሮን እንቴርናሽል ሆቴል ፊት ለፊት ይህ መኪና በፍጥነት እያሽከረከረ ሲሄድ እንዲህ እንደምታዩት ተገልብጧልሰዎችም መኪናውን ገልብጠው አባት ...
23/10/2022

ሐዋሳ ፒያሳ 🚘

ዛሬ ጥዋት 3 ስአት አካባቢ ፒያሳ ሐሮን እንቴርናሽል ሆቴል ፊት ለፊት

ይህ መኪና በፍጥነት እያሽከረከረ ሲሄድ እንዲህ እንደምታዩት ተገልብጧል

ሰዎችም መኪናውን ገልብጠው

አባት ና ልጅን ምንም ሳይሆኑ በሰላም አውጥቷዎቸዋል::

Via Abebayehu Assefa

እረ እየተጠነቀቅን ስንነዳ

🥺

ታማኝነት በተግባር!አቶ ደመላሽ ዲዳሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይርጋዓለም ቅርንጫፍ የጥበቃ ሠራተኛ ናቸው። በዕለተ ዐርብ በቀን 11/02/2015 ዓ.ም የባንኩ የረጅም ጊዜ ደንበኛና የቡና ነጋ...
23/10/2022

ታማኝነት በተግባር!
አቶ ደመላሽ ዲዳሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይርጋዓለም ቅርንጫፍ የጥበቃ ሠራተኛ ናቸው።
በዕለተ ዐርብ በቀን 11/02/2015 ዓ.ም የባንኩ የረጅም ጊዜ ደንበኛና የቡና ነጋዴ የሆኑት አቶ ከድር አህመድ ለስራ በመጣደፍ ከባንኩ ያወጡትን አንድ መቶ ሺ ብር ይዘው በችኮላ መኪናቸው ውስጥ አስገብተው በሩን ሲዘጉት ብሩ መሬት ላይ መውደቁን አላወቁም ነበርና በቀጥታ ወደ ስራቸው መኪናቸውን አስነስተው ሄዱ።

አጋጣሚ ሆኖ ምንም እንኳ ገንዘቡ በፌስታል እንዳለ ከባንኩ ፊትለፊት ባለው አስፋልት ላይ ቢወድቅም ቀድመው ያዩትና ያነሱት ጥበቃው አቶ ደመላሽ ነበሩ።
ይሁንና ለራሳቸው ሳይመኙ አስቀጠውት ካቆዩ በኋላ ደንበኛውን ጠርተው አስረክበዋል።
ደንበኛውም በደስታ ወሮታውን ከፍለው አመሰግነው ገንዘባቸውን ተረክበዋል ።
መልካም ስም ከመልካም ሽቶ ይበልጣል።

የማላዊ ፖሊስ የ25 ኢትዮጵያዊያንን አስክሬን አወጣ፣ 72 የሚሆኑትን አሰረ   |ቅድመ ምርመራ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን እንደሚያሳይ ተገልጿል የማላዊ ፖሊስ በሰሜን ማላዊ ምዚምባ ወረዳ...
22/10/2022

የማላዊ ፖሊስ የ25 ኢትዮጵያዊያንን አስክሬን አወጣ፣ 72 የሚሆኑትን አሰረ

|ቅድመ ምርመራ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን እንደሚያሳይ ተገልጿል

የማላዊ ፖሊስ በሰሜን ማላዊ ምዚምባ ወረዳ በሚገኘ ደን ውስጥ በጅምላ ተቀብረው የተገኙ ኢትዮጵያዊያን ናቸው የተባሉ 25 ወንዶች የውጭ አገር ዜጎች አሟሟት እያጣራ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ፖሊስ እንደገለጸው የመንደሩ ነዋሪዎች የጅምላ መቃብሩን ያገኙት በጫካው ውስጥ የዱር ነፍሳትን በማደን ላይ እያሉ መሆኑ ተመልክቷል፡፡

በሟቾቹ ላይ የተደረገው ቅድመ ምርመራ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን እንደሚያሳይ ተገልጿል፡፡

ፒተር ካላያ የማላዊ ፖሊስ አገልግሎት ቃል አቀባይ ይህንን ሲያስረዱ “የእነዚህን ሰዎች ስምና ዜግነት የሚያመለክቱ ሁለት ጊዜያዊ የጉዞ ሰነዶችን አግኘተናል፡፡

***
25 ኢትዮጵያውያን በማላዊ "ሞተው ተገኝተዋል" በሚል የተሰራጨውን ዘገባ እያጣራሁ ነው !

~ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ምዚምባ በሚባለው የማላዊ ሰሜናዊ ግዛት በሚገኝ ጥብቅ ደን ውስጥ በተገኘ የጅምላ መቃብር የኢትዮጵያውያን ስደተኞች አስክሬን እንደተገኘ የሀገሪቱን ፖሊስ ዋቢ አድርገው የተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን መዘገባቸው ይታወሳል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ባውጣው መግለጫም÷25 ኢትዮጵያውያን በማላዊ "ሞተው ተገኝተዋል" በሚል የተሰራጨውን ዘገባ ከማላዊ መንግሥት ጋር በመሆን እያጣራ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ወይኔ ዜና 🙆‍♂️😳😳  ኢትዮጵያ ወስጥ የሚገኙ የቤቲንግ አወራራጅ ድርጅቶች እጅግ ትርፋማ እየሆኑ አንደመጡና በባንኮች ዉሰጥ በርካታ ሚሊዮኖች እያንቀሳቀሱ እንደሆነ  AFRICA INSIDER ...
21/10/2022

ወይኔ ዜና 🙆‍♂️😳😳

ኢትዮጵያ ወስጥ የሚገኙ የቤቲንግ አወራራጅ ድርጅቶች እጅግ ትርፋማ እየሆኑ አንደመጡና በባንኮች ዉሰጥ በርካታ ሚሊዮኖች እያንቀሳቀሱ እንደሆነ AFRICA INSIDER የተባለዉ የዜና አዉታር ከሰሞኑ ዘግበዋል።😳😳

በአፍሪካ የሚገኙ በርካታ የአወራራጅ ድርጅቶችም አይናቸዉን ወደ ኢትዮጵያ እንደ ጣሉ እና በርካቶች ወደ ኢትዮጵያ ገብተዉ መስራት እንደሚፈልጉ እየተነገረ ይገኛል።

እኔ በግሌ በርካቶች ለት/ቤት የሚሰጣቸዉን ክፍያ ጨምሮ ስልኮቻቸዉን በማሲያዝ ደሞዛቸዉን ጭምር ሙሉ በመሉ መስዋዕት አድርገዉ ሲበሉ አዉቃለዉ... 🥺

⁉️ ቤቲንግ ምን ያህል ጠቃሚ ወይስ ጎጂ ነዉ ብለቹ ታስባላቹ?? እስኪ ከቤቲንግ ጋር የገጠማቹን ወይም የሰማቹትን አጫዉቱን ለሌሎች መማሪያ ይሆናል??

በአዲስ አበባ ፒያሳን ካቀኑት መካከል አንዱ የሆኑት ወ/ሮ ደሀብ በ97 አመታቸው ለሊቱን ከዚህ አለም የተለዩ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸው ዛሬ በ9 ሰአት በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክር...
20/10/2022

በአዲስ አበባ ፒያሳን ካቀኑት መካከል አንዱ የሆኑት ወ/ሮ ደሀብ በ97 አመታቸው ለሊቱን ከዚህ አለም የተለዩ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸው ዛሬ በ9 ሰአት በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ይፈፀማል። በፒያሳ የሚገኘው ደሐብ ሆቴላቸው ህንፃ ከ1920 አንስቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየና በቅርስነት የተመዘገበ ነው።
ነፍስ ይማር!

እግዚኦ የወንድ ልጅ ፈተና??አሳዛኙ አጋጣሚ 😢ይሄ ወንድማችን የሚወዳትን ልጅ ለማግባት፣ጓደኞቹን ጠርቶ፣እሺ ስትል አጨብጭቡ በማለት አንድ የመዝናኛ ቦታ ዝግጅቱን አጠናቆ ተገኝቷል።ልጅት ሆዬ ...
20/10/2022

እግዚኦ የወንድ ልጅ ፈተና??
አሳዛኙ አጋጣሚ 😢

ይሄ ወንድማችን የሚወዳትን ልጅ ለማግባት፣ጓደኞቹን ጠርቶ፣እሺ ስትል አጨብጭቡ በማለት አንድ የመዝናኛ ቦታ ዝግጅቱን አጠናቆ ተገኝቷል።

ልጅት ሆዬ አገር ሰላም ነው ብላ ፍቅረኛዋ የቀጠራት ቦታ መገኘት።

እሱ እንደተዘጋጀው ከመምጣቷ በርከክ ብሎ በሚል ተስፋ ቀለበቱን መዥረጥ አደረገና ጠየቃት።

አጅሪት ታዲያ ብላው እርፍ።ወንድማችንም ኩምሽሽ፣ታዳሚው ብርግግ፣ካሜራዎች ቀጭ ቀጭ ብለው ሁነቱ ተጠናቋል😢

ቤተክርስቲያን ውስጥ ገብቶ መኪና ሊሰርቅ ሲል የተያዘው ሌባሾላ የካ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ጊቢ ውስጥ ዛሬ ከስአት 9:00 አካባቢ በተመሳሳይ ቁልፍ መኪና ሊሰርቅ ሲልለቀብር የመጣው የመኪናውን...
20/10/2022

ቤተክርስቲያን ውስጥ ገብቶ መኪና ሊሰርቅ ሲል የተያዘው ሌባ

ሾላ የካ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ጊቢ ውስጥ

ዛሬ ከስአት 9:00 አካባቢ በተመሳሳይ ቁልፍ መኪና ሊሰርቅ ሲል

ለቀብር የመጣው የመኪናውን ባለቤት እጅ ከፍንጅ ይዟታል

የመኪናው ባለቤት ሌባውን
መጀመሪያ እሽት ካደረገው በኃላ

ለፖሊስ አስረክቧት::

ድፍረቱ ግን አይገርምም
ከእምነት ቦታ ላይ ሄዶ ለመስረቅ መሞከሩ

ሌብነት ተፀየፉ

😡😡😡

መልስ ሰጠችበት 😎ቬሮኒካ :- ጥሩ እልል ያልኩኝ እህት እሆንሀለው 🥺🥺👉አፍቃሪ ብሩክ ናዝራዊ  እና ተፈቃሪ ቬሮኒካ አዳነ አሁን ታዲያስ አዲስ ላይ እያወሩ ነው የልጁ ልቅሶ 😎የእሷ ሳቅ! 🥺በ...
18/10/2022

መልስ ሰጠችበት 😎

ቬሮኒካ :- ጥሩ እልል ያልኩኝ እህት እሆንሀለው 🥺🥺

👉አፍቃሪ ብሩክ ናዝራዊ እና ተፈቃሪ ቬሮኒካ አዳነ

አሁን ታዲያስ አዲስ ላይ እያወሩ ነው
የልጁ ልቅሶ 😎
የእሷ ሳቅ! 🥺

በመጨረሻ ግን ድምፃዊ ቬሮኒካ

ለአፍቃሪዋ ብሩክ ጥሩ እህት እሆናለሁ ብላዋለች::

Via Nati Manafe

በአርባምንጭ ከተማ በስሙ አደባባይ የተሰየመለት ድምፃዊአብሌ ጨዶ መስከረም 1/1957 ዓ.ም በጨንቻ ወረዳ በዶርዜ ሃይዞ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ተወለደ። በ1984 ዓ.ም በዞኑ ፖሊስ ኦርኬስትራ ...
18/10/2022

በአርባምንጭ ከተማ በስሙ አደባባይ የተሰየመለት ድምፃዊ
አብሌ ጨዶ መስከረም 1/1957 ዓ.ም በጨንቻ ወረዳ በዶርዜ ሃይዞ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ተወለደ። በ1984 ዓ.ም በዞኑ ፖሊስ ኦርኬስትራ ውስጥ በድምጻዊነት ተቀጠረ።

ዘመን ተሻጋሪ የሆኑ ሦስት የጋሞኛ የዘፈን አልበም/ በካሴት ሰርቶ ከአድማጭ ጆሮ አድርሷል ።

አርቲስት አብሌ ጨዶ ሥራውን አክባሪ ፣ሀገሩን ወዳድ በ1992 ዓ.ም ግንባር ዘምቶ ሰራዊቱን በሙዚቃ ሥራው ያነቃቃ ጀግና ነበር።

አብሌ በሙዚቃ ሥራዎች የዞኑን የተፈጥሮ መስህብ ፣ ባህላዊ እሴቶች (ሰርግ ፣ ስለእውነት ፣ ስለቁንጅና ፣ስለአንድነት ወዘተ . . .) በተስረቅራቂ ድምጹ ፣ በልዩ የመድረክ እንቅስቃሴው ተጫውቷል።

የጋሞ ዞን በርካታ ታሪካዊ ተፈጥሯዊ እሴቶች ለዘመናት ሳይዘከሩ የቆዩትን Nu derey Gaamo Gofa Ooychcha Arbamincce በሚለው አልበሙ ለዓለም ያስተዋወቀ ጀግና አርቲስት ነው።

በማህበራዊ ሕይወቱ የሚታወቅ ተወዳጅ እና ከሁሉም ጋር ተግባቢ አርቲስትም ነበር።
አራተኛ ካሴቱን በመስራት ላይ እያለ ነሐሴ 11/1996 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

የጋሞ ዞን እና የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር አቢሌ ጨዶ ለዞኑ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በገንዘብ ፣ በአይነት ለቤተሰቡ ድጋፍ ሲያደርግላቸው ቆይቷል።

በህይወት ዘመኑ አይረሴ የአከባቢውን ገጽታ ፍንትው አድርጎ ሁሌም ዘመን በማይሽራቸው ባህላዊ ሙዚቃዎች በመረዋ ድምጹ ያቀነቀነ በመሆኑ በጋሞ ዞን 2015 ዓ.ም ዘመን መለወጫ ዮ-- ማስቃላ በዓል ላይ አርቲስት አብሌ ጨዶ በኪነ ጥበብ ዘርፍ ልዩ ክብር ተሸላሚ በማድረግ በአርባምንጭ ከተማ ከለምለም ሆቴል ፊት ለፊት የሚገኘው አደባባይ በስሙ ተሰይሟል ።
መረጃው የጋሞ ኮሚኒኬሽን ነው

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Smartmereja.net posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share