Qafar xongolo

  • Home
  • Qafar xongolo

Qafar xongolo Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Qafar xongolo, Media/News Company, .

𝘼𝙠𝙖𝙙𝙚𝙧 𝙄𝙗𝙧𝙖𝙝𝙞𝙢 / 𝘼𝙠𝙠𝙪 𝘼𝙛𝙖𝙧 Duma Sanat 2005- ilaa 2011 Qafar Qunxaaneyta Digital Giclo Fan Culusak, Qafar Qunxaaneytih Xu...
07/10/2023

𝘼𝙠𝙖𝙙𝙚𝙧 𝙄𝙗𝙧𝙖𝙝𝙞𝙢 / 𝘼𝙠𝙠𝙪 𝘼𝙛𝙖𝙧 Duma Sanat 2005- ilaa 2011 Qafar Qunxaaneyta Digital Giclo Fan Culusak, Qafar Qunxaaneytih Xukko Cinak Firqawaytuuy, Qunxaaneytah Giclok Ukummo Yekke Numu.

Usug Mango Uddur Mabla Sabaabiyyol Rakuh Gacca Iyyeh Acayuk Sugeh, Nabsiyyat Axawah Tan Uma Yaabitte Fan Is Culusak Masugo.

Laakin Tawak Nabsiyyak Aboyyah Amoh Is Baahem Ekkelemmay Woo Duma Xabuxxak Qari Kaak Edde Raaqekket Yanim Yakkaleh Giclo Qembiseh Iyyah😄

Toowak Akaadarow Ta 4 Sanatah Mango Mari Casbi Culeh Sugeh, Mango Mari Baahe Qellatak Gaanun Gabat Diggalsimak Yemeetehik, Ku Kasah Casbi Kah Waasime Mara Maay Le?😀 Maca Saddik Qammih Baxah Kok Yeneksah Kaah Waaso Maay Le?🙄

Tama Doolatih Gabat Mango Mari Yontoxoyyimeh Immay Ahaay Dumah Casbi Wagsiisak Booxal Obteh Masugittohuk, Saddik Axawih Waqdi Maay Badadde?🙈....
Labhay Maabina Hay, Kedo-Baxiini Goori, Siyaasak Eyyeeqa🙄

16/01/2023
“የብልፅግና ጉዞ ይሳካል ወይ?” ብሎ ለሚጠይቁን፡-መልሳችን ይቻላል የሚል ነው። ይህ የሚቻለው ግን አራቱን የብልጽግና 4-I መርሆችን ስንከተል ነው። እነዚህም1ኛው -I = imagination...
16/01/2023

“የብልፅግና ጉዞ ይሳካል ወይ?” ብሎ ለሚጠይቁን፡-

መልሳችን ይቻላል የሚል ነው። ይህ የሚቻለው ግን አራቱን የብልጽግና 4-I መርሆችን ስንከተል ነው። እነዚህም

1ኛው -I = imagination (ትላልቅ ነገሮችን ማለም፣ ከጊዜያዊ ችግሮች በላይ ሆኖ መገኘት)። ማለም የማይችል መሪ እንኳን ትላልቅ ነገሮችን መቀየር ቀርቶ ቢሮውን እንኳ አይቀይርም። 2ኛው - I= initial ማለም ብቻውን በቂ ስላልሆነ የጀመርከውን ነገር ለመጨረስ በእጅህ/ሽ ምን አለ? የሚል ነው። አሁን ኢትዮጵያ ተነግሮ የማያልቅ የተፈጥሮ ሃብት አላት። 3ኛው - I= initiation መጀመር ነው። ማለም ብቻ በቂ አይደለም። ተነሳሽነት ወስዶ መጀመር በየጊዜው ሥራዎችን መጀመር ነው። 4ኛው - I = improvement በየጊዜው ሥራዎቻችንን እያሻሻለን መሄድ መቻል አለብን።

እነዚህን ማድረግ ከቻልን ኢትዮጵያ በልፅጋ በዓለም ላይ የማደግና ከፍተኛ ደረጃ የመያዝ ሙሉ አቅም አላት።

ጠ/ሚ ዶ/ር አቢይ አህመድ ለብልጽግና ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ.

በአፋር ክልል ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለሁለት ቀናት ሲያካሂዱ የነበረው ውይይት ተጠናቀቀ::የክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በ...
16/01/2023

በአፋር ክልል ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለሁለት ቀናት ሲያካሂዱ የነበረው ውይይት ተጠናቀቀ::

የክልሉ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለሁለት ቀናት ሲያካሂዱ የነበረው ውይይት የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተጠናቀቀ።

የውይይት መድረኩን የመሩት የኮሚንኬሽን አግልግሎት ሚንስትር ዶር ለገሰ ፣ የማዕድን ሚንስትር ዴታ አቶ ሚሊዮን እና የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕረዚዳንት አቶ አወል አርባ ሲሆኑ የውይይቱ ዋና ዓላማ እንደ ሀገር የተጀመረውን የሰላም ፣ የልማትና የአመራሩ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ አንድነትና ግንዛቤ እንዲኖረው ለማስቻል ያለመ መሆኑን ተመለከቷል።

የአፋር ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ኢሴ አደም የመድረኩን መጠናቀቅ በማስመልከት መግለጫ ስቷል።

በመግለጫቸው የፓርቲያችንን ሁለንተናዊ ጤንነት ለማረጋገጥ መርህና እሴትን በማክበር ፣ ስህተትን በማመን ለመተራረም ዝግጁ መሆን እንደሚገባ አስታውቀዋል ።

በሀገሪቱ ብሎም በክልሉ ሁለንተናዊ ሰላምን ለማረጋገጥ የፀጥታ ፣ የዴሞክራሲና የፍትህ ተቋማትን የማጠናከር ሥራ መሥራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ፣ ወንድማማችነታችንንና እህትማማችነታችንን በማጽናት በውስጣችን መተማመንን የሚፈጥር አቅጣጫ በመከተል ለዚሁ የሚመጥን አመራር መፍጠር ያሰፈልጋል ብለዋል ።

አመራሩ የዓላማ ፅናትና የትግል ቁርጠኝነትን በመላበስ የተደራጀ ስርቆትንና ብልሹ አሠራርን እንዲሁም ጽንፈኝነትን በጽናት መታገል እንደሚገባ አሳስበዋል ።

የብልጽግና ጉዟችንን በድል እንደጀመርነው ሁሉ በድል ለማስቀጠል እንደሀገር የተጋረጠብንን እርስ በርስ የመጠፋፋት ሴራ በጣጥሶ በመጣል በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ መስኮችን የተመዘገቡ አንጸባራቂ ድሎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ኃላፊነታቸው በቁርጠኝነት መወጣት እንደሚገባ አስታውቀዋል።

በመግለጫቸውም አመራሩ ባለፉት አመታት ያጋጠመውትን ተግዳራቶች በጋራ እንደተሻገረው ሁሉ ውስጣዊ አንድነቱን ለመሸርሸር የሚጥሩ ሀይሎች በጋራ መታገል እንደሚጠበቅበት አፅንኦት ሰጥቶ መክሯል።

04/09/2020

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ለነገ በጠራው አስቸኳይ ስብሰባ ምርጫው ህገ መንግስታዊ ስርአቱን አደጋ ላይ የሚጥል ነው የሚል ክስ አቅርቦ የፌዴራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ ያዛል ተብሎ ይጠበቃል። የበጀት ቀመር መከለስ የሚል አድካሚ ሂደት ይጀምራሉ ብዬ አልገምትም። ይህ የሚሆን ከሆነ አብይ አህመድ ትኩስ ድንች ይጎርሳል ማለት ነው። ከባድ አጣብቂኝ ነው። በዚህ አካሄድ የሚኖረው አንድና አንድ አማራጭ ነው። የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እንደመሆኑ የመከላከያ ሰራዊቱን ለግዳጅ ወደ ትግራይ ማንቀሳቀስ። ግጭት ወይም የለየለት ጦርነት የመከሰት እድሉ ሰፊ ነው። ይህን አስቀድሞ የጠረጠረው የትግራይ ክልል መንግስትም አካሄዱን የጦርነት አዋጅ ሲል ገልፆታል። አብይ ምርጫው እንዲካሄድ የማይፈልግበት አንድ ሶስት ምክንያቶች መጥቀስ ይቻላል።

አንደኛ የአማራ ክልል በትግራይ የሚደረገውን ምርጫ የፌዴራል መንግስት እንዲያስቆም ከፍተኛ ውትወታ ማድረጉ ነው። እንደውም ዘግይቷል በሚል ኩርፊያ ውስጥ የገቡ በርካታ የክልሉ ሃላፊዎች አሉ። ከወር በፊት የሽመልስ አብዲሳ ንግግር ከሾለከ በኋላ ባደረጉት ስብሰባ "በዚህ ወቅት ጠላት ማብዛት የለብንም እንመለስበታለን" በሚል ውሳኔ ነበር ዝምታን የመረጡት። ሆኖም በዚህ ሳምንት በተደረጉ የብልጥግና ስልጠና መድረኮች የፌዴራል መንግስት ትግራይ የሚካሄደውን በቸልታ እያየ ነው በሚል የአማራ ክልል አመራሮች ላይ ከፍተኛ ወቀሳ ቀርቧል። በዚህ ወኔው የተነሳሳው ተመስገን ጥሩነህም ጉዳዩ ከተረሳ በኋላ "የተበላነው ቁማር የለም ኮንፊውዝም ኮንቪንስም አልተደረግንም" የሚል የመልስ ምት ለሽመልስ ወረወረ። አብይ የአዴፓን ድጋፍ ካጣ ብልጥግና (በጣጢና) ፓርቲ አመት ሳይሞላው አፈር ድሜ መጋጡ እርግጥ ስለሚሆን ምርጫውን አስቁሞ የአዴፓ እምነት ለማግኘት የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም።

ሁለተኛ የትግራይ ክልል ምርጫውን ካካሄደ አብይ የሚመራው የፌዴራል መንግስት በአለም አቀፉ ማህበረሰብ እይታ ይኮሰምናል። ምርጫው እንደማንኛውም የታዳጊ ሀገር ምርጫ እንከኖች ይኖሩታል። ነገር ግን በ periodic election የህዝብ አመኔታ ለማግኘት ጥረት ያደረገ ክልልና ተቃዋሚን ባጠቃላይ አስሮና ገድሎ በማናለብኝነት ምርጫ አያስፈልግም የሚል አንድ ጀብደኛ ግለሰብ በአንድ ሚዛን አይቀመጡም። አብይ የኢሳያስ አፈወርቂ ግርፍ መሆኑን አለም በይፋ የሚያይበት ይሆናል። በቀጠናውም ሆነ በምእራባውያኑ አይን በከፍተኛ ጥርጣሬ መታየት ከጀመረ ሰንበትበት ያለው አብይ ከዚህም የከፋ ዲፕሎማሲያዊ ኪሳራ ይደርስበታል።

ሶስተኛ በአብይ አደራጅነት ለወራት "ፈንቅል" በሚል ስያሜ ሲካሄድ የነበረው የሚዲያ ሰርከስ በጀት ከመፍጀት ያለፈ ይህ ነው የሚባል ጥቅም ያላስገኘ መሆኑ የሚታይበት ይሆናል። በአራት ኪሎ ቀጭን ትእዛዝ ፊንፊኔ ላይ ተቀምጦ የክልል ፕሬዚደንት ነኝ የሚለው ነብዩ ስሁል ሚካኤልን ስታይ አብይ ራሱ መጠነኛ የፕሮፓጋንዳ ስልጠና እንደሚያስፈልገው ትረዳለህ። ምርጫው ከተካሄደ ሽመልስ አብዲሳና ተመስገን ጥሩነህን የኋላ ኪሱ ውስጥ ከክሮ በሁለቱ ክልሎች የሱ ጉዳይ አስፈፃሚ እንዳደረጋቸው ሁሉ ነብዩ ስሁልን መቀለ ላይ መሰየም እንደማይችል እርግጥ ይሆናል። ሌሎች ክልሎችም ወደፊት ራስን በራስ የማስተዳደር ጉዳይ ላይ ጠንከር ያለ አቋም እንዲይዙ ያደርጋል። በአጭሩ ንጉሰ ነገስት አብይ ትናንሽ ነገስታትን በየክልሉ የመሾም አሃዳዊ ህልሙ በሂደት ይከስማል። የፌዴራል መንግስቱን ጥርስ አልባነት የሚረዱት የአዴፓና ኦዴፓ አመራሮችም የሽመልስን ንግግር ከእንደገና መዘው እርስ በርስ የመናከስ እድላቸው ይጨምራል።

በነዚህና በሌሎች ምክንያቶች ምርጫውን አስቀድሞ ለማስቆም ሰይፍ እስከመማዘዝ ሊደረስ ይችላል። ለማንኛውም ጦርነት የማያባራ የእርስ በርስ ግጭት ውስጥ ሀገሪቱን ከመክተት ያለፈ ፋይዳ እንደማይኖረው ማሳሰብ ያስፈልጋል። የምክር ቤቱ አባላትም ይህን ከግምት ውስጥ ቢያስገቡ ጥሩ ይሆናል። በማን መተዳደር እንዳለበት የመወሰን መብቱን ለትግራይ ክልል ህዝብ መተዉ የተሻለ ነው።

01/09/2020

ሰበር ዜና : በቃ ፖለቲካ ልተንተን መሰለኝ ! ተከተሉኝ

የፌድሬሽን ም/ቤት ወሳኝ ውሳኔዎች ለማሳለፍ አስቸኳይ ስብሰባ ጠርተዋል 😝!
የአስቸኳይ ስብሰባው ዋና አላማ እና ቀዳሚ ጉዳይ ጳግሜ 2 ሁለት ልካሄድ ቀናት የቀረው የትግራይ ክልል ታሪካዊ ምርጫ ነው በተመለከተ ነው ።

ሌላኛውው ትኩሳት ደሞ ዛሬ የፌ/ን ም/ቤት የጠራው ስብሰባ በአህዳዊያን አክትቭስቶች ዘንድ ሌላ ትርጉም እየሰጡ ከልክ በላይ እየተቀባበሉት ስበዛ እየተደሰቱትም ይገኛሉ 🤔

ከአንዳንድ የትግራይ አክትቭስቶች በኩል ደሞ የስብሰባው ህግ ወጥነትን የሚገልፁ መጠነኛ ስጋት እና ትችት እየተሰማ ነው ።

ግን እኔ ጥያቄ የፈጠረብኝ የስብሰባው ጥሪ ሳይሆን የዛሬ ፌድሬሽን ም/ቤት የጠራው አስቸኳይ የውሳኔ ስብሰባ ምን የተለዬ ነገር ይከሰታል ብለው ነው ይሄ ህዝዝ ሰበር ዜና አድርገው የምያካበዱት ብዬ አሰብኩ ከዛ የራሴን ምልከታ ለማስቀመጥ ብዕረን አነሳሁ ይሄው ነው !
እስቲ መጀመሪያ ልጠይቃችሁ ዛሬ ፌድሬሽን ም/ቤት የጠራው ስብሰባ አመት ሙሉ ስንሰማ ከሰነብትነው እንዴት ተለየባችሁ❓

ምነው ከዚህ በፊት ሰለ ትግራይ ምርጫ ዙሪያ ከፌድራል መንግስት በኩል ምን ያልተወሰነ ውሳኔ ቀረና ነው ? ወይስ ሰሌላ ትግራይ ምርጫ ጉዳይ ነው የሚሰበሰቡት ?

ከጠቅላይ ሚኒስተር እስከ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የትግራይ ምርጫ ህግ ወጥ መሆኑን ስንተ ነው የነገሩን ? 😁

የተወካዮች ም/ቤት እና የፌድሬሽን ምክርቤት ሰለ ትግራይ ምርጫ አመት ሙሉ ስንተ ነው በአሰቸኳይ ጠርተው የተሰበሰቡት ግን ምን ለውጥ አመጣ ??😂
የፌድሬሽኑ የአሁን ስብሰባ ምን የተለዬ ተአምር ይወሰናል ተብሎ ነው የተደሰቱት የሚደሰቱት የሰጉት ደሞ የሚሰጉት😝

የፌድሬሽኑ ስብሰባ በመጨርሻ የሚያዋጣው መግለጫ እንደተለመደው ለሚዲያ ያሰራጫሉ በመግለጫው ርዕስ የትግራይ ምርጫ ህግ ወጥ መሆኑን ያትተታሉ ከዛ ኮፒው በደብዳቤ ጠቅልለው ወደ መቅሌ መላክ ነው 😂 ህወሓት ደብዳቤያቸውው እንኳን ለማንበብ ግዜ አታቃጠልም የትግራይ ህዝብ ምርጫ ማድረግ እንደምችል የህግ አንቀፅ በማታቀስ የትግራይ ህዝብ በተያዘለት ግዜ ክልላዊ ምርጫ እንደሚያደርግ አንድ የትግራይ ዩኒቨርስት ሙሁር ወይም ጌታቸው ረዳ በDW እና Tigray Tv አቅርበው አቋማቸው ተዝናንተው ያሳወቃሉ ይሄው ነው ሌላ ተአምር የለም ።

ይሄ ደሞ ህወሓት ከመቀሌ አያስወጣም የትግራይ ህዝብ ከምርጫ ማድረግ አያስተጓጎልም ።

ጠቅላይ ሚኒስትር የትግራይ ክልል አደርጋለው ያለው ምርጫ ህግ ወጥ ነው ብሎ በግልፅ ነግሮናል ‼️

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የትግራይ ምርጫ ህግ ወጥ ነው በማለት በግልፅ አውጀዋል ‼️

የፌድሬሽን ም/ቤት በበኩሉ የትግራይ ምርጫ ህግ ወጥነት በግልፅ በጉባኤ አፅድቆ በደብዳቤ ለትግራይ ክልል አሳውቀዋል ‼️

የተወካዮች ም/ቤት በሙሉ ድምፅ ምርጫ አራዘመዋል ‼️
ይሄ ሁሉ የፌድራል መንግስት ስብሰባና ውሳኔ በትግራይ ክልል መንግስት ዘንድ ተቀባይነት ሳያገኝ ክልሉ ወደ ምርጫ እየገሰገሰ ነው ።
ይልቅ እውነት እንነጋገር ከተባለ የትግራይ ምርጫ ሊያደናቅፍ የምችለው የፌድሬሽን ም/ቤት ውሳኔ ሳይሆን ምናልባት ካደረገ የጠቅላይ ሚኒስተር አብይ ወታዳዊ እርምጃ ነው ።

ግን በእርምጃ ዙሪያ ከባባድ ጥያቄዎች ይነሳሉ ?!🤔

አንደኛ:- ጠቅላይ ሚኒስተሩ ራሱ ለውሳኔ ዝግጁ ነው ወይ ?

ሁለተኛ :- በጠቅላዩ የሚመራው መከላከያ ሰራዊት ትግራይ ክልል ለመረጋጋት እና ምርጫ ለማስቆም የሚያስችል የሰነ ልቦና ዝግጅተና የወታደራዊ ቁመና ያሟላሉ ወይ ?

ሦስተኛ :- የትግራይ ክልል ወታደራዊ አቅምና የህዝቡ ሰነ ልቦና ዝግጅት በራስ መከላከል ያላቸው የዘመናት ስራ ልምድና እንደ ሀገር ያላቸው የመሪነት ስራ ልምድ ተጨምሮ የተደራጀ የተረጋጋ ሀይል አዘጋጀተው በመጠባበቅ ላይ ያለው ትግራይ ክልል መዝመት ምን ልያስከትል ይችላል ❓😁

እንድሁም በህዝባዊ አመፅ ፖለቲካ ውጥንቅጥ ውስጥ በብሔር እና በሀይማኖት ሴራ እየተባላች ያለችው ኢትዮጲያ የምትመራው ብልፅግና መንግስት ባልተደራጀ አቋምና ዝግጅት ከትግራይ ክልል ጋር ለጦሪነት መጋፈጥ ቄሮ እንደ መጨፍጨፍ እና ታዬ ደንደአ መግለጫ ቃላል ይሁንላቸዋል ወይ ??😁❓

ሌላ ያልጠቀስናቸው የትግራይ ራሳቸው ከየተኛው ሀይል የመከላከል አቅም ዜዴዎች እንዳሉ ሆነው ከላይ የጠቀስኳቸው የአብይ መንግስት ድክመቶች ትግራይ(ህወሓት) አስፈላጊ ከሆነ ወደ አራት ኪሎ ለመመለስ የምያስችል በቂ የማሸነፍያ እድሎች ናቸው።

አሁን ኢትዮጲያ ያለችበት የፖለቲካ ሁኔታና የመንግስት አቋም እንኳን ትግራይ ለብልፅግና ህልውና የማይበጅ መሆኑን አለመረዳት ከይዋህነትም በላይ ቅልነት ነው ። 🙂

የትግራይ ምርጫ ይካሄዳል አይ እንቅፋት እንሆናለን የምል አካል ካለ ብልፅግና ከአራት ኪሎ የምትወጣበት ግዜ ለመገመት ቃላል ይሆናል ‼️
2013 በትግራይ ህዝብ ዘንድ ሁለት ክስተት ብቻ ይጠበቃል !
1 ሰላማዊ ምርጫ ማካሄድ !
2 ያ አንፈቅድም የምል ከመጣ ወደ አራት ኪሎ ተመልሰው ሀገሪቷን መረጋጋት !
ሶስተኛ አማራጭ ኢንጂሩ 😁
ከዚህ ሁሉ መጠላለቅና እና መጨናነቅ እኔ እንደ አፋር የማተርፈው ሁለት አብይ ጉዳይ አለ !

አንደኛ / የአሸባሪው አደም ፋራህ ጎል ማግባት ነው ለዘመናት የአፋር ህዝብ በአደራጀው አሸባሪ ስጨፈጭፍ የኖረው የብዙ ህፃናት፣ እናቶች፣ ወጣቶች፣ አዛውንቶች፣ ህይወት በአሳቃቂ ሁኔታ አስገድለው የአፋር ህዝብ ከቂያ በማፈናቀል ልዑላዊነታችን በአሸባሪዎ በቀጥታ የስደፈረው ደም ጠጪው የአለማቀፍ ወንጀለኛ ያለ አቅሙ በመሀል እየገባ የፖለቲካ ነጥብ እየጣለ ጎል ውስጥ እየገባ በመሆኑ ለኔ ትርፍ ነው ።

2ተኛ ግን አደጋ የሆነ የውድቀት ትርፍ ነው አሁን እየተናወጠ ያለው የውስጥ ለውስጥ የፖለቲካ ቀውስ እና እርስበርስ ግጭት እንደ ሀገር ለሚያደርሰው ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ቀውስ እንደ ዜጋ እንጎዳለን ‼️

31/08/2020

ነሐሴ 25፣ 2012

የቢሾፍቱ ከተማ ፍርድ ቤት የአቶ ልደቱ አያሌውን የምርመራ ፋይል ዘጋ፡፡

የቢፍሾቱ ከተማ አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት የኢዴፓ መሥራችና የስራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ልደቱ አያሌው በተከሰሱበት ጉዳይ ላይ ለፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ለመስጠት ባለመፍቀድ የምርመራ ፋየሉን መዝጋቱ ተሰማ፡፡

ሸገር የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር የሆኑትን አቶ አዳነ ታደሰን በስልክ አነጋግሮ አቶ ልደቱ ተጠርጥረው ለእስር የተዳረጉበት የምርመራ መዝገብ መዘጋቱን አረጋግጧል፡፡

አቶ ልደቱ አያሌው፣ የምርመራ ፋይሉ መዘጋቱን ተከትሎ ወዲያወ በነጻ እንዲለቀቁ ለፍርድ ቤቱ ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ማመልከቻ እንዲያቀርቡ መታዘዛቸውን ሸገር ከአቶ አዳነ ሰምቷል፡፡

አቶ ልደቱ አያሌው የድምፃዊ ሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በቢሾፍቱ በተፈጠረው ረብሻ አመፅ በማነሳሳትና በገንዘብ በመርዳት በሚል ጠርጥሬአቸዋለሁ ባለው የቢሾፍቱ ከተማ ፖሊስ አዲስ አበባ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውለው በፍርድ ቤት ጉዳያቸውን ሲከታተሉ መክረማቸው ይታወቃል፡፡

ሸገር የአቶ ልደቱ ጉዳይ የተጓዘበትን የፍርድ ቤቱ ውሳኔ አስመልክቶ ያነጋገራቸው የሕግ ባለሙያ ፍርድ ቤቱ የምርመራውን ፋይል ሲዘጋ፣ አቶ ልደቱን እንደለቀቃቸው ሊቆጠር ቢችልም፣ ይህ ግን አቶ ልደቱ ክስ አይመሠረትባቸውም ማለት አይደለም ብለዋል፡፡

ፖሊስ እስካሁን ባሰባሰበው መረጃ ላይ ተመሥርቶም ሆነ ተጨማሪ መረጃ አሰባስቦ ክስ ሊመሠርትባቸው እንደሚችልም የሕግ ባለሙያው ለሸገር ነግረዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የኢዴፓው ሊቀ መንበር አቶ አዳነ ታደሰ፣ ፍርድ ቤቱ የጠየቀውን የዋስትና ማመልከቻ በነገው ዕለት እናቀርባለን ብለዋል፡፡

ዘከሪያ መሐመድ



የሸገርን የቴሌግራም ቻናል በመቀላቀል፣ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
http://bit.ly/39BaChP

31/08/2020

የገዳ ስርአት እና እሴት ከአፄዎች ትርክት በላይ የሀገር ቅርፅ እና ፀጋ ነው ሰለዚህ የገዳ ስርአት እንደ ሀገር ልንጠቀመው ልንስፋፋው የምገባ የሀገር ውበት መሆኑን አምነን ልንቀበለው ልናውቀው የዜግነት ግዴታ አለብን።
እንድሁም ሌሎች ኢትዮጲያዊያን ያላቸው ጠቃሚ ሀገር በቀል እሴት እንድሁ የሀገር ሀብት መሆኑን ማመን ውዴታ ሳይሆን ግዴታ መሆኑን መቀበል ይኖርብናል።

በአጠቃላይ የገዳ ስርአት በአድስ አበባ ስርአተ ትምህርት ውስጥ ልካተት ነው ብለህ የምትንጫጫ ውልክፍ ሆይ ሀገር ብቻ በአናንተ አስተሳሰብና ፈላጎት የምትገደብ ትንሽዬ ሰፈር እንዳልሆነች መዘንጋት የለባችሁም ።

የገዳ ስርአት ውስጤ ነው ።

በዚህ መሠረት ልክ እንደ ገዳ ስርአት የኩሽ ልጆች ስልጣኔ መርህ የሆነው የአፋር ማድዓ (ህግ) ለሺዎች አመታት ህዝቡ ስተዳደር የኖረበት አሁንም ከሀገሪቷ ህግ መንግስት በላይ በህዝቡ ዘንድ አግልግሎት እየሰጠ ያለው የስልጣኔ መሠረት ሰለሆነ እንደ ሀገር በስርአተ ትምህርት እንዲካተት ማድረግ የአፋር ሙህራን ብቻ ሳይሆን ሁላችን ሀላፊነት መሆን አለበት ።

31/08/2020

Neo-neftegna 👣👣

26/08/2020

Visit our page to get more information about adal

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Qafar xongolo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share