Fana Tv

Fana Tv Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Fana Tv, TV Channel, .

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የፌዴራል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ጥር 23 /2016 ዓ.ም የሰጠውን መግለጫ አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።በዚህ መግለጫው ፤ ከፕሪቶርያ ስምምነ...
05/02/2024

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የፌዴራል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ጥር 23 /2016 ዓ.ም የሰጠውን መግለጫ አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።

በዚህ መግለጫው ፤ ከፕሪቶርያ ስምምነት አፈፃፅም ጋር በተያያዙ በኮሚኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ ላይ የተጠቀሰውና ከትግራይ ሉአላዊ ግዛት መረጋገጥ ጋር በተያያዘ " ጉዳዩን በሪፈረንደም ለመፍታት መረዳዳት ተደርሶ ነበር " በሚል የቀረበው መግለጫ ፍፁም የተሳሳተ ነው ብሏል።

" ጊዚያዊ አሰተዳደሩም ሆነ ፌደራል መንግስቱ በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ሕገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ ጉዳዩን ለመፍታት ከደረሱበት ስምምነትም ሆነ ካላቸው ስልጣን ውጪ የሆነ ተግባር መሆኑን በተደጋጋሚ ያነሳነው ስለሆነ ተቀባይነት የሌለዉ መሆኑን መግለፅ እንወዳለን። " ሲል አክሏል።

ሌላው ፤ ከተፈናቃዮች መመለስ ጋር ተያይዞ " ትክክለኛ ተፈናቃዮች ተመልሰዋል " በሚል የቀረበው የመግለጫው ክፍል እጅግ አደገኛና በጉልበት የሃገሪቱ ካርታ ለመቀየር የፌዴራል መከላከያ ሆነ የጎረቤት ሃገራትን አቅም ተጠቅሞ የተደረገን አውዳሚ እንቅስቃሴ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የሚያግዝ ነው ብሏል።

ከምንም ነገር በላይ ግን " ትክክለኛ ተፈናቃይ " ፤ " ትክክለኛ ያልሆነ ተፈናቃይ " በሚል መፈታት የነበረበትን ችግር የበለጠ የሚያባብስ አደገኛ ትንታኔ ስለሆነ አንቀበለዉም ሲል አሳውቋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው ፤ " አሁንም ከሚልዮን በላይ ቁጥር ያላቸው ተፈናቃዮች በአስከፊ ሁኔታ የሚኖሩበት፤ ያፈናቀላቸዉ ፀረ ህዝብ እና ሕገ ወጥ አስተዳደሪዎች ፌደራል መንግስቱ ከመንበራቸው ሊያስወግዳቸው ሲገባ አሁንም ሕግ አስከባሪዎች ነን ብለው በሚመፃደቁበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው እንደዚህ ዓይነት መግለጫ መውጣቱ የፌደራል መንግስቱ የመፍትሄው አካል መሆን ሲገባው የችግሩ አካል ለመሆን የወሰነ የሚያስመሰለው ስለሆነ በፍፁም ተቀባይነት የለውም " ብሏል።

" የፌደራል መንግስቱ ከፕሪቶርያ ስምምነት ወዲህ የወሰናቸው በተለይም ከበጀትና መሰል ጉዳዮች ጋር የተያያዙ አበረታችም ሆኑ መታረም ያለባቸው ጉዳዮች በሚመለከት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፓርት የሚቀርብ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የምንለው ነገር አይኖርም " ሲል አሳውቋል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፤ ሰላም በሁሉም የትግራይ እና የኢትዮጵያ አከባቢዎች በተሟላ መልኩ የሚረጋገጥበት ሁኔታ እስኪፈጠር ድረስ ከፌደራል መንግስት በመቀራረብ እንደሚሰራ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

 #ይነበብ !  #ይሰራጭ !• አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ?• የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ቢሮ ?(ይህ መረጃ ከፋና የምርመራ ዘገባ የተወሰደና አዘጋጁ መርማሪ ጋዜጠኛ ሞሊቶ ኤል...
16/08/2023

#ይነበብ ! #ይሰራጭ !

• አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ?

• የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ቢሮ ?

(ይህ መረጃ ከፋና የምርመራ ዘገባ የተወሰደና አዘጋጁ መርማሪ ጋዜጠኛ ሞሊቶ ኤልያስ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአንባቢያን ያሳውቃል)

(ፅሁፍ ዝግጅት በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ)

ጉዳዩ እንዲህ ነው...

ታህሳስ 7 /2015 ዓ/ም በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኘው አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል በተጓደሉ የህክምና ባለሞያዎች ምትክ የሰው ኃይል ለማሟላት የቅጥር ማስታወቂያ ያወጣል።

በዚህም ማስታወቂያ መሰረት 286 ጠቅላላ ሃኪም፣ 67 የላብራቶሪ ባለሞያዎች፣ 117 የመድሃኒት ቤት ባለሞያዎች ፈተናውን ለመውሰድ ይመዘገባሉ።

ተወዳዳሪዎች በግልፅና በይፋ በወጣ የፅሁፍ ፈተና ማስታወቂያ ጥሪ መሰረት ጥር 3/2015 ዓ/ም ላይ ፈተና ወስደዋል። የፅሁፍ ፈተናውን በአብላጫ ውጤት ያለፉት ተወዳዳሪዎች ውጤቱን አይተው የቃል ፈተና ወስደዋል። ያሉ ተወዳዳሪዎችም በግልፅ ተለጠፈ።

ሆስፒታሉ ከተመዘገቡት ውስጥ ብቁ ናቸው ያላቸውን በአጠቃላይ 16 የጤና ባለሙያዎች፦
👉 8 ጠቅላላ ሀኪም
👉 5 ፋርማሲስት
👉 3 የላብራቶሪ ባለሞያዎች ይፋዊ ጥሪ አቅርቦ ቅጥር ፈፀመላቸው።

ከዚህ ለኃላ ባለሞያዎቹ የወር ደመወዝ ተከፏለቸው፣ እስከ መጋቢት 13 ጥዋት ድረስ በስራ ላይ ከቆዩ በኃላ ስብሰባ አዳራሽ ትፈላጋላችሁ ተብለው ይጠራሉ።

ባለሞያዎቹ ኑ ሲባሉ የመሰላቸው የ " እንኳን ደህና መጣችሁ " ስነስርዓት ነበር ነገር ግን ያልጠበቁት ዱብእዳ ተናገራቸው። ይህም የቅጥር ሂደቱ ላይ የህገወጥነት ጥርጣሬ ስላለ ምርመራ እስኪደረግ መታገዳቸው ተገለፀላቸው። እግዱን የሚመለከት ደብዳቤም ተሰጣቸው።

የእግድ ደብዳቤው መጋቢት 13 በሆስፒታሉ የበላይ ኃላፊ የተፃፈ ነው። ጥርጣሬ አለኝ ሂደቱ መረምራለሁ ያለው የሲደማ ፐብሊክ ሰትቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ነው።

ቢሮው ምንድነው የሚለው ?

- ከቅጥሩ ህጋዊነት ጋር በተያየዘ ጥቆማ ደረሰን እሱን አጣራን።
- የማጣራት ስራው የተሰራው በአጣሪ ቡድን ተቋዉሞ ነው። ቡድኑ ሁለት ሰዎች ነው ያሉት።
- የማጣራት ስራው የፈጀው ሁለት ቀን ነው።

ይኸው አጣሪ ቡድን ከሁለት ቀን የመረጃ ማሰባሰብ ስራ በኃላ የቅጥር ሂደቱ " ህገወጥ ነው " በሚል የህክምና ባለሞያዎቹ ቅጥር መሰረዝ አለበት የሚል ምክረ ሃሳብ ለቢሮው አቅርበዋል።

በዚህ ጥናት መነሻ ቢሮው " የተፈፀመው የስራ ቅጥር ተሰርዟል ፤ በምትካቸው አዲስ ማስታወቂያ ይውጣና የሰው ኃይል ይቀጠር " የሚል ውሳኔ አሳለፈ።

የቢሮው አጥኚ ቡድን ጥናት በተደረገበት ወቅት ሆስፒታሉ ምንም መረጃ ሳይደብቅ ሰጥቶታናል በሚል ምስጋና አቅርቧል። እውነት ሆስፒታሉ የደበቀው ነገር የለም ?

ጥናቱ ሲፈተሽ...

ለምን ቅጥሩ እንዲሰረዝ ተወሰነ ?

ይኸው 2 አባላት ያሉት አጥኚ ቡድን ወደ ሆስፒታሉ ሄጄ ከ " ሰው ሃብት አ/ደ/የሥ/ሂደት " አገኘሁ እና አሰባሰብኩ ባለው መረጃ መሰረት ለቅጥሩ መሰረዝ ምክንያቶች ናቸው ያላቸው፦

1. የአዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል የቅጥር ኮሚቴ ሕጉን ጠብቆ ቢቋቋምም የህክምና ባለሞያዎቹ ቅጥር ሲፈፀም ከኮሚቴው ሰብሰቢ አቶ በረከት አመሎ በስተቀር ሌሎች አባላት አልተሳተፉም የሚል ነው።

፦ ይህ የጥናቱ ውጤት የተሳሳተ ሲሆን ባለሞያዎቹ ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት የቅጥር ኮሚቴ አባላት ተሰብስበው በፈተናው አሰጣጥ ሂደት ላይ የተወያዩበትና የምልመላ መስፈርቶችን በተመለከተ ውሳኔ ያሳለፉበት ቃለ ጉባኤ ሰነድ ተገኝቷል። በዚህም የኮሚቴው ሰብሰቢ እና ፀሀፊ ጨምሮ 9 አባላት ውሳኔውን በፊርማቸው አፅድቀዋል።

2. ሁለት (2)

 የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የ " ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል " መስራች ጉባኤ ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ስራ ማጠናቀቁን አሳውቋል።በሰባት የክልል ማእከላት እየተደራጀ ያለው የ " ማዕከላዊ ኢት...
16/08/2023



የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የ " ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል " መስራች ጉባኤ ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ስራ ማጠናቀቁን አሳውቋል።

በሰባት የክልል ማእከላት እየተደራጀ ያለው የ " ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል " ነሀሴ13 /2015 ዓ/ም በጉራጌ ዞን፤ በወልቂጤ ከተማ የምስረታ ጉባኤውን እንደሚያካሂድ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ እንዳለ ስጦታው ተናግረዋል።

ከንቲባው ፤ አስተዳደሩ በዚህ ጉባኤ ምክንያት ከ2500 እስከ 3000 እንግዶችን ለመቀበል የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን አመልክተዋል።

ከፀጥታው ጋር በተያያዘ ሁሉም የፀጥታ መዋቅር የዞን ፣ ከተማ ፣ አበሽጌ እና ቀቤና ወረዳ በጋራ በመሆን የከተማውን ሰላም ለማስጠበቅ በጋራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

መረጃው የከተማው ኮሚኒኬሽን ነው።

26/01/2023

Welcome to Fana tv

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fana Tv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share