05/03/2023
ሰበር ዜና
እናት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤውን እንዳያካሂድ "በመንግሥት" ተከለከለ! ከዚህ በፊት እናት ፓርቲ ጠቅለላ ጉባኤውን ለማካሄድ ለምርጫ ቦርድ አሳውቆ ለየካቲ 4/2015 ቀጠሮ ይዞ ነበር። ነገር ግን በወቅቱ በነበረው ሀገር ዓቀፍ ችግር ከምርጫ ቦርድ ጋር በመነጋገርና በማሳወቅ ለሌላ ጊዜ በመራዘሙ ሳይካሄድ ቀረ። እንዲሁም ከምርጫ ቦርድ ጋር በመነጋገር ለየካቲት 26/2015ዓ.ም ተወስኖ ነበር። በትናንትናው ዕለት (24/06/2015)ለጠቅላላ ጉባኤው የተጠሩ አባላት አዲስ አበባ ከደረሱ በኋላ ከ48 ሰዓት ባነሰ ጊዜ የስብሰባ ቦታውን "መንግሥት" ይፈልገዋል በሚል ምክንያት ተከለከለ። በወቅቱ ሌሎች ሆቴሎችም ፈቀደኛ ሊሆኑ አልቻሉም። በወቅቱ ምንም ማድረግ ስለማይቻል በከፍተኛ ዋጋ ክፍያ ተፈጽሞ ሌላ የስብሰባ አደራሽ መገኘቱን ቀደመው የተጠሩት የሚዲያ አካላት እንዲያውቁት ተደረገ። ዛሬ (26/06/2015ዓ.ም) ጥዋት ሁሉም የጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎችና የሚዲያ አካላት ከተገኙ በኋላ በ"መንግሥት ኃይል" ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄድ አትችሉም በሚል ስለተከለከለ ጉባኤው በታቀደለት መሠረት ማካሄድ አልተቻለም። ገዥ ሆየ! በ"ዲሞክራሲያዊ "መንገድ ለውጥ እንቢ ብለሃልና! እያለቃቀስን የህዝባችን ሁለገብ ሰቆቃ እንዲቀጥል አንፈቅድምና... በነፃ ነፃ ሀገር አልተረከብንምና!
Meseret Worku
26/06/2015ዓ.ም