Damot silase press

  • Home
  • Damot silase press

Damot silase press Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Damot silase press, Media/News Company, .

  ተጠቃሚዎች ሰሞኑ   የሚባል ማህበራዊ ሚዲያ ፔጅ አዲስ የሚደራጀውን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ማዕከልና በሌሎች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የህዝቡን ቀልብ በውሸትና የተቀነባበረ መረጃ በማሰራጨት...
03/08/2023

ተጠቃሚዎች

ሰሞኑ የሚባል ማህበራዊ ሚዲያ ፔጅ አዲስ የሚደራጀውን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ማዕከልና በሌሎች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የህዝቡን ቀልብ በውሸትና የተቀነባበረ መረጃ በማሰራጨት ትኩረት ስቧል።

በገጹ የሚለጥፉ አብዛኛው መረጃዎች አሁን ያለውን ነባራዊ ሁኔታና አዝማሚያውን በመጠቀም ከእውነት የራቀ እና የተቀነባበሩ መረጃዎች እያሰራጨ በመሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። ምክንያቱም በዚህ ፔጅ የተለጠፉ አብዛኛው መረጃዎች ከሁለትና ሶስት ቀን በኃላ እየጠፋ ነው። በተጨማሪም የቆዩ ፎቶችን በመወሰድ አንድ ቀን በስብሳባም(በውሳኔውም) ላይ ያልተሳተፉ ግለሰቦችን እየሞገሰ ይውላል።

ይህ ፔጅ ከዚህ በፊት በሌላ ሰው ስም ስያሜ ያለና አሁን ወደ የተቀየረ ነው። በዚህ ፔጅ ከዚህ በፊት የወላይታ ህዝብ ስም የሚጠላሹና ውሸት መረጃዎችን ሲያሰራጭ ነበር። ከ4.5 ሺህ ተከታያ ያለው ሲሆን ከ8 ሺህ በላይ ተከታይን በአንድ ወር ውስጥ በማግኘት ከ13 ሺህ በላይ ተከታይ አፍርቷል።

የዚህ ፔጅ ዋና ዓላማው የወላይታ ህዝብ ጥቅም ለማጠልሸት ከወንድም ህዝቦች ጋር ለማሻከርና ከሌሎች አጋሮባች ዞኖች ጋር ያለውን አብሮነትና አንድነትን ለማፋለስ እየሰራ መሆኑን መረጃዎች እያሳዩ ናቸው።

እንዲሁም አምስት ዞኖችና ስድስት ልዩ ወረዳዎች ህዝቦች በየምክር ቤቶቻቸው በአንድ ክልል ተደራጅተው ለመኖር የተስማሙትን መልካም ሀሳባቸውን በተሳሳተ ሁኔታ አደገኛና ስጋት የሚጫሩ መረጃዎችን እያሰራጨ መሆኑን እንመለከታለን።

ለወላይታ ህዝብ ጠቃሚ መረጃዎችን እያሰራጨ በማስመሰል የወላይታ ህዝብን ዳግም ዋጋን ለማስከፈል እየሰራ መሆኑን ህዝቡ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መቀመጫዎች ወላይታ የድርሻውን ማግኘቱ አይቀርም ሌሎችም እንደዛው። እውነታው ይህ ነው ከዚህ ውጪ አዲስ ነገር አንጠብቅ።

በዚህ ፔጅ የተቀነባበረና ውሸት መረጃውን የሚያሰራጨውን ግለሰብ ማንነት እየተጣራ ጫፍ ላይ የደረሰ ሲሆን የግለሰቡን ማንነት በቅርቡ ለህዝቡ ይፋ እናደርጋለን።

በአጠቃላይ በዚህ ፔጅ ላይ የሚሰራጩ
ጨው ምንጩ ያልታወቀና ያልተረጋገጠ መረጃዎችን ላይክ፣ ኮሜንትና ሼር የሚያደርጉ ግለሰቦች እንድትቆጥቡ እናሳስባለን።

01/08/2023
01/08/2023

የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦቸና ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት ከፊታችን አርብ ጀምሮ መደበኛ ጉባኤውን ያካሂዳል።

ወላይታ ሶዶ፣ ሐምሌ 25 ፣ 2015 የደቡብ ብሄሮች፣ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከፊታችን አርብ ከሀምሌ 28 ቀን 2015 ዓመተ ምህረት ጀምሮ ያካሂዳል።

የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ምክር ቤቱ ከመጪው አርብ ሀምሌ 28 እስከ 30/2015 ባሉት ቀናት በሚያካሂደው መደበኛ ጉባኤ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል።

ለዚህ ጉባኤ ስኬትም የተለያዩ ኮሚቴዎች ተዋቅረው የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቃቸውን ወ/ሮ ፋጤ ተናግረዋል።

በዚሁ መሰረትም የክልሉ ምክር ቤት በ3 ቀናት ቆይታው በባለፈው መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ፣በክልሉ አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የ2015 በጀት አመት የስራ አፈጻጸም ፣በክልሉ ዋና ኦዲተር፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና ምክር ቤት ጽ/ቤት አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘም በክልሉ የ2016 በጀት ረቂቅ የበጀት አዋጅ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል ያሉት ወ/ሮ ፋጤ ከአዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጋር የስልጣን ርክክብ እንደሚደረግም አስታውቀዋል።

01/08/2023

#ብልጽግና ፓርቲና በፓርቲዉ የሚመራዉ መንግስት፦

፨ ብሔራዊ መግባባት እና እርቅን በመፍጠር ጠንካራ ሀገራዊ መንግስት ለመገንባት ይሠራል።

፨ ብሔራዊ መግባባትን ለማዳበር በሚያደርገው እንቅስቃሴ ቅድሚያ ሰጥቶ ከሚሰራቸው ተግባራት አንዱ በሀገራችን የቂም እና የጥላቻ ታሪክ ምዕራፍ እንዲዘጋ ማድረግ ነው፡፡ ይህን ለማሳካት ባህላዊና ዘመናዊ የእርቅ ሰላም ግንባታ አማራጮችን በመጠቀም እርቀ ሰላምን ለማምጣት በቁርጠኝነት ይሰራል፡፡

፨ለቀጣይ ትውልድ ቂምንና ቁርሾን ሳይሆን ሠላምና ወንድማማችነትን ለማውረስ የእርቀ ሰላም አማራጮችን ሁሉ ይጠቀማል፡፡

፨ለሀገረ መንግስታችን ቀጣይነት መሰረታዊ በሆኑ ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባት ላይ ለመድረስ ሁሉንም የሀገራችን ህዝቦች አካታች በሆነ መልኩ የምክክር አውድ እንዲፈጠር ይሰራል፡፡

01/08/2023

ይህ የታገልነለት እንዲሁም በርካቶችን መስዋእት ያደረግንበት ወርቃማ ሀሳብ ነው።ነፃነትን የተጠማው ህዝባችን አካላዊ፣መንፈሳዊ እንዲሁም ስነ አእምሮአዊ ነፃነቱ ዴሞክራሲያዊ እና ሰብአዊ መብቶቹ ተከብረውለት በነፃነት እንዲረሰርስ ታግለናል አታግለናል።

ነፃ ካልሆነ ህዝብ መሀል ብልፅግና እንደማይወለድ ስለተረዳን እንዲሁም እንደሀገር የለውጥ እንቅስቃሴ ውስጥ ስንገባ የነበረውን የታፈነ ስሜት ስለተገነዘብን ህዝባችን የሚፈልገውን ነፃነት ለመለገስ አቅም በፈቀደ መልኩ ጥረናል።

ይህ ጥረታችን አሁንም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።የነፃነት ጣእም በህዝባችን ዘንድ ሰርፆ ለሀገራችን ብልፅግና አቅም መፍጠር እስኪችል ድረስ አበክረን የምንሰራ ይሆናል።

ነፃነት ለህዝባችን!!
ብልፅግና ለሀገራችን!!

01/08/2023

ጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግስት !!

የተረጋጋ ዴሞክራሲያዊ ስርዓተ መንግስት ለሀገር ብልፅግና እና ለዜጎች ዘላቂ ሰላም ፋይዳው የጎላ መሆኑ አያሻማም። በመደመር ሀገር በቀል እሳቤ የተቃኘውና በአደረጃጀት፣ በስትራቴጂውና በፖሊሲው እንዲሁም በአባላትና በደጋፊዎቹ ብዛት በሀገራችን ከሚገኙ ተፎካካሪ ፓርቲዎች እጅጉን ልቆ በመገኘቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ለአምስት ዓመት እንዲመራው ይሁንታውን በድምፁ ያረጋገጠለት ብልፅግና ፓርቲ ጠንካራና ዘለቄታዊ ተቀባይነት ያለው ሀገረ መንግስት የመገንባት ፅኑ እምነት ተጥሎበታል፤ አቅሙም አለው።

ጠንካራና የተረጋጋ ሀገረ መንግስት ካለመገንባት ጋር ተያይዘው በሚመጡ ችግሮች በርካታ የአፍሪካና የዓለም ሀገራት ሉዓላዊነታቸው ለአደጋ ይጋለጣል ዜጎቻቸውም በሰላም እጦት ይሰቃያሉ። በአንፃሩ በሀገር ጉዳይ የማይደራደሩ ጥራት ያላቸው ጠንካራ ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ያሏቸው ሀገራት በተፈጥሯዊና በሰው ሰራሽ አደጋዎች ውስጥም ሆነው ለችግሮቻቸው በቀላሉ እጅ አይሰጡም።

ብልፅግና ፓርቲም በሀገር ህልውና ላይ የተጋረጡ ችግሮችን ለብዙዎች ለማመንና በሚከብድ መልኩ በጥበብ እያለፈ መሆኑ ሲታይ በእርግጥም ትክክለኛውን መንገድ እንደያዘ መረዳት ይቻላል።

"የሚያጠግብ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል" እንደሚባለው ብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ከማስፋት በተጨማሪ በህዝብ ይሁንታ ካገኘው ሀገር የመምራት ሀላፊነት ላይ ተፎካካሪ ፓርቲዎችንም በማሳተፍ ቀጣይነት ያለው ሀገረ መንግስትን በፅኑ መሰረት ላይ እየገነባ መሆኑን እያስመሰከረ በመደመር ጎዳና ጉዞውን ቀጥሏል።

በፖለቲካዊ አሰላለፍ ሁሉም ፓርቲ አማራጭ የሚለውን ሀሳብ ለህዝብ ያቀርባል፤ በምርጫ ተቀባይነት ያገኘው ልክ አሁን ብልፅግና ፓርቲ እያደረገ እንዳለው ሀገር ይመራል። በሀገር ጉዳይ ደግሞ ያለው ብቸኛ አማራጭ በአንድነት መቆም በመሆኑ ከዚህ ውጪ ያለው አማራጭ ከህዝብ መብትና ፍላጎት የሚፃረር ነውና የትም አያደርስም።

ፓርቲያችን ብልፅግና በጠንካራ ፓርቲ ጠንካራ ሀገረ መንግስት እውን እንዲሆን በተራማጅ እሳቤው እራሱን ብቁና ተወዳዳሪ ለማድረግ በተቋም ግንባታ፣ በህዝብ አሳታፊነትና በአሰራር ግልፀኝነትና ተጠያቂነት እንዲሁም የህግ የበላይነት መከበር ላይ በትኩረት ይሰራል። እየሰራም ይገኛል።

ሰላም እና ብልፅግና ለኢትዮጵያና ለህዝቦቿ !!

01/08/2023

ኅብረ ብሔራዊነትን ያረጋገጠ 'አንድነት' ለሁላችንም የምትመች ኢትዮጵያን ለመገንባት መሠረት ነዉ።

'አንድነት' ማለት #አንድዓይነትነት አለመሆኑን ያገናዘበ፣ የመደማመጥና የመከባበር መንፈስ የሰፈነበት ሕብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያዊነት ለብዝሃነት ምቹ መሠረት በመሆኑ ሁሉንም ፍላጎቶች፣ ማንነቶች፣ አመለካከቶች ሚዛናዊ በሆነ መንገድ ማስተናገድ ይችላል ።

የኢትዮጵያን ዘላቂ ሠላም ለማረጋገጥም ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ምሠሦ ሆኖ ያገለግላል፤ ጠንካራ ሀገረ መንግስት የመገንባቱን ሂደትም ያግዛል። ኅብረትና አንድነት ለዉጥን ለማሳለጥ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።

በተቃራኒው የፅንፈኝነት አስተሳሰብና ድርጊት ከለዉጥ ይልቅ ለነዉጥ ምቹ ሁኔታን ያደላድላል፤የአብሮነት መንፈስን በማዳከም ልዩነቶችን ያሰፋል። የትብብርና የፉክክር ሚዛን እንዲዛባ በማድረግ የተወሰኑ ቡድኖችን ፍላጎት ብቻያቀነቅናል።

ለፅንፈኛ አስተሳሰቦችና ድርጊቶች ተጋላጭ የሚያደርጉ ሁኔታዎችን በጋራ በመታገል ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር ለጋራ ሀገራችን ኢትዮጵያ ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት መፅናት የየበኩላችንን 'ጠጠር ' እናበርክት።

ከሰባ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች፣ በርካታ ሃይማሮቶች፣ ከ1 መቶ ሃያ ሚልዮን በላይ ሕዝቦች ባሉባት ኢትዮጵያ በመከባበርና በመተባበር ላይ የተመሠረተ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ከማፅናት የተሻለ አማራጭ አለን?!
በጉዳዩ ላይ ከልብ እንምከር ! እንወያይ!

01/08/2023

የዲፕሎማሲያችን ፍሬያማነት ሌላው ማሳያ! የአለም ባንክ ፕሬዘዳንት አጃይ ባንጋ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው።

የአለም ባንክ እንዳስታወቀው ፕሬዘዳንቱ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በኢትዮጵያ የሁለት ቀን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያደርጋሉ።

ለወጣቶች እና ለሴቶች ስራ የሚፈጥሩ ዕድሎች መለየት የጉብኝታቸው ዋና ትኩረት መሆኑን ባንኩ ገልጿል። የጨርቃጨርቅ እና የጫማ ፋብሪካዎችን እንቅስቃሴንም ይመለከታሉ ። በተጨማሪም ከአርሶ አደሮች ጋር በማስተሳሰር የሚከናወነውን የብቅል ምርት ሂደትን ይጎበኛሉ።ከጥቃቅንና አነስተኛ ሴት የንግድ ባለቤቶች ጋር እንደሚወያዩም ባንኩ አስታውቃል።

የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማሳደግ ከሚደረገው ጥረት ጋር ተያይዞ ከንግድ መሪዎች እና ከስራ አስፈጻሚዎች ጋር ውይይት አንደሚያደርጉም ባንኩ አስታውቋል።

ባንጋ በአዲስ አበባ ቆይታቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጨምሮ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ እና ከብሄራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ ጋር ይወያያሉ ።

የ78 ዓመቱ አንጋፋ ተቋም የሚመሩት አጃይ ባንጋ ዓለም አቀፍ ጉብኝት የመጀመሪያ መዳረሻ ኢትዮጵያ ስትሆን በቀጣይ ወደ ናይጄሪያ እንደሚያቀኑ ባንኩ አስታውቋል ።

29/07/2023
29/07/2023
25/07/2023

ብልፅግና ፓርቲ ለኢትዮጵያና መላው ዜጎቿ ልዕልና ይተጋልⵑ

የብልፅግና ፓርቲ የኢትዮጵያ ህዝቦች መገለጫቸው የሆነውን ህብረ ብሔራዊ ማንነትና ብዝሃ እምነት ይዘው፣ ቱባ ባህሎቻቸው ተከብረውና እንዲያብቡ ተደርገው፣ እንደ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ከተንቀሳቀሱ፣ አሁን ካለው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ችግር ተላቀው እንደበለፀጉት ሀገሮች በተድላና በእርካታ በሰላም የሚኖሩባት ህብረ ብሔራዊ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መሰረት አድርጎ የተገነባ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ያላት የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ እንደሚችሉ ፅኑ እምነቱ ነው፡፡

ብልፅግና በቀጣይ ጊዜያት ሀገራችን ኢትዮጵያን በሁለንተናዊ ብልፅግና አፍሪካዊ የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ እንደ ፓርቲ ሲነሳ የሀገራችን ፖለቲካ የአሁኑንና የመጪውን ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስከብር አስተማማኝ መሰረት ዛሬ ላይ በመገንባት ጭምር ነው፡፡ ሰላም፣ ዴሞክራሲ፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነት፣ የዜጎች ክብር፣ ፍትህና የጋራ ብልፅግና የተረጋገጠባት ሀገር እንድትሆን ያለፈውን ጥፋት በይቅርታ መጪውን ጊዜ በብሔራዊ መግባባት እና ዴሞክራሲያዊ ድርድር በማድረግ ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት እንደሚያስፈልግ በሚገባ ተገንዝቦ በርካታ ሀገራዊ ለውጦችንና ስኬቶችን እውን እያደረገ ይገኛል፡፡

በፖለቲው መስክ የብሔር ማንነትን እና ሀገራዊ ማንነትን አጣጥሞ በዘላቂነት የሚያስኬድ የሀገረ መንግስትና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ማካሄድ ያስፈልጋል፡፡ ህብረተሰብን በጎራ በመክፈል አግላይ የነበረው አካሄድና አደረጃጀት አቃፊና አካታች በሆነ ብሎም የሀገራችንን ተጨባጭ የፖለቲካ ችግር በሚፈታ ማዕቀፍ ማሻሻልና ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል፡፡ ፖለቲካዊ ብልፅግናችን ሁሉን አቀፍ ማህበረሰብ ለመገንባት የምናደርገውን ጥረት የሚደግፍና አንድ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ማህበረሰብ የመገንባት ትልም ያለው እንዲሆን ለማድረግ ተግቶ መስራት አስፈላጊ ይሆናል፡፡

25/07/2023
25/07/2023

ጠንካራና ቅቡልነት ያለው ዘላቂ ሀገረ መንግሥት መገንባት፣

የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ ፕሮግራም ዋነኛ ዓላማ ጠንካራና ቅቡልነት ያለው፣ የብሔር ማንነትን እና የሀገራዊ አንድነትን ሚዛን የጠበቀ ሀገረ መንግሥት መገንባት ነው። ከጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ አንጻር ፓርቲያችን ሕዝብ ከቀጥተኛ የህልውና አደጋ ተጠብቆ የልማት፣ የእኩልነት እና የነጻነት ፍላጎቶቹ እንዲሟላለት የሚያስችል ነጻ፣ ገለልተኛና ብቃትን መሰረት ያደረገ ሀገራዊ ተቋማዊ አደረጃጀት መገንባት ያስፈልጋል ብሎ ያምናል። በመሆኑም የሀገረ መንግሥት ግንባታ ጅምራችን ጠንካራና የማይናወጥ ተቋማዊ መሰረት ያለው እንዲሆን የብልጽግና ፓርቲ ግቡ አድርጎ ይንቀሳቀሳል።

የብልጽግና ፓርቲ ዴሞክራሲን በተቋማዊና ሕዝባዊ ባህል ላይ መገንባት አስፈላጊ እንደሆነ ይገነዘባል። በሌላ በኩል ከሀገረ መንግሥት ቅቡልነት አንጻር የብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ጥንካሬን ለማሳደግ በሕገ መንግሥታችን የተቀመጠውን አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ የመፍጠር ግብ ለማሳካት ይሠራል።

በመሆኑም የሀገረ መንግሥቱን ቅቡልነት በሚጨምሩና ሀገራዊ መግባባትን በሚያመጡ፣ የሕዝቦችን ግንኙነት በሚያሳልጡ እና የእውነተኛ ዕርቅ መንፈስን በሚያጎለብቱ ፖለቲካዊ ርምጃዎች ላይ ትኩረት አድርጎ ይንቀሳቀሳል።

ፓርቲያችን የሀገረ መንግሥት ግንባታችን ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን የተላበሰና ብዝኃነትን የሚያንፀባርቅ መሆን እንዳለበት በጽኑ ያምናል።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Damot silase press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share