ethiohow.com

ethiohow.com Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ethiohow.com, Media/News Company, .

27/03/2020

በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ተጠቂዎች 16 ደረሰዋል!

የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ፡-

ታማሚ 1 ፦

የ72 ዓመት ሞሪሸሳዊ ሲሆኑ መጋቢት 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከኮንጎ ብራዛቪል የተመለሱ ናቸው፡፡ መጋቢት 13፣2012 ዓ.ም ወደ ጤና ተቋም የሄዱ ሲሆን ተቋሙም ለኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖርት በማደረጉ በተደረገላቸው የላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፡፡ ታማሚውም በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከታማሚው ጋር ግንኙነት የነበራቸው 6 ሰዎች በክትትል ላይ የሚገኙ ሲሆን ከነሱ ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሌሎች ሰዎችን የማጣራት ሂደት እየተከናወነ ይገኛል፡፡

ታማሚ 2፦

የ61 ዓመት የአዳማ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያዊ ናቸው፡፡ በተገኘው መረጃ መሠረት ግለሰቡ የውጭ የጉዞ ታሪክ ባይኖራቸውም በስራ ባህሪያቸው ምክንያት ከአንድ የውጭ ሀገር ዜጋ ጋር ግንኙነት ነበራቸዉ፡፡

ታማሚው ግለሰብ መጋቢት 9 ቀን 2012 ዓ.ም የህመም ስሜት ሲሰማቸው ራሳቻውን አግልለው እንደቆዩና መጋቢት 16፣ 2012 ዓ.ም ወደ ጤና ተቋም የሄዱ ሲሆን ተቋሙም ሪፖርት ባደረገው መሰረት በላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፡፡ በአሁኑ ወቅት ታማሚው በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከታማሚው ጋር ግንኙነት የነበራቸው 24 ሰዎች በክትትል ላይ የሚገኙ ሲሆን ከነሱ ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሌሎች ሰዎችን የማጣራት ሂደት እየተከናወነ ይገኛል፡፡

ታማሚ 3 ፦

የ28 ዓመት ኢትዮጵያዊት ስትሆን የመጨረሻ ጉዞዋም መጋቢት 12፣ 2012 ዓ.ም እስራኤል ሀገር ደርሳ የተመለሰች ናት፡፡ ግለሰቧም በቀን 16፣ 2012 ዓ.ም በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
በተደረገላት የላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዙዋ ተረጋግጧል፡፡ በአሁኑ ወቅት ታማሚዋ በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የህክምና ክትትል እየተደረገላት ይገኛል፡፡ ከታማሚዋ ጋር ግንኙነት የነበራቸው 7 ሰዎች በክትትል ላይ የሚገኙ ሲሆን ከነሱ ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሌሎች ሰዎችን ማጣራት ሂደት
እየተከናወነ ይገኛል፡፡

ታማሚ 4 ፦

የ24 ዓመት ኢትዮጵያዊት ስትሆን የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የሌላት ቢሆንም የበሽታው ምልክት ከታየባቸው ሰዎች ጋር የነበራት ግንኙነት እየተጣራ መሆኑ እና ግለሰቧም በቀን 17፣ 2012 ዓ.ም በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በተደረገላት የላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዙዋ ተረጋግጧል፡ በአሁኑ ወቅት ታማሚዋ በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የህክምና ክትትል እየተደረገላት ይገኛል፡፡

በአዳማ ከተማ 1 በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ተገኘ!በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አንድ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው መገኘቱን በክልሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተቋቋመው ግብረ ሃይል ገለጸ...
27/03/2020

በአዳማ ከተማ 1 በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ተገኘ!

በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አንድ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው መገኘቱን በክልሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተቋቋመው ግብረ ሃይል ገለጸ፡፡

ከግለሰቡ ጋር ንክኪ የነበራቸው 24 ሰዎች ተለይተዋልም ነው የተባለው። ግብረ ሃይሉ በህብረተሰቡና በተቋማት የሚታየው ቸልተኝነት አሁንም #አሳሳቢ ነው ብሏል።

 - በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድ ተጨማሪ ሰው በመገኘቱ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 12 ደርሰዋል።- ይህ ታማሚ የ34 ዓመት ኢትዮጵያዊ ነው፤ መጋቢት 10 ነው ከዱባይ ወደ ኢትዮጵያ የ...
24/03/2020



- በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድ ተጨማሪ ሰው በመገኘቱ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 12 ደርሰዋል።

- ይህ ታማሚ የ34 ዓመት ኢትዮጵያዊ ነው፤ መጋቢት 10 ነው ከዱባይ ወደ ኢትዮጵያ የገባው።

- ግለሰቡ የህመም ምልክት ያሳየው መጋቢት 13/2012 ዓ/ም ነው። በተደረገለት ምርመራ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጣል።

- ከታማሚው ጋር ግንኙነት የነበራቸው 15 ሰዎች በክትትል ላይ ይገኛሉ።

በአፍሪካ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 1,872 ደርሷል። 50 ሰዎችም በቫይረሱ መሞታቸውን   ዘግቧል።
24/03/2020

በአፍሪካ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 1,872 ደርሷል። 50 ሰዎችም በቫይረሱ መሞታቸውን ዘግቧል።

የማህበራዊ ርቀት አሁንም በሚፈለገው መልኩ ተግራባራዊ እየተደረገ አይመስልም። ይህ ፎቶ ዛሬ ጥዋት ቦሌ ክፍለ ከተማ መሬት ማኔጅመት ፅ/ቤት የነበረውን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። እኚህ ትንሽ የሚመ...
24/03/2020

የማህበራዊ ርቀት አሁንም በሚፈለገው መልኩ ተግራባራዊ እየተደረገ አይመስልም። ይህ ፎቶ ዛሬ ጥዋት ቦሌ ክፍለ ከተማ መሬት ማኔጅመት ፅ/ቤት የነበረውን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። እኚህ ትንሽ የሚመስሉ ችግሮች ነገ ዋጋ ማስከፈላቸው አይቀርም።

በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] እንዳንጠቃ ብቸኛው መፍትሄ በጤና ባለሞያዎች የሚሰጡትን ምክሮች መተግበር ብቻ ነው። በሽታው እስካሁን ምንም አይነት የተረጋገጠ መድሃኒት አልተገኘለትም። በብዙ ሺ...
24/03/2020

በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] እንዳንጠቃ ብቸኛው መፍትሄ በጤና ባለሞያዎች የሚሰጡትን ምክሮች መተግበር ብቻ ነው። በሽታው እስካሁን ምንም አይነት የተረጋገጠ መድሃኒት አልተገኘለትም።

በብዙ ሺህ የሚቆጠር ሰው በየዕለቱ በቫይረሱ እየተጠቃ ነው። በሺህ የሚቆጠርም ሰው እየሞተ ነው። ብዙ ሀገራት በመዘናጋታቸው ዋጋ እየከፈሉ ነው። እኛም የሌሎች በርካታ ሀገራት ዕጣ እንዳይደርሰን የጤና ባለሞያዎችን ምክር እንተግብር።

ሰው የሚሰበሰብበት ቦታ አትገኙ ከተባልን ከጤናችን ስለማይበልጥ ባንገኝ ይመረጣል። ርቀታችሁን ጠብቁ ከተባልን ርቀታችን እንጠብቅ፣ የእጃችሁን ንፅህና ጠብቁም ከተባል ያን እናድርግ!

መንግስት ግን እየተላለፉ ያሉ መመሪያዎች ተፈፃሚ እየሆኑ እንዳልሆነ ካወቅ አሁንም ጊዜው ሳይረፍድ ሁሉንም ሰው ቤት ውስጥ እንዲቀመጥ ማድረግ ይኖርበታል። በእዚህ አይነት እንቅስቃሴዎች ከቀጠሉ ፍፁም የከፋ ችግር ላይ መውደቃችን ስለማይቀር።

ስለ   virus  ትክክለኛ እውቀት አሎት? እራሶን ቤተሰቦን ይጠብቁ #ሁላችንም ሀላፊነታችንን ባግባቡ እንወጣ
24/03/2020

ስለ virus ትክክለኛ እውቀት አሎት?
እራሶን ቤተሰቦን ይጠብቁ
#ሁላችንም ሀላፊነታችንን ባግባቡ እንወጣ

22/03/2020

በአርባ ምንጭ ከተማ በኮሮና ቫይረስ ተጠርጣሪዉ ግለሰብ በዛሬዉ ዕለት ናሙና ተወስዶ በምርመራ እንዲረጋገጥ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ከክልል ጤና ቢሮ ጋር በጥምረት እየተሰራን እንደሚገኝ ተልጿል፡፡ ህብረተሰቡ በምርመራ ባልተረጋገጠ መረጃ መረበሽና መደናገር እንደሌለበት የዞኑ ጤና መምሪያ መልዕክት አስተላልፏል።

በአርባ ምንጭ ከተማ በኮሮና  ቫይረስ ጋር የተጠረጠረ የ36 ዓመት ግለሰብ በለይቶ ማቆያ ክትትል እየተደረገለት እንደሚገኝ የዞኑ ጤና መምሪያ ገለጸ!የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊና የዞኑ ምክት...
22/03/2020

በአርባ ምንጭ ከተማ በኮሮና ቫይረስ ጋር የተጠረጠረ የ36 ዓመት ግለሰብ በለይቶ ማቆያ ክትትል እየተደረገለት እንደሚገኝ የዞኑ ጤና መምሪያ ገለጸ!

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊና የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተሻለ ማናዬ ዛሬ በሰጡት መግለጫ የ36 ዓመት ግለሰብ ጉንፋን መሰል ምልክቶች ታይቶበት አርባምንጭ ሆስፒታል ለህክምና በመጣበት ተጠርጥሮ ለጥንቃቄ ሲባል ለይቶ ማቆያ መዕከል ላይ እንዲቆይና የባለሙያ ክትትል እየተደረገለት ይገኛል፡፡

ግለሰቡም በቀን 07/07/2012 ዓ.ም. ለአንድ ቀን በኬንያ ለንግድ የተንቀሳቀሰ በመሆኑና ኬንያ ደግሞ የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት አገር በመሆኑ ምክንያት ግለሰቡ ሊጠረጠር ችሏል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ግለሰቡ በመልካም የጤንነት ሁኔታ ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ተሻለ ከግለሰቡ ጋር ንኪኪ ያላቸዉን ሰዎች የመለየት ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡

ምንጭ፦ የጋሞ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን

https://www.facebook.com/100002069490657/posts/2920861214659500/?app=fbl
17/03/2020

https://www.facebook.com/100002069490657/posts/2920861214659500/?app=fbl



አሜሪካ ኮሮና ቫይረስን የሚያጠቃ እና በሽታውን ለመከላከል ያስችላል ያለችውን ክትባት ለመጀመሪያ ጊዜ በሰው ላይ ሙከራዋን አድርጋለች፡፡

አራት በጎ ፈቃደኛ በሽተኞችም ክትባቱን ዋሽንግተን በሚገኘው የምርምር ተቋም መቀበላቸውን አሶሺዬትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

ክትባቱ Covid-19 ወይም ኮሮና ቫይረስን የማያስከትል ሲሆን በቫይረሱ ምክንያት የሚፈጠሩ በሽታ አምጪ ተዋህሲያን ግን ሊገድል እንደሚችል ተስፋ ተጥሎበታል፡፡

ባለሙያዎቹ እንደሚናገሩት ይህ ክትባት ወይም ሌሎች በምርምር ላይ ያሉ መድኃኒቶችም ቢሆን ከቫይረሱ ያድናሉ ብሎ በሙሉ ልብ ለመናገር በርካታ ወራቶችን መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡

ምንጭ፦ ETHIO FM 107.8

 የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮሮና ቫይረስ በአየር ትራንስፖርት ዘርፉ ላይ ያመጣውን ቀውስ ተከትሎ የተለያዩ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ እንዳለ ገልጿል፡፡አየር መንገዱ ቫይረሱ በአለም ዙሪያ በ...
16/03/2020



የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮሮና ቫይረስ በአየር ትራንስፖርት ዘርፉ ላይ ያመጣውን ቀውስ ተከትሎ የተለያዩ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ እንዳለ ገልጿል፡፡

አየር መንገዱ ቫይረሱ በአለም ዙሪያ በስፋት መሰራጨቱ ያስከተለውን የተጓዦች መቀነስ ተከትሎ አንዳንድ እርምጃዎችን ብወስድም ሰራተኛን እስከመቀነስ የሚያደርስ ሁኔታ ላይ ግን አይደለሁም ብሏል፡፡

አየር መንገዱ ለኃይማኖቶች አባቶች ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር እየሰራ ያለውን ስራ አስጎብኝቷል።

ምንጭ፦ ኢቢኤስ

ይሄ page ትክክለኛ ስለ corona virus  በ ሀገራችን ኢትየጵያ ውስጥ ያለውን መረጃ  የሚዳሰስበት ነው።ሀሰት ከሆነ መረጃ እራሳችንን እና ሀገራችንን እንጠብ።  በማድረግ ለሌሎች እናድ...
16/03/2020

ይሄ page ትክክለኛ ስለ corona virus በ ሀገራችን ኢትየጵያ ውስጥ ያለውን መረጃ የሚዳሰስበት ነው።
ሀሰት ከሆነ መረጃ እራሳችንን እና ሀገራችንን እንጠብ።
በማድረግ ለሌሎች እናድርስ
ፈጣሪ ሀገራችንን ይጠብቅ

 ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ በኳታር ውስጥ ባሉ ካፌዎች እና ምግብ ቤቶች ውስጥ ምግብ እና መጠጥ መጠቀም የተከለከለ ሲሆን ፣ ይህን ክልከላ የተላለፈ አካል እርምጃ እንደሚወሰድበት ተገልጿል...
16/03/2020



ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ በኳታር ውስጥ ባሉ ካፌዎች እና ምግብ ቤቶች ውስጥ ምግብ እና መጠጥ መጠቀም የተከለከለ ሲሆን ፣ ይህን ክልከላ የተላለፈ አካል እርምጃ እንደሚወሰድበት ተገልጿል። ሆኖም ግን ካፌዎች እና ምግብ ቤቶች የትዕዛዝ (take away) አገልግሎት ብቻ መስጠት ይችላሉ ተብሏል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ዶሃ

በተጨማሪ፦ዛሬ አንድ ግለሰብ በሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ምልክቶች ታይተውበታል በሚል በሀዋሳ ከተማ የተቋቋመው ግብረ ሀይል ልዩ የምርመራ እና የክትትል ስራን የ...
16/03/2020

በተጨማሪ፦

ዛሬ አንድ ግለሰብ በሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ምልክቶች ታይተውበታል በሚል በሀዋሳ ከተማ የተቋቋመው ግብረ ሀይል ልዩ የምርመራ እና የክትትል ስራን የሰራ ሲሆን፤ ውጤቱ በግለሰቡ ላይ ምንም አይነት የኮሮና ቫረስ እንዳልተገኘበት የሚያሳይ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ ህዝብ ግንኙነት

 ግብፃዊው ግለሰብ ከቫይረሱ ነፃ ነው!አንድ  ግብጻዊ  የመንገድ ስራ ባለሙያ ከዲላ ወደ ሀዋሳ በመግባት እና የበሽታው ምልክቶች ይሆናሉ በሚል በሀዋሳ ከተማ በልዩ ማቆያ ተደርጎ ናሙናው ተወስ...
16/03/2020



ግብፃዊው ግለሰብ ከቫይረሱ ነፃ ነው!

አንድ ግብጻዊ የመንገድ ስራ ባለሙያ ከዲላ ወደ ሀዋሳ በመግባት እና የበሽታው ምልክቶች ይሆናሉ በሚል በሀዋሳ ከተማ በልዩ ማቆያ ተደርጎ ናሙናው ተወስዶ ምርመራ ተደርጎበታል፤ የምርመራው ውጤት ምንም አይነት የኮሮና ቫይረስ በግለሰቡ አለመኖሩን የሚያስረዳም ሆኖ ተገኝቷል፡፡፡

ተጓጓዥ መንገደኞች ማድረግ ያለባቸው ጥንቃቄ፦ - የተሸከርካሪ መስኮቶች /መስታዎቶች በአግባቡ መከፈታቸውን ማረጋገጥ፣- በጉዞም ሆነ ያለጉዞ የተሸከርካሪ መስኮቶችን እና መስታዎቶችን ሙሉ ለሙሉ...
16/03/2020

ተጓጓዥ መንገደኞች ማድረግ ያለባቸው ጥንቃቄ፦

- የተሸከርካሪ መስኮቶች /መስታዎቶች በአግባቡ መከፈታቸውን ማረጋገጥ፣

- በጉዞም ሆነ ያለጉዞ የተሸከርካሪ መስኮቶችን እና መስታዎቶችን ሙሉ ለሙሉ መክፈት፣

- በህግ ከተፈቀደ የመጫን አቅም በላይ በዝቶና ተጨናንቆ አለመጫን፣

- በተሸከርካሪ ውስጥ ሀክታን እና የተጠቀሙበትን ሶፍቶች እና ማህረቦችን/ ጨርቆችን አለመጣል፣

- በተቻለ መጠን መስኮቶችን እና በሮችን ለመክፈት እንዲሁም በእጅ የሚያዙ የተሸከርካሪ ቦታዎችን ሲያዙ ጓንት፣ ጨርቅና ሶፍት መጠቀም፣

- የትራንስፖርት ክፍያ የገንዘብ ልውውጥ በተቻለ መጠን በጓንት በመጠቀም መለዋወጥ ወይም በእጆት የተለዋወጡ ከሆነ በውሀና በሳሙና ሳይታጠቡ ፊቶትን/አፍንጫዎት፣ አፎትን እና እና ወዘተ/ አለመንካት እና ምግብን አለመመገብ፣

ምንጭ፦ የትራንስፖርት ሚኒስቴር

 የጤና ሚንስትር  ዶ/ር  ሊያ  ታደሰ  ከአምቡላንስ አምልጦ የጠፋውና በለጋምቦ ወረዳ የተያዘው ግለሰብ ልየታ ማዕከል ገብቶ ናሙና የተወሰደለት ትላንት ለሊት በመሆኑ እስካሁን ድረስ የምርመራ...
16/03/2020



የጤና ሚንስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ከአምቡላንስ አምልጦ የጠፋውና በለጋምቦ ወረዳ የተያዘው ግለሰብ ልየታ ማዕከል ገብቶ ናሙና የተወሰደለት ትላንት ለሊት በመሆኑ እስካሁን ድረስ የምርመራው ውጤት እንዳልደረሰ ለetv ገልፀዋል።።

ዶክተር ሊያ ታደሰ፦- ጃፓናዊውን ጨምሮ 3ቱ የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ተጠቂዎች ጤናቸው በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል። የጉንፋን አይነት ምልክት ነው ያላቸው ከዛ ውጭ የከፋ ነገር የላቸ...
16/03/2020

ዶክተር ሊያ ታደሰ፦

- ጃፓናዊውን ጨምሮ 3ቱ የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ተጠቂዎች ጤናቸው በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል። የጉንፋን አይነት ምልክት ነው ያላቸው ከዛ ውጭ የከፋ ነገር የላቸውም።

- ዛሬ የተገለፀው 5ኛው የቫይረሱ ተጠቂ፤ በMARCH 12 ነው ወደሀገር ውስጥ የገባው። ግለሰቡ ሲገባ ምንም አይነት ምልክት አልነበረውም። ከአንድ ቀን በኃላ ነው ምልክት ያሳየው። ትኩሳት ስለነበረው ወደጤና ተቋም በመምጣት ወደልየታ መዕከል ገብቷል። ምርመራውም ቫይረሱ እንደሚገኝበት አረጋግጧል።

ተጨማሪ መረጃ፦ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በያሉበት ካምፓስ እንዲቆዩ ፤ በያሉበት ካምፓስም አስፈላጊው የጤና፣ የንፅህና ፣ ክትትል ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።የትምህርት  ስርዓቱ...
16/03/2020

ተጨማሪ መረጃ፦

ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በያሉበት ካምፓስ እንዲቆዩ ፤ በያሉበት ካምፓስም አስፈላጊው የጤና፣ የንፅህና ፣ ክትትል ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የትምህርት ስርዓቱን በሚመለከት ተማሪዎች በክፍላቸው (Rooms) ሆነው መማር የሚችሉባቸውን መንገዶች ለማመቻቸት የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሚያወጣቸውን መመሪያዎች እና አሰራሮች እንዲከታተሉ ብለዋል።

አክለውም እነሱን ካሉበት መበተኑ ተጨማሪ አደጋ ሊያስከትል ስለሚችል እዚያው እንዲቆዩና ጤናቸውን መጠበቅ ይበልጥ የተሻለ መሆኑን ተግባብተንበታል ሲሉ ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ ከኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ስጋት ጋር በተያያዘ ለ15 ቀን እንዲዘጉ የተወሰነው የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶችን እንጂ ዩኒቨርሲቲዎችን አያካትትም።
16/03/2020

በኢትዮጵያ ከኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ስጋት ጋር በተያያዘ ለ15 ቀን እንዲዘጉ የተወሰነው የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶችን እንጂ ዩኒቨርሲቲዎችን አያካትትም።

በመንግስት የተላልፉ ውሳኔዎች፦• ሰፋ ያለ ቁጥር ያላቸው ስብሰባዎች ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት እንዳይካሄዱ • የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ጨምሮ ሰፋ ያሉ የስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ለሁለት ...
16/03/2020

በመንግስት የተላልፉ ውሳኔዎች፦

• ሰፋ ያለ ቁጥር ያላቸው ስብሰባዎች ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት እንዳይካሄዱ

• የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ጨምሮ ሰፋ ያሉ የስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ለሁለት ሳምንታት እንዳይካሄዱ

• የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላ ሀገሪቱ ለሁለት ሳምንታት እንዲዘጉ

• እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባሉበት ቦታ ሆነው ሳይወጡ እና ሳይገቡ ክትትል እየተደረገላቸው እንዲቆዩ

• በእምነት ተቋማት የሚደረጉ ሰፋ ያሉ የአምልኮ ሥርዓቶች ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት እንዲቀንሱ የሚደረግበትን አግባብ የሃይማኖት መሪዎች እንዲያመቻቹ ተጠይቋል፡፡

 በኢትዮጵያ ካለው የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ስርጭት ስጋት ጋር በተያያዘ ከዩኒቨርሲቲዎች ውጪ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የትምህርት ቤቶች ለ15 ቀን እንዲዘጉ ትዕዛዝ ተላልፏል።
16/03/2020



በኢትዮጵያ ካለው የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ስርጭት ስጋት ጋር በተያያዘ ከዩኒቨርሲቲዎች ውጪ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የትምህርት ቤቶች ለ15 ቀን እንዲዘጉ ትዕዛዝ ተላልፏል።

ሰበር ዜና!ከዛሬ ጀምሮ ትምህርት ቤቶች ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እና ትላልቅ ስብሰባዎች ለ15 ቀናት እንደሚዘጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ትዕዛዝ ሰጥተዋል። #ኤፍቢሲ
16/03/2020

ሰበር ዜና!

ከዛሬ ጀምሮ ትምህርት ቤቶች ፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እና ትላልቅ ስብሰባዎች ለ15 ቀናት እንደሚዘጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።

#ኤፍቢሲ

ናይሮቢ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት አቋረጠ!ናይሮቢ ዩኒቨርሲቲ ከኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ስርጭት ስጋት ጋር በተያያዘ የመማር ማስተማር ስራውን አቋርጧል። በዚህ ሳምንት ሊሰጡ የነበሩ ፈተናዎች...
16/03/2020

ናይሮቢ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት አቋረጠ!

ናይሮቢ ዩኒቨርሲቲ ከኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ስርጭት ስጋት ጋር በተያያዘ የመማር ማስተማር ስራውን አቋርጧል። በዚህ ሳምንት ሊሰጡ የነበሩ ፈተናዎችም ተሰርዘዋል። ትምህርት በኦንላይ እንዲቀጥል ተብሏል። በአሁን ሰዓት በኬንያ በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 3 ናቸው።

ትምህርት ቤትን መዝጋት በተመለት!የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ትምህርት ቤትን መዝጋት በተመለከተ ለጊዜው የተወሰነ ውሳኔ የለም፤ በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማሩ ስራ ይቀጥላል ሲል ለ...
16/03/2020

ትምህርት ቤትን መዝጋት በተመለት!

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ትምህርት ቤትን መዝጋት በተመለከተ ለጊዜው የተወሰነ ውሳኔ የለም፤ በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማሩ ስራ ይቀጥላል ሲል ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ተናግሯል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ወላጆች ፣ የትምህርት ቤት ባለቤቶች ፣ የትምህርት አመራሩም በዚህ ጉዳይ ጥያቄ እያቀረበ መሆኑን አንስተው ወላጆች፣ ተማሪዎችም እርሳቸውን በማረጋጋት የመማር ማስተማር ሂደቱን እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የተለየና እጅግ በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ በሚደረስበት ወቅት እና ስጋቱ መጠን ከፍተኛ ሲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር መግለጫ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል፤ ለጊዜው የትምህርት ቤት አመራሮች፣ መምህራንና ተማሪዎች በከፍተኛ ጥንቃቄ የመማር ማስተማር ሂደቱን እንዲመሩና እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1

16/03/2020
 በለጋምቦ ወረዳ በኮሮና ቫይረስ ተጠረጠርጥሮ የተያዘው ግለሰብ ከፌዴራል በመጣ ቡድን አማካኝነት ወደ ማቆያ ቦታ ይወሰዳል ተብሏል። ህብረተሰቡ ግለሰቡ ተጠርጣሪና በበሽታው መያዙ ገና ያልተረጋ...
16/03/2020



በለጋምቦ ወረዳ በኮሮና ቫይረስ ተጠረጠርጥሮ የተያዘው ግለሰብ ከፌዴራል በመጣ ቡድን አማካኝነት ወደ ማቆያ ቦታ ይወሰዳል ተብሏል። ህብረተሰቡ ግለሰቡ ተጠርጣሪና በበሽታው መያዙ ገና ያልተረጋገጠ መሆኑን በመረዳት ብሎም አካባቢው ገብቶ ሳይሰወር በቁጥጥር ስር መዋሉን አውቆ ተረጋግቶ ራሱን እንዲጠብቅ ሲሉ የለጋምቦ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌትነት አበባው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በኮሮና ቫይረስ ተጠርጥሮ ወደ ማቆያ ቦታ በመውሰድ ላይ ሳለ አምቡላንስ ሰብሮ ያመለጠው ግለሰብ በደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቦ ወረዳ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከፌዴራል እ...
16/03/2020

በኮሮና ቫይረስ ተጠርጥሮ ወደ ማቆያ ቦታ በመውሰድ ላይ ሳለ አምቡላንስ ሰብሮ ያመለጠው ግለሰብ በደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቦ ወረዳ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡

ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከፌዴራል እና ከለጋምቦ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት እንዲሁም የፀጥታ መቃቅሩ የጋር ትብብር ማድረጋቸው ተጠቁሟል፡፡

ግለሰቡ በለጋምቦ ወረዳ 07 ቀበሌ ሰላም በር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነዋሪ ሲሆን ከአንድ ወር በፊት ከሀገር ውጭ የወጣና አሁን የተመለሰ ነው፡፡

የለጋምቦ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌትነት አበባው እንደገለጹት በቁጥጥር ስር የዋለው ግለሰብ ከውጭ ሀገር ተመልሶ አዲስ አበባ ሲደርስ የበሽታው ምልክቶች ታይተውበት ወደ ምርምራ በመወሰድ ላይ እያለ አምቡላንስ ሰብሮ ያመለጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ተጠርጣሪው ግለሰብ በትናንትናው እለት ደሴ ከተማ ያደረ ሲሆን ዛሬ ጧት በሳይንት አጅባር አገር አቋራጭ አውቶቡስ ተሳፍሮ ገነቴ ከተማ ለመድረስ ከአራት ኪሎ ሜትር ያልበለጠ ጎዞ ሲቀረው ወለቃ ወንዝ ላይ በተደረገ ፍተሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን አቶ ጌትነት አስረድተዋል፡፡

ምንጭ፦ Legambo communication

ለጤና ባለሞያዎች ክብር አለን!በበርካታ ሀገራት በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ምክንያት ትምህርት ቤቶች፣ ዩኒቨርሲቲዎች ተዘግተዋል፤ መስሪያ ቤቶችም ተዘግተዋል፣ ሰራተኞችም ቤታቸው ሆነው እ...
16/03/2020

ለጤና ባለሞያዎች ክብር አለን!

በበርካታ ሀገራት በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ምክንያት ትምህርት ቤቶች፣ ዩኒቨርሲቲዎች ተዘግተዋል፤ መስሪያ ቤቶችም ተዘግተዋል፣ ሰራተኞችም ቤታቸው ሆነው እንዲሰሩ ተድርጓል፣ የንግድ ማዕከላትም ተዘግተዋል፣ በረራዎችም፣ ዝግጅቶችም ተሰርዘዋል።

ይህ ሁሉ ሲሆን ግን በሁሉም ሀገራት ሆስፒታሎች 24 ሰዓት ክፍት ናቸው። የሰዎችን ህይወት ለማትረፍ ይረባረባሉ። ዶክተሮች ፣ የጤና ባለሞያዎች የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው በሽተኞችን ለማዳን ሁሌም የሚችሉት ያደርጋሉ።

ክብር ይገባቸዋል!

 ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ዛሬ ጠዋት  ከጃክ ማ  ጋር በአፍሪካ የCOVID19ን ስርጭት ለመግታት በጋራ ለመሥራት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ስምምነት ላይ መደረሱን ይፋ አድርገዋል። ጃክ ማ ለእያን...
16/03/2020



ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ዛሬ ጠዋት ከጃክ ማ ጋር በአፍሪካ የCOVID19ን ስርጭት ለመግታት በጋራ ለመሥራት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ስምምነት ላይ መደረሱን ይፋ አድርገዋል።

ጃክ ማ ለእያንዳንዱ የአፍሪካ ሀገር ከ10 ሺህ እስከ 20 ሺህ የሚደርሱ ኮሮናን መመርመሪያ ኪቶችን እና 100 ሺህ ማስኮችን ለማሰራጨት ከኢትዮጵያ ጋር ለመተባበር በመምረጣቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አድንቀዋል።

የሚደረገው ድጋፍ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎችን ለመንከባከብ የሚያስችሉ መመሪያዎችን አካትተው በቅርቡ የተዘጋጁ መጽሐፎችን ይጨምራልም ብለዋል።

የፊት ማስክ 500 ብር ?ትላንት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ 'የፊት ማስክ' በ500 ብር እንሸጣለን በሚል 'በማህበራዊ ድህረ ገፅ' ሲያስተዋውቁ የነበሩ ግለሰቦች የኢትዮጵያ የምግብና የመድኃኒት...
16/03/2020

የፊት ማስክ 500 ብር ?

ትላንት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ 'የፊት ማስክ' በ500 ብር እንሸጣለን በሚል 'በማህበራዊ ድህረ ገፅ' ሲያስተዋውቁ የነበሩ ግለሰቦች የኢትዮጵያ የምግብና የመድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን ከአራዳ ክፍለ ከተማ ፓሊሰ ጋር በጋራ በመሆን በቁጥጥር ስር እንዲውሉ አድርጓል።

ጥቆማ ስጡ፤ አይታችሁ አትለፉ!ማስክ እና የእጅ ንፅህና መጠበቂያ ግብዓቶች በተጋነነ ዋጋ እየሸጡ የሚገኙ መድሃኒት ቤቶች አልያም ሌሎች አካላትን ስትመለከቱ በአቅራቢያችሁ ላሉ የፍትህ አካላት ...
16/03/2020

ጥቆማ ስጡ፤ አይታችሁ አትለፉ!

ማስክ እና የእጅ ንፅህና መጠበቂያ ግብዓቶች በተጋነነ ዋጋ እየሸጡ የሚገኙ መድሃኒት ቤቶች አልያም ሌሎች አካላትን ስትመለከቱ በአቅራቢያችሁ ላሉ የፍትህ አካላት እና የጤና ተቆጣጣሪዎች ጥቆማ ስጡ፤ እንዲሁም በ8482 ነፃ የስልክ መስመር በመደወል ጥቆማ መስጠት ትችላላችሁ።

[የምግብና የመድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን]

16/03/2020

ይሄ page ትክክለኛ ስለ corona virus በ ሀገራችን ኢትየጵያ ውስጥ ያለውን መረጃ የሚዳሰስበት ነው
ሀሰት ከሆነ መረጃ እራሳችንን እና ሀገራችንን እንጠብ።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ethiohow.com posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share