03/06/2022
በእስራኤል ቴላቪቭ የኢትዮጵያን መንግስት የሚያወግዝ ሰልፍ ተካሄደ
በኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ዕጥረት በከፋተኛ ሁኔታ መከሰቱን ተከትሎ የግል ባንኮች ከአንድ ዶላር 30 ብር ኮሚሽን እየተቀበሉ መሆኑ ተገለፀ።
ከሰሞኑን "በህግ ማስከበር" ሽፋን በኢትዮጵያ በንፁሃን አማሮች፣የፋኖ አባላት እና አመራሮች፣በጋዜጠኞች፣የማህበረሰብ አንቂዎች እና ጦማሮች፣በሙሁራን፣በፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ባጠቃላይ በንፁሃን ዜጎች ላይ የሚደረገውን አፈና በመቃውም በእስራኤል ቴላቪቭ ሰልፍ ተካሄደ።
"እኔም ፋኖ ነኝ፤በአማራ ላይ የሚደረገው የዘር ጭፍጨፋ ይቁም፤! በግፋ የታፈኑ እስረኞች ይፈቱ!ገዥው ስርዕት ይበቃዋል" የሚሉ ድምጿች በሰልፉ ተሰምተዋል።
የግል ንግድ ባንኮች ለምርት አስመጭ ደንበኞቻቸው የውጭ ምንዛሬን ለመፍቀድ በአንድ የአሜሪካ ዶላር እስከ 30 ብር ኮሚሽን እያስከፈሉ መሆኑን ተገለፀ።
አስመጭዎች እንደነገሩን በተለያዩ የግል ንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬን ለማስፈቀድ የአንድ የአሜሪካ ዶላር ይፋዊ የመሸጫ ዋጋው 52 ብር ከ64 ሳንቲም እንዳለ ሆኖ ኮሚሽን 30 ብር በመጨመር ለእያንዳንዱ የአሜሪካ ዶላር 82 ብር ይከፍላሉ።
የውጭ ምንዛሬ ሽያጩ እየተከናወነ ያለውም የምንዛሬ ፈላጊዎችን ምርት ወደ ውጭ ልከው የውጭ ምንዛሬ ካላቸው ሌሎች የባንክ ደንበኞች ጋር በማገናኘት ነው። ለእያንዳንዱ የውጭ ምንዛሬ የሚከፈለው ኮሚሽንም ባንኮቹ እና የውጭ ምንዛሬ ያላቸው ሰዎች የሚከፋፈሉት ይሆናል።
ለአንድ የአሜሪካ ዶላር የሚከፈለው ኮሚሽን ከምንዛሬው ይፋዊ ዋጋ ከ50 በመቶ በላይ መሆኑም በሀገሪቱ የተፈጠረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ያሳየ መሆኑ ተገልጿል።
#ድልለኢትዮጵያ