ነገደ አማራ - Negede Amhara

  • Home
  • ነገደ አማራ - Negede Amhara

ነገደ አማራ - Negede Amhara I am Neftegna - ነፍጠኛ ነኝ

28/06/2023

ደቡብ ጎንደር የተቸከለ የህወሓት ካድሬ እስካሁን አልተነቀለም ክልስ ካድሬ ሆኖ በብልፅግና ወንጌል ተጠምቆ እስካሁን ዞኑን እያወከ ይገኛል።

ሰሞኑን እብናት ላይ እየተፈፀመ ያለው አስነዋሪ ድርጊት እናንተኑ ያጠፋ ካልሆነ ፋኖ ጀግኖቻችን ላይ የምትፈጥሩት ነገር የለም።

ከእርስ በርስ መጠፋፋት ወጥታችሁ የጋራ ጠላታችን የሆነውን የአብይ አገዛዝ ከስሩ መንግለን ለመጣል አጋዥ ባትሆኑን መሰናክል አትሁኑብን።

12/04/2023

ጀግናው የአማራ ልዩሀይል ፋኖ እና ሚሊሻ ከጎኑ የሚገኙ ባንዳዎችን እያፀዳ ወደ ፊት እየገሠገሠ ነው።

31/03/2023

ሁሉም የአማራ ልዩሀይል ፋኖ ነው ‼

22/03/2023

በዐማራ ላይ ዘግናኝ ሆሎካስት የፈጸመውን ኢንተርሃምዌ ሕወሓትን ከሽብርተኝነት መዝገብ ፍቀህ፣ ”ዐማራን አከርካሪውን ሰብረነዋል” ያለውን አቦይ ስብሀት ከእስር ለቀህ ሲያበቃ ዘመነ ካሴን እስርቤት የምታቆይበት ምንም ምክንያት የለም። "ሀጫሉን የገደለው ነ*ፍ*ጠ*ኛ ነው" በማስባል ዐማሮችን ያስጨፈጨፉትን እነጃዋርንና በቀለ ገርባ በነፃ ለቀህ ሲያበቃ፣ ዘመነ ካሴ አስረህ የምታቆይበት ምንም ምክንያት የለም። ዐማራ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ እንደ አንድ ልብ መካሪ ሆኖ ይሄን ዘመን እንዲሻገር ከተፈገ ዘመነ ካሴን ፍቱት። በየእስር ቤቱ የታጎሩ ፋኖዎችና ልዩ ኃይሎችን ልቀቋቸው።

22/03/2023

የአብይ መንግስት ህወሓትን ከሽብር ወንጀል ማስወጣቱ ለሰራዊቱ ሞት ግዴለሽ መሆኑን ግልጥ አድርጎ ያሳየ ነው!

22/03/2023

ረመዳን ሙባረክ !

04/02/2023


ሁሉም ሰው ደርሶ ፀሀፊ እየሆነ ነው እንዲህ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ትክክለኛ እና ተአማኒ መረጃ ማግኘት አዳጋች ነው ስለዚህ ውድ የፌስቡክ ተጠቃሚ ኦርቶዶክሳዊያን እባክችሁ መረጃዎችን በቤተክርስቲያን ውስጥ ካሉ አባቶች እና ሀላፊነት ካላቸው ሰዎች ብቻ እንቀበል ተቀብለንም እናጋራ እንጅ በመሰለኝ ደርሰን ባንፅፍ ጥሩ ነው።

03/02/2023

የአብይ አህመድ የፌስቡክ አካውንት ፎሎወር በ100,000 ቀንሷል።
Challenge Accepted‼

01/02/2023

የጠቅላይ ሚኒስተሩ አድሏዊ የንግግር ግድፈቶች
***

ጠቅላይ ሚንስትሩ ቅድስት ቤተክርስትያን ያጋጠማትን ፈተና ላይ ያደረጉትን ንግግር አዳመጥኩኝ።

የጠላይ ሚንስትር ንግግር ህግን የሚያስከብር እንደ ትልቅ ሀገራዊ የመንግስት መሪ ሳይሆን በሁለት ጎን ተወዳጅ ሸንጋይ ቃል ወርዋሪ አካል ተጫውተው አልፈዋል።

"ባለውለታ ሆኜ እንዴት እታማለው" አይነት ልብ የሚያራራ ንግግሮች ረጅሙን ሰዓት ቢወስዱም ለማሳዘን በተኬደው ሆደ ቡቡ ቃላቶች መሃል እነዚህ ግድፈቶች ግን ፈጠው ይታያሉ።

***
ግድፈት ፪

>

ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስተሩ ነካ አድርገው ለማለፍ የሞከሩት ንግግር ከዬትኛው የታሪክ ዶሴ እንደተገኘ ባላውቅም "የነገስታት ሃይማኖት" ተብላ በሐሰት ለማማት በር ላይ ለቆሙ ሰዎች" አይዟችሁ በርቱ " የሚል አይነት ጉልበት ሰጪ የተቀበረ ፈንጅ ንግግር ሆኖ አይቸዋለው።

ይህን መንግስታዊ ማማት ብለኸው ትደመድማለህ።
**
ግድፈት ፪

""የትግራይ ጳጳሳት ከኢ/ኦ/ተ/ቤ ሲገነጠል መግለጫ ሳይወጣ የኦሮሚያው ጉዳይ ላይ ግን ጮኸት በዛ"

ይህ ደግሞ ሊደብቁት ያሰቡትን የወሊሶ ህገወጥ ድርጊት ስውር ድጋፍ ሰጪነት ያመላከተ ይመስለኛል።

ይህን ንግግር ከእሳቸው በፊት የወሊሶ ህገ ወጥ ሹመት ደጋፊዎች ሲያደነቁሩን የወላቱን ቃል ከአንድ ሀገር መሪ መስማት በጣም ያስተዛዝባል።

የትግራይ ሊቃነጳጳሳት ኩርፊያን መሰረት ያደረገ ግንጠላ ለማካሄድ ወሰኑ እንጅ የእራሳቸውን ሲኖዶሳዊ መስመር አልዘረጉም።

የትግራይ ጉዳይ በሁሉም ሃይማኖቶች ላይ ፓለቲካው ያመጣው ጥቁር ጠባሳ እንጅ በኢ/ኦ/ተ/ቤ ላይ ብቻ በተናጠል የተካሄደ ልዩ ዘመቻ አይደለም።

የትግራይ ጳጳሳት ፍትህ ነገስትን ጨፍልቀው ህገወጥ ሲመት እና ቅዱስ ፓትርያርክ ምርጫ እቃቃዎሽ ላይ አልገቡም።

ስለዚህ የወሊሶው እን የትግራይ ጉዳይን ማነጻጸር አኩራፊ እና ወንበዴ ልጅን በእኩል ለመዳኘት እንደሞሞከር ነው።

***

ግድፈት ፫

>

ይህን ንግግር ስስማ በእውነት ድንጋጤ ወሮኛል። የእዚህ ንግግር አወንታዊ መገለጫው ቅድስት ቤተክርስቲያን የቋንቋ አገልግሎትን ታፍናለች ለሚል ትርጉም ይጠጋጋል። ጥላቻ እንዲህ ፈጦ ሲገኝ "እግዚኦ" ብለን እንለፈው።
***
ግድፈት ፬



ቤተክርስቲያን በመንግስት ዘንድ ህጋዊ አካል ናት። ስለዚህ ህጋዊ አካል ለወሰነው ውሳኔ ህግ አስከብርልን ተባልክ እንጅ መቼ የመንግስትን ድጋፍ ሻትን?

የአመጸ አካል ሁሉ መቅደስ እየሰበረ በገባ ቁጥር ተደራደሩ ከተባልን ቤተክርስቲያኒቷ በህግ ፊት ያላት እውቅና ከወረቀት አይዘልም።

የኦሮሚያ ልዩ ኃይል እጀባ የሚሰበሩ የሀገረስብከት ጽ/ቤቶች ግን ለማንም ድጋፍ ሰጪ እንዳልሆነ የሚያሳይ እንደሆነ እንቀበል ዘንድ ህጻን መስለንላችዋል መሰለኝ።
***

ትዝብት ፭

>

ይህ ንግግራቸው ደግሞ የአኃዝ ማጭበርበር ተጠቅመው ህዝቡን ህጻን በማድረግ ለመሸወድ ጥረዋል ።

ሃቁን ስንበረብር ግን ወ/ሮ አዳነች አበቤ ከወራት በፊት ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ባደረጉት ሪፓርት

ለእስልምና....................... 260,938 ካሬ
ለወንጌላውያን አማኞች........98,290 ካሬ
ለአድቨንቲስት ቸርች............6812 ካሬ
ለካቶሊክ.......................... 7700 ካሬ
ለኦርቶዶክስ .....................ከአንድ ሚሊዬን በላይ ተብሎ ተገልፆል።

ይህን አሐዝ ስናሰላ ከኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውጪ 373,740 ካሬ ሲያገኙ በጠቅላይ ሚንስትር ንግግር ግን ፣350,000 ሲሉ ለመቀነስ ሞክረዋል።

በነገራችን ላይ የአዲስ አበባ ህዝብ ሃይማኖታዊ ንጽጽር መንግስት እጅ ላይ ባለው ይፋዊ ሰነድ ስንመለከት

ኦርቶዶክስ...... 74.6℅
ሙስሊም....... 16.2℅
ፕሮቴስታንት.....7.8℅
ካቶሊክ ..........0.5%
እና ሌሎች....... 0.9 ይይዛሉ።

በተነገረልን አሐዝ መሰረት እንኳን ስንመለከት

ለአንድ ፐርሰንት ሙስሊም ተከታይ.....16,107 ካሬ መሬት
ለአንድ ፐርሰንት ካቶሊክ ተከታይ....... 15,400 ካሬ መሬት
ለአንድ ፐርሰንት ኦርቶዶክስ ተከታይ.... 13,405 ካሬ መሬት

መሬት እንደተከፋፈለ ቁጥሮች ያሳያሉ። ስለዚህ በመሬት እድላ በኩል እንኳን ለኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ልታደሉ ቀርቶ ከሌላው ቤተእምነት ጋር እኩል መመልከት እንዳልቻላችሁ ያሳያል እና መሬትን አስታካችሁ የምታራግቡት የድጋፍ መሰብሰቢያ ፊሽካ ቢቆም መልካም ነው

መሬት ሰጥተናል በሚለው ሪፓርት ጋር እነ መስቀል አደባባይን ጨምሮ በ4 ዓመት ውስጥ የተወረሱ ኦርቶዶክሳዊ ርስቶችም ምን ያህል እንደሆነ ቢካታቱ መልካም ነው።

ትዝብት ብቻ!!! ለማይቀረው ሰማዕትነት ተዘጋጅ።

Kune Demelash kassaye -Arba Minch

01/02/2023


ክህነት የሌለው ሲኖዶስ የካድሬ ጉባዔ እንጂ የክርስቶስ መንጋ እረኛ ሊሆን አይችልም። አሁን ያለው በአብይ አህመድ የሚመራው "የኦሮሙማ" መንግሥት የዘር መንግሥት ነው። ከሰው ልጅ ነፍስና ከሀገር የበለጠ የሚያስጨንቀው ሥልጣኑ ነው። ሥልጣኑን በከፋፍለህ ግዛ የቅኝ ገዥዎች መርህ ለማስጠበቅ ኦርቶዶክስን መከፋፈል ሥራዬ ብሎ ፈጽሞታል። ትኩረቱ ነፍሱን ትቶ ልብሱን እንደሚሻ ሰነፍ ሰው ይመስላል። ለሰው ልጅ ነፍስ የማይጨነቅ መሆኑን በተግባሩ ገልጦታል። ወለጋና ቤኒሻንጉል የሚፈጁትን ከመጠበቅ ይልቅ ሕገወጦችን የሚያጅቡ ወታዶርች ይመድባል፡- ይህን የልጣጭ ፅንሰ ሀሳብ ቀደም ሲል በትምህርት መልክ ቀርቦ ተመልክቼዋለሁ። በብሔር ፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ለተወናበዱ ወጣት ክርስቲያኖች እንዲደርስ አጋሩልን

31/01/2023

ውድ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታይ ምዕመናን እና ምዕመናት አሁን አዲስ የተሾሙ ጳጳሳት ቢሮ ሰብረው መግባት መጀመራቸው እና የግዕዝ መፅሐፍትን አውጡ እያሉ እንደሆነ በሶሻል ሚዲያ ሲዘዋወር እያየሁ ነው። ስለዚህ ምን አልባትም ድጋሜ ልናገኛቸው የማንችላቸው ሀይማኖታዊ መፃህፍት እንዳይጠፉ ተገቢው ጥበቃ ቢደረግላቸው ወይም ደግሞ በምስጢር ዘወር ብለው የሚቆዩበት ቦታ ቢመቻች መልካም ነው።

31/01/2023

መፈንቅለ ሲኖዶስን የደገፈው መንግስት መፈንቅለ መንግስትንም ከደገፈ ብንሞክር??😂

31/01/2023

ነገደ አማራ🙏

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ነገደ አማራ - Negede Amhara posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share