Boloso Sore media Times/BSMT

  • Home
  • Boloso Sore media Times/BSMT

Boloso Sore media Times/BSMT Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Boloso Sore media Times/BSMT, Media, .

በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ አምሪፍ ሄልዝ አፊሪካ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።ቦሎሶ ሶሬ፦ ህዳር 11/2016 ዓ.ም በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ አምሪፍ ሄልዝ አፊሪካ...
21/11/2023

በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ አምሪፍ ሄልዝ አፊሪካ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

ቦሎሶ ሶሬ፦ ህዳር 11/2016 ዓ.ም በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ አምሪፍ ሄልዝ አፊሪካ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

የቦሎሶ ሶሬ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኃ/ገብርኤል ካሣዬ በበኩላቸዉ አምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ በተለያዩ ቀበሊያት በጤናው ዘርፍ ከወረዳው ጤና ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት ዘርፈብዙ ተግባራትን እያከናወነ መቆየቱን በመጥቀስ ለጤና አገልግሎት ጥራቱንና ተደራሸነቱን ለማሰፋፋት ከአጋር ድርጅት ጋር በቅንጅት መስራት የጎላ ሚና እንዳለው ገልፀዋል ።

አክለውም ድርጅቱ በወጣቶች ሥነ ተዋልዶ እና በቤተሰብ ጤና አገልግሎት በተጨማሪ በጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ዙሪያ ለማህበረሰብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እየተሰጠ መቆየቱን አክሎ ገለፃ አድረገዋል ።

በባለፉት ጊዜያት የተስተዋሉ የጤና ተግባር ዝንፈቶችን በማረምና ሊያጋጥሙ የሚችሉ ጉዳዮችን ከወዲሁ በመለየት በአስተሳሰብ የበለፀገ ጤናማ ህብረተሰብ ለማፍራት በጋራ እንደሚሰሩም የወላይታ ዞን አምሪፍ ሄልዝ አፊሪካ አስተባባሪ አቶ ደምሰው ገ/ማሪያም ተናግረዋል።

የድርጅቱን ራዕይ እና ዕቅድ ከግብ ለማድረስ የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በባለፉት የነበሩ ጉድለቶችን በማረም ለውጤታማነቱ ሁሉም መረባረብ ያስፈልጋል ብለዋል።

ያለ ዕድሜ ጋብቻና ያልተፈለገ እርግዝና ለተለያዩ ጤና እክል የሚያደረግ በመሆኑ ወጣቱ ከእንደዚህ አይነት አደጋዎች ራሱን መጠበቅ እንዳለበትም አሳስበዋል።

የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን ቦልጣና ድርጅቱ በወጣቶች ሥነ ተዋልዶ እና በቤተሰብ ጤና አገልግሎት በተጨማሪ በጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ዙሪያ ለማህበረሰብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እየተሰጠ መቆየቱን አክሎ ገለፃ ከተደረገ በኃላ በድርጅቱ የታቀፉ ቀበሌያትና ጤና ጣቢያዎች መካከል የሄምበቾ ማዘጋጃ ላይ የተሰሩ ሥራዎች ጉብኝት ተደርገዋል።

ይፋዊ የደቡብ ኢትዮጵያ ክል ማብሰሪያ መልእክቶች በወላይታ ሶዶ ከተማ በድምቀት እየታዩ ይገኛሉ።የተለያዩ ተቋማት የአጋርነት መልእክት የሚገልፁ ባነሮችን በትልቁ ሰቅለዋል። እንኳን ወደ ደቡብ ...
21/11/2023

ይፋዊ የደቡብ ኢትዮጵያ ክል ማብሰሪያ መልእክቶች በወላይታ ሶዶ ከተማ በድምቀት እየታዩ ይገኛሉ።

የተለያዩ ተቋማት የአጋርነት መልእክት የሚገልፁ ባነሮችን በትልቁ ሰቅለዋል።

እንኳን ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማብሰሪያ ፕሮግራም በሰላም መጣችሁ የሚሉ መልእክቶች እና ፅሁፎች የታሪካዊውን ቀን መቃረብ እያሳዩ ነው።

የኢትዮጵያን ብዝሃነት ያከበረና ኢትዮጵያን አንድ የሚያደርግ ትርክት መገንባት ያስፈልጋል።አቶ አገኘሁ ተሻገርኢትዮጵያ የብዝሃነት ሀገር ናት። አሰባሳቢና አንድ የሚያደርገን ትርክ መገንባት አለ...
21/11/2023

የኢትዮጵያን ብዝሃነት ያከበረና ኢትዮጵያን አንድ የሚያደርግ ትርክት መገንባት ያስፈልጋል።
አቶ አገኘሁ ተሻገር

ኢትዮጵያ የብዝሃነት ሀገር ናት። አሰባሳቢና አንድ የሚያደርገን ትርክ መገንባት አለብን። የብዙ ባህሎች፣ ታሪኮች፣ ወጎችና ልማዶች ሀገር ናት።
የኢትዮጵያን ብዝሃነት ያከበረና ኢትዮጵያን አንድ የሚያደርግ ትርክት መገንባት ያስፈልጋል።

ትርክታችን ፅንፈኝነት፣ ተነጣይነትና ጠቅላይነትን የማያጠቃው መሀል ያለ፤ የኢትዮጵያን አንድነት እና ብሔራዊነትን የሚሰብክ ግን ደግሞ ለኢትዮጵያ ብሔረ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እውቅና የሚሰጥ እኩልነት የሚሰብክ መሆን አለበት።

ደጋግመን በመነጋገር፣ ደጋግመን በመወያየት፣ በመግባባት የበላይ የሆነ ገዥ አስተሳሰብ ሆኖ እንዲወጣ መስራት ይጠበቅብናል ።

የሚያዋጣን አንድነት ነው። ህብረተሰቡ ይህን አውቆ ለአንድነትና ለእውነተኛ ፌዴራላዊ ስርዓት መኖር መስራት መቻል አለበት።

አቶ አገኘሁ ተሻገር የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፌ-ጉባኤ

ኅዳር 11/2016ዓ/ም

የታክሲ ማህበራት ለክልሉ የምስረታው ማብሰሪያ ታሪካዊ ቀን ስኬት እና ድምቀት እንደሚሰሩ አስታወቁ።ቦሎሶ ሶሬ፤ ህዳር 11/2016 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማብሰሪያ ምእራፍ ላይ ያተኮረ የጋራ ...
21/11/2023

የታክሲ ማህበራት ለክልሉ የምስረታው ማብሰሪያ ታሪካዊ ቀን ስኬት እና ድምቀት እንደሚሰሩ አስታወቁ።

ቦሎሶ ሶሬ፤ ህዳር 11/2016 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማብሰሪያ ምእራፍ ላይ ያተኮረ የጋራ መድረክ ተካሂዷል ።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ታጠቅ ምትኩ የታሪፍ እና ስምሪት መስመሮች በተገቢው ማክበር ትርፍ አለመጫን በእጅጉ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ እንገኛለን ብለዋል።

አቶ ታጠቅ አክለውም የተለያዩ እንግዶችን በጨዋነት በመቀበል እና በእንክብካቤ ማስተናገድ እንደሚገባ መክረዋል።

የከተማው ሰላም እና ፀጥታ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ካሳሁን በሊላ የማብሰሪያው ፕሮግራም በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን አስረድተዋል።

ስለሰላም የትራንስፖርት ዘርፍ ማህበራት በሚገባ እንደሚገነዘቡ የገለፁት አቶ ካሳሁን ዘውትር ለፀጥታ ስራው ተባባሪ እንዲሆኑ አሳስበዋል።

በከተማው ፓሊስ ማህበረሰብ አቀፉ ወንጀል መከላከል ሀላፊ ዋና ሳጅን አድማሱ አንጎ
የደቡብ ኢትዮጵያ ምስረታን ከወንጀል እና የትራፊክ አደጋ ነፃ ሆኖ እንዲከበር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን
አብራርተዋል።

ፖሊስ እና ህብረተሰቡ በቋሚነት የሚሰሩ አጋሮች በመሆናቸው ለማንኛውም አጠራጣሪ ነገር በከተማ ፖሊስ የስልክ መስመር 0465510146 ጥቆማ መስጠት እንደሚቻል ጥሪ ቀርቧል።

አጠቃላይ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ የባለ 3 እግር ባጃጅ አሽከርካሪዎች እና የታክሲ ማህበራት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የማብሰሪያ ፕሮግራም ላይ በተነሳሽነት እንደሚሳተፉ ገልፀዋል ሲል የዘገበው የወላይታ ሶዶ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት።

ይፋዊ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምስረታን ምክንያት በማድረግ የወላይታ ሶዶ ከተማን የማጽዳት ዘመቻ ተካሂዷል ቦሎሶ ሶሬ፣ ህዳር 11/2016 የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላን  ጨ...
21/11/2023

ይፋዊ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምስረታን ምክንያት በማድረግ የወላይታ ሶዶ ከተማን የማጽዳት ዘመቻ ተካሂዷል

ቦሎሶ ሶሬ፣ ህዳር 11/2016 የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላን ጨምሮ የዞንና የሶዶ ከተማ አመራሮች እና ነዋሪዎች የተሳተፉበት የጽዳት ዘመቻ ተካሂዷል።

የጽዳት ዘመቻው ለመርሀ ግብር ማሟያ ሳይሆን በታሪክ አጋጣሚ ከተማችንን ሊያዩ የሚመጡ እንግዶች እውነትም ሶዶ ውብ መሆኗን የምናሳይበት አጋጣሚ ነው ብለዋል የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ።

አቶ ሳሙኤል አያይዘውም ሁሉም ሰው 'ጽዳት ለኔ ነው' በሚል ተነሳሽነት በሁሉም የከተማዋ ክፍሎች ቀጣይነት ባለው መልኩ መፈጸም አለበት ብለዋል።

በየመንገዱ ያለውን ቆሻሻ ማንሳት ብቻ ሳይሆን "እያንዳንዱ ደጁንና አካባቢውን ቢያጸዳ ከተማው ውብ ይሆናል" በሚል መርህ በማጽዳት ቀጣይነት ያለው የጽዳት ሥራ መሠራት አለበት ብለዋል አቶ ሳሙኤል።

የጽዳት ዘመቻው አንዴ ሠርተን የምንተወው ሳይሆን ውቢቷን ሶዶ በተጨባጭ የምናሳይበት ነው በማለት የመንግስት ሠራተኞች የሚሠሩባቸውን ተቋማት ግቢ እንዲሁም የከተማው ነዋሪ ያለበትን ሠፈር ውብና ጽዱ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።

በወላይታ ታሪክ አስተናደን የማናውቀው እንግዳ የምናስተናግድበት ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በተለመደው የእንግዳ አቀባበል ባህላችን ወጣቶችና የከተማው ነዋሪዎች እንዲቀበሉ አደራ ብለዋል።

የሶዶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጃጋና አይዛ እንደተናገሩት ዛሬ እንግዳ ለመቀበል ብቻ የምናደርገው ሳይሆን ሁል ጊዜ ደጃችንና አካባቢያችንን በማጽዳት ለመኖር ምቹ የማድረግ ሥራ ቀጣይነት ያለው ሥራ ሊሆን ይገባል።

የጽዳት ዘመቻው ጽዳት ባህላችን እንዲሆን የግንዛቤ መፍጠሪያም ነው በማለት የሚመጡ እንግዶች የከተማችን ቆይታ በተዝናኖት የሚያሳልፉበት እንዲሆን በከተማችን የቆይታ ጊዜም እንዲራዘም ያደርጋል ብለዋል አቶ ጃጋና።

መላው የከተማው ነዋሪ ጽዳትን ሥራዬ ነው ብሎ እንዲፈጽም ጥሪ አቅርበዋል ዋና ከንቲባው።

 #2 ቀናት ብቻ ቀረየሰላምና የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በውቢቷ ወላይታ ሶዶ ከተማ ህዳር 13/2016 ዓ.ም ይካሄዳል።የደቡብ ኢትዮ...
21/11/2023

#2 ቀናት ብቻ ቀረ

የሰላምና የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በውቢቷ ወላይታ ሶዶ ከተማ ህዳር 13/2016 ዓ.ም ይካሄዳል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአስተዳደርና የፖለቲካ ማዕከል የሆነችው ወላይታ ሶዶ ህዳር 13/2016 ዓ.ም #ሐሙስ ዕለት እንግዶቿን ለመቀበል አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቅቃ ሽር-ጉድ እያለችም ነው።

በእንግዳ አቀባበል የዳበረና ቱባ ባህል ያለው የወላይታ ህዝብ ወደ ዉቢቷ ወላይታ ሶዶ ከተማ የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል በደስታ እየተጠባበቀም ይገኛል።

ውቢቷ ወላይታ
20/11/2023

ውቢቷ ወላይታ

ውድ ወንድሜን ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮንን ከኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ ጉባኤ ጎን በማግኘቴ ደስታ ተሰምቶኛል:: የተጠናከረው ግንኙነታችን ብሎም ዘርፈ ብዙው ትብብራችን በመተማመን እና ዘላቂነት ...
20/11/2023

ውድ ወንድሜን ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮንን ከኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ ጉባኤ ጎን በማግኘቴ ደስታ ተሰምቶኛል:: የተጠናከረው ግንኙነታችን ብሎም ዘርፈ ብዙው ትብብራችን በመተማመን እና ዘላቂነት ላለው ልማት ባለን የጋራ ፍላጎት መሰረት ላይ የፀና ነው::

Pleased to meet my good brother President Emmanuel Macron on the sidelines of the Compact with Africa Summit. Our strengthened relations and multifaceted cooperation continues to be anchored in trust and mutual interests for sustained development.

ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ( ዶ/ር )

ህብረብሔራዊቷ የአዲሱ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአስተዳደርና የፖለቲካ ማዕከል የሆነችው ወላይታ ሶዶ ከተማ እንግዶቿን ለመቀበል ከወትሮ በበለጠ ሁኔታ አምራ ተውባ ደምቃለች። የዳሞታ ጸዳል ነፋሻ...
20/11/2023

ህብረብሔራዊቷ የአዲሱ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአስተዳደርና የፖለቲካ ማዕከል የሆነችው ወላይታ ሶዶ ከተማ እንግዶቿን ለመቀበል ከወትሮ በበለጠ ሁኔታ አምራ ተውባ ደምቃለች።

የዳሞታ ጸዳል ነፋሻማ አየሯ፣ ለሁሉም ተስማሚ የሆነች የፍቅርና የሠላም ከተማ፣ እንግዳ አክባሪ እና ተቀባይ ህዝቦቿ እንግዶቻቸውን ለመቀበል እንዲህ ባማረ ሁኔታ ተዘጋጅታለች።

በከተማችን የሚገኙ አለምአቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች ወደ ውቢቷ ወላይታ ሶዶ ከተማ የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል።

20/11/2023
የነገይቱን ኢትዮጵያ የሸፈናት አቧራ ተራግፎ፤እውነተኛ ውበቷ ጎልቶ መውጣት አለበት፤አዲሱ ትውልድ የተፈጥሮ ፀጋዎች ለምተውና ተጠብቀው፤ለዓይን ከሚማርኩ ሰው ሰራሽ መሰረተ ልማቶች ጋር ተሳልጠው...
20/11/2023

የነገይቱን ኢትዮጵያ የሸፈናት አቧራ ተራግፎ፤እውነተኛ ውበቷ ጎልቶ መውጣት አለበት፤አዲሱ ትውልድ የተፈጥሮ ፀጋዎች ለምተውና ተጠብቀው፤ለዓይን ከሚማርኩ ሰው ሰራሽ መሰረተ ልማቶች ጋር ተሳልጠው፤ድንቅ ውበትን የሚያጎናፅፉ እንዲሆኑ ይሰራል፡፡

ሀገራችን ጥንታዊነትና ዘመናዊነት፤እንዲሁም ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ውበቶች በአንድ ላይ የተዛመዱባት የማራኪ ገፅታ ባለቤት እንድትሆን፤ዘመን ተሻጋሪ ስራዎችን መስራት ይኖርብናል፡፡

ያኔ ነባር ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መስህቦቻችን ከዘመናዊ ኪነ ህንፃዎችና ወቅታዊ ስልጣኔዎች ጋር ተዋድደው ልዩ ውበትን ይፈጥራሉ፡፡

የመደመር ትውልድ ገፅ 122

ባንኮች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደረጃቸውን የጠበቁ ህንጻዎችን በመገንባቱ እና በሌሎች ልማቶች ተሳትፏቸውን ማሳደግ በሚቻልበት አሠራር ላይ ከክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በወላይታ ሶዶ ከ...
20/11/2023

ባንኮች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደረጃቸውን የጠበቁ ህንጻዎችን በመገንባቱ እና በሌሎች ልማቶች ተሳትፏቸውን ማሳደግ በሚቻልበት አሠራር ላይ ከክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ እየመከሩ ነዉ

ቦሎሶ ሶሬ፣ ህዳር 10/2016 መድረኩን እየመሩ ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተስፋዬ ይገዙ በአካባቢው በሚሠሩ ልማት ሥራዎች ተሳትፏቸውን ማጉላት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ በበኩላቸዉ የባንኮችን የልማት ተሳትፎ ለማሳደግ የክልሉ መንግሥት ሁኔታዎችን ያመቻቻል ሲሉ ተናግረዋል ።

የዲስትሪክት ኃላፊዎች በሰጡት አስተያየት ለክልሉ ሁለንተናዊ ልማት የሚጠበቅባቸውን ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

በቆይታቸው ዉጤታማ ምክክር ማድረጋቸውንም አመላክተዋል ።

በምክክር መድረኩ በክልሉ ያሉ የመንግስትና የግል ባንኮች ዲስትሪክት ኃላፊዎች እና ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አዋሽ ባንክ፣ ዳሽን ባንክ፣ አሀዱ ባንክ እና ኦሞ ባንክ ዲስትሪክት ኃላፊዎች ተገኝተዋል ።

ኢትዮጵያ የየወቅቱን ፈተናዎች በመቋቋም የብሩህ ዘመን ጉዞዋን ቀጥላለች ።  በዜጎቿ ህብረት፣ፅናትና ትጋት ዘላቂ ሠላሟን በማረጋገጥ፣ ፀጋዎቿን እና እምቅ አቅሞቿን በማልማት ከራሷ ተርፋ ለሌሎ...
20/11/2023

ኢትዮጵያ የየወቅቱን ፈተናዎች በመቋቋም የብሩህ ዘመን ጉዞዋን ቀጥላለች ።

በዜጎቿ ህብረት፣ፅናትና ትጋት ዘላቂ ሠላሟን በማረጋገጥ፣ ፀጋዎቿን እና እምቅ አቅሞቿን በማልማት ከራሷ ተርፋ ለሌሎች አጋዥ የምትሆንበት አዲስ ምዕራፍ እዉን እንዲሆን ኢትዮጵያ እየተጋች ትገኛለች ።

ኢትዮጵያ ሠላሟን ዘላቂ ለማድረግ የምታደርገዉ ጥረት አስተማማኝ ዉጤት ያመጣ ዘንድ ደግሞ ሁሉም የበኩሉን ሊያበረክት ይገባዋል ።

ዘላቂ ሠላምን እያረጋገጥን ፤ በእጆቻችንና በደጆቻችን የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ፀጋዎችን እና እምቅ አቅሞችን በማልማት ለኢትዮጵያ ዕድገት በጋራ እንትጋ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር ከወላይታ ሶዶ ከተማ እና አካባቢው ማህበረሰብ ጋር ውይይት በማካሄድ ላይ ናቸው።ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ  በክልሉ የማብሰሪያ ፕሮግራም ቅድመ ዝ...
20/11/2023

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር ከወላይታ ሶዶ ከተማ እና አካባቢው ማህበረሰብ ጋር ውይይት በማካሄድ ላይ ናቸው።

ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በክልሉ የማብሰሪያ ፕሮግራም ቅድመ ዝግጅት ላይ አፅንኦት የሰጡት ሲሆን በስራ እና ፍቅር ወደ ፊት እንሄዳለን ሲሉም ተናግረዋል።

ልዩ የሆነ ከተማ አቀፍ እና ክልላዊ የሰላም የፍቅር እና የመቻቻል ተምሳሌት ክልል መስርተን ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ገብተናል ሲሉም የክልሉ ርእሰ መስተደድር አቶ ጥላሁን አክለዋል።

አቶ ጥላሁን ክልሉ ተመስርቶ ይስራ ጀምረናል በይፋ ታሪኳዊ የማብሰሪያ ቀኑን በጋራ እናበስራለን ሲሉም ተናግረዋል።

ይበልጥ መቀራረብ እና አብሮ በመስራት ከምስረታው ማግስት ጀምሮ ህዝቡን የለውጥ ማእከል በማድረግ ብልፅግናችንን እያረጋገጥን ነው ያሉት ክቡር ርእሰ መስተደድር አቶ ጥላሁን ከበደ።

የወላይታ ዞን አስተዳደሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ በህዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አብሮ የመበልፀግ እድል የተፈጠረበት ምእራፍ መሆኑን ገልፀዋል።

ይፋዊ የክልል ማብሰሪያ ፕሮግራም ቅድመ ዝግጅት ተጠናቆ እንግዶች እየተጠበቁ እንደሚገኝ አቶ ሳሙኤል አስረድተዋል።

በአሁኑ ሰአት የመድረኩ ተሳታፊዎች የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በሚሰጡት አስተያየት ላይ እየገለፁ ይገኛሉ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ይፋዊ የማብሰያ ፕርግራም የፊታችን ሀሙስ ይካሄዳል ሲል የዘገበው የወላይታ ሶዶ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ"G20 Compact with Africa (CwA)” ጉባኤ አስቀድሞ ከጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ጋር ለሁለትዮሽ ውይይት ተገናኝተዋል::ሁለቱ ወገኖች ...
19/11/2023

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ"G20 Compact with Africa (CwA)” ጉባኤ አስቀድሞ ከጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልዝ ጋር ለሁለትዮሽ ውይይት ተገናኝተዋል::

ሁለቱ ወገኖች በጋራ ትብብር መስኮች፣ በሀገር ውስጥ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የጀርመኑ መራሄ መንግስት በዚህ አመት መጀመሪያ የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት መገናኘታቸው ይታወሳል።

Prime Minister Abiy Ahmed met with Chancellor Olaf Scholz in a bilateral meeting earlier today, ahead of the G20 Compact with Africa (CwA)Summit.

The two sides conferred on areas of bilateral cooperation, domestic and regional issues.

It is to be recalled that the two leaders met earlier this year during the Chancellor’s visit to Ethiopia.

በወላይታ ዞን የተሰሩ የልማት ስራዎች በየአካባቢያችን ለማስፋት ልምድ የወሰድንበት ነው፦ የመንግስት አመራሮችቦሎሶ ሶሬ፤ ህዳር 9/2016 በወላይታ ዞን የተሰሩ የልማት ስራዎች በየአካባቢያችን...
19/11/2023

በወላይታ ዞን የተሰሩ የልማት ስራዎች በየአካባቢያችን ለማስፋት ልምድ የወሰድንበት ነው፦ የመንግስት አመራሮች

ቦሎሶ ሶሬ፤ ህዳር 9/2016 በወላይታ ዞን የተሰሩ የልማት ስራዎች በየአካባቢያችን ለማስፋት ልምድ የወሰድንበት ነው ሲሉ በወላይታ ሶዶ ማዕከል ስልጠና እየወሰዱ ያሉ የመንግስት አመራሮች ገለጹ።

በ3ኛ ዙር በወላይታ ሶዶ ማዕከል ስልጠና እየወሰዱ ያሉ የመንግስት አመራሮች በወላይታ ዞን የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

"ከዕዳ ወደ ምንዳ" ብለን የጀመርነውን ግብ እውን ለማድረግ በወላይታ ዞን የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አንዱ ማሳያ መሆናቸውንም የመንግስት አመራሮች ጠቅሰዋል።

በወላይታ ዞን አስደማሚ የልማት ስራዎችን ተመልክተናል ያሉት የመንግስት አመራሮች ይህንን በየአካባቢያችን ለማስፋት ልምድ የቀሰምንበት ነው ብለዋል።

በየአካባቢያችን ያሉ እምቅ አቅሞቻችንንና ሀብቶቻችንን አቀናጅተን ከተጠቀምን የምንመኘውን ሁለንተናዊ ብልጽግናን በቅርቡ እውን እናደርጋለን እውን እናደርጋለን ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

በተለይም በስራ ዕድል ፈጠራ ተደራጅተው የሚሰሩ ወጣቶች ማሳ እየለሙ ምርትና ምርታማነቱን ለመጨመርና የሚያደርጉትን ጥረት አድንቀው ኑሮ ውድነትንም ለማቃለል ሁነኛ ሚና እንዳለውም ተመልክተናል ብለዋል።

ከተቀናጀንና እጅ ለእጅ ተያያዘን ከሰራን የማንወጣው ተራራ የለም ያሉት የመንግስት አመራሮቹ ለዚህም በቁርጠኝነትና በትጋት መሰራት ሁነኛ መፍትሔ እንደሆነም ጠቅሰዋል።

የፍቅር ከተማ በመባል ትታወቃለች ፣ ከመላው ኢትዮጵያ መተው በአብሮነት የሚኖሩት ህዝቦቿ የፍቅር ከተማ ስለመሆኗ ይመሰክራሉ። ባለሰባት በር የንግድና እንቨስትመንት ከተማ እንድሁም የደቡብ ኢት...
19/11/2023

የፍቅር ከተማ በመባል ትታወቃለች ፣ ከመላው ኢትዮጵያ መተው በአብሮነት የሚኖሩት ህዝቦቿ የፍቅር ከተማ ስለመሆኗ ይመሰክራሉ።

ባለሰባት በር የንግድና እንቨስትመንት ከተማ እንድሁም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአስተዳደር እና ፓለቲካ ማዕከል ናት ወላይታ ሶዶ ከተማ ።

ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምስረታ ከፌደራልና ከሁሉም ክልሎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እያደረገች ትገኛለች።

አመራሩ በንድፈ ሐሳብ ደረጃ ያየውን በተጨባጭ መኖሩን እንዲያዩ የተዘጋጀ መድረክ ነው። አቶ ሳዳት ነሻቦሎሶ ሶሬ፦ ኅዳር 09/2016 ዓ/ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት በወላይታ ዞን  ...
19/11/2023

አመራሩ በንድፈ ሐሳብ ደረጃ ያየውን በተጨባጭ መኖሩን እንዲያዩ የተዘጋጀ መድረክ ነው። አቶ ሳዳት ነሻ

ቦሎሶ ሶሬ፦ ኅዳር 09/2016 ዓ/ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት በወላይታ ዞን ወላይታ ሶዶ ማዕከል 3ኛ ዙር የመንግስት አመራሮች የአቅም ግምባታ ሰልጣኞች የግልገል ጊቤ ቁጥር 3 ኃይል ማመንጫን ጎብኝተዋል።

በሚኒስቴር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግምባታ ማዕከል አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሳዳት ነሻ አመራሩ የሀገሪቷን ሀብት ማወቅ እንዳለበትና ሀብቷን አውቆ መምራት አለበት ብለዋል።

አመራሩ በንድፈ ሐሳብ ደረጃ ያየውን በተጨባጭ መኖሩን እንዲያዩ በተጨባጭ ይህ ሀገር ለውጥ ውስጥ ከገባ ጊዜ ጀምሮ ሪፎርም ከጀመርን ጊዜ ጀምሮ ምን ዓይነት ተጨባጭ ለውጥ አምጥተዋል የሚለውን ያሳየ ጉብኝት መሆኑንም አቶ ሳዳት አስረድቷል።

አቶ ሳዳት አክለውም ሀገሪቱ ለወደፊት ምን ተስፋ አለው፤ በንግግር የሚገለጽ ተስፋ ነው ወይስ በተጨባጭ የሚታይ ነው የሚለውን በደምብ ማየት እንዲችሉ የመስክ ጉብኝቱ አንዱ የስልጠና አካል ተደርጓል ብለዋል።

የግብርና ሥራዎች ታይተዋል፣ እስካሁን ያልተነካ ሀብት ፣ ያልተነካ የውሃ አቅም እንዲሁም ሌሎች ግብአቶች መኖሩን አመራሩ እንዲያውቅ ዕድል የፈጠረ ምልከታ መሆኑንም አቶ ሳዳት አስረድተዋል።

በተጨማሪ ባለን የውሃ አቅም ምን ያህል እየተጠቀምን ነው የምለውን በተግባር ያሳየ ጉብኝት ነው ብለዋል።

ጊቤ ቁጥር 3 ኃይል ማመንጫ 1870 ኪሎ ዋት የሚመነጭ በሀገሪቱ ህዳሴ እስኪጠናቀቅ ትልቁ ኃይል ማመንጫ ግድባችን ነው።

የውጭ ምንዛሬ እየፈጠረ ያለ ኃይል በመሆኑ፤ ሌሎች የሌማት ትሩፋት የሆኑትን ከዚህ በፊት ያልነበሩ አዳዲስ እሳቤዎችን ዓይን ከፍቶ ማየት ያስፈልጋል ፤ አመራሩ አካባቢውን ማወቅ አለበት። በአካባቢው ምን ሀብት አለ የምለውን ለይቶ ማወቅ የሚችልበት ዕድል ተመቻችቷል ብለዋል።

ለሀገራችን ልማት ለማፋጠንና የህዝባችንን ፍጆታ በአግባቡ ለመሸፈን ንቁና ጠንካራ ዜጋ ለመፍጠር አመራሩ ብቁ ሆኖ መገኘት አለበት ብለዋል።

አመራሩ በመስክ ምልከታ የተመለከተውን ከስልጠናው ጋር ከስልጠናው ጋር በማመዛዘን ወደሚመራበት አካባቢው ስመለስ እዚህ ያገኘውን በተጨባጭ ወደ ተግባር እንዲቀየር ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም አቶ ሳዳት አንስተዋል።

አመራሩ በትክክል ከመራ በተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ያሳየ ምልከታ ነው። ሀብት መኖሩንም ማረጋገጥ የተቻለበት ነውም ተብሏል።

የአመራሩን አቅም ማጎልበትና ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጣ ቁርጠኛ ልሆን ይገባልም ብለዋል አቶ ሳዳት።

የደቡብ ኢትዮጵያ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነ በበኩላቸው ሀገሪቱ ያላትን ሀብት በአግባቡ እንዲትጠቀም አቀናጅቶ የመምራት ችግር እንደነበር አንስተው ስልጠናው በዋናነት ያለንን ያልተነካ ሀብት አመራሩ አቀናጅቶ በመምራት የብልጽግና ጉዞ እንዲያሳካ ጉብኝቱም ሀገሪቱ ያላትን ሀብት አመራሩ እንዲረዳ ያደርጋል ብለዋል።

ሀገሪቱን ከድህነት ለማላቀቅና አመራሩ ታሪክ ለመስራት ያየውን ነገር በአካባቢው ተግባራዊ ለማድረግ ሊሰራ እንደሚባም አቶ ዮሐንስ አሳስበዋል።

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ባዩት ነገር መደነቃቸውን ገልፀው መሥራትና በአካባቢውን ያለውን ሀብት ለሀገሪቱ ዕድገት በመጠቀም ተግተው መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

በወላይታ ሶዶ ማዕክል 3ኛ ዙር የአቅም ግንባታ ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ ለመንግሥት አመራሮች  በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ እና  በአረካ ከተማ አስተባባሪነት የምሳ ግብዣ ፕሮግራም ተደረገቦሎሶ ሶሬ፤ ህ...
19/11/2023

በወላይታ ሶዶ ማዕክል 3ኛ ዙር የአቅም ግንባታ ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ ለመንግሥት አመራሮች በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ እና በአረካ ከተማ አስተባባሪነት የምሳ ግብዣ ፕሮግራም ተደረገ

ቦሎሶ ሶሬ፤ ህዳር 9/2016ዓ.ም "ከእዳ ወደ ምንዳ"በሚል መሪ ቃል ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል የተወጣጡ የ3ኛ ዙር ሰልጣኞች በወላይታ ሶዳ ማዕከል በቦሎሶ ሶሬ ወረዳ እና በአረካ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪነት የምሳ ግብዣ ፕሮግራም ተደርጓላቿል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ አያኑ ብራጋ እና የአረካ ከተማ ከንቲባ አቶ ደመቀ ደጄኔ ለእንግዶቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

አጆራ መንትያ ፏፏቴዎችን በሶስተኛው ዙር ስልጠና እየወሰዱ ያሉ የመንግስት አመራሮች ጎበኙአጆራ መንትያ ፏፏቴዎች ታሪካዊና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦች መካከል ቀዳሚ ሥፍራ የሚይዘው በወላይታ ...
19/11/2023

አጆራ መንትያ ፏፏቴዎችን በሶስተኛው ዙር ስልጠና እየወሰዱ ያሉ የመንግስት አመራሮች ጎበኙ

አጆራ መንትያ ፏፏቴዎች ታሪካዊና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦች መካከል ቀዳሚ ሥፍራ የሚይዘው በወላይታ ዞን በቦሎሶ ቦምቤ ወረዳ አጆራ ቀበሌ የሚገኝ የተፈጥሯዊ መስህብ ሥፍራ ነው ፡፡

ሁለቱ ፏፏቴዎች 400 ሜትር ተራርቀው ገደል እየተምዘገዘጉ የሚወርዱ አጃንቾ 210 ሜትር ወደ ትልቁ ገደል ጢሰ መስሎ ሲወርድ በተመሳሳይ ሶከ 170 ሜትር ቀልቁል የሚወረወር ድንቅ የተፈጥሮ ስጦታዎች ናቸው፡፡

ይህ ተፈጥሮ መስህብ ውብና ማራኪ የሆነ የሰውን ልጅ ከሚያማልለ ከተፈጥሮ ፀጋዎች ተርታ የሚጠሩ ለአገር ውስጥም ሆነ ለውጪ አገር ቱሪስቶች ቀልብ የሚስብ ለጎብኚዎች ምቹና ማራኪ ቦታ ነው።
ርቀቱ ከአዲስ አበባ በሆሳዕና መንገድ 320 ኪ.ሜ፣
ከአዲስ አበባ በሻሸመኔ መንገድ 435 ኪ.ሜ ከስዳማ ክልሉ ከተማ ሀዋሳ በ212 ኪ.ሜ፣

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና ዞናችን ርዕሰ ከተማ ሶዶ በ56 ኪ.ሜ፣
ከወረዳው ከተማ ቦምቤ በ5 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡

አጆራ ፏፏቴ ሶኬ እና አጃንቾ ከሚባሉ ትላልቅ ወንዞች የሚፈጠሩ መንትያ ፏፏቴዎች ናቸው፡፡ የወንዞቹ መነሻ አጃንቾ በአጠቃላይ በወላይታ በኩል ሲሆን ሶኬ በወላይታና ካንባታ ድንበር መሃል የሚፈስ ወንዝ ነው፡፡

ስያሜያቸውን ያገኙት ፏፏቴዎቹ ከሚወርዱበት ትልቅ ገደል ውስጥ ለረዥም ጊዜ ሲኖሩ ከነበረው አጆራ ከሚባለው ጎሣዎች ስያሜ ነው፡፡

ከፏፏቴዎቹ በተጨማሪ ሌሎች በርካታ የዱር እንስሳትም መኖርያ ነው፡፡በተላይም ጉሬዛ፣ድኩላ፣ከርከሮ፣ዝንጆሮ፣ነብር፣አጋዘን፣ጦጣ እና የተፈጥሮ የዕፅዋት ዝሪያዎች በአከባቢው የተለያየ ስያሜ የሚሰጣቸው ከመኖራቸውም አልፎ በምግብነት የሚጠቀም ቦይና/ጎዳሬ የሚባለውና ሌሎች ሥራ ሥር ተክል በብዛት ይገኛሉ፡፡

ስለዚህ ይህንን ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህብ ልዩ የሚያደርገው፡-

ፏፏቴው በሚገርም ሁኔታ የተለያዩ ወንዞች መንትያ ሆነው መውረድ ፏፏቴዎች በ400 ሜትር ተራሪቀው ጎን ለጎን መፈሰሳቸው ፏፏቴው ብቻ አይደለም አከባቢው በተለያዩ የዱር እንስሳትና የዕፅዋት ዝሪያዎች በመኖሩ የቱሪስቶችን ልብ መሳብ የሚችሉ መሆኑ ታውቀዋል፡፡

በጧት ፈረቃ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ጥቤ መስኖ ተፋሰስ በሥልጠና ያሉ አመራሮች

በሶስተኛው ዙር የመንግስት አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ በወላይታ ሶዶ ስልጠና ማዕከል እየተሳተፉ ያሉ አመራሮች የመስክ ምልከታ እያደረጉ በዞኑ ውስጥ ይገኛሉ።

በሶስተኛው ዙር የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠናን በወላይታ ሶዶ እየተከታተሉ ከሚገኙ አሰልጣኞች መካከል ወደ ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ፣ አረካ እና አጆራ ፏፏተ- ለመጎብኘት የሚሔደው ቡድን ቦሎሶ ሶሬ...
19/11/2023

በሶስተኛው ዙር የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠናን በወላይታ ሶዶ እየተከታተሉ ከሚገኙ አሰልጣኞች መካከል ወደ ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ፣ አረካ እና አጆራ ፏፏተ- ለመጎብኘት የሚሔደው ቡድን ቦሎሶ ሶሬ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል::

“መቼም የትም በምንም ሁኔታ የፆታዊ ጥቃትን ዝም አንበል” በሚል መሪ ቃል የአለም የህፃናት ቀን ተከበረበዓለም ለ34ኛ እና በኢትዮጵያ ለ18ኛ ጊዜ «ለዛሬዎቹ ህፃናት ፍቅርንና በጎነትን እናው...
18/11/2023

“መቼም የትም በምንም ሁኔታ የፆታዊ ጥቃትን ዝም አንበል” በሚል መሪ ቃል የአለም የህፃናት ቀን ተከበረ

በዓለም ለ34ኛ እና በኢትዮጵያ ለ18ኛ ጊዜ «ለዛሬዎቹ ህፃናት ፍቅርንና በጎነትን እናውርስ» በሚል መሪ ቃል አለም አቀፍ የህፃናት ቀን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካና የአስተዳደር ማዕከል በሆነችው ወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ አቶ አዳማ ትምጳዬ በበኩላቸው አንድ ሀገር ቀጣይነቱ የሚረጋገውና ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገር ሀገሪቱን የሚረከቡ ታዳጊ ህፃናት ከጨቅላነታቸው በመንከባከብና በማሳደግ፤ ህይወታቸው የፀና መሰረት ላይ እንዲገነባ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደነገጉ የህፃናት መብቶችን ሀገራችን ተቀብላ እየተተገበረች በመሆኑና የህጎች ሁሉ የበላይ በሆነው ህገ መንግስት ላይም ሰፍሮ የሚገኝና ክልላችንም አዲስ በተደነገገው ህገ መንግስት ላይ የተካተተ በመሆኑ ለተፈፃሚነቱ ሁሉም መረባረብ ይኖርበታል ብለዋል ክቡር አቶ አዳማ።

በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ፆታዊ ትንኮሳዎችን ለመከላከል ከኢፌዴሪ ህገ መንግስት ጀምሮ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህገ መንግስትም የተደነገጉ ድንጋጌዎችን ተግባራዊ በማድረግ ጥቃት ስፈፀምም ህጋዊ እርምጃዎችን በመውሰድ ሀገራችን የጀመርችውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ሴቶች በእኩልነት የሚሳተፉበትን ምህዳር በመፍጠር የሀገራችንን ትንሳኤ የሚረጋገጥበት ወቅት ላይ እንገኛለን ሲሉም ክቡር አቶ አደማ ተናግረዋል።

የደቡብ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ካሰች ኤልያስ በበኩላቸው ህፃናት የነገ ሀገር እጣ ፈንታ የዕድገቱ ቀልፍ በመሆናቸው ህፃናቱ ላይ መስራት የነገይቱን ሀገር ላይ መስራት እንደሆነ ገልጸዋል።

የህፃናትን መብትና ድህንነት በተሟላ ሁኔታ ማስጠበቅና ተሳትፎንና ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ከሁሉም ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ልሆን እንደሚገባ የቢሮ ኃላፊዋ ወ/ሮ ካሰች አሳስበዋል።

በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርግቶችን ለመከላከል በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትን በዘላቂነት ድጋፍ እንዲደረግላቸው በከፍተኛ ንቅናቄ መሰራት ይገባል ።
ለረዥም ጊዜ በተሳሳተ ግንዛቤና አስተሳሰብ የሚፈፀመውን ፀረ ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል ሁላችንም የበኩላችንን ድርሻ ማበርከት ይገባል ሲሉም ወ/ሮ ካሰች አሳስበዋል።

የወላይታ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ መስፍን ዳዊት ህፃናት የነገ ሀገር ተረካቢ የምንመካባቸው አለኝታዎቻችን በመሆናቸው መንከባከብና ፍቅር መስጠት ያስፈልጋቸዋል ብለዋል።

በበርካታ ችግሮች አማካኝነት ብዙ ህፃናት ለጎዳና ተዳዳሪነት፣ ለህገ ወጥ ፍልሰትና ለጉልበት ብዝበዛና ለወሲባዊ ጥቃት እየተዳረጉ እንደሆነ የገለፁት አቶ መስፍን ልዩ ትኩረት በማድረግ ህፃናትን መታደግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የህፃናትን መብት በማስከበር ረገድም ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ያሳሰቡት አቶ መስፍን የፀረ ፆታዊ ጥቃትን በዕቅዶቻችን አካቶ በመስራት የሚደርስባቸውን ጫና መከላከል እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአስተዳደርና የፓለቲካ ማዕከል ስለሆነችው ስለ ዎላይታ ሶዶ ከተማ ከብዙ በጥቂቱ እነሆ ! ዎላይታ ሶዶ ስያሜዋን ያገኘችው ከ150 ዓመታት በፊት በአከባቢው ይኖሩ ከነበ...
18/11/2023

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአስተዳደርና የፓለቲካ ማዕከል ስለሆነችው ስለ ዎላይታ ሶዶ ከተማ ከብዙ በጥቂቱ እነሆ !

ዎላይታ ሶዶ ስያሜዋን ያገኘችው ከ150 ዓመታት በፊት በአከባቢው ይኖሩ ከነበሩ "ሞቼና ቦራጎ ሶዶ" ከተባሉ አንድ ታዋቂ ነጋዴ ስምና ከተማዋ አሁን በምትገኝበት አቅራቢያ ይገኝ ከነበረው "ሶዷ ሹቻ" ከሚባለው ሲሆን ትርጓሜውም "የሶዶ ድንጋይ" ተብሎ ከሚታወቅ ትልቅ የድንጋይ አለት የተወሰደ እንደሆነ ይነገራል፡፡

ውቧ ዎላይታ ሶዶ ከተማ ከአዲስ አበባ በሻሸመኔ 390 ኪ.ሜ፤ በቡታጅራ ሆሳዕና 329 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች።

16 ሺ 164 ሄክታር ላይ ነው ከተማዋ ያረፈችው፡፡ የመልክዓ ምድር አቀማመጡ ከባህር ጠለል በላይ 1784-2346 ኪ.ሜ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡

በከፍተኛ ዕድገትና ለውጥ ጎዳና የምትገኘው ውቧ ዎላይታ ሶዶ ከተማ በርካታ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች የሚደረጉባት 7 መግቢያና መውጫ በሮች ባለቤት ነች።

ዎላይታ ሶዶን ከሌሎች አጎራባች ከተሞች ያስተሳሰሯት ዋና ዋና መንገዶቿም ከሶዶ ሻሸመኔ አዲስ አበባ፣ ከሶዶ አርባምንጭ ጂንካ፣ ከሶዶ ጎፋ ሳውላ፣ ከሶዶ ታርጫ ጅማ፣ ከሶዶ ቢጣና ሞሮቾ ሐዋሳ፣ ከሶዶ ሆሳዕና አዲስ አበባ እና ከሶዶ ጉልጉላ ዲላ ናቸው።

በአሁኑ ጊዜ 340 ሺህ የሚጠጋ ሕዝብ ተቻችሎ፤ ተከባብሮ በጋራ ተፈቃቅሮ ይኖርባታል፡፡

በሆቴልና ቱሪዝም፤ በኢንዱስትሪ፤ በማህበራዊ አገልግሎትና በከተማ ግብርና በከፍተኛ ሁኔታ ኢንቨስት ለማድረግ ምቹ አቅም አላት።

ዎላይታ ሶዶ የፍቅርና የመቻቻል ከተማ ናት።

በዞኑ ከ466 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ ገብተዋልበ2016 በጀት ዓመት ባለፉት ሦስት ወራት 466 ሚሊዮን 300 ሺህ ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ወደ ሥ...
18/11/2023

በዞኑ ከ466 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ ገብተዋል

በ2016 በጀት ዓመት ባለፉት ሦስት ወራት 466 ሚሊዮን 300 ሺህ ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወላይታ ዞን አስተዳደር ገለጸ፡፡

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሩብ ዓመቱ አጠቃላይ ካፒታላቸው 466 ሚሊዮን 300 ሺህ ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 11 ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡

ወደ ሥራ እንዲገቡ ፈቃድ የተሰጣቸው 11 ፕሮጀክቶች እያንዳንዳቸው በአማካኝ ከ80 እስከ 100 ሚሊዮን ብር ካፒታል ማስመዝገባቸውን አስረድተዋል፡፡

ፕሮጀክቶቹ የተሠማሩባቸው የኢንቨስትመንት ዘርፎች በዋናነት በግብርና ሥራ ሲሆን፣ የግብርና ምርቶችን በማቀነባበር፣ በአገልግሎትና በማዕድን ቁፋሮ ዘርፍ የተሠማሩ አልሚዎች መኖራቸውን አስታውቀዋል።

በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በርካታ ባለሀብቶች ለማልማት ጥያቄ ያቀረቡ በሆንም፤ ክልሉ አዲስ እየተዋቀረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ጥያቄውን ተቀብሎ በፍጥነት ጉዳዩን ለማስጨረስ ችግር አጋጥሟል ብለዋል።

በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ወደ ሥራ ለማስገባት የታቀዱ ከ100 በላይ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን አንስተው፤ ፕሮጀክቶቹ ለክልል ቀርበው እንዲፀድቁ የሚደረግ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሂደቱ ላይ መዘግየት መፈጠሩን አመልክተዋል።

ከባለሀብቶቹ የተነሳው የእናልማ ጥያቄ ቀደም ብሎ የቀረበ ቢሆንም፤ የቀድሞ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ለሁለት ተከፍሎ በአዲስ መልክ በመዋቀሩ የተነሳ ፕሮጀክቶቹ በአዲሱ አደረጃጀት መሠረት ቀርበው እንዲፀድቁ ይደረጋል ሲሉ አስረድተዋል።

አዲሱ ክልል ገና እየተደራጀ ከመሆኑም ጋር ተያይዞ ፕሮጀክቶችን መርምሮ ፈቃድ የሚሰጥ ባለሙያ እጥረት በማጋጠሙና በሌሎች ችግሮች ምክንያት መጓተቶች መከሰቱን ጠቁመው፤ ችግሩን ፈትቶ ብዛት ያላቸውን አልሚዎች ወደ ሥራ ለማስገባት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ ከባለሀብቶች የመልካም አስተዳደር ቅሬታ እየቀረበ መሆኑን የተናገሩት አቶ ሳሙኤል፤ ዞኑ ጥያቄዎቹ በፍጥነት ምላሽ እንዲያገኙ ከክልሉ ጋር በመተባበር እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በ2016 በጀት ዓመት በዞኑ ከ200 በላይ ፕሮጀክቶችን ወደ ሥራ ለማስገባት እቅድ መያዙን አስታውቀው፤ ዞኑ በግብርና በርካታ ፀጋዎች ያሉት በመሆኑ ሰፊ ዕድል እንዳለው ተናግረዋል።

ወደ ወላይታ ዞን በርካታ ቱሪስቶች ለጉብኝት እንደሚመጡ አስታውሰው፤ በአገልግሎት ዘርፉ ሰፊ የሥራ ዕድልና ገቢ መፍጠር የሚቻልበት አማራጭ መኖሩን አስገንዝበዋል።

በአካባቢው በርካታ የማዕድንና የተፈጥሮ ሃብት እንዲሁም ለባለሀብቶች ምቹ ዕድል የሚፈጥሩና ለንግድ የእንቅስቃሴ አማራጭ የሆኑ የተለያዩ መንገዶች በመኖራቸው ወደዞኑ ለማልማት የሚመጡ ባለሃብቶች ተጠቃሚ የሚሆኑበት ሰፊ ዕድል እንዳለ አመላክተዋል።

ዘገባው ኢ ፕ ድ

የሰላም፥የመቻቻል፥የብልጽግና ተምሳሌት ደቡብ ኢትዮጲያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ ኅዳር 13 የክልሉ ማብሰሪያ እና ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም ይካሄዳል። #6ቀን ብቻ ቀረ!!
18/11/2023

የሰላም፥የመቻቻል፥የብልጽግና ተምሳሌት ደቡብ ኢትዮጲያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ ኅዳር 13 የክልሉ ማብሰሪያ እና ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም ይካሄዳል።

#6ቀን ብቻ ቀረ!!

በመደመር ትውልድ ግንባታ ውስጥ ሚዲያ በሚኖረው ሚና ላይ የተደቀነ ዋነኛው ፈተና፤ ከብዙ አማራጮች የሚሰራጩ አሉታዊ መረጃዎችን ተቆጣጥሮ፤ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን፣ ውበትና የሀገር ፍቅር ስሜ...
18/11/2023

በመደመር ትውልድ ግንባታ ውስጥ ሚዲያ በሚኖረው ሚና ላይ የተደቀነ ዋነኛው ፈተና፤ ከብዙ አማራጮች የሚሰራጩ አሉታዊ መረጃዎችን ተቆጣጥሮ፤ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን፣ ውበትና የሀገር ፍቅር ስሜትን ማሥረጽ መቻል ነው።

ሚዲያው ለትርክት ግንባታ የሚኖረውን ሚና ተጠቅሞ የኅብረ ብሔራዊ አንድነትና የወንድማማችነት ትርክት፤ በሕዝብ ውስጥ እንዲቀረጽ ማድረግ አለበት። በሌላ በኩል ደግሞ፤ በሚዲያው የሚሰራጨውን የጥላቻ ትርክት መግራትና መቆጣጠር ያስፈልጋል።

የመደመር ትውልድ መጽሐፍት ገጽ 214

የመደመር ትውልድን የፈጠረው አብዮት አይደለም! የመደመር ትውልድን የፈጠረው አብዬት አይደለም፤ ጥቂት ግለሰቦች ወይም የለውጥ ተዋንያን ሐሳብና ፍላጎታቸውን ጭነውበት የተፈጠረም አይደለም፡፡ በ...
17/11/2023

የመደመር ትውልድን የፈጠረው አብዮት አይደለም!

የመደመር ትውልድን የፈጠረው አብዬት አይደለም፤ ጥቂት ግለሰቦች ወይም የለውጥ ተዋንያን ሐሳብና ፍላጎታቸውን ጭነውበት የተፈጠረም አይደለም፡፡ በጊዜ ሂደት ትውልዱ ክፉና ደጉን ተመልክቶ የሚጠቅመውን መንገድ ለመምረጥ በሚያደርገው መውተርተር ውስጥ የወለደው የጋራ ጠባይና የኑሮ ዘይቤ ነው፡፡ ይኼ በህዝብ ግፊትና በብዙሃኑ ልሂቃን ትብብር በታሪክ ሂደት የተፈጠረ የህብረተሰብ የአኗኗር ዘይቤ ለውጥ ፍጹም ነው አንልም።

ብዙዎችን ወደ ሚያግባባና ይሄ ነው ተብሎ ወደ ተበየነ ግብ ለመጓዝ የሚያስችለውን ትክክለኛ አቅጣጫ ገና በመፈለግ ላይ መሆኑም አይካድም፡፡

እንደቀደሙት ለውጦች ያለፈውን በዜሮ አባዝቶና አማራጭ ምዕራፎችን ዘግቶ እንደ አዲስ ከመጀመር ይልቅ ቀስ በቀስ ሪፎርም እያደረጉ መጓዝን የመረጠ ነው፡፡

በዚህ ምክንያት ዙሪያውን ወንዞች ተደርድረው እንደሚያጠጡትና የዘሩበትን እንደሚያበቅል ለም መሬት ተደርጎ ሊታሰብ ይችላል፡፡ በአግባቡ ከተያዘ መሬቱ ለብሩህ ዘመን መነሻ የሚሆን ትልቅ የለውጥ ስንቅ ነው፡፡

የ3ኛው ዙር የመንግስት አመራር አቅም ግንባታ ሥልጠና የሶዶ ማዕከል ሠልጣኞች የወላይታ ዞን አስተዳደር የእራት ግብዣ አደረገቦሎሶ ሶሬ፤ ህዳር 06/2016 ዓ.ም የ3ኛው ዙር የመንግስት አመራ...
16/11/2023

የ3ኛው ዙር የመንግስት አመራር አቅም ግንባታ ሥልጠና የሶዶ ማዕከል ሠልጣኞች የወላይታ ዞን አስተዳደር የእራት ግብዣ አደረገ

ቦሎሶ ሶሬ፤ ህዳር 06/2016 ዓ.ም የ3ኛው ዙር የመንግስት አመራር አቅም ግንባታ ሥልጠና የሶዶ ማዕከል ሠልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ዝግጅት ተደረገላቸው።

የአቀባበል ዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ የወላይታ ሶዶ ከተማ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካና የአስተዳደር ማዕከል እና ከ80 በላይ ብሔር ብሔረሰቦች ተከባብረው እና ተቻችለው የሚኖሩባት ባለሰባት በር የንግድና ኢንቨስትመንት ከተማ መሆኗን ገልጸዋል።

ወላይታ ዞን በርካታ ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ቅርሶችና መስህቦች ባለቤት፤ የራሱ የዘመን መለወጫ በዓል 'ጊፋታ' ያለው፣በርካታ የኢንቨስትመንት አማራጮች ያሉት እንዲሁም ኦፓልን የመሳሰሉ ማዕድናት ባለቤት መሆኑንም ለታዳሚዎች አብራርተዋል አቶ ሳሙኤል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም የወላይታ ህዝብ ከሌሎች ወንድም ህዝቦች ጋር በተለያዩ ጊዜያት የተቃጡብንን ወረራዎች በመቀልበስ ለሀገር ዋጋ የከፈለ ህዝብ እንደሆነም አንስተዋል።

ሠልጣኞች በሥልጠናው የቀሰሙትን ዕውቀት ወደ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት እንዲተጉም አነሳስተዋል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሚካሄደው ዘጠነኛው "የከተሞችን ቀን" ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ ህዳር 06/03/2016 ዓ/ም በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሚካሄደው ዘጠነኛው "የከተሞችን ቀን" ቅድ...
16/11/2023

በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሚካሄደው ዘጠነኛው "የከተሞችን ቀን" ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

ህዳር 06/03/2016 ዓ/ም በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሚካሄደው ዘጠነኛው "የከተሞችን ቀን" ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።

በከተሞች ዘላቂ ልማት እና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚሰናዳው ሀገራዊ የከተሞችን ቀን በወላይታ ሶዶ ከተማ በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

በፈጣን ዕድገት ላይ የምትገኘውን የወላይታ ሶዶ ከተማ በሀገር ደረጃ የሚከበረውን የከተሞች ቀን በጋራ እና በውጤት ለመፈጸም የሚያስችል ፍሪያማ ውይይት መካሄድ ነው የተገለጸው።

ለዘጠነኛ ጊዜ የሚዘጋጀው የከተሞች ቀን በወላይታ ሶዶ ፍፁም ሰላማዊ ፣ አስደሳች እና ልማትን አስቀጥሎ እንዲከበር በቅንጅት እንደሚሰሩ ተሳታፊዎች አስረድተዋል።

በከተሞች መሀከል ጤናማ የውድድር መንፈስ በመፍጠር እና የከተማ ዘርፍ አመራሮችን በማቀናጀት ተፈላጊውን ልማት ለማምጣት ያስችላል ነው የተባለው።

ለነዋሪዎች ምቾት ፣ ፅዳት እና ውበት እንዲሁም የመሰረተ ልማት ተደራሽ ተሞክሮዎችን በመጋራት ከተሞች በልማት ጎዳና ለመገስገስ ዕለቱ ምቹ አጋጣሚ እንደሚፈጥር ተገልጿል።

በመድረኩ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞን ጨምሮ የሶዶ ከተማ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

በወላይታ ሶዶ በሶስተኛው ዙር የአቅም ግንባታ ላይ እየተሳተፉ ላሉ ለመንግሥት አመራሮች የራት ግብዣ ፕሮግራም እየተደረገ ነውቦሎሶ ሶሬ፤ ህዳር 6/2016 በወላይታ ሶዶ የአቅም ግንባታ ላይ እ...
16/11/2023

በወላይታ ሶዶ በሶስተኛው ዙር የአቅም ግንባታ ላይ እየተሳተፉ ላሉ ለመንግሥት አመራሮች የራት ግብዣ ፕሮግራም እየተደረገ ነው

ቦሎሶ ሶሬ፤ ህዳር 6/2016 በወላይታ ሶዶ የአቅም ግንባታ ላይ እየተሳተፉ ላሉ ለመንግሥት አመራሮች የራት ግብዣ እየተደረገላቸው ይገኛል።

"ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ በወላይታ ሶዶ ስልጠና ማዕከል እየተሳተፉ ላሉ ለመንግሥት አመራሮች የራት ግብዣ ፕሮግራም እየተደረገላቸው ይገኛል።

ከመላው ሀገሪቲ ክልሎች የተወጣጡ 2 ሺህ የሚጠጉ የመንግስት አመራሮች በውቢቷና ህብረ ብሔራዊቷ ወላይታ ሶዶ ከተማ ስልጠናውን እየወሰዱ ናቸው።

በፕሮግራሙ በሚኒስቴር ማዕረግ ዋናው ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሳዳት ነሻ፣የደቡብ ኢት/ያ ክልል ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነ፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሣሙኤል ፎላ እና የወላይታ ዞን አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት የራት ግብዣ ፕሮግራም እየተደረገ ነው።

ኦቢ ኤን ቴሌቪዥን የወላይትኛ ቋንቋ ስርጭት ሊጀምር ነው፡፡ቦሎሶ ሶሬ፣ህዳር 6/2016 ከ18 ዓመታት በላይ በሚዲያው ኢንዱስትሪ የቆየው ኦ ቢ ኤን ቴሌቪዥን ከወላይታ ቴሌቪዥን ጋር በመተባበር...
16/11/2023

ኦቢ ኤን ቴሌቪዥን የወላይትኛ ቋንቋ ስርጭት ሊጀምር ነው፡፡

ቦሎሶ ሶሬ፣ህዳር 6/2016 ከ18 ዓመታት በላይ በሚዲያው ኢንዱስትሪ የቆየው ኦ ቢ ኤን ቴሌቪዥን ከወላይታ ቴሌቪዥን ጋር በመተባበር የወላይትኛ ቋንቋ ስርጭት ለመጀመር መዘጋጀቱን የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ገቢሳ ተናግረዋል፡፡

የቴሌቪዥኑ ስራ አመራር የወላይታ ቴሌቪዥን ጣቢያን የጎበኘ ሲሆን ከስርጭቱ በተጨማሪ ተቋሙን በቴክኖሎጂ እና በአቅም ግንባታ ስራዎች ይደግፋል ብለዋል፡፡

ሚዲያዎቹ በጋራ ሲሰሩ የወላይታን እና የኦሮሞን ህዝብ ለማቀራረብ ትልቅ ኃላፊነት ይወጣሉ የሚሉት የኦ ቢ ኤን የሚዲያ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ተዘራ በቀለ የወላይታ ቴሌቪዥንን በቴክኖሎጂ ዘርፍ በመደገፍ ውጤታማነቱን ለማሳደግ ታቅዷል ይላሉ፡፡

የወላይታ ቴሌቪዥን በኦ ቢ ኤን ወላይትኛ ፕሮግራም ኦ ቢ ኤን ደግሞ በወላይታ ቴሌቪዥን ኦሮሚኛ ፕሮግራም ለማሰራጨት የተጀመረው ንግግር የህዝብ ለህዝብ ግኑኝነትን የሚያጠናክር እንደሆነ የጠቁሙት ደግሞ የወላይታ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ ወ/ሮ መስከረም ደገፉ ናቸው፡፡

ሁለቱ ጣቢያዎች በጋራ መስራታቸው የውስጥ አቅማቸውን ከማጎልበት ባሻገር የህዝብ ለህዝብ ግኑኝነትና ህብረ ብሔራዊነትን የሚያጠናክር ነው የሚሉት ደግሞ በጉብኝቱ የወላይታ ዞን አስተዳደርን ወክሎ የተገኙት የመንግስት ረዳት ተጠሪ ወ/ሮ መስከረም ደገፉ እና የወላይታ ቴሌቪዥን የቦርድ አባል አቶ ዎይሻ ቦጋለ ናቸው፡፡

የወላይታ ቴሌቪዥን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሴባ ናና በበኩላቸው ኦ ቢ ኤን ብዙ ልምድ ያካበተ በመሆኑ በጋራ ለመስራት ሲወጠን የጣቢያውን ተጠቃሚነት በይዘትም በቴኬኖሎጂም ያጎላል ብለዋል፡፡

የኦ ቢ ኤን ቴሌቪዥን ስራ አመራሮች በወላይታ ቴሌቪዥን ጽህፈት ቤት ካደረጉት ጉብኝት ባሻገር የጋራ ምክክር ያካሄዱ ሲሆን በአሰራሩ ላይ ከስምምነት ሲደረስ በቅርቡ የወላይትኛ ቋንቋን በኦቢኤን ኦሮሚኛ ቋንቋን በወላይታ ቴሌቪዥን ስርጭት ለማስጀመርም ታቅዷል፡፡

#ወቴቪ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ የሱዳን ሪፐብሊክ ሉአላዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃንን እና ልዑካን ቡድናቸውን በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በመገኘት ተ...
15/11/2023

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ የሱዳን ሪፐብሊክ ሉአላዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃንን እና ልዑካን ቡድናቸውን በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በመገኘት ተቀብለዋል:: በመቀጠል ሁለቱ መሪዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የጋራ በሆኑ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።

Prime Minister Abiy Ahmed received at Bole International Airport General Abdelfattah Alburhan, President of the Transitional Sovereignty Council of the Republic of the Sudan and his delegation. The two sides later exchanged views on current issues of mutual interest at the Office of the Prime Minister.

ከመላው የሀገራችን ክፍሎች ለተውጣጡ የመንግሥት አመራሮች በሚሰጠው ስልጠና ላይ ለመሳተፍ በደቡብ ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ወላይታ ሶዶ ተገኝቻለሁ ፤ የሶዶ እና አካባቢው ማህበረሰብ ላደረገልኝ ደማ...
15/11/2023

ከመላው የሀገራችን ክፍሎች ለተውጣጡ የመንግሥት አመራሮች በሚሰጠው ስልጠና ላይ ለመሳተፍ በደቡብ ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ወላይታ ሶዶ ተገኝቻለሁ ፤ የሶዶ እና አካባቢው ማህበረሰብ ላደረገልኝ ደማቅ አቀባበል ከልብ አመሰግናለሁ::

መንግስታችን በ17 ማዕከላት ስልጠና በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን ፤ስልጠናው የአመራሩን የአመለካከትና የተግባር አንድነትን አስጠብቆ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና እና የሀገረ መንግስት ግንባታ ጉዞ የሚያሳኩ ጉዳዮችን ተረድቶ ፣በጋራ ለመተግበርና የትናንት ወረትን ወደ ዛሬና ነገ ምንዳ ለማሸጋገር አቅም ለመገንባት የሚያስችል ይሆናል።

ክብርት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል

በብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን በቻይና የዱጂያንግያን የመስኖ ፕሮጀክትን ጎበኘ።በብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተ...
15/11/2023

በብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን በቻይና የዱጂያንግያን የመስኖ ፕሮጀክትን ጎበኘ።

በብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን በቻይና የዱጂያንግያን መስኖ ኢንጂነሪንግን ጎብኝቷል፡፡

የመስኖ መርሃ ግብሩ ጎርፍን የሚቆጣጠር፤ ለቼንዱ ሜዳማ አካባቢ የመስኖ ውሃ ምንጭነት እንዲሁም የቱሪስት መስህብ ሆኖ እንዲያገልግል ነው ተብሏል፡፡

የመስኖ ፕሮጀክቱ የአመራር ስርዓት፣ የጥንታዊት ቻይናን የአመራር ጥበብን እና የዘመናዊ የምህንድስና ሳይንስ አቅም ያያዘ ነው።

"በተያዘው በጀት ለ3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዷል፡፡ እስከ አሁን ባለው ሂደት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል፡፡በተጨማሪም  በውጭ አገራት...
15/11/2023

"በተያዘው በጀት ለ3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዷል፡፡ እስከ አሁን ባለው ሂደት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል፡፡በተጨማሪም በውጭ አገራት በህጋዊ መንግድ 100 ሺህ ለሚሆኑ ሰዎች የስራ ዕድል እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡"

#የጠሚሩ ምላሾች

ከወላይታ ዞን አትክልትና ፍራፍሬ ኮሪደሮች በጥቂቱ
14/11/2023

ከወላይታ ዞን አትክልትና ፍራፍሬ ኮሪደሮች በጥቂቱ

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Boloso Sore media Times/BSMT posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share