ETHIO_Post

ETHIO_Post Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ETHIO_Post, Media/News Company, .

27 ቀናት ብቻ ቀረ!እኔና ቤተሰቦቼ ሰኔ 12/2015 ህዝበ ውሳኔ ድምጽ ለመስጠት ወስነናል፡፡     ሰኔ 12 አንቀርም!   በነቂስ ወጥተን እንመርጣለን!!
23/05/2023

27 ቀናት ብቻ ቀረ!
እኔና ቤተሰቦቼ ሰኔ 12/2015 ህዝበ ውሳኔ ድምጽ ለመስጠት ወስነናል፡፡
ሰኔ 12 አንቀርም!
በነቂስ ወጥተን እንመርጣለን!!

ምርጫ ቦርድ የወላይታ ህዝብን ድምጽ ባላከበረ ሁኔታ የወሰነውን ውሳኔን ተከትሎ በከፍተኛ ፍርድቤት ቢከሰስ ህዝቡ እንደሚያሸንፍ ተገለጸየወላይታ ህዝብ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ፣ የድምጽ አ...
07/03/2023

ምርጫ ቦርድ የወላይታ ህዝብን ድምጽ ባላከበረ ሁኔታ የወሰነውን ውሳኔን ተከትሎ በከፍተኛ ፍርድቤት ቢከሰስ ህዝቡ እንደሚያሸንፍ ተገለጸ

የወላይታ ህዝብ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ፣ የድምጽ አሰጣጥና ውጤት በተመለከተ የወሰነው ውሳኔን ተከትሎ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ሰበር ችሎት ቢከሰስ እንደሚያሸንፍ የህግ ምሁራኖች ገለጹ።

ህዝበ ውሳኔው ጋር ተያይዞ ምርጫ ቦርድ የወጣው መግለጫ መራጩን መላው የወላይታ ህዝብንና የዞኑን መንግስትን እንደማይወክልና እንደማይመለከትም ጭምር አስታውቋል። ምክንያቱም የመራጮች ምዝገባና የድምጽ አሰጣጥና ውጤት በተመለከተ ተዘርዝረው የተቀመጡ ነጥቦች በአጠቃላይ የምርጫ አስፈጻሚዎች ጉድለትና ጥሰት መሆኑ ያሳያልም ብሏል።

ከእነዚህም መካከል ለአብነቱ #የውጤት መግለጫ ቅጾችና የመራጮች መዝገብ ላይ ምርጫ አስፈጻሚዎች ፊርማቸውን በሠነዶቹ ላይ አለማሥፈራቸው" የሚለውን ብቻ ካየን በቂ ነው።

ይህ የወላይታ ህዝብን ለማሸማቀቅ የተቀናጀና የተቀነባበረ ሴራ መሆኑን ገልጿል። ለዚህም መላው የወላይታ ህዝብ ተስፋ ሳይቆርጥ የአይበገሬነት ወኔን በመላበስ ዳግሚ የሚካሄደው ምርጫ ታርክ መስራት ያስፈልጋል።

በቁጫ ህዝብ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ፥ ምርጫ ቦርድ ሆን ብሎ የምርጫ ውጤት እንዲሰረዝና እንዲካሄድ ህገወጥ ውሳኔን ተከትሎ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ሰበር ችሎት ተከስሶ የቁጫ ህዝብ ሰሞኑ ማሸነፉን በመጠቀስ ይህም የምርጫ ቦርዱ ገለልተኝነት አደጋ ላይ መውደቁን ተናግረዋል።

የወላይታ ህዝብ ከወንድም ህዝቦች ጋር በአንድ ክልል ለመደራጀት የወሰነውን ውሳኔን ለመቀልበስና የፖለቲካ ትርፍ ለመግኘት እየሰሩ ያሉ አጭበርባሪዎች መኖራቸውን ጠቅሷል።

አንድ ሚሊዮን ገደማ የሚጠጋ ህዝቡ ከለሊቱ 9:00 ጀምሮ ተሰልፎ እንዲሁም ብርድና ፀሐይ ሳይበግረው የሰጠው ድምጽ ምርጫ ቦርድ የወሰነው ውሳኔ እጅግ የሚቃረን ነው ብሏል።

የህዝበ ውሳኔ ድምጽ አሰጣጥ ጋር ተያይዞ አንዳንድ ጥቃቅን ችግሮች ከዚህ በፍትም፣ ወደፊትም የሚካሄዱ ምርጫዎች የህግ ጥስት ሊኖሩ እንደሚችል አንስቷል።

በአጠቃላይ አንድ ምርጫ ልሰራዝ የሚቻለው ሠላማዊ፣ ነጻ፣ ገለልተኛ እና ፍታሃዊ ሆኖ ሳይጠናቀቅ ስቀር እንደሆነም ጠቁመዋል።

በመጨረሻም አንዳንድ ጽንፈኞችና የፀረ-ሠላም ኃይሎች አጀንዳ ለማስፈጸምና የወላይታን ገጽታ ለማበላሸት በማህበራዊ ሚዲያ ሀሰተኛና የተዛቡ መረጃዎችን የሚሰራጩ አካላት ላይ መንግስት የማይዳገም እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ጠይቀዋል።

28/01/2023
28/01/2023

በወላይታ ዞን ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ወደ ሥራ ገብተዋል

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2015 በተያዘው በጀት ዓመት ስድስት ወራት ውስጥ ከ1 ቢሊዮን 349 ሚሊዮን በላይ ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን የወላይታ ዞን አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ በተያዘው ዓመት ስድስት ወራት በኢንዱስትሪው ዘርፍ 49 ኢንቨስትመንቶችን ወደ ሥራ ለማስገባት ታቅዶ 34 ኢንቨስትመንቶችን መሳብ ተችሏል።

በዚህም በዞኑ አንድ ቢሊዮን 349 ሚሊዮን በላይ ብር ያስመዘገቡ ኢንቨስተሮች ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡

አቶ አክሊሉ እንደገለፁት፣ በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ሁለት ቢሊዮን የሚጠጋ ካፒታል ያላቸውን ባለሀብቶች ወደ ዞኑ ለመሳብ ሲሠራ የቆየ ሲሆን፤ ከ1 ቢሊዮን 349 ሚሊዮን ብር በላይ ኮፒታል ያስመዘገቡ ኢንቨስተሮች ወደ ሥራ መግባት ችለዋል።

ወደ ሥራ ገብተዋል ከተባሉት 34 ኢንቨስትመንቶች 18 ያህሉ በግብርና ዘርፍ የተሰማሩ መሆናቸውን ያብራሩት አቶ አክሊሉ፤ ሌሎች 11 የአገልግሎት እና 5 የሚሆኑ ደግሞ በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፎች ወደ ሥራ ገብተዋል ሲሉ አስረድተዋል።

በገጠሩ አካባቢ 500 ሄክታር መሬት ለኢንቨስተሮች ለማቅረብ ታቅዶ ከአንድ ሺህ 500 በላይ ሄክታር መሬት ማቅረብ መቻሉንና በከተማው አካባቢ በካሬ የነበረውን ወደ ሄክታር በመቀየር አምስት ሄክታር መሬት ለማቅረብ ዕቅድ ተይዞ ከስምንት ሄክታር በላይ መሬት ለኢንቨስተሮች አቅርቦት መዋሉንም አክለው አብራርተዋል፡፡

የኢንቨስትመንት ሌላኛው ዓላማ የሥራ ዕድል መፍጠር ነው ያሉት አቶ አክሊሉ፤ ለ10 ሺህ 51 ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የታቀደ ሲሆን፤ ከስድስት ሺህ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል አግኝተዋል ሲሉ አስረድተዋል።

መሬት ከተሰጣቸው በኋላ የተለያዩ ምክንያቶችን በማንሳት በሚፈለገው ፍጥነት ወደ ሥራ የማይገቡ ኢንቨስተሮች እንዳሉ በመግለጽም፤ ወደ ሥራ ገብተው ማልማት ከጀመሩ በኋላ የሚያቋርጡ መኖራቸውን ጠቅሰዋል።

ይህን ድርጊት በሚፈጽሙ ባለሀብቶች ላይ የማስጠንቀቂያና የተቀበሉትን መሬት በመንጠቅ በተገቢ ሁኔታ ለሚያለሙ ባለሀብቶች እየተሰጠ መሆኑን አስረድተዋል ሲል ኢፕድ ዘግቧል።

28/01/2023

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህዝበ ዉሳኔ ልዩ ምልክት ነጭ እርግብ ነዉ።

27/01/2023

ነጭ ርግብን መምረጥ አብሮነትን መምረጥ ነው!
ጥር 29 የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ነጭ ርግብን በመምረጥ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን ይመሰርቱ፡፡

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ETHIO_Post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share